📚👳‍♂ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት👳‍♂📚


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ የሆነውን የህይወት ቃል ጌታ እግዚአብሔር በገለጠልን ፀጋ መጠን የምንካፈልበት ሲሆን!
" ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤"ቲቶ ፩÷፲፩

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций




ከ17 ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ


❤️“ ንዑ ንትመሀር ልሳነ ግእዝ ”
🔅ኑ የግእዝ ቋንቋ እንማር🔅

📜 የሀገራችን የኢትዮጵያ ቀዳማዊና ጥንታዊ ስለሆነው የግእዝ ቋንቋ መሠረታዊ ትምህርት እንሰጣለን። እርስዎም አባቶቻችን ያቆዩልንን ቋንቋ በመማርና ለትውልድ በማስተላለፍ ኃላፊነትዎን ይወጡ!
📜


Репост из: 🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏
🗓ማኅበራዊ ሚድያን እንደ ቋሚ ዕውቀት መጠቀም ብዙ በሽታዎችን ወደ ውስጣችን ማስተጋባት ነው።
ለአእምሯችን እድገት ሊሆኑ የሚችሉ መጻሕፍትን በማንበብ ግን ከደዌው መላቀቅ ይቻላል።

ፍጡራዊ ሰው ሙሉ የሚሆነው  በትምህርት እና በንባብ ነው።
ከትምህርት እና ከንባብ የተገታ ሰው ግን የወሬ ጋን ነው የሚሆነው።
ማህበራዊ ሚድያ ሀሳብን ለመሸጥ መረጃን ለማየት ነው እንጂ ቋሚ የዕውቀት ቦታ አይደለም።
በረጂም አንቀጽ የተጻፉትን ለማየት ዓይኑን የሚያመው አፉን የሚያዛጋው ሰው በወሬ ሱስ የተሞላ ስለሆነ ነው።
ይሄ ደዌ  ደግሞ በደንብ ተንፍሶ መፈወስ የሚችለው በመጻሕፍት ምርመራ ነው።

✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


Репост из: 🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏
🗓 ነገ ማለትም
ዕለት:- ረቡዕ
#ቀን:- ጥር ፲፬ ፳፻፲፯ ዓ.ም
በቅድስት ቤተክርስቲያናችን


አቡነ አረጋዊ (አመታዊ)
አባ ጳኩሚስ ፣ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ፣ አቡነ ተስፋ ጽዮን ፣ ሰማዕቱ አብሮኮሮስ ፣ አባ ዘሚካኤል ፣ ሙሴ ጸሊም


አክብረን እና አስበን እንውላለን

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


Репост из: ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
+ ንስሐ ግቡ +

የጌታቻን የኢየሱስ ክርስቶስ መጠመቅ አሰቀድሞ በዮሐንስ ለሀጥያት ስርየት ማጥመቅ መንገድ ጠራጊነት የተጀመረ ነው እርሱም እኔስ ለጠጅ ፡ ቢረሌን ፡ ለልብስ ፡ ገላን ፡ እንዲያጥቡለት ፡ ለሱ ፡ ጥምቀት በሚያበቃ ጥምቀት አጠምቃቹሀለው ይል ነበር እንዲሁም እርሱ የሚያጠምቀው ጥምቀት ክርስቶስ ከሚያጠምቀው ጥምቀት ልዩ መሆኑን ሲገልፅ "በመንፈስ : ቅዱስ : እሳትነት" ክፍውን : ሕሊና : ከበጎው : ሕሊና የሚለይበት ስልጣነ ክህነት ገንዘቡ የሚሆንለት በማለት ይገልፃል ። ዮሐንስ ትንቢት የተነገረለት ያለነቀፌታ ይኖሩ ከነበሩ በእግዚአብሔር ፈት ጻድቃን ከነበሩ ከካህኑ ዘካርያስ እና ከኤልሳቤጥ የተወለደ ነው ። በሉቃ 8-11"

***
በእግዚአብሔር ፈት በቤተ መቅደስ ገብቶ የማጠን ተራ በመዓት አንድ ጊዜ የደረሰበት ካህኑ ዘካርያስ በመሰዊያው ቀኝ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት ታየው ። ይህም በዓመት አንዴ ሳይሆን አንድ ጊዜ በፈሰሰ ደሙ አለምን የሚያድን አምላክ ሊወለድ መሆኑን ሲነግረው ነው አንድም ካለመታዘዝ ወደ መታዘዝ የሚመልስ ከጣኦት አምላኪነት ወደ እግዚአብሔር አምላኪነት የሚመልስ ልጅ ትወልዳለህ ሲለው ነው በተጨመሪም በቀኝ እጁ አምላክን የሚያጠምቅ ልጅ ትወልዳለህ እያለ መንገሩ ነው ("ጸያሔ ፍኖት" ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ ) ።

ለዚህም ነበር በሰፈው ፈት ፃድቃን መስለው ይታዩ ለነበሩት በእግዚአብሔር ፈት ፅድቃቸው ከተመሰከረላቸው ቤተሰብ የተገኘው ዮሐንስ እርሱ በጌታ ፈት ታላቅ የሆነ ሉቃ 1፡15 በህሊና የተሰወረውን ክፍ ግብራቸውን ሳይፈራ እግዚአብሔር ገልጦለት ይገስፃቸው ነበር ፈሪሳውያንን "መልካም ፍሬ የማያፈራ ይጣላል " ማቴ 3-10 እያለ የነብያት ልጆች መሆናቸው ብቻ ንስሃ ካለመግባታቸው የሚመጣባቸውን ቅጣት እንደማያስመልጣቸው ክቡዳነ አእምሮ ለሆኑት ለእነርሱ "ንስሀ ግቡ" እያለ ያስተምራቸው ነበር ። ምንመካባቸው ብዙ የተከማቹ ሀብት ይዘን ሊሆን ይቻላል በዘመንድ ብዛት የእከሌ ዘመድ የእከሌ ዘር እያልን ምንመፃደቅባቸው በሰው ፈት ከሁሉ የተሻልን ለመምሰል የምናቀርባቸው ቁሶች ከመቃብር አይሻገሩም ያለን ግዙፍ ቤት በሁሉ ፈት ለመመካት ይዘነው አንዞርም አንድ ቦታ እንደተተከለ ይቀራል የሰማይ መንግስት እንወርስ ዘንድ ዮሐንስ ዛሬም "እንግዲህ ለንስሐ የሚያበቃቹሁን በጎ ስራ ስሩ" ይለናል " ማቴ 3-8 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይለናል " ጸጋስ ይሉሃል የኃጥያት ስርያት ማግኘት "

እንኳን አደረሳቹሁ ። !!!

(ዲያቆን ፍፁም ከበደ)

#ኦርቶዶክሳዊ_አእምሮ


Репост из: ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
#እንኳን_አደረሳቹ #ታኅሳስ_19

"እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ" (ሉቃ 1:19) እና ስለ ነቢዩ ሙሴ "... ስለ ሕዝቡ ባይቆም ኖሮ ሊያጠፋቸው ተናገረ።" (መዝ 125) ... ሁለቱን አነጋገሮች እናስተውላቸው። አንዱ በዚህች ምድር የተደረገ "ስለ ሕዝብ መቆም" (ምልጃ) ነው። ሌላው ደግሞ በመንፈሳዊው ዓለም በቅዱሳን መላእክት የሚደረግ "መቆም" (ምልጃ) ነው። አንዱ በእስንፋሰ እግዚአብሔር ዘመድ በሆነ (በሰው) የተደረገ ነው።... ሌላው ደግሞ በፍቅር እና በመንፈሳዊ ኅብረት አዛማጅነት የሚደረግ ነው።... ሰው ከክርስቶስ በተቀበላት ቤተ ክርስቲያን እና ቤተ ክርስቲያንነት በእርሱም ትክክለኛ እውነታ (Reality) ቅዱሳን ምልጃን ያደርጋሉ። ... በሌሎች ሰዎች የሕይወትና ሞትን መንፈሳዊ ትርጉም ባላገናዘበ፣ ክርስቶስ መጥቶ የ3 ዓመት ትምህርትን "በግል ለግል ያስተማረ" ይመስል ቤተ ክርስቲያንን "ግል" (individual) ብቻ ባደረገው አስተሳሰብ፣ የእውነት ውሏን በትሕትና ከመፈለግ ከማግኘትም ይልቅ በቲፎዞነት፣ "ከእኔ (ከእኛ) በላይ አዋቂ" በሚል የኅሊና ጥመት ባደከመው ዘንድ ቅዱሳን አይማልዱም። ሰው "ጌታ ይበቃኛል" በማለት ራሱን ያታልላል እንጂ "እኔ ለራሴ እበቃዋለሁ" እያለ መሆኑን ከመረዳትም የዘገየ ነው።

