የጀበና ቡና እና 3,000,000 ብር ተገናኙ !
የአዳማ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ለምለም ሽፈራው የጀበና ቡና በመሸጥ የሚተዳደሩ ሲሆን ሲበዛ ደጋግመው ሎተሪ የመቁረጥ ልምድ አላቸው ፡፡ ታዲያ እንደተለመደው የሎተሪ አዟሪው ቡና በሚያፈሉበት ቦታ ድረስ በመሄድ የልዩ ሎተሪ ቲኬት እንዲገዙት ይሰጣቸዋል ዕድልም ከሳቸው ነበረችና በገዙት ሙሉ ዕጣ የ3ሚሊየን ብር ዕድለኛ ሆነዋል ፡፡ ወ/ሮ ለምለም የሁለት ልጆች እናት ሲሆኑ ገንዘብ በሚያስፈልገኝ ጊዜ የሎተሪ ዕድል ደረሰኝ በማለት በደስታ ገልጸዋል ፡፡