Фильтр публикаций


" የ12ኛ ክፍል ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

ሚኒስትሩ ፥ " ይሄ አራተኛው ነው በአዲሱ የፈተና አሰጣጥ ፈተና የሚሰጥበት " ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከትምህርት ቤቶች ወጥቶ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስገብቶ ፈተና እንዲሰጥ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ስለዘንድሮው የ2017 ዓ/ም ፈተና በተናገሩበት ወቅት 150 ሺህ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይ እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ብርሃኑ (ፕሮፌሰር) ፥ " እንደ ከዚህ ቀደሙ አድካሚ በሆነ ከቦታ ቦታ ልጆችን እያዘዋወሩ ከመሄድ ባለፈው ዓመት 29 ሺህ ተማሪ ነበር ኦንላይን ፈተና የሰጠነው ዘንድሮ ደግሞ 150 ሺህ ተማሪ ኦንላይን ፈተና ለመስጠት እየተዘጋጀን ነው " ብለዋል።

ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ቆርጠው ባይናገሩም ፈተናው ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንዲሰጥ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
📄

@officialexit


የመምህራን የኅብረት ሥራ ባንክ” በሚቀጥለው ዓመት ሥራ ሊጀምር እንደሚችል ተስፋ እንዳላቸው የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ ተናገሩ

የኑሮ ውድነት የበረታባቸው የኢትዮጵያ አስተማሪዎችን ለመርዳት ይቋቋማል የተባለው “የመምህራን የኅብረት ሥራ ባንክ” በሚቀጥለው ዓመት ሥራ ሊጀምር እንደሚችል የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ ፍንጭ ሰጡ።

መንግሥት ለአስተማሪዎች ለቤት መሥሪያ የሚሆን መሬት ቢያቀርብ የሚቋቋመው ባንክ በአነስተኛ ወለድ ብድር የሚሰጥ ይሆናል።

ፕሮፌሰር ብርሀኑ ባንኩ በሚቀጥለው ዓመት ሥራ ሊጀምር እደሚችል ተስፋቸውን የገለጹት ትላንት ማክሰኞ የትምህርት ሚኒስቴርን የ2017 የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት ነው።

በትላንትናው የምክር ቤቱ ውሎ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል በግጭት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎች ቁጥር እና ችግሩን እንዴት ይፈታል የሚለው ይገኝበታል።

ከትምህርት ቤት ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ቁጥር በተባበሩት መንግሥታት የሕጻናት መርጃ ድርጅት “እስከ 10 ሚሊዮን ያደርሰዋል” ያሉት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ “ቢያንስ ሰላም እስኪሰፍን ድረስ ምን እየተሠራ” እንደሆነ ጠይቀዋል።

ፕሮፌሰር ብርሀኑ ግን በተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት የተጠቀሰውን ቁጥር “በፍጹም አላምንም” ሲሉ ተናግረዋል።

ቢሆንም “7.2 ሚሊዮን ልጆቻችን ትምህርት ቤት አለመግባታቸው በጣም በጣም ሊያሳስበን የሚገባ ጉዳይ ነው” ሲሉ ተደምጠዋል። የኢትዮጵያን ልጆች ከትምህርት ገበታ ያራቀው “ትልቁ” ምክንያት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚካሔዱ ግጭቶች መሆናቸውንም አምነዋል።

📄

@officialexit


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
📄

@officialexit

4k 0 18 1 23

ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ

👉የሁለተኛ ሴሚስቴር እና የመውጫ ፈተና ካላንደርን ስለ ማሳወቅ



ትምህርት ሚኒስቴር የ12 ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 18 /2017 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ያሳወቀ ሲሆን ከዚያ በፊት ዩኒቨርሲቲዎች ባወጡት አመታዊ  የጊዜ ሰሌዳ መሠረት

~2ኛ ሴሚስቴር ማጠቃለያ ፈተና የሚሰጠው ከግንቦት 25 እስከ ሰኔ 10/2017 ዓ/ም

~ ለተመራቂ ተማሪዎች ማጠቃለያ ፈተና ከግንቦት 13-28/2017 ዓ/ም

~የመውጫ ፈተና  ከሰኔ 02/2017 ዓ/ም እስከ ሰኔ 10/2017 ዓ/ም

~የምረቃ ስነ -ስርዓት ከ14 እና 15  2017 ዓ/ም  መሆኑን እናሳውቃለን

አ/ም/ዩ/ተማሪዎች ህብረት /ጽ/ቤት

   
📄

@exitnewss


#Digital_ID

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ማውጣት ይጠበቅባቸዋል።

ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች እና ሰራተኞችን መረጃ በተደራጀ መልኩ እንዲይዙ እና የሀገር አቀፍ ፈተናዎችን ደኅንነት ለማስጠበቅ ጠቀሜታ አለው ተብሏል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ኮራ ጡሹኔ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በጻፉት ሰርኩላር፤ በዚህ ዓመት ሰኔ 2017 ዓ.ም ላይ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ሁሉም የግል እና የመንግሥት ዕጩ ተመራቂዎች የፋይዳ መታወቂያ እንደ ቅድመ ሁኔታ የተቀመጠ መሆኑን አስታውሰዋል።

በመሆኑም ሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂ ተማሪዎቻቸው የፋይዳ መታወቂያ እንዲያወጡ እንዲያደርጉ እና የተማሪዎቹን የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ቁጥር በኤሜል አድራሻ eyobie2002@yahoo.com በኩል እንዲልኩ አሳስበዋል።

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ምዝገባ ማድረግ መጀመራቸው ይታወቃል።

📄

@officialexit


#Update

ከሚያዝያ 1-3/2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ አመልካቾች፥ የፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (Orientation) እና የሙከራ ፈተና (Mock Exam) ማክሰኞ መጋቢት 30/2017 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት የሚሰጥ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

📄

@officialexit


#ExitExamCertificate

ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች የምስክር ወረቀት ቅፅ አዘጋጅቶ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ልኳል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ብሔራዊ የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል።

በቅድመ-ምረቃ መውጫ ፈተናው የአፈጻጸም መመሪያ መሰረት፥ የመውጫ ፈተና ውጤት በተማሪዎች ሰርተፍኬት (Temporary Degree) ወይም ትራንስክሪፕት ላይ አልፏል (PASS) ወይም ወድቋል (FAIL) በሚል እንዲቀመጥ ሚኒስቴሩ አዟል።

በዚህም የመውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች የሚሰጡ ኮርሶችን ማጠናቀቃቸውን የሚያረጋገጥ ሰርተፊኬት የሚሰጣቸው ሲሆን፤ ጊዜያዊ ዲግሪ የሚሰጠው ተፈታኙ/ተፈታኟ የመውጫ ፈተናውን በድጋሚ ወስዶ/ወስዳ የማለፊያ ነጥብ ሲያስመዘግብ/ስታስመዘግብ ብቻ እንደሚሆን በሰርተፊኬቱ ይገለጻል።

(የትምህርት ሚኒስቴር ውሳኔ እና የመውጫ ፈተና የውጤት ሰርተፍኬት ፎርማት ከላይ ተያይዟል።)

📄

@officialexit


'የመምህራን ባንክ' መምህራን በኢኮኖሚ እንዲጠናከሩ የሚያስችል ነው - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ


'የመምህራን ባንክ' በማቋቋም የመምህራንን የኑሮ ሁኔታ በማሻሻል በኢኮኖሚ እንዲጠናከሩ ለማድረግ እንደሚሰራ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታውቀዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በጋራ በመሆን 'የመምህራን ባንክ' ለማቋቋም እንቅስቃሴ መጀመሩን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

በዚህም መምህራን መሰረታዊ በሆኑ ነገሮች ላይ ለአብነትም በአነስተኛ ወለድ የመኖሪያ ቤት ባለቤት እንዲሆኑ ማድረግ እና ሌሎችም መሰል ኢኮኖሚያዊ ድጋፎችን ከባንኩ እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ነው የገለፁት።

“ለትምህርት ጥራት መጠበቅ የመምህራን የኢኮኖሚ ጥያቄ መመለስ አለበት” ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፣ በአንድ ጊዜ ከፍተኛ የሆነ የደሞዝ ጭማሪ ማድረግ ስለማይቻል በመሰል አማራጮች መምህራንን ለማገዝ እንደሚሰራ ነው ያመላከቱት።

ሚኒስትሩ በዘርፉ በቂ የሆነ የሰው ኃይል በእውቀት ብሎም በቁጥር እንደሌለ በመግለፅ፣ ሞያው አማራጭ ስላጡ የሚገባበት መሆኑን ለማስቀረት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

አያይዘውም “የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ” በሚል በ2019 ዓ.ም ላይ ለመተግበር የታቀደው አሰራር በዘርፉ ያለውን የመምህራን እጥረት ይፈታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልፀዋል።

ሚኒስትሩ ይህን ያሉት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ውጤት ዝቅተኛ የሆነበትን መንስዔ በተመለከተ በቀረበ ጥናት ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ በተገኙበት ውይይት ባደረገበት መድረክ ላይ ነው።
📄

@officialexit


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
🎙የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ንግግር

ከተቻለ በሚቀጥለው ዓመት ካልሆነም በ2019 ዓ.ም. የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት የተማሩበትን ማህበረሰብ እንዲያስተምሩ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

፨ይህ አዲስ አሰራር ተግባራዊ መደረግ ሲጀምር ለምሳሌ አምስት ዓመት የሚማር የምህንድስና ተማሪ የአራተኛ ዓመት ትምህርቱን ሲጨርስ ለአንድ ዓመት የተማረበትን ማህበረሰብ እንዲያስተምሩ ይደረግና በቀጣዩ ዓመት አምስተኛ ዓመት ትምህርቱን ይቀጥላል። ከዚያም ይመረቃል።

📄

@officialexit

6k 0 15 1 38

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት  እንዲያስተምሩ ሊገደዱ ነው


ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ማኅበረሰቡን ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያስተምሩ ወይም እንዲያገለግሉ የሚያደርግ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ዕቅድ መያዙን አስታወቀ።

ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ውጤት ዝቅተኛ የሆነበትን መንስዔ በተመለከተ በቀረበ ጥናት ላይ  ውይይት ሲደረግ፣ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ላይ ስለተያዘው እቅድ አብራርተዋል።

ላለፉት ዓመታት(እሳቸው  በኃላፊነት ከተሾሙ ጀምሮ)፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ውጤት በከፍተኛ ደረጃ ዝቅተኛ  እንዲሆን ካደረጉ መንስዔዎች መካከል፣ የመምህራን ብቃትና የተነሳሽነት ማነስ ተጠቃሽ መሆናቸው ጠቁመዋል።

ችግሩን በአጭር ጊዜ ለመፍታት እንዲቻል የተለያዩ ተግበራት እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

''የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ'' የሚል መጠሪያ የተሰጠው አሠራር ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ዕቅድ የተያዘ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ "በአራት ዓመት የሚመረቅ ተማሪ፣ የሦስተኛ ዓመት ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ ወደ አስተማረው ማኅበረሰበብ ተመልሶ ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት ይሰጥና (ማኅበረሰቡን እንዲያገለግል ይደረግና) እንዲመረቅ ይደረጋል"ሲሉ ተናግረዋል። ይህም ሲሆን የተማሪዎቹ መሠረታዊ ወጪ የሚሸፈን እንደሚሆንም አክለዋል።

ይህ አሰራር ለተማሪዎች ለራሳቸው የተግባር ትምህርት እንደሚሆንና የበለጠ እንዲበስሉ እንደሚያደርጋቸውም ተናግረዋል።

ተማሪዎች የመምህርነትን ሙያ ተላብሰው በዚያው ወደ ሙያው እንዲያመሩ ዕድል በመፍጠር ለጊዜውም ቢሆን በዘርፉ እየቀነሰ የመጣውን ወደ ሙያው የሚገባ የአስተማሪን ቁጥር ለማሳግ እንደሚረዳም ሚንስትሩ አብራርተዋል።

በቅርቡ በመምህራን ላይ በተደረገ ግምገማ ፣ 100,000 የሚደርስ የመምህራን ዕጥረት መኖሩ መታወቁን የተናገሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ አሰራሩ በከፍተኛ ደረጃ ያለውን የመምህራን ዕጥረት እንዲቀንስ የበኩልን እንደሚወጣ አስረድተዋል።

ወደ መምህርነት ሙያ የሚገቡ ሰዎችን ክፍተት ለማስተካከል ከተያዙ ዘርፈ ብዙ የማትጊያ ሥርዓቶች አንዱ፣ መምህራን በአገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ የራሳቸው ድርሻ እንዲኖራቸውና የኑሮ ውድነቱን እንዲቋቋሙ ለማድረግ፣ "የመምህራን ባንክ" ማቋቋም አንዱ እቅድ መሆኑን አንስተዋል።

ባንኩ "በአንድ ዓመት ውስጥ ወደ ሥራ ይገባዋል ብለን እንጠብቃለን" ያሉት ሚኒስትሩ፣ በ2019 ዓ.ም ደግም በእርግጠኝነት ወደ የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ አሰራር እንደሚገባ ጠቁመዋል።
📄

@officialexit


MRT.pdf
208.2Кб
Nursing.pdf
3.5Мб
Optometry.pdf
23.8Кб
PCHN.pdf
30.2Кб
Public Health.pdf
1.1Мб
Surgical Nursing.pdf
42.5Кб
1. የፈተናው መርሃ-ግብር


ሁሉም ተፈታኝ መጋቢት 30/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ በ 3፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፤ የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት ይኖርበታል::

2. በፈተናው ዕለት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ (የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድ ወይም ሌላ በግልጽ የሚታይ ህጋዊ መታወቂያ) ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡

3. ከላይ ከተጠቀሱት ነገሮች ውጪ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎችን፣ እንዲሁም ባዶ ወረቀቶች፣ ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡

4. በፈተናው ወቅት ተመዛኞች በሁለቱም ክፍለ ጊዜ (ጠዋት እና ከሰዓት በኋላ) አቴንዳንስ ላይ በአግባቡ መፈረማችሁን ማረጋገጥ ይኖርባችኋዋል፣

5. ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን QR code ያለው የፈተና መግቢያ /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እያሳሰብን:-

▪️ ተመዛኞች ወደ ጣቢያ ከመምጣታችሁ በፊት ከዚህ ማስታወቂያ ጋር የተያያዘውን attachment በመክፈት የመረጣችሁትን የፈተና ጣቢያዎች መመልከት ይኖርባችኋል።

▪️ተመዛኞች ስማቸው ከተጠቀሰበት የመፈተኛ ጣቢያ (ተቋም) ውጪ በፍጹም ፈተናውን መውሰድ አይፈቀድም፡፡

▪️ በፈተና ወቅት ለሚገጥማችሁ ማንኛውም ችግር በስልክ ቁጥር 0115186275/ 0115186276 መደወል የምትችሉ መሆኑን ከወዲሁ እናሳስባለን፡፡
📄

@officialexit




#EidAlFitr

የዒድ አልፈጥር በዓል ነገ እሁድ ይውላል።

ዛሬ የሸዋል ወር ጨረቃ በመታየቷ 1446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ነገ እሁድ ተከብሮ ይውላል።


📄

@officialexit




የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ቅደመ ሁኔታ ሆነ
****

ከሰኔ 2017 ዓ.ም ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ቅደመ ሁኔታ መቀመጡ ተገልጿል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደሚመቻችም ነው ተቋሙ ያስታወቀው።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የተማሪዎችን እና የሰራተኞችን መረጃ በተደራጀ መልኩ ለመያዝና ከከፍተኛ ትምህርት መረጃ አገልግሎት ጋር በማስተሳሰር ጥራት ያለው መረጃ ለማግኘት እና የሚሰጡ ሀገር ሀቀፍ ፈተናዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ይረዳል።

📄

@officialexit



Показано 16 последних публикаций.