ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ።
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ››
ት.ኢሳ 58÷3
https://youtu.be/csxxAMGtC4I
ለመቀላቀል
http://t.me/ortodoxtewahedo

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций




ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo.


የተሰበረ ጽዋዕ
እዚኽ ፎቶ ውስጥ በአካል የማውቀው ዘማርያምን ብቻ ነው፡፡ ሌሎች ግን በማኅበራዊው ሚዲያ መልስ ሲሰጡና ሲጠይቁ አያቸዋለሁ እንጂ ፊት ለፊት ተገናኝተን አናውቅም፡፡በወንድሞቻችን ፊት ፕሮቴስታንት ሰባክያን ምላሳቸውን ሲተሳሰር ብዙ ጊዜ አይቻለኹ፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ "ከኦርቶዶክስ ወንድሞች ጋር እንዳትከራከሩ" የሚል አዋጅ ሲያውጁ ሰምቻለኹ ጰንጤዎቹ፡፡
በአጭሩ፥ እኒኽ ወንድሞቻችን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳን መላእክትና ሰዎችን ታመልካለች የሚለውን ፕሮቴስታንታዊ የድር ምሽግ ሲበጣጥሱ ተመልክቻለኹ፡፡ ከዐይን ያውጣችኹ አልላችኹም፡፡ ዐይንም ጆሮም ውስጥ ናችኹና፡፡
ጽንዑ ወኀይሉ፡፡ ለማለት ነው አመጣጤ፡፡
ከእኒኽ ወንድሞች መኻል አንዱ ወይም ኹሉም ሊሳሳቱ የሚችሉ ናቸው፡፡ የቀለም ሠረገላ የማያሰናክለው የለምና፡፡
ደግሞም እኔ እንኳ የሰማኋቸው የሚታረሙ ስሕተቶች አሉ፡፡የሚታረም ነገር ተገኘ ማለት ግን፥ ሙሉ እርሻው አረም ነውና አያስፈልግም የሚል ቧልት መናገር ቅንነትና ወንድማዊ ፍቅር ይጎድለዋል፡፡
በአንድ ወቅት፦
አንድ እጅግ የተከበሩ ሊቅ ከአንዲት ሴት ጋር ድቀት አገኛቸው፡፡ እኒኽን ሊቅ ብዙ ሰው ያውቃቸዋል፡፡ በዚኽኛው ታሪክ ግን ሰፊው ሕዝብ ስለማያውቃቸው ስማቸውን ልለፈው፡፡
ይኽን ድቀታቸውን የሰማ ደብተራ አንድ ቀን ማሕሌት ውስጥ አገኛቸው ሊቁን፡፡"ደግሞ አንተ እዚኽ ምን ልታደርግ ገባኽ?"
ሲል በፍና ተሣልቆ አፌዘባቸው፡፡ እርሳቸውም "እኔኮ የተሰበርኩ ጽዋዕ ነኝ" ብለው አንጀት የሚበላ መልስ ሰጡት፡፡
የተሰበረ ጽዋዕ ሰባራ ስለኾነ አይጣልም፡፡ንዋይ ቅዱስ ነውና በክብር ከዕቃ ቤት ይቀመጣል እንጂ፡፡

እንደዚያ ደብተራ ለቤተክርስቲያን የቀናን እየመሰለን ጥቂት ሸራፋ ያገኘንባቸው ጽዋወችን ኹሉ አውጥተን እንጣል ማለት እጅግ የከፋ በደል ነው፡፡ክርስቶሳዊውን መንገድ የረሳ ነውና፡፡ "ድኅረ ተሰብረ አጽንዖ ለሰብእናነ ልሕኵት፥ ለብሓዊ ክርስቶስ በማየ ሐዲስ ጥምቀት" የምትል ድንቅ የንጉሥ ጉባኤ ቃና አለች፡፡ ግርድፍ ትርጉሟ፦ ገላ'ችን ከተሰበረ በኋላ ሸክላ ሠሪው ክርስቶስ በአዲስ የውኀ ጥምቀት እንደገና ሠራው፡፡ ማለት ነው፡፡ ቤተክርስቲያን ከጌታዋ የተማረችው የተሰበረን መጠገን ነው፡፡
ችግሩ፥ መጠገን እንደመስበር ቀላል አይደለም፡፡ ለመጠገን ዕውቀትና ቅንነት ያስፈልጋል፡፡ ለመስበር ግን ኦርቶዶክሳዊ የዘብነት ቀለም የተቀባች ምላስ በቂ ናት፡፡
ወንድሞች በጎ ሲሠሩ እናበርታ፡፡ሲስቱ እንክርዳድ ከስንዴ እየለየን በፍቅር እናርም፡፡አልታረምም የሚል ካለ ደግሞ የቤክርስቲያን ቱንቢ ያርመዋል፡፡እንደ ግለሰብእ እኔ ነኝ ቱንቢው ማለት ግን የስሕተት ስሕተት ነው፡፡

በየሚዲያው ሌሎች ጥሩ ወንድሞችም አሉ፡፡ ነገር ግን በልዩ ልዩ የቤተክርስቲያን አገልግሎት የተገለጡ ናቸውና ተውኳቸው፡፡

መ/ር ስሙር

ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo.


💕ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይ ፈ ል ጋ ሉ ? 🔔 💕

[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛


🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧


Репост из: ኦርቶዶክሳዊ ቻናል
መልካም ዜና ለአእላፍት ዝማሬ ቤተሰቦች ❤️‍🔥

የአእላፍት ዝማሬ መዝሙሮችን በነፃ የምታገኙበት አዲስ ቻናል ተገኝቷል፣ በቀላሉ ቻናሉን ለማግኘት
👇


ተአምረ ማርያም
             
Size:-120.6MB
Length:-2:10:16

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo.


#ቅዱስ_ኡራኤል_እንኳን_አደረሳችሁ_አደረሰን

ኡራኤል ማለት ምን ማለት ነው ?

ኡራኤል ማለት ትርጉሙ #የብርሃን_ጌታ_የአምላክ_ብርሀን ማለት ነው ::
ቅዱስ ኡራኤል ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ  ጋር ወደ ግብፅ ስትሰደድ መንገድ የመራ የረዳ መልአክ ነው ::ክርስቶስ ለአለም ቤዛ በተሰቀለ ጊዜ ክቡር ደሙን በብርሀን ፅዋ ተቀብሎ በብርሀን በመነስነስ ለአለም የረጨ "ለነብዩ እዝራ ሱቱኤል ፅዋ ጥበብ ያጠጣ እርሱ ነው ::ይህ መልአክ ያፅናናናል ይታደገናል ይመግበናል ይመራናል ስሙ ከወጥመድ ከሰይጣን ከክፉ መናፍስት ውጊያ ሁሉ ይጠብቀናል ::

#ኡራኤል ፦ እግዚአብሔር ፍጹም ብረሃን ነው ፣የብረሃናት ጌታ ፣የብረሃናት አምላክ እራሱ የምያበራል የነፍሳችን ብረሃን ሲል ይተርጉመዋል።

ይህ ቅዱስ መላዕክ በመብርቅ ፣በነጉድጓድ ላይ ከፍጥረት ጅምሮ የተሾመ ቅዱስ መላዕክ ነው።

ለመቅስፍት ሳይሆን ለበረከት ለበዓት ሳይሆን ለይቅርታ የሚላክ መላዕክ ነው ።

የጌታችን መዳኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ደም በብርሃን #ጽዋ ቅድቶ ለአለም የረጨ ቅዱስ መላዕክ ነው። (#ሔኖክ28;13)

እንኳን አደረሰቹ አደረስን የመላኩ ጥበቃው አይለየን ።

  ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo.


የሰማዕታት ውበት
             
Size:-59.9MB
Length:- 1:04:40

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

  ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo.


#አስተርዮ ማርያም ።

  ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo.


