Фильтр публикаций


Репост из: Wave folder
🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑
ሰበር ዜና በ አጭር ግዜ ተወዳጅነትን የገኙ በአማርኛ በኦሮሚኛ እና በእንግሊዝኛ የሚለቀቁ አስተማሪ ና አዝናኝ ቻነሎችን ይ🀄️ላ🀄️ሉ 👇👇
Free promotion የሚትፈልጉ
Channel ያላችሁ በ @seer_lewi አነግሩኝ 👇👇👇


ከእግዚአብሔር ጋር የሚቆዩት እስከ መብል የሚከተሉት አይደሉም፤ የሚቆዩት እርሱ የሚሰራባቸው ናቸው፤ የሚቆዩት ቁምነገራቸው የሕይወት ቃል እንጂ የእንጀራ ጉዳይ አይደለም። ከመብልና ከመጠጥ እልፍ ያላሉት ግን የሚፈልጉት የሆዳቸው ጉዳይ አይጉደል እንጂ ስለ ምግቡ ሲሉ መከተላቸው አይቀርም፤ ጉዳያቸው ከመብሉ ሳይሆን ከሰጪው የሆነላቸው ግን ባይሰጣቸው፣ ባያበላቸው እንኳን ስለ ሕይወት ቃል ሲሉ መከተላቸውን አያቆሙም። እርሱም ጉዳያቸው መብሉ ሳይሆን እርሱ ራሱ መሆኑን ያወቁትን፦ ለመብል የመጡትን ሁሉ የሚፈልጉትን ሰጥቶ ካሰናበተ በኋላ ሊሰራቸው፣ ሊሰራባቸው ከራሱ ጋር ያቆያቸዋል።