የመልአኩን ረድኤት አይለይብን። በቅዱሳን ጸሎት ይማረን።

(ዲያቆን ሚኪያስ አስረስ)

#ኦርቶዶክሳዊ_አእምሮ


Репост из: 🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏
🗓🌴
ከአንድ የሾላ ዛፍ ሥር ስትቃርም የነበረችን አይጥ ከነነፍሷ ለመያዝ ከወደሰማይ የነበረው አሞራ ቁልቁል ተምዘግዝጎ ይወርዳል። ሙከራው ለጥቂት በሚባል ሁኔታ ተሳክቶ የአይጧን ጭራ ይይዛል።

: አካሏ ግን ከዛፋ ሥር ካለ ጉድጓድ ገብቶ በልቀቀኝ ዐይነት መታገል ጀምራለች ጉልበቷን ያልተማመነችው አይጥ አሞራውን ለማጃጃል ጥበብ የተሟላ ንግግሯን ተጠቀመች።

: በዚህ መሰረት "አያ አሞራ! የእኔን ጭራ የያዝክ መስሎህ ከሾላው ሥር ጋር ስትታገል መንቁርህ እንዳይሰበር። ይልቅስ የሾላውን ሥር ልቀቅ አትልፉ"አለችው።

:  ቂላቂሉ አሞራም የያዛትን የአይጥ ጭራ ለቀቀ ይባላል

🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅
🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿
እኛ ክርስቲያኖች ብልህ ልንሆን ይገባል ጠላት ዲያቢሎስ ሊያጠቃን ሲያደባ የአባቶችን ጥበብ በመጠቀም ልናመልጥ ይገባናል
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
የጥበብ አምላክ እግዚአብሔር ማስተዋልና ጥበቡን ያድለን


ለባለ✝️ ማህተቦች ሼር ያድርጉ⁉️
📣📣📣📣📣📣📣
#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ
📣📣📣📣📣📣📣


#ማንም የለኝም ማንም ስለኔ ግድ አይሰጠውም ለምን እንላለን ?

#ከሰው በላይ የሚገዝፈውና የሚበልጠው ስለእኛ የሚያስበው አምላካችንን ለምን እንዘነጋዋለን?

#ስለምን ሲቸግረንና ስንበደል ብቻ ፈጣሪን እናስታውሳለን?

#በተድላም በሃዘንም ጊዜና ቦታ ሳይመርጥ የሚያግዘንና የሚረዳን እርሱ እያለ ስለምን በአላፊ ጠፊ እንታለላለን

#በተሰጠን ነገር አመስንነን ሳንጨርስ ለምን የሩቁን እናልማለን?

^#ለምን#




Репост из: 🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤
የቀድሞው ዘማሪ ሐዋዝ ተገኝ ወደ ቀደመው የአባቱ ቤት ወደሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት መቅደስ ተመልሷል
***

በተ*ዶሶ እንቅስቃሴ ላይ የነበረው የቀድሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዘማሪ የነበረው ሐዋዝ ተገኝ

ቀድሞ ያገለግልባት ወደነበረችው ቅድስት እና ንጽሕት ወደሆነችው ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ መቅደስ በንሰኃ ጥምቀት ተመልሷል።

እግዚአብሔር ይመስገን !!!

#ድምፀ_ተዋህዶ


Репост из: 🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤
+++ድንቅ ልዩነት ተመልከቱ+++

በዓለም ለመጀመሪያ ጊዜ ፈርዲናንድ ማጄላን ዓለምን በመርከብ ዞረ።

👉ሐዋርያቱ ደግሞ መርከባቸውን ጥለው ዓለምን ዞሩ!

ዛሬ ይዘንባል እያሉ ትንቢት የሚተነብዩ ሜትሮሎጂስቶች ሞልተዋል።

👉እንደ ኤልያስ ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን የዘጋ ዳግመኛም ዝናብን ያዘነበ ከቶ የለም።

በላብራቶሪው ተመራምሮ ህሙማንን የፈወሰ ሞልቷል።

👉እንደ ጴጥሮስ ጥላው ድውይ የፈወሰ ከቶ አላየሁም።

በዘፈኑ አጋንንትን የጠራ እንደ ማይክል ጃክሰን ሞልቷል።

👉እንደ ዳዊት በበገና መዝሙሩ አጋንንትን ያስወጣ እስከ ዛሬ አልተገኘም።

ከረቫትና ሱፉን ለብሰን የምንጎራደድ ሞልተናል።

👉የልብሱ ቁጨት አጋንንት ያስወጣ እንደ ጳውሎስ ከቶ አልተገኘም።

የግብጽ ነገሥታት አጽማቸው በክብር ይቀመጣል።

👉ዐጥንቱ ሙት ያስነሳ እንደ ኤልሳዕ ከቶ አላየንም።

በአሜሪካ የነገሥታትን ምሥጢር የሚሰልሉ ድርጅቶች ሞልተዋል።

👉እንደ ኤልሳዕ በእስራኤል ሆኖ በሶሪያ ቤተመንግሥት የሚደረገውን ምሥጢር ያወቀ አልተገኘም።

ለመጀመሪያ ጊዜ ጨረቃን በእግሩ የረገጠ ዩሪ ጋጋሪ ዛሬ ብዙዎቹ አድርገውታል።

👉እንደ ኢያሱ ፀሐይን ያቆመ ከቶ አልተገኘም።

በነገራችን ላይ በተፈጥሮ ሕግ መሰረት ፀሐይ በመሃል ቆማ መሬት ዙሪያውን ትዞራለች። በፀሐይ ፊት ያለው የመሬት ክፍል ቀን ሲሆን ሌላኛው ጎን ደግሞ ማታ ይሆናል።

እነ ኢያሱ በሚዋጉበት ጊዜ መሬት ከፀሐይ ፊቷን አዙራ ቀኑ ሊጨልም ነበር።

👉ኢያሱ ግን መሬት እንዳትዞር አደረጋት! ፀሐይን በገባኦን አቆመ ተባለ! መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ

ሕዝቡም ጠላቶቻቸውን እስኪበቀሉ ድረስ ፀሐይ ቆመ፥ ጨረቃም ዘገየ። ይህስ በያሻር መጽሐፍ የተጻፈ አይደለምን? ፀሐይም በሰማይ መካከል ዘገየ፥ አንድ ቀንም ሙሉ ያህል ለመግባት አልቸኰለም።

👉 እግዚአብሔር ለእስራኤል ይዋጋ ነበርና ((እግዚአብሔር የሰውን ቃል የሰማበት እንደዚያ ያለ ቀን ከዚያም በፊት ከዚያም በኋላ አልነበረም።))
የዓለም መሪዎች ከአስር በላይ ቋንቋ መናገራቸውን እንጃ፤

👉ሐዋርያቱ ግን 72 ቋንቋ ተገለጠላቸው።

ኃያላን ነገሥታት ድውይ እንኳን መፈወስ አይችሉም።

👉ቅዱሳኑ ግን የ70 የ80 ዘመን ሬሳ አስነሱ።

👉ጠቢባን ነን የሚሉ ጸሐፍት ፈሪሳዊያንን ምላሽ ያሳጣቸው ዘንድ ጥበብ ያልነበራቸውን ዓሳ ወጋሪ የነበሩ ሐዋርያትን መረጠ።

ኃያላን ነገሥታት የመሰሉ መሪ ዳዊትን የመሰሉ ነገሥታትን የወለዱ የከበሩ እናቶች ሞልተዋል።

👉የነገሥታትን ንጉሥ ክርስቶስን የወለደች እናት ግን አንድ ብቻ ናት።

ይህችውም ከሴቶች መካከል ተለይታ የተባረከችው ድንግሊቱ 👉 ማርያም ናት 👈

           
ስብሐት ለእግዚአብሔር!

#ድምፀ_ተዋህዶ

https://t.me/dmtse_tewaedo


Репост из: ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ
ጾመ ነብያት ነገ እሑድ ኅዳር 15 ይገባል ።

ነቢያት ጌታ "ይወርዳል ይወለዳል" ብለው የተናገሩት ትንቢት እንዲፈጸም ተመኝተው ጾሙ ጸለዩ:: እኛ ስለምን እንጾማለን? ክርስቶስ ተወልዶ ፣ ተጠምቆ ፣ አስተምሮ ፣ ተሰቅሎ ፣ ሞቶ ፣ ተነሥቶ ፣ ዐርጎ ፣ በአባቱ ቀኝ አይደለምን? አሁን ለምን እንጾማለን? ብለን እናስባለን::

ጌታ በእኔና አንተ ልብ ውስጥ እውነት ተወልዶአልን? እውነት የእኛ ልብ እንደ ቤተልሔም ግርግም ለክርስቶስ ማደሪያ ሆኖአል? ማደሪያ አሳጥተን ከእናቱ ጋር አልመለስነውም?

የጥምቀቱ ትሕትና በእኛ ልብ መቼ ደረሰ? የስቅለቱ ሕማም መች በእኛ ሕሊና ተጻፈ? የትንሣኤው ተስፋ የዕርገቱ ልዕልና በእኛ ልቡና መቼ ዐረፈ?

ስለዚህ ነቢያት "ውረድ ተወለድ" ብለው የጾሙትን ጾም እንጾማለን:: ጌታ ሆይ በእኔ ሕይወትም ውስጥ ውረድ ተወለድ የእኔን ሰውነት ማደሪያህ አድርገው:: ሕዋሳቶቼ ከኃጢአት አርፈው እንደ ቤተልሔም ግርግም ማደሪያህ ይሁኑ::

(ዲያቆን ኄኖክ ኃይሌ )

#ኦርቶዶክሳዊ_አእምሮ


Репост из: 🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤
ጾም በእግዚአብሔር ታዟል፤ተፈቅዷልም ።
++++++++++++++++++++++++++
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾምን እንድንጾም ባርኮ የሰጠን እሱ ነው ።ለዚህም ማረጋገጫ ፦
"ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ።"
ማቴ 9:15
በዚህ መሰረት ፦
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የራሷ የሆነ የጾም ህግና ስርዓት አላት ።
"ነገር ግን ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን ።"እንዲል
1ኛ ቆሮ 14፥40
በቤተክርስቲያናችን ህግና ሥርዓት ተሰርቶላቸው
ከሚጾሙ 7 የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ጾመ ነብያት ይባላል ።የጾሙ ጊዜ ከህዳር 15-እስከ ጌታ ልደት ታህሳስ 28 ድረስ ያለው ነው ።ይህን ጾም የምንጾመው ነቢያት በየዘመናቸው ስለክርስቶስ መምጣት ንጽህት ከምትሆን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን በናፍቆት ይጾሙና ይጸልዩ ስለነበር የእነርሱን አርአያ ተከትለን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት ከማክበራችን ቀደም ብለን ይህን ጾም እንድንጾም በሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ሥርዓት ተሰርቷል። (ፍት.መ.ን.አንቀጽ 15)
ስለሆነም እኛም ክርስቲያኖች ይህን ተከትለን ብልቶቻችንን ሁሉ(አይን ይጹም ፤እጅ ይጹም፤ እግር ይጹም ፤አንደበት ይጹመ...እንዳለ ቅዱስ ያሬድ) ከኃጢአት ጠብቀን፤እግዚአብሔርን ከማያስደስቱ ማናቸውም ነገሮች ራሳችንን አርቀንና ፤በወንድሞቻችን በማናቸውም ላይ ቂም በቀልን በማስወገድ ይቅርም በመባባል ፤ጸሎትን ስግደትን ምጽዋትንም በመጨመር በንጹህ ልቦና መጾም ይገባናል።ይህን ካደረግን ዘወትር የሚዋጉንና የሚፈታተኑን የአጋንንት ሰራዊት በሙሉ ይደመሰሳሉ፤ኃይላቸውም ይደክማል ።ከእግዚአብሔር ከአምላካችን ፍቅርን ሰላምና በረከትንም እንቀበላለን ።
"የጌታ ቃል የታመነ ነውና።"ቲቶ 3:8
".....ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም አላቸው።"
ማቴ 17:21

#ድምፀ_ተዋህዶ

        📹📹📹📹
   ✨ፊላታዎስ ሚዲያ✨
               👇👇
https://youtu.be/PYhgHxupzLI?si=pQaqogjyj_DUcNXW


Репост из: 🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤
በሶሪያ ኦርቶዶክስ  ያዕቆባዊት ቤተክርስቲያን የሕንድ ሜትሮፖሊታን የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፉ

  ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ እ.ኤ.አ ሐምሌ 22 ቀን 1929 ዓ.ም ቡቸንክሩዝ በተባለ የሕንድ ግዛት የተወለዱ ሲሆን እ.ኤ.አ ከሐምሌ 26 ቀን 2002 ዓ.ም ጀምሮ በሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሥር የምትተዳደረውን የሕንድ ቤተ ክርስቲያን ለበርካታ ዓመታት በሊቀ ጵጵስና መርተዋል።

ብፁዕነታቸው በዕድሜና በሕመም ምክንያት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ዕረፍት በማድረግ ሕክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን በዛሬው ዕለት አመሻሽ ላይ በሕንድ ኮቺ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል።

በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ሞር አግናጢዮስ ኤፍሬም ዳግማዊ፣ ለሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣ ለመላው የቤተ ክርስቲያን አባላት፣ ቀሳውስትና ምእመናን በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን። 

የብፁዕነታቸው በረከት አይለየን !!!

© ተሚማ

#ድምፀ_ተዋህዶ

https://t.me/dmtse_tewaedo


Репост из: 🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤
መምህራችን መምህር ኤርሚያስ ታሟል።
አንድ ሰላም ለኪ ድገሙለት እግዚአብሔር በጤና ይመልሰው።

ሰላም ለኪ
ሰላም ለኪ፤ እንዘ ንሰግድ ንብለኪ ፤ ማርያም እምነ ናስተበቊዐኪ ፤ እምአርዌ ነዓዊ ተማሕፀነ ብኪ ፤ በእንተ ሐና እምኪ ፤ ወኢያቄም አቡኪ ፤ ማኅበረነ ዮም ድንግል ባርኪ ።

ጸሎተ እግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ : -
ታዐብዮ ነፍስየ ለእግዚአብሔር ፤ ወትትሐሠይ መንፈስየ ፤ በአምላኪየ ወመድኃኒየ ፤ እስመ ርእየ ሕማማ ለአመቱ ፤ ናሁ እምይእዜሰ ያስተበፅዑኒ ኵሉ ትውልድ ፤ እስመ ገብረ ሊተ : ኃይለ ዐቢያተ ፤ ወቅዱስ ስሙ ፤ ወሣህሉኒ : ለትውልደ ትውልድ ፤ ለእለ ይፈርህዎ ፤ ወገብረ ኃይለ በመዝራዕቱ ፤ ወዘረዎሙ ለእለ የዐብዩ ኅሊና ልቦሙ ፤ ወነሠቶሙ ለኃያላን እመናብርቲሆሙ ፤ አዕበዮሙ ለትሑታን ፤ ወአጽገቦሙ እምበረከቱ ለርኁባን ፤  ወፈነዎሙ ዕራቆሙ ለብዑላን ፤ ወተወክፎ ለእስራኤል ቊልዔሁ ፤ ወተዘከረ ሣህሎ ፤ ዘይቤሎሙ ፤ ለአበዊነ : ለአብርሃም ፤ ወለዘርዑ እስከ ለዓለም ፤ አሜን ።

አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ትምጻእ መንግሥትከ። ወይኩን ፈቃድከ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር ሲሳየነ ዘለለ ዕለትነ ሀበነ ዮም። ኅድግ ለነ አበሳነ ወጌጋየነ ከመ ንህነኒ ንኅድግ ለዘአበሰ ለነ። ኢታብአነ እግዚኦ ውስተ መንሱት። አላ አድኅነነ ወባልሓነ እምኲሉ እኩይ እስመ ዚኣከ ይእቲ መንግሥት ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም።

በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል መልአክ ኦ እግዝእትየ ማርያም ሰላም ለኪ ድንግል በኅሊናኪ ወድንግል በሥጋኪ እመ እግዚአብሔር ጸባዖት ሰለም ለኪ ቡርክት አንቲ እም አንስት ወቡሩክ ፍሬ ከርሥኪ ተፈስሒ ፍስሕት ኦ ምልዕተ ጸጋ  እግዚአብሔር ምስሌኪ ሰአሊ ወጸልዪ  ምሕረተ ኀበ ፍቁር ወልድኪ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ይሥረይ ለነ ኃጣውኢነ።
ምህረቱን ይላክሎት መምህር


Репост из: 🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤
የ ሀዋሳ ዩንቨርሲቲ 3ኛ አመት የAccounting ተማሪ
የሆነችው እህታችን ሀይማኖት ደግፌ ባደረባት ህመም ምክንያት ትምህርቷን መከታተል አልቻለችም ህመሟም የጡንቻካንሰር አይነት ሲሆን በህክምና አጠራሩ Rhabdomiosarcoma ሲሆን ለዚህም በሰርጅሪ ህክምና ተድርጎላት አሁን የ chemotherapy ህክምና እየወሰደች ትገኛለች ቀጥሎም የ Radiotherapy ህክምና ያስፈልግታል ለዚህም ደግሞ የሚያስፈልገው ገንዘብ ሲሰላ ከ 100,000 ብር በላይ ድረስ ያስፈልጋታል ለዚህም እሷም ሆነ ቤታሰቦቹዋ የማሳከም አቅም ስለሌላቸው እናንተ
ወገኖቻችን ወገናዊ እጃችሁን እንድትዘረጉልን ስንል በትህትና እንጠይቃለን።
እባካችሁ እህታችንን በአቅማችን በመርዳት ወደ ቀድሞ ጤንነቷ ተመልሳ ትምህርቷን እንድትከታተል እንድትተባበሩን እንጠይቃለን።


Haymanot Degife Bosen 1000191370922

በስልክም ማነጋገር ለምትፈልጉ 0986252118


"እንዲሁ እየደከማችሁ ድውዮችን ልትረዱና እርሱ ራሱ፡ ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው እንዳለ የጌታን የኢየሱስን ቃል ልታስቡ ይገባችሁ ዘንድ በሁሉ አሳየኋችሁ።" ሐዋ 20:35




Репост из: 🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤
እንኳን ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደርሳቹ❗️

ጥቅምት 5-ኑሮአቸው እንደሰው ያይደለ በምድረ በዳ እንደመላእክት የኖሩትና በዝቋላ ተራራ ባለው ባሕር ውስጥ 100 ዓመት ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ሰዎች ምሕረትን የለመኑት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታላቅ ቃልኪዳን የተቀበሉበት ዕለት ነው፡፡ 

አባታችን አራት ሺህ እልፍ እየሰገዱ፣ 300 ጊዜ የቀኝ 300 ጊዜ ደግሞ የግራ ፊታቸውን በድንጋይ እየመቱ፣ መዝሙረ ዳዊትን እየደገሙ፣ 15ቱን መኅልየ ነቢያት፣ መኅልየ ሰለምንንና ውዳሴ ማርያም እየጸለዩ ለኃጥአን ምሕረትን ሲለምኑ ዕንባቸው እንደ ውኃ ይፈስ ነበር፡፡ ጌታችንም ‹‹በተወለድሁባት፣ በተጠመቅሁባትና ከሞት በተነሣሁባት ዕለት እልፍ እልፍ ነፍሳትን እምርልሃለሁ›› የሚል ቃል ኪዳን ሰጣቸዉ

አምላካችን በቃል ኪዳናቸው ይማረን


✝️#ድምፀ_ተዋህዶ ✝️


Репост из: 🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤
“አሁን ባለን የአስተዳደር ክፍተቶችና በውስጣችን ያሉ ግልጽነት የጎደላቸው አሠራሮች ለአገልግሎታችን እንቅፋት እየሆኑብን ነው”ሲሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገለጹ፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት 43ኛው ዓለም አቀፍ መደበኛ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ለተገኙ ተሳታፊዎች መልእክት አስተላልፈዋል።

ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው አሁን ባለን የአስተዳደር ክፍተቶችና በውስጣችን ያሉ ግልጽነት የጎደላቸው አሠራሮች ለአገልግሎታችን እንቅፋት እየሆኑብን ነው። በዚህ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን የሚታየውን  ችግር ለመፍታት በጥናት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ማምጣት ይገባል ሲሉ አፅዕኖት ሰጥተዋል፡፡

ቅዱስነታቸው ጨምረው እንደገለጹት ቅዱስ ሲኖዶስ ተግባራዊ እንዲሆን የወሰነውን የቤተ ክርስቲያን የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ ውጤታማ ለማድረግ ሁላችንም በትብብር መሥራት ይገባናል ብለዋል።

በዛሬው ዕለት የተጀመረው 43ኛው አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ ከሀገር ውስጥ እና ውጪ ከሚገኙ አህጉረ ስብከቶች፣ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራት እና ገዳማት እንዲሁም ከተለያዩ መንፈሳዊ ማኅበራት የተወከሉ ተሳታፊዎች በተገኙበት እየተከናወነ ይገኛል።

#ድምፀ_ተዋህዶ


Репост из: 🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤
አዲስ መፅሐፍ ምረቃ

ርእሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረኪዳን ግርማ አሐቲ ድንግል የተሰኘውን መጽሐፍት ሊያስመርቁ ነው

ጥቅምት 2/2017 ዓ.ም በቦሌ መድኃኔዓለም አዳራሽ ከቀኑ 7:30 ጀምሮ

መጽሓፉ
ርእሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ:
1•የእመቤታችንን  ሕይወት  የያዘ ሙሉ የነገረ ማርያም  አስትምህሮ
2•በነገረ ድኅነት ያላት ድርሻ
3•ዕርገቷን የሚመለከቱ
4•እመቤታችንን የሚመለከቱ ጥያቄዎች
5•በእመቤታችን ፍቅር እንዴት መጽናትና ማደግ ይቻላል?

የሚሉትን ዓበይት ጉዳዮች የሚተነትን ነው

628 ገጾች
12 ምእራፎች አሉት
#ድምፀ_ተዋህዶ
https://t.me/dmtse_tewaedo

Показано 20 последних публикаций.