#አስተርዮ ማርያም

የማይታየው የታየበት፣ የራቀው የቀረበበት፣ የረቀቀው መለኮት በገዘፈ ሥጋ ማርያም የተገለጠበት፣ የወልድ ልጅነት በአብና በመንፈስ ቅዱስ የተመሰከረበት፣ በልደቱ፣ በጥምቀቱ አንድነት በሦስትነት እንዲሁም መለኮት በሥጋ ሥጋም በመለኮት በተዋሕዶ ተገልጦ ምሥጢሩ ገሃድ የሆነበት የመገለጥ የመታየት ጊዜ የሆነው ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ  ዘመነ አስተርዮ እየተባለ ይጠራል፡፡
በዚሁ በዘመነ አስተርዮ መካከል የሚገኝ ስለሆነ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም “በዓለ ዕረፍት አስተርዮ ማርያም” እየተባለ ይጠራል፡፡ ይህ አስተርዮ ማርያም የምንለው ታላቅ በዓል እናታችን እመቤታችን ከዚህ ዓለም ድካም ያረፈችበት መታሰቢያ ሲሆን ቀኑም ጥር ፳፩ ነው፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን የወሰነች፣ ሞትን በሞቱ የመሻር ሥልጣን ያለውን፣ ዓለምን በመዳፉ የጨበጠውን የወለደች ክብርት ቅድስት እመቤታችን ከዚህ ዓለም ድካም የምታርፍበት ቀን በደረሰ ጊዜ ይኸውም ጥር ፳፩ ቀን በዕለተ እሑድ በ፷፬ ዓመቷ፣ በ፵፱ ዓ.ም መንፈስ ቅዱስ የዕረፍቷ ጊዜ መድረሱን ነግሯት በልጇ መቃብር ሆና ጸሎት ታድርስ ነበር፡፡ እንዲህም ብላ ጸለየች፤ ‹‹ልጄ ወዳጄ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሐንስን በዚህች ሰዓት አምጣው፤ እንዲሁም በሕይወተ ሥጋ ያሉ ሐዋርያትን ሁሉንም፣ ነፍሳቸውንም የለየሃቸውን አምጣቸው፤ አንተ የሕያዋንና የሙታን አምላክ ነህና›› አለች፡፡ (የጥር ፳፩ ስንክሳር)
በዚህ ጊዜ ዮሐንስን ደመና ተሸክማ ከኤፌሶን አመጣችው፤ ምስጋናም አቀረበላት፤ ሁሉም ሐዋርያት የሞቱትም ከመቃብር ተነሥተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት፡፡ እንዲህም ስትል ጠየቀቻቸው፤ ‹‹ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ፤ ከዚህ ዓለም እንደምለይ ከወዴት ሰማችሁ?›› አለቻቸው፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ‹‹ወደ አንቺ እንድንመጣ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን፤ በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወደ አንቺ እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን›› አላት፡፡ በዚያን ጊዜ የክብር ባለቤት ልጇ ወዳጇ ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍ መላእክቱን አስከትሎ ወደ እርሷ መጣ፡፡ (ጥር ፳፩ ስንክሳር)
እንዲህም አላት ‹‹እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጥቻለሁ›› አላት፡፡ እርሷ ግን ‹‹ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑህን ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማኅፀኔ ተሸክሜህ፤ በድንግልና ወልጀህ እሞታለሁን?›› አለችው፡፡ በዚህ ጊዜ በሲኦል የነበሩ ነፍሳትን ሁሉ አሳያትና ‹‹እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ሁሉ ነፍሳት መዳን ምክንያት (ቤዛ) ይሆናቸዋል›› አላት፡፡ ‹‹እነዚህን ሁሉ ከማርክልኝስ ይሁን››  አለች፡፡ በዚህ ጊዜ ቅድስት ሥጋዋን ከክብርት ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በይባቤ መላእክት በክብር ነፍሷን ዐሳረጋት፡፡ (መዝገበ ታሪክ ቁጥር አንድ ገጽ ፻፶፭፣ ጥር ፳፩ ስንክሳር)
የእመቤታችን አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን!

ምንጭ 👉 ማኅበረ ቅዱሳን


አስተርዮ ማርያም ።

  ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo.




ብርብር ማርያምን የማያውቅ ኦርቶዶክስ የአንድ ብሔር ይመስለዋል
***

የኦርቶዶክሳዊት መቅደስ ባለቤቷ ማን ነው ከተባለ በአንድ ቃል ....ኢየሱስ ከሚል ስም ላይ ይወድቃል።

ባህሪዋም ቅድስት እና ኩላዊት ሲሆን ብዛቷም አንድ ነው።

ጠላት ግን ሲከሳት የነፍጠኛ ሃይማኖት፣የገዢ መደብ ቤት ብሎ ባልዋለችበት ስሟን ይጠራሉ።

ባሻዬ ....

በእርግጠኝነት ብርብር ማርያም የሚባል ገዳምን ብታውቅ ቅድስት ቤተክርስቲያን ከየትኛውም ብሔር ትከሻ ተንጠልጥላ እንዳልመጣች ትረዳለህ።

ደቡብ በሚባለው ስፍራ ህዝብ እንዲህ ሳይሰፍር ብርብር በምትባል ስፍራ ላይ ንጉስ ቆስጢንጢኖስ አርዮስን በኒቂያ ጉባኤ ይወገዝ ዘንድ ጉባኤ አበው ከዘረጋ ከ3 ዓመት በኃላ በ328 ዓ.ም

ወደእዚህች ስፍራ ታቦተ ገብርኤል እና ታቦተ ማርያምን ይዞ በመምጣት ለ1100 ዓመት በስፍራው ተሰርቶ የነበረውን መሰዋተ ኦሪት ለውጦ ወደ ህገ ወንጌል ቀይሯል።

በእዚህ ስፍራ የነበሩት ቀደምት የጋሞ ህዝቦች ከእግዚአብሔር ጋር የተዋወቁት ክርስቶስ በቤቴልሔም ከመወለዱ ከ800 ዓመታት በፊት በካህኑ ሳዶቅ ልጅ አዛርያስ በኩል እንደሆነ ብነግርህስ?

አንተ ከምትከሳቸው ነገስታት የሥነ ህዝብ ስርዓት በፊት ብርብር በሚባል ማማ ላይ ከህገ ኦሪት እስከ ህገ ወንጌል ተዘርግቶ በአዲስ ኪዳን ዘመን ኦርቶዶክስ የምትባል የእምነት አስተሳሰብ የያዘች መቅደስ በእዚህ ከፍታማ ስፋራ ላይ ነበረች።

የዛሬን አያድርገው እና ይህቺ ስፍራ የእውቀት ፣የምስጋና እና የሊቃውንት መፍለቂያ እንደሆነች አባ ባሕርይ የተባሉ መኖክሴ አማናዊ ምስክር ናቸው።

የቅድስት ቤተክርስትያን የጸሎት እና የታሪክ መጽሐፍ ብርብር ከሚባል ማማ ላይ እንደሚገኝ መዝሙረ ክርስቶስን ብታገላብጥ ታውቅ ነበር።

ስለዚህ ባሻዬ.... ለኦርቶዶክስ ገዢ ፈላጭ እና ፈጣሪ አካል ስትሰጣት "ኢየሱስ" ከሚለው ስም ውጪ ዕጣ አትጣልባት።

ለኦርቶዶክሳዊት መቅደስ ብሔርም ይመደብ ዘንድ ከተገባ ብሔሯ ሰማያዊት እንደሆነች ከእኛ ከልጆቿ አንደበት ሰምተህ አስተጋባ።

@ጥንታዊት ጽዮን ሰማያዊት ብርብር ማርያም 2015 ዓ.ም

እግዚአብሔር ይመስገን!!!

Kune Demelash kassaye -Arba Minch

@ortodoxtewahedo


አስተርዮ ማርያም ።

@ortodoxtewahedo


ገብርኤል ሆይ፤ ከሰው ወገን ጠዋትና ማታ ከቶ እንደ እኔ ኀዘንና ትካዜ የሚበዛበት የለም፣
ከመላእክትም ወገን እንደ አንተ ያዘኑትን የሚያረጋጋ የለም፣
ገብርኤል ሆይ፤ ስለዚህ እኔም አውቄና አንተን አምኜ ያቀረብኩትን ይህን ጸሎት እንደ ትልቅ ዋጋ ቆጥረህ የሚያረጋጋ ቃልህን አሰማኝ።

መልክአ ገብርኤል

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓል በሰላም አደረሰን።

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo


# መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል

❖ ከ7ቱ ሊቀነ መላእክት አንዱ ነው።

❖ ገብርኤል ማለት የስሙ ትርጉም የእግዚአብሔር ልጅ የሚመስል የእግዚአብሔር ሰው ማለት ሲሆን
ት.ዳን 3+25ሕዝ 9፥2 በተጨማሪም መጋቤ ሐዲስ( የሐዲስ ኪዳን አስተማሪ) እግዚእ ወገብረ (እግዚአብሔር አደረገ ) ማለት ነው።

❖ ብስራታዊ (አብሳሪው) መልአክ ነው። እመቤታችንንና ዘመዷ ኤልሳቤትና አብስሮአልና።

❖ ቅዱስ ገብርኤል አርባብ የተበለው ነገደ መላእክት አለቃ ነው።

❖ በመጀመሪያው የመላእክት ጦርነት ጊዜ አምላካችንን እስክናውቅ ባለንበት ፀንተን እንቁም በማለት መላእክት ያፀናቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው።
❖ ተራዳዩ መልአክ ነው።

ዳን ፫፥፲፱-፳፯፣ዳን ፰፥፲፭ ዳን፱፥፳፩-፳፯
❖ ቅዱስ ገብርኤል ከ፯ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ነው።

❖ በጎ በጎውን የምንሰማበት መልካም መልካሙን የምናደርግበት መልካም ቀን ይሁንልን።

ቅዱሳኑን ያዳነ ቅዱስ መልአክ እኛንም ያድነን ዘንድ እንደ አባቶቻችን "አድኅነኒ ዘአድኃንኮሙ በአክናፊከ ምንትው:: አመ ውስተ እሳት ተወድዩ ሠለስቱ እደው::" እያልን እንለምነው::

(መልክዐ ገብርኤል)

"በአምላኬም በእግዚአብሔር ፊት ስለ ተቀደሰው ስለ አምላኬ ተራራ ስለምን: ገናም በጸሎት ስናገር አስቀድሜ በራእይ አይቼው የነበረው ሰው ገብርኤል እነሆ እየበረረ መጣ:: በማታም መሥዋዕት ጊዜ ዳሰሰኝ:: አስተማረኝም ." †

(ዳን. ፱፥፳)

ቅዱሳኑን ያዳነ ቅዱስ መልአክ እኛንም ያድነን ዘንድ እንደ አባቶቻችን "አድኅነኒ ዘአድኃንኮሙ በአክናፊከ ምንትው:: አመ ውስተ እሳት ተወድዩ ሠለስቱ እደው::" እያልን እንለምነው::

(መልክዐ ገብርኤል)

"በአምላኬም በእግዚአብሔር ፊት ስለ ተቀደሰው ስለ አምላኬ ተራራ ስለምን: ገናም በጸሎት ስናገር አስቀድሜ በራእይ አይቼው የነበረው ሰው ገብርኤል እነሆ እየበረረ መጣ:: በማታም መሥዋዕት ጊዜ ዳሰሰኝ:: አስተማረኝም ." †

(ዳን. ፱፥፳)

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo


"ቤተክርስቲያንን የሚያስቀጥሉ ሦስት ሰንሰለቶች አሉ እነርሱም:---
ትዳር ፣ ምንኩስና እና ክህነት ናቸው።

እነዚህ እክል ስለገጠማቸው ነው ቤተክርስቲያን እየተቸገረች ያለቸው እንጂ ሌሎች ሰዎች ወይም አህዛብ ክፉ ስለሆኑ አይደለም። እነሱ ደግ የሚሆኑበት ዘመን ነገም እኔ አልጠብቅም ሰይጣን ባለበት መልካም ነገር አይመጣም።

እኛ ግን የጎደለን ይህ ነው፣ በተከበረ ትዳር ፣በተከበረ ምንኩስና እና በተከበረ ክህነት ቤተክርስቲያን ትቀጥላለች።

ምሳሌ እንዴት ካልን፦
የተከበረ ትዳር:- የተከበረ መነኩሴ ይወልዳል።
የተከበረ መነኩሴ:- የተከበረን ጵጵስናን ያመጣል።
የተከበረ ጳጳስ:- የተከበረን ክህነትን ይሾምና
የተከበረው ክህነት:- የተከበረ ትዳርን ባርኮ ያጋባል። የተከበረው ትዳር መልሶ እንደገና የተከበረ ካህንን ይወልዳል።

በዚህ ዑደት ነው ቤተክርስቲያን ተጠብቃ የምትኖረው። አሁን ግን ምንጩ ደፍርሷል። ለዚህም ሁላችንም መስተካከል አለብን። አሁን እኔ ሁሉም ሥርዓት እየፈረሰ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ! ተምረን ማግባትና፣ተምረን መመንኮስም ሆነ ክህነት መያዝን ማስቀጠል አለብን።"

ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
   ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo


# መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል

❖ ከ7ቱ ሊቀነ መላእክት አንዱ ነው።

❖ ገብርኤል ማለት የስሙ ትርጉም የእግዚአብሔር ልጅ የሚመስል የእግዚአብሔር ሰው ማለት ሲሆን
ት.ዳን 3+25ሕዝ 9፥2 በተጨማሪም መጋቤ ሐዲስ( የሐዲስ ኪዳን አስተማሪ) እግዚእ ወገብረ (እግዚአብሔር አደረገ ) ማለት ነው።

❖ ብስራታዊ (አብሳሪው) መልአክ ነው። እመቤታችንንና ዘመዷ ኤልሳቤትና አብስሮአልና።

❖ ቅዱስ ገብርኤል አርባብ የተበለው ነገደ መላእክት አለቃ ነው።

❖ በመጀመሪያው የመላእክት ጦርነት ጊዜ አምላካችንን እስክናውቅ ባለንበት ፀንተን እንቁም በማለት መላእክት ያፀናቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው።
❖ ተራዳዩ መልአክ ነው።

ዳን ፫፥፲፱-፳፯፣ዳን ፰፥፲፭ ዳን፱፥፳፩-፳፯
❖ ቅዱስ ገብርኤል ከ፯ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ነው።

❖ በጎ በጎውን የምንሰማበት መልካም መልካሙን የምናደርግበት መልካም ቀን ይሁንልን።

ቅዱሳኑን ያዳነ ቅዱስ መልአክ እኛንም ያድነን ዘንድ እንደ አባቶቻችን "አድኅነኒ ዘአድኃንኮሙ በአክናፊከ ምንትው:: አመ ውስተ እሳት ተወድዩ ሠለስቱ እደው::" እያልን እንለምነው::

(መልክዐ ገብርኤል)

"በአምላኬም በእግዚአብሔር ፊት ስለ ተቀደሰው ስለ አምላኬ ተራራ ስለምን: ገናም በጸሎት ስናገር አስቀድሜ በራእይ አይቼው የነበረው ሰው ገብርኤል እነሆ እየበረረ መጣ:: በማታም መሥዋዕት ጊዜ ዳሰሰኝ:: አስተማረኝም ." †

(ዳን. ፱፥፳)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †

ለመቀላቀል👉@weludebirhane

#አቤቱ የሆነብንን አስብ

#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/

@ortodoxtewahedo


ገብርኤል ሆይ፤ ከሰው ወገን ጠዋትና ማታ ከቶ እንደ እኔ ኀዘንና ትካዜ የሚበዛበት የለም፣
ከመላእክትም ወገን እንደ አንተ ያዘኑትን የሚያረጋጋ የለም፣
ገብርኤል ሆይ፤ ስለዚህ እኔም አውቄና አንተን አምኜ ያቀረብኩትን ይህን ጸሎት እንደ ትልቅ ዋጋ ቆጥረህ የሚያረጋጋ ቃልህን አሰማኝ።

መልክአ ገብርኤል

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓል በሰላም አደረሰን።

@ortodoxtewahedo


✞ ጊዮርጊስ ✞

ሰማዕተ ኢየሱስ የእውነት ምስክር
ኅያውን ነው በሰማይ
ብጹዕ ነው በምድር
ደራጎንን በጦር ወግቶ ገደለና
ከሞት አፍ አዳነኝ ጊዮርጊስ ደረሰና

የሀዘን ማዕበል እንዳያንገላታኝ
ታምር ሰሪው ሰማዕት ፈጥኖ አረጋጋኜ
በእግዚአብሔር ጣዕም በፍቅሩተጠምዷል
ይህን አለም ንቆ በክብር አጊጧል
አፍጣኒተ ረድኤት ቅዱስ ጊዮርጊስ
ፈጥነህ የምትደርስ ከአውሎ ነፋሴ
ስምህ የተጠራ የኢትዮጵያ ገበዝ
አድናት ሃገሬን ከገጠማት ትካዝ
አዝ= = = = =
እርሱ ለምጠራው ሲመሽም ሲነጋ
ዋስ ጠበቃዬ ነው በነፍስም በስጋ
ድንቅ የሚፈፅም ሀያል ሰማዕት ነው
በቅድመ እግዚአብሔር ለእኔ የሚቆመው
አፍጣኒተ ረድኤት ቅዱስ ጊዮርጊስ
ፈጥነህ የምትደርስ ከአውሎ ነፋሴ
ስምህ የተጠራ የኢትዮጵያ ገበዝ
አድናት ሃገሬን ከገጠማት ትካዝ
አዝ= = = = =
የምስጋናን አውታር የታጠቀ ሰማዕት
ስሙን ተሸክሞ የታመነ እስከሞት
ሙታንን የሚያስነሳ ስልጣን ተቀብሏል
በአባቱ መንግስት እንደ ፀሐይ ደምቋል
አፍጣኒተ ረድኤት ቅዱስ ጊዮርጊስ
ፈጥነህ የምትደርስ ከአውሎ ነፋሴ
ስምህ የተጠራ የኢትዮጵያ ገበዝ
አድናት ሃገሬን ከገጠማት ትካዝ


መዝሙር
ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ

   ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo.


የቸርነት በር
             
Size:-93.4MB
Length:-1:40:54

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

   ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo.

Показано 20 последних публикаций.