@revealjesus


የእሷ ጥንካሬ ለሌሎችም የሚጋባ ዓይነት ነው፤ ጽናቷ ሌሎችን የሚያበረታ ነው። ለመንፈሳዊ ጉዳዮች ትኩረት ስለምትሰጥም ትምህርቷም ሌሎችን ወደ ከፍታው የሚያሻግር፤ ምክሯ ከስህተታቸው የሚመልስ ነው። ደጋግሞ በመሞከር የምታምን ትዕግሥትን የተላበሰች፣ ባልተሳካው ጉዳይ ፀፀትና ቁጭት የምታዘወትር በመሆኗም በማኅበራዊ ሕይወቷም ሆነ በሌሎች ተግባራቶቿ ብዙዎችን ታስቀናለች። በዙሪያዋ ያሉ ሁሉ ለማደግ እንዲንጠራሩ ታደርጋለች።
ሰዎች ማንነታቸውን ከተቀበሉ ድከመታቸውን ማረም እንደሚችሉ፤ ጥንካሬያቸውን ለሰው ሁሉ እንደሚያሳዩ፤ ለሌሎች ሰዎች መብራት እንደሚሆኑና ራሳቸውን ከጨለማው ወደ ብርሃኑ ማውጣት እንደማይሳናቸው ታስባለች። በዚህ ውስጥ ደግሞ እርሷ ለሌሎች የነገ መውጫቸው መሰላል እንደሆነችም ትገነዘባለች።
ያብስራ ትናንትን በብዙ እያማረረች ብትቆይም ዛሬ ላይ ግን ማንንም ሳትወቅስ ወደፊት ትራመዳለች። እንደውም አሁን ላይ ቆም ብላ ስታስበው ‹‹በእኔ እንዲህ መሆን ማንም ተወቃሽ የለም›› ትላለች። ‹‹ፈጣሪ በዚህ ደረጃ የፈጠረኝ መጥፎ ስለሆነ ወይም ቤተሰቦቼ ኃጢአት ስለሠሩ አይደለም። እኔን ስለሚወደኝና ቤተሰቦቼም የበለጠ ጠንካራ እንደሆኑ ስላሰበ ነው። ሌሎች በእኔ ውስጥ ተምረው ደስተኛ ኑሮን እንዲኖሩ ስለፈለገ ነው። እኔም ደስታዬ በሌሎች ለውጥ ውስጥ እንዲሆን ስለፈለገኝ ነው እንጂ ፈጣሪ በፍጥረቱ የሚሳሳት ሆኖ አይደለም።» በማለትም በእርሷ አካል ጉዳተኝነት ዙሪያ ተወቃሽ የሚባል ነገር እንደሌለ ትናገራለች።
ፈጣሪ ለእርሷ የሰጣት ልዩ ጸጋ እንዳለ የምታምነው ያብስራ፤ በዛሬዋ ውስጥ ማንም ሰው እርሷን ካገኘ የተፈጠረበትን ዓላማ እንዲረዳ የማድረግ አቅም እንዳላት አውቃለች። በዚህ ደግሞ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች፤ ለዚህ ያበቋትን ቤተሰቦቿንና ጓደኞቿን አመስግና አትጠግብም።
ምሳሌ ፋውንዴሽን
ያብስራ ማንም ሰው በሕይወቱ ስኬታማ ለመሆን ስንፍናንና አልችልም ባይነትን ማስወገድ ነው የሚል አቋም አላት። በተለይም ራስን ማሸነፍና ራስን መቀበል ከምንም በላይ ለሕይወት ጉዞ አስፈላጊ እንደሆነም ታምናለች። በዚህ አቋሟም ላይ ሆና በመንቀሳቀሷ ከፍታዋን እንደገነባች ታስባለች። ምክንያቱም ዛሬ ላይ ያብስራ የተለዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ትገኛለች። አንዱ ከራሷ አልፋ በጎ አድራጎት ድርጅት ከፍታ ለሌሎች መድረስ ችላለች።
ድርጅቱ ምሳሌ ፋውንዴሽን ይባላል። ዋና ተግባሩ በየዓመቱ በበዓላት እና በትምህርት ማስጀመሪያ ወቅት በኢኮኖሚያቸው ዝቅ ያሉ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ማገዝና የማዕድ ማጋራት ሥራ ማከናወን ነው።
ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁሶችን ማቅረብ፤ አቅመ ደካማን ከእነ ቤተሰባቸው በዓልን በደስታ እንዲያሳልፉ ማገዝ ሲሆን፤ ትኩረት የሚሰጣቸው የማኅበረሰብ ክፍሎቹም የአዕምሮ እድገት ውስንነት፤ ሴተኛ አዳሪዎች፤ ጎዳና ላይ ኑሯቸውን ያደረጉ ሰዎችና ጧሪና ቀባሪ ያጡ አዛውንቶች ናቸው። እናም በሁለቱ ወቅት ቢያንስ 700 ቢበዛ ደግሞ 1000 ሰዎችን እንዲታገዙ ለማድረግ በሀዋሳ ከተማ አካባቢ ያሉ አጋሮቿ ጋር በመተባበር ተግባሩን ትከውናለች።
ያብስራ በድርጅቷ በኩል ብቻ አይደለም ሰዎችን የምታግዘው። ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተከታይ ቲክቶከር በመሆኗ የራሷን ገቢ ለማሳደግ የተለያዩ ማስታወቂያቸውን ከመሥራት ጎን ለጎን ወጣቶችን በተለያየ አግባብ ታስተምራለች። በርካቶችን ታነቃቃለች፤ ለተሻለ ሥራም እንዲነሱ ታበረታታለች። ከዚያ ወጣ በማለትም በግሏም ሆነ በቡድን ለወጣቶች ማይንድ ሴትአፕ ላይ የተለያዩ ሥልጠናዎችን ትሰጣለች። ተቀጥራ በምትሠራበት መሥሪያ ቤት በኩልም አርሶ አደሩ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆንም ትተጋለች።
መልዕክት ያብሰራ
የሰዎች ታላቅነት የሚመዘነው ባላቸው አቅምና እድል ተጠቅመው ለሌሎች መትረፍ ሲችሉ እንደሆነ የምታምነው ያብስራ፤ አካል ጉዳተኞችን መደገፍ የአንድ አካል ብቻ እንዳልሆነ አበክራ ትናገራለች። ቤተሰብ ግዴታው ቢሆንም ማኅበረሰቡ ካልደገፈው ውጤታማ መሆን አይችልም ባይ ነች። ደከመኝ ሳይሉ፤ ለነገ የሚሆናቸውን ነገር ሳይሰስቱ ሊሰጧቸው እንደሚገባ ታነሳለች።
አካል ጉዳት ተፈልጎ የሚመጣ ባለመሆኑ በሁሉም በኩል ትኩረት ሊሰጠው ይገባል። ከመንግሥት እስከ ቤተሰብ ድረስ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እንክብካቤ ሊያደርግላቸው ያስፈልጋል። በሁኔታዎች ሁሉ ያልተገደበ ድጋፉን ማድረግ ይገባል። ማኅበረሰቡም ቢሆን ከማሸማቀቅ ይልቅ ብርታት ሊሆነው ያስፈልጋል ትላለች።
ማንነትን አለመቀበል ለነገሮች ውስብስብነት ያጋልጣል፤ ወቃሽነትን ያመጣል፤ ተስፋ መቁረጥንና አለመሥራትን ከፍ ያደርጋል። ይህ ደግሞ በሰው ጫንቃ ላይ እንድናርፍ ያስገድደናል። ሕይወትንም ጨለማ ያደርጋል። ስለሆነም አካል ጉዳተኞች ጉዳታቸውን ተቀብለው መጓዝና ለጥያቄዎቻቸው በራሳቸው መፍትሔ ማምጣት ነው በማለት ትመክራለች።
ራሳችንን ለመለወጥ የምንሠራው ሥራ፤ ስለራሳችን ጠንካራ ግምት የምንሰጥ ከሆነና ከውስጣችን የምናወጣቸው ቃላቶች ሳይቀሩ ይገነቡናል። እናም ለዓላማ የተፈጠርን እንደሆንን ለማወቅ ለራሳችን የምንነግረውን ነገር እንምረጥ ትላለች። እስትንፋስ ያላቸው ሁሉ ምንም ዓይነት አፈጣጠር ይኑራቸው ለዓላማ ተፈጥረዋልና አደርገዋለሁ ብለው ከተነሱ ተአምር መሥራት ይችላሉ። ለዚህ ደግሞ እድልም፤ ተስፋም አላቸው ባይ ነች።
የያብስራ የመጨረሻ መልዕክት ራሳችን ላይ እንሥራ የሚል ነው። ራሳችን ላይ ስንሰራ አሸናፊ እንሆናለን፤ የምንፈልገው ላይ እንደርሳለን፤ ጠንካራ ነሽ የሚሉ ሰዎችን እናበረክታለን። በአካል ጉዳታችን የሚያሸማቅቀንም ሆነ አትችሉም የሚለንን እንቀንሳለን ትላለች።

ጽጌረዳ ጫንያለው
አዲስ ዘመን መጋቢት 30 ቀን 2017


የአካል ጉዳት ያላንበረከካት ክንደ ብርቱ
 
አንዳንድ ጊዜ መክሊታችን ምንድነው የሚለውን በውል ባለመገንዘብ ለምን ሕይወቴ፣ ሥራዬ፣ ትምህርቴ … አልተሳካልኝም። ለምን ውጤታማ መሆን አልቻልኩም በሚል የሚበሳጩ ብዙ ናቸው። «ለምን» የሚል ጥያቄን በማንሳት ብቻ ወርቅ የሆነውን ጊዜያቸውን ያለ ውጤት ያባክናሉ። ሁሉም ሰው ውጤታማ የሚሆነው ሰዎች ተሳክቶላቸው ያየውን ሥራ ለመሥራት በመሞከር ብቻ አይደለም። አንዳንዶች የራሳቸው የሆኑ ሞዴሎች ይኖሯቸውና ያንን ተከትለው ለውጤታማነት ይበቃሉ። ሌሎች ደግሞ በተቃራኒው። ነገር ግን የራሱን መክሊት ፈልጎ ያገኘ ሰው ምንም ቢሆን አይወድቅም። የማደግና የስኬታማነት እድሉ ሰፊ ነው።
በተለይም አካል ጉዳት ያጋጠመው ሰው ብዙ ጊዜ ጥገኛ ላለመሆን ምን መሥራት እንዴት መሥራት እንዳለበትና ሕይወትን ማስቀጠል እንደሚችል ከማሰብ ይልቅ አእምሮን ወደ አንድ መንገድ ብቻ ይመራል። አካል ጉዳተኛ ሠርቶ መለወጥ አይችልም ብለው የሚያስቡ ጥቂቶች አይደሉም። ነገር ግን ሙሉ አካል ላላቸው ሁሉ አርአያ የሚሆኑ ጀግና የሆኑ አካል ጉዳተኞች አሉ። የአካል ጉዳታቸው ሳይበግራቸው በጥረታቸው ዝናን ያተረፉ አንቱ የተባሉ። ከእነዚህ ክንደ ብርቱዎች መካከል የሀዋሳዋ ወጣት ያብስራ ፍሬው አንዷ ናት። ያብስራ ችግርን እንዴት ተጋፍጦ ማሸነፍ እንደሚቻል ከሕይወት ተሞክሮዋ ያሳየች ወጣት ነች። ተወልዳ ያደገችው ሲዳማ ክልል አለታጭኮ በሚባል ቦታ ነው። ገና ስትወለድ ጀምሮ እጇ ላይ የአካል ጉዳት አጋጥሟታል። ቤተሰቦቿ የእርሷን አካል ጉዳት ተቀብለው የሚቻላቸውን ሁሉ ቢያደርጉላትም ራሷን ካወቀች በኋላ የተለያዩ ጥያቄ ታነሳ ነበር።
ማንነቷንም ለመቀበል ረጅም ዓመታትን ፈጅቶ ባታል። ጥያቄዎቿ መልስ በማጣታቸውና ራሷን ማሸነፍ ባለመቻሏ አንዳንዴ ጭምት ሆና ራሷን አግልላ ትቀመጣለች። አንዳንዴ ደግሞ ተናዳጅና ተደባዳቢ እንዲሁም ለቤተሰቡ አስቸጋሪ ልጅ ትሆናለች። በዚህ ባሕሪዋ ግን ማንም አይወቅሳትም፤ ተይም ሊላት አይወድም። ይልቁንም ንዴቷ ከምን የመነጨ እንደሆነ ስለሚረዷት ይህንን ብታደርጊ ነገሮችን ማቅለል ትችያለሽ እያሉ መልካም መንገዶችን ይመሯታል። ጭንቀቷን የሚያስረሱ ሃሳቦችንም ይሰጧታል። ይህንን ተጠቅማ ሕይወቷን ማስተካከል ችላለች።
አስተማሪው ፈልም
ያብስራ ማንነቷን መቀበል ከቤተሰቦቿና ጓደኞቿ ምክር ባልተናነሰ ከአካል ጉዳት ጋር ተያይዞ ያሉ ፈልሞችንን መመልከቷ አስተዋጽኦ ነበረው። በፊልሞቹ ፈጣሪ በምንም መልኩ እንደማይሳሳት ተምራለች፤ ለዓላማ መፈጠሯን እንድትረዳ ሆናለች። በተለይም ከእርሷ የባሰ አካል ጉዳት የገጠማቸውን ስታይ ለምን ለሚለው ጥያቄዋ አወንታዊ ምላሽ አግኝታበታለች።
‹‹የሕይወቴ መቀየር መሠረት የሆነው ሚግ(ሚኪ) እየተባለ የሚጠራው እጅም እግርም የሌለው የውጭ ሀገር ዜጋ የሚያከናውናቸው ተግባራት ናቸው›› ትላለች። እርሷ ምንም የአካል ጉዳት ያልገጠማቸው እግሮች አሏት። በጥቂቱም ቢሆን ሊይዙ የሚችሉ ጣቶችም እጇ ላይ አላት። ስለዚህም ምንም ማድረግ እንደማያቅታት ብርታት ሰጥቷታል። ይህንን አቅሟን እንድትጠቀም ደግሞ የሚያግዟት፤ የሚያበረታቷት ቤተሰቦችና ጓደኞች ስላሏት ደስተኛ ሆና ታደርገዋለች፤ እያደረገችው እንደሆነ ታስረዳለች።
ያብስራ ፊልም ማየት ከምንም የመነጨ አይደለም። ቤተሰቦቿ ይህንን ብታደርጊ እያሉ የመከሯት ነው። የጓደኞቿም ድጋፍ ታክሎበት ነው። በዚህ ደግሞ ትምህርቷን ጭምር እንድትገፋበት አግዟታል። የመጀመሪያ ዲግሪዋን በቢዝነስ ማኔጅመንት እንድትመረቅና ሥራ ተቀጥራ መሥራት ችላለች። ከጓደኞቿና ከአካባቢው ማኅበረሰብ የሚደርስባትን ጫና መቋቋም ችላለች።
ያብስራ ከዚህ በመነሳትም ስለቤተሰቦቿና ጓደኞቿ የምትለው አላት። ‹‹እኔ የቤተሰቦቼ ድምር ውጤት ነኝ። በጣም ደካማና ምንም አልችልም በሚል ሁኔታ ውስጥ ሆኜ ብርታት ሰጥተውኝ ከጨለመው አስተሳሰቤ አውጥተውኛል። ሁሌም አንቺ ታደርጊዋለሽ እያሉ ከፍታዬን ገንብተውልኛልም። ጓደኞቼም ስብራቴን የጠገኑ ናቸው። እኛ ምን ሠራን እያሉ ብርቱነትን አጎናጽፈውኛል። በተስፋ እንድራመድ፤ እድሎቼን እንድጠቀምባቸው አስችሎኛልና ስለ ውለታቸው ዘወትር አመሰግናቸዋለሁ›› ትላለች።
እግርን እንደ እጅ
እያንዳንዱ የሰውነት ክፍላችን የራሱ አገልግሎት ቢኖረውም ያብስራ ጋር ግን ይህ አይሠራም። በተፈጥሮዋ ጉዳትን ያስተናገደች በመሆኗ ለእርሷ እግር የእጅንም አገልግሎት ያከናውናል። በእርግጥ አገልግሎቱን ለማስጀመር ጥረትን ፤ ልምምድንና ፈተናን መጋፈጥን የግድ ይላል። ያብስራም ይህንን በአግባቡ ለመወጣት በብዙ ታግላለች፤ ተፈትናለችም። ከዚህ ጋር ተያይዞ አንድ ጠንከር ያለ ጉዳይን አጫውታናለች። ይህም ከወር ግዳጇ ጋር በተያያዘ የተፈተነችበት ነው።
በወቅት ሞዴስ እንዴት እንደምታደርግ አታውቅም፤ ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ ላይም አይደለችም። ስለዚህ ምርጫዋ የሌሎችን እርዳታ መጠየቅ ነው። ሀፍረትን ገልጦ ለሌሎች ማሳየት ደግሞ በጣሙን ይሰቃል። ስቃዩ የአንዱ ሰው ብቻ ሳይሆን በሁለቱም ወገን የሚመጣ ነው። ግን ምርጫ የላትምና ለዓመታት ምላሽ እስክታገኝ ድረስ አድርገዋለች። በዚህ ውስጥ ግን ተፈጥሮዋን በየጊዜው ታማርር ነበር። ብስጭቷም መና ሆኖ ቆይቶ ነበር። አንድ ቀን ግን ከሰዎች ጫንቃ ላይ ለመውረድ ቪዲዮችን መከፋፈት ጀመረች።
በእግሯ ነገሩን ማከናወን እንደምትችልም አወቀች። ተለማምዳም ተፈጥሮዋን በተፈጥሮ መልሳ ደስታዋን ወደራሷ አመጣች። ከዚህ የተነሳም ዘወትር ለራሷ አንድ መርህ አስቀምጣለች። ይህም ‹‹ተፈጥሮ ለራሷ ተፈጥሯዊ ምላሽ አላትና ከማማረር ይልቅ ለምላሽ መፋጠን ያስፈልጋል›› የሚል ነው።
ያብስራ አንዱ አካላችን ቢጎልም በአንዱ ተጠቅሞ ችግሩን ማለፍ ይቻላል የሚል እምነት ያላት ወጣት ነች። በዚህም እግሯን ለተለያዩ አላማዎች መጠቀም ችላለች። በእርሷ የሕይወት ጉዞ ውስጥ ሽንኩርት የመከተፍ ሥራ የእጅዋ ብቻ ሳይሆን የእግሯ ነው። ከበድ ያሉ እቃዎችንም ማንሳትና ከቦታ ቦታ ማንቀሳቀስ የእጇ ተግባር ሳይሆን የእግሯ ዋነኛ ሥራ ነው። እግሯ የእጅን ተግባር በሙሉ ይከውናል።
ልክ እንደ እጇ ጸጉሯንና ሰውነቷን የምትታጠብው፤ዘወትር አልጋ የምታነጥፈው፤ ቤት የምታጸዳው፤ ልብስ የምታጥበውና ዋና የሚባሉ ተግባራትን የምትከውነው በእግሯ አማካኝነት ነው። ያብስራ ባሏት ጣቶች አንዳንድ ሥራዎችን ትሰራለች። ወጥ ታማስላለች፤ ገላዋንም ትታጠባለች፤ በኮምፒውተር ላይ ትጽፋለች። ይህንን በማድረጓ ደግሞ አካል ጉዳተኛ እንደሆነች ሳይሰማት ጊዜዋን እንድታሳልፍ አግዟታል። ማንኛውም ሰው የሚሰራውን መሥራት እችላለሁ እንድትልም ወኔ ሰጥቷታል። በሁነቶች እንዳትማረርና እንዳትሸነፍም አግዟታል።
ያብስራ ዛሬ እንደ ትናንቱ አትቆዝምም፤ አትናደድም፤ ተበሳጭታ ነገሮችን ከማድረግ ወደ ኋላ አትልም። እንዳውም አዲስ ነገር ፈጥራ ሰዎችን ማስደመምና አትችልም ሲሏት የነበሩትን ማሳፈር ምርጫዋ ታደርጋለች። ሁልጊዜ ሀዘኗን ወደ ደስታ ቀይራ ደስታን ትፈጥራለች። ፍልቅልቅ ሆና ለሰዎች በመታየቷ ደስታን ታጋባለች።






" ስሜት ያለስሌት ከቁጥጥር ዉጭ ይሆናል ።
ስሜት ዛሬን እንጂ ነገን አያሳይም በስሜት መነፅር የሚታየዉ ዛሬ ብቻ ነዉ ።

ስሜት ዛሬዉን የመጨረሻ ቀንና ሰዓት አድርጎ ይወስዳል ይረዳል ።
ስሜት ብቻዉን ነገን አያይምና

ብዙዎች በዉስጣቸው የሚፈጠሩ ስሜቶችን ያለ ስሌት ስለሚያስተናግዱ ዉሳኔዎቻቸዉ በስህተት የተሞሉ ይሆናሉ ።

አብረዉህ ለማይሰነብቱ አሻግረው ከማዶ ከራዕይ እና ዓላማ ጋር ለማይሰለፉ ግዜያዊ ሥሜቶች ማንነትህ በመቀማት ራዕይ ፣ አላማ እና ህልምህን አትለዉጥ ፤ ግዜያዊ ነገር ግዜያዊ ነዉና "

✍️ ስዉር ቁልፎች ከተሰኘው
በምንተስኖት መኩሪያ ከተጻፈው መጽሐፍ የተወሰደ

@revealjesus


☕አንድ ሸክላ ሰሪ ቡና የሚያፈላበትን እቃ መስራት ቢፈልግ የሚሰራው ጀበናን ነው ።
ይሄንን ጀበና ለመስራት ያነሳሳው ቡና ለማፍላት ያለው ፍላጎቱ ነው ፤ ስለዚህ ይሄንን ጀበና የሚሰራበት ምክንያት አለው ማለት ነው ።

👉በሌላ አማርኛ ደግሞ ቡና የሚያፈላበት እቃ ባያስፈልገው ይሄንን ጀበና አይሰራውም።

⚠️ ለሰራው ጀበናም የሚሰጠው ቅርፅ ቡና ለማፍላት የሚያመቸውን ቅርፅ ነው።
እንግዲህ ይሄ ጀበና የተፈጠረበትን አላማ አሳክቷል የሚባለው "በዘመኑ ሁሉ ቡና በማፍላት የሰራውን ሰው ሲያገለግል ነው።

👉ሸክላ ሰሪ  አንድ ህይወት የሌለውንና ከጭቃ የሚሰራውን ጊዜያዊ እቃ ለመስራት ምክንያትና አላማ ካስፈለገው በራሱ ምስልና እስትንፋስ ህያው አርጎ የፈጠረውን ሰው እግዚአብሄር እንዴት ያለ ምክንያት ይፈጥረዋል??

👉እንዴትስ ያለ አላማ ይፈጥረዋል??
እግዚአብሄር እኮ የአላማ አምላክ ነው። የሚያደርገውን ሁሉ የሚያደርገው ከዘላለም ሀሳቡ አንፃር ነው።

👉ጊዜ ለማባከን ወይንም ሰአት ለመግደል ብሎ ማንንም አይፈጥርም ፤ ሰማይና ምድርን እንዲሁም እስትንፋስ የሌላቸውን ግኡዝ ፍጥረታት እንኳን የፈጠራቸው ክብሩን ሊናገርባቸው ነው።

አላማ ማለት ፦እግዚአብሄር እያንዳንዳችንን ከመፍጠሩ በፊት ልቡ ውስጥ የነበረ ሀሳብ ማለት ነው ።
አላማ ማለት ፦ እግዚአብሄር እያንዳንዳችንን ለመፍጠር ያነሳሳው ምክንያት ማለት ነው ።

               

      T.me/revealjesus


በሃያላን መሀል ሃይል የእግዚአብሔር ነው 🙏


【DPK-AI ትሬዲንግ】 አውቶማቲክ መጠናዊ ስርዓቱ ዝቅተኛውን የዲጂታል ገንዘቦች መሸጫ ዋጋ እንደ BTC፣ ETH፣ USDT ወዘተ በዋና ልውውጦች ላይ መፈለግ እና በሰከንዶች ውስጥ በፍጥነት መግዛት ይችላል።

1.DPKAI-quantitative, ፈንዶች ተቀማጭ እና ማውጣት በራስ-ሰር ወደ መለያው ገቢ ይደረጋል.

2. VIP1-VIP11፣ መጠናዊ ተመላሾች 20% -35%.

3. ከ 25% ወደ 40% በመጨመር ብዙ ምንዛሬዎችን እና ብልጥ የኢንቨስትመንት ገቢን ይደግፉ.

4. መጠኗ በየ24 ሰዓቱ እንደገና ይጀመራል፣ እና እያንዳንዱ ሰው በቀን አንድ ጊዜ በመጠን የገቢ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ይችላል።

5. የሶስተኛ ደረጃ ወኪል ግብዣ ሽልማቶችን ጠቁም። ብዙ ግብዣዎች ባደረጉ ቁጥር፣ የበለጠ ሽልማቶችን ያገኛሉ። ምንም ከፍተኛ ገደብ የለም [አንድ ሽልማት 10%, B ሽልማት 5%, C ሽልማት 3% = 18% ሽልማት]. እንደ ቲክቶክ፣ ፌስቡክ፣ ትዊተር፣ ዩቲዩብ፣ ኢንስታግራም፣ የዋትስአፕ ቡድን፣ የቴሌግራም ቡድን፣ ወዘተ ባሉ ማህበራዊ ሶፍትዌሮችዎ ላይ ለማጋራት የግብዣ ሊንኩን ይላኩ።

【DPK-AI ትሬዲንግ】 የምዝገባ አገናኝ፡ https://dpk-ai.com/#/register?ref=870258

【DPK-AI ትሬዲንግ】 የመስመር ላይ የደንበኞች አገልግሎት፡ https://chat.ssrchat.com/service/gomw2j


ለሚያወራህ ውበት ለሚለብስህ ጌጥ
ሮጦ ለተጠጋህ የማምለጫ አለት
ህይወት ከሞት ወዲያ እርስቱ ላረገህ
ለአፍታ እንኩዋን የማትጎድል ለሰው ሙላቱ ነህ
አንተን ነው እንጂ ጥብቅ አድርጎ መያዝ ያዘኝ እያሉ
ማልዶ በጠዋት በአንተው እጅ ደምቆ መዋል ደጅ እየጠኑ
አንተን ነው እንጂ ጥብቅ አድርጎ መያዝ ያዘኝ እያሉ
ማልዶ በጠዋት በአንተው እጅ ነቅቶ መዋል ደጅ እየጠኑ

አይኔን ጉዳዬ ላይ ማድረግ
ፍለጋዬን እድሜ ልክ መፈለግ
ናፍቆቴን ሳላርፍ መናፈቅ
ጉጉቴን ሳልደክም መፈለግ
እንዲሆንልኝ ይብዛልኝ ጸጋህ
ጊዜው ደርሶ እስክደርስ አንተ ጋ
ገባ ወጣ እግሬ ሳይልብኝ
ፍለጋዬ ሳትጎድል ብዛልኝ

በድነቴ ጠዋት በገባኸኝ ማግስት
ጨዋታ ወሬዬ መወደዴን ማድነቅ
ዘምሬህ አልጠግብ አውርቼህ አልረካ
ይቺህ ትንሽ ልቤ ለፍቅርህ ሸፍታ

አልደግ አንተላይ እራሴን አልቻል
አጓጉል ነው ሁሉም ያላንተ መች ያምራል
መጠበቂያ አጥሬ መሰንበቻዬ ነህ
ልኑር እንደፈዘዝኩ አይኔ አንተን እያለ

ጉዳዬ አንተው ነህ
መናፈቄ መምጣትህን
ጉጉቴ አይኔ እስከሚያይህ

| @revealjesus
| @revealjesus


ከትንንሽ ዘሮች ዘልቆ መሄድ

“በጥቂት የሚዘራ በጥቂት ደግሞ ያጭዳል፥ በበረከትም የሚዘራ በበረከት ደግሞ ያጭዳል” (2ቆሮ.9፡6)፡፡

ሕይወት የመዝራትና የማጨድ ሂደት ነች፡፡ ከትናንት ወዲያ የዘራናቸውን የዘሮች ፍሬ ትናንት በልተን ዛሬ ደርሰናል፡፡ ትናንት የዘራነውን ዘር ደግሞ ዛሬ እየበላነው ነው፡፡ ዛሬ የዘራነውን ደግሞ ነገ መብላታችን አይቀርም፡፡

ይህ የማይቀር ሂደት የሕይወታችንን እውነታ የሚያሳይ ከሆነና የምንዘራውን መጠን የምናጭድ ከሆነ ምናባት ዘርን አስመልክቶ የአቅጣጫ ለውጥ ማድረግ ይኖርብን ይሆናል፡፡ ትንሽ እየዘሩ ብዙ መጠበቅ ጊዜን ማባከን ነው፡፡

“ምድር እስካለች ድረስ፣ የዘር ወቅትና መከር፣ ሙቀትና ቅዝቃዜ በጋና ክረምት፣ ቀንና ሌሊት፣ አይቋረጡም” (ዘፍ. 8፡22) ስለዚህ አንደኛችንን በመዝራትና በማጨድ ሕጎች መብሰል አማራጭ የሌለው መንገድ ነው፡፡

1. የማይለወጠው መርህ፡- ያልዘራነው አይበቀልም

“አትታለሉ … ሰው የሚዘራውን ያንኑ ያጭዳል” (ገላ. 6፡7)፡፡

በሕይወታችን ያለውን ማንኛውም ነገር እንመልከተው፣ አሁን ያለው ነገር በሙሉ የትናንት ዘር ነው፡፡ ይህ ዘር ምናልባት እኛው የዘራነው ነው፣ ወይም ደግሞ ሌሎች ሰዎች በሕይወታችን እንዲዘሩት የፈቀድንላቸው ዘር ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ፣ “ሰው ሁሉ ተኝቶ ሳለ፣ጠላቱ መጥቶ በስንዴው መካከል እንክርዳድ ዘርቶ” ይሄዳል (ማቴ. 13፡25)፡፡ ዘሩ በዚህም በዚያም ተዘራ ያው የተዘራው ነገር ነው የሚበቅለው፡፡ ስለዚህም መልካም ነገር እንዝራ! አብዝተን እንዝራ!

2. ብዙ የመዝራትና የማጨድ መነሻ፡- በልግስና ለመስጠት

“ለዘሪ ዘርን፣ ለመብላት እንጀራን የሚሰጥ እርሱ የምትዘሩትን አትረፍርፎ ይሰጣችኋል፤የጽድቃችሁንም ፍሬ ያበዛላችኋል። ሁል ጊዜ በልግስና መስጠት እንድትችሉ በሁሉ ነገር ያበለጽጋችኋል፤ ልግስናችሁም በእኛ በኩል የሚደርሳቸው ሰዎች እግዚአብሔርን ለማመስገን ምክንያት ይሆናቸዋል።” (2ቆሮ. 9:10-11)፡፡

ይህ አጭርና ግልጽ የሆነ አውነት ነው፡፡ ጌታ ብዙ እንድንዘራ ይመክረናል፡፡ የምንዘራውንም ዘር ደግሞ እርሱ ራሱ ይሰጠኛል፡፡ እርሱ የሚሰጠን ዘር አትረፍርፎ ነው፡፡ ይህንን ሁሉ የማድረጉ የመጨረሻ ዓላማ፡- “ሁል ጊዜ በልግስና መስጠት እንድትችሉ”፡፡

3. ዘርቶ የማጨድ እርግጠኛነት፡- ወቅትን ማወቅ

“ዘር ቋጥረው፣ እያለቀሱ የተሰማሩ፣ ነዶአቸውን ተሸክመው፣ እልል እያሉ ይመለሳሉ” (መዝ. 126፡6)፡፡

በመዝራት ወቅት ነዶን የሚጠብቁ ሰዎች ተስፋ ይቆርጣሉ፡፡ የመዝራት ወቅት አለ፣ የማጨድ ወቅት አለ፡፡ ስለዚህ የዘራነውን ትልልቅ ዘር በእርግጠኝነት መቀበል ከፈለግን ወቅትን መለየት አስፈላጊ ነው፡፡ ምናልባት አሁን የምንዘራበት ወቅት ሊሆን ይችላል፡፡ ታማኝነት፣ ፍቅርን፣ ትእግስትን፣ ገንዘብን፣ ጊዜን እየዘራን ያለንበት ወቅት ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ ጊዜ ከባድና አንዳንዴም ሊያስለቅስ የሚችል ጊዜ ነው፡፡ ሆኖም፣ ነዷችንን ተሸክመን በደስታ የምንዘምርበት ዘመን መምጣቱ አይቀርም፡፡

ይህ ክፍል ተጠናቀቀ! በክፍል ስድስት እስከማገኛችሁ ጌታ ኢየሱስ ይባርካችሁ!

ከዶ/ር ኢዮብ ማሞ ጋር በአካል በመገኘት ስልጠና ከሚወስዱ ወጣቶች ጋር ለመቀላቀልና ለመሰልጠን ከፈለጋችሁ ስማችሁና ስልካችሁን inbox ማድረግ ትችላላችሁ፡፡


ከትንንሽ ዘሮች ዘልቆ መሄድ


ከትንንሽ ጸሎቶች አልፎ መሄድ

“ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ ይህን ተራራ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል” (ማር. 11፡23)፡፡

አንዳንድ ሰዎች እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ ትልልቅ ነገር ስለሚጠይቁት የሚያዝንባቸውና የሚቸገር ይመስላቸዋል፡፡ እግዚአብሔር ግን ትልቅ ነው! እኛ ትልቅ ነው ያልነውን ነገር እርሱ ከምንም አይቆጥረውም፡፡ ልመናችንና እምነታችንን ከተራራ አንጻር ከፍ እንድናደርግ የሚነግረን ለእርሱ ተራራ ትልቅ ሆኖ አይደለም፤ ከእኛ አንጻር ሁኔታዎችን ሊያሳየንና ከትንንሽ ጸሎቶች እንድንወጣ ስለሚፈልግ ነው፡፡

እግዚአብሔርን ለትልልቅ ነገር ማመንና ከትንንሽ ጸሎቶች መውጣት የሚነሳው ትልልቅ ራእይን ከማየትና ትልልቅ እቅዶችን ከማውጣት ነው፡፡ ሆኖም፣ ራእያችንም፣ እቅዳችንም ሆነ ልመናችን ትልቅ የመሆኑ ዋናው ምንጭ እርሱው እግዚአብሔር ነው፡፡ በራሳችን ምንም ትልቅነት ስለሌለን ማለት ነው፡፡

ስለዚህ፣ ከትንንሽ ጸሎቶች ማለፍ ማለት እግዚአብሔርን በሚመጥነውና በሚያሳየኝ ልክ ለትልልቅ ነገሮችእርሱን ወደ ማመን መዝለቅ ማለት ነው፡፡

“ለምነኝ፤ መንግሥታትንርስትአድርጌ፣ የምድርንምዳርቻግዛትእንዲሆንህእሰጥሃለሁ” (መዝ. 2፡8) ያለን ጌታ ራእያችንን ሰፋ አድርገንና የጸሎት ርእሳችንን ገዘፍ አድርገን እንድንቀርበው ይፈልጋል፡፡

1. ታላቅነትና ትልቅነት ማንነቱ ነው

“እኔ ኤልሻዳይ (ሁሉን ቻይ) ነኝ” (ዘፍ. 17፡1)፡፡

ጌታ ስለማንነቱ በግልጽ ነግሮናል፡፡ ሁሉን እንደሚችልና ምንም አይነት ጥያቄ ለእርሱ እንደማያቅተው በቃሉ ከመንገር አልፎ በተግባርም አሳይቶናል፡፡ ባህርን የከፈለበት፣ በጠላቶቹ ላይ በቁጣ የተነሳበት፣ ሙታንን ያስነሳበትና ምንም ከማይመስል ነገር በረከትን ያወጣበት ተአምራቱ የብሉይና የአዲስ ኪዳን ታሪኮች ብቻ አይደሉም፡፡ ዛሬም ይሰራል፡፡

2. ልቆ መገኘት ባህሪው ነው

“ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው” (ኤፌ. 3፡20)፡፡

እንኳን ትልቅን ነገር ለምነነው ቀርቶ፣ ቀድሞውኑ እርሱ ከለመንነው አልፎ የማድረግ ባህሪይ አለው፡፡ ለምስኪኖች እንኳን ሲሰጥ እንደምስኪንነታቸው ሳይሆን በማትረፍረፍ ነው፡፡ “በተነ፤ ለድኾችም ሰጠ” (2ቆሮ. 9:9)፡፡ አለቀ! ጌታ ለምስኪኖር ቆጥሮ አይሰጥም፣ በትኖ እንጂ!

3. ታላቅ ነገር ማድረግ ብቃቱ ነው

“የማይመረመረውን ታላቅ ነገርና የማይቈጠረውን ተአምራት ያደርጋል” (ኢዮ. 5፡9)፡፡

አንዳንድ ሰዎች፣ “ጌታ ከምንለምነው በላይ ታላቅ ነገር እስካደረገ ድረስ እኛ ልመናችን ትልቅ ሆነ ትንሽ ምንም ትርጉም የለውም” ብለው ያስባሉ፡፡ እንዲያውም፣ “ከመለመናችሁበፊትምንእንደሚያስፈልጋችሁያውቃልና” (ማቴ. 6፡8) ተብለናል፡፡ ማስታወስ ያለብን ነገር ግን ትንንሽ ጸሎቶች የትንንሽ አመለካከቶች ውጤት መሆኑን ነው፡፡ አመለካከታችን አናሳና ጠባብ ከሆነ ጌታ ምንም ነገር ለማድረግ ቢፈልግም እንኳን አመለካከታችን ሊገድበው ስለሚችል ከአመለካከታችን በመነሳት የጸሎት አድማሳችንን ማስፋት አስፈለጊ ነው፡፡

የሚቀጥለው ትምህርት፡ “ከትንንሽ ዘሮች ዘልቆ መሄድ”

ከዶ/ር ኢዮብ ማሞ ጋር በአካል በመገኘት ስልጠና ከሚወስዱ ወጣቶች ጋር ለመቀላቀልና ለመሰልጠን ከፈለጋችሁ ስማችሁና ስልካችሁን inbox ማድረግ ትችላላችሁ፡፡




ከትንንሽ ንግግሮች መላቀቅ

“ደካማውም ሰው፣ እኔ ብርቱ ነኝ ይበል” (ኢዩ. 3፡10)፡፡

ከትንንሽ ንግግሮች ነጻ መውጣት ማለት ካለሁበት እውነታ በላይ በሚያደርጉኝ ንግግሮች መሞላት ማለት ነው፡፡ እውነታው ደካማነቴ ቢሆንም እንኳን ብርታትን ማወጅ፤ እውነታው ጨለማ ቢሆንም እንኳን ብርሃንን ማወጅ፤ እውነታው አለመሳካት ቢሆንም እንኳን ጌታ ሁኔታዎችን እንደሚለውጥ ማወጅ

ይህ ከላይ የጠቀስነው ልምምድ እንዲሁ አይመጣም፡፡ ምስጢሩ መለኮታዊ፣ መነሻው ደግሞ ከእግዚአብሔር ጋር ያለ የጠበቀ ሕብረት ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር ሕብረት ስናደርግ በአይነ-ስጋችን ከምናየው አልፈን በአይነ-ህሊናችን እርሱ የሚያየውን ማየት እንጀምራለን፡፡

በአይነ-ስጋችን ከምናየው አልፈን ወደ መንፈሳዊው እይታ ስንገባ፣“አይናችን የሚያተኩረው በሚታየው ነገር ላይ ሳይሆን በማይታየው ላይ ነው፤ የሚታየው ጊዜያዊ ነውና፤ የማይታየው ግን ዘላለማዊ ነው” (2ቆሮ. 4:17)፡፡

የዚህ አይነቱ እምነት የተሞላው የሕይወት ዘይቤ ምንጩ፡-

1. ደካማነትን እንደዘር የማየት መገለጥ

“በድካም ይዘራል፣ በኃይል ይነሳል” (1ቆሮ. 15:43)፡፡

ከትንንሽ ንግግሮች አልፈን ለመሄድና ተቃራኒውን ለመናገር ድፍረትን የሚሰጠን በሕይወታችን ያለ ማንኛውም በድካም የሚዘራ ዘር በእኛ ዘንድ በሚኖረው የክርስቶስ የትንሳኤ ኃይል አማካኝነት በኃይል የመነሳት ብቃት ስላለው ነው፡፡ ይህ መንፈሳዊ ምስጢር ሲገባን ማንናውንም ደካማ ጎናችንን ከማስተጋባት በማለፍ በእኛ ውስጥ የሚሰራውን የክርስቶስ ኃይል የሚመጥን ንግግር መናገር እንጀምራለን፡፡

2. ደካማነትን የጌታ ኃይል መገለጫ እንደሆነ ማየት

“ኃይሌ ፍጹም የሚሆነው በድካም ጊዜ ነውና” (2ቆሮ. 12:9)

ከትንንሽ ነግሮች እንድንወጣ የሚነሳሳን ሌላኛው መንፈሳዊ ምስጢር የጌታ ኃይል በእኛ ደካማ ጎን ወደፍጽምና የመምጣቱ ብቃትና ኪዳን ነው፡፡ ሁሉን ቻይ የሆነው ጌታ የእኛን ታናሽነት የእርሱን ታላቅነት ለመግለጥ፣ የእኛን ደካማነት ደግሞ የእርሱን ብርታት ለማሳየት፣ የእኛን መሸነፍ የእርሱን አሸናፊነት ለማወጅ መጠቀም ይፈልጋል፡፡ የእኛ ሃላፊነት ከተራና ከትንንሽ ንግግሮች ወጣ በማለት እርሱ የሚውጀውን ማወጅ ነው፡፡

3. ደካማነትን በጌታ ተደግፎ የመታደሻ መንገድ እንደሆነ ማመን

“እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን፣ ኃይላቸውን ያድሳሉ” (ኢሳ. 40፡31)

በአናሳ ሁኔታው ውስጥ ሆነን አናሳነትን የማናወራው፣ በድካም ውስጥ ሆነን እንኳን ደካማነትን የማናወራው፣ በማይሆን ሁኔታው ውስጥ ሆነን እንኳን አለመሆንንና አለመሳካትን የማናወራው በጭፍንነት እውነታውን ለመካድ ሳይሆን የተሃድሶ ተስፋ ስላለን ነው፡፡ በምንም ሁኔታው ውስጥ ብንሆን ያለንበት ልምምድ የእኛ ልምምድ እንጂ እኛ የያዘን ጌታ ልምምድ እንዳልሆነ ማሰብ አስፈላጊ ነው፡፡ እኛን ያስፈራን እርሱን አያስፈራውም፤ እኛን ትንሽ እንደሆንን ያሳየን ሁኔታ እርሱን አያሳንሰውም፡፡ ስለዚህ ከአናሳ ንግግሮች እንወጣና ጌታ የሚለውን እናስተጋባለን፡፡

የሚቀጥለው ትምህርት፡ “ከትንንሽ ገጠመኞች በላይ መኖር”


ከትንንሽ ንግግሮች መላቀቅ


ለፈገግታ   

😂😂😂😂😂
እዚሁ አዲስ አበባ የሚኖሩ  ሁለት ጥንዶች በክርስትያን ቤተሰብ👪 👨‍👩‍👧 ያደጉ ናቸዉ፡፡ ግን ያው ወንዱ አዋዋሉ🕺 ጥሩ አይደለም ፡፡ ይህ ልጅ ሴት ጓደኛውን ብዙ ጊዜ #ወሲብ እንፈፅም እያለ በብዙ መልኩ ይነዘንዛት ነበር ፡፡
አንድ ቀን እንደድንገት መፀሀፍ ቅዱስ ሲያነብ👨‍💻 ደስ የሚያሰኘውን ቃል አገኘ፡፡ ወድያውኑ ለጓደኛዉ ደውሎ እንደሚፈልጋት ነገራት፡፡
በነጋታው ተገናኙ!! 👫👫
ሰላምታ ከተለወጡ በኋላ💑
ልጁ ፡ አንቺ ግን እስከዛሬ አብረን እንተኛ እያልኩ ስለምንሽ። መፀሀፍ ቅዱስ ራሱ ምን እንደሚል ታውቂያለሽ?💁‍♂💁‍♂
ልጅቷ ፡ እሺ ምን ይላል 🙇‍♀
ልጁ ፡ " #ስጡ_ይሰጣችሁማል ፤
(የሉቃስ ወንጌል 6:38)
ይላል እኮ ።🙎‍♂🙎‍♂
ልጅቷ ፡ ረጋ ብላ አየችውና🙎 ማቴዎስ ላይ ምን እንደሚል ታውቃለህ?🤦‍♀
ልጁ ፡ ምን ይላል🙇

ልጅቷ ፡ #በእግራቸው_እንዳይረግጡት_ተመልሰውም_እንዳይነክሱአችሁ_የተቀደሰውን_ለውሾች_አትስጡ ፥ ዕንቁዎቻችሁንም በእሪያዎች ፊት አትጣሉ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 7:6) ተብሎ ደግሞ ተፅፏል ፡፡ 🏃‍♀🏃‍♀🏃‍♀🏃‍♀🏃‍♀🏃‍♀
ተበላህ😝😝😝😝😝
ስለዚህ እህቶች ከመጽሐፍ ቅዱሳችሁ ጋር ፍቅር ሊይዛችሁ ያስፈልጋል ከቃሉ ጋር ዋሉ የሚፈትናችሁ ቃሉን የሚያውቁት ናቸው እናንተም ከቃሉ ጋር መዋል ቃሉን ማወቅ አለባችሁ አይደለም እናንተን ኢየሱስን የፈተነው በቃሉ ነው

አይርሱ ያናግሩን share ማድረግ አይርሱ
ተባረኩ

ሊያደርግ ያለውን ያውቃል!!!


ከትንሽነት አመለካከት መውጣት

“ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ” (መዝ. 139፡14)፡፡

በክርስቶስ በመሆናችን ምክንያት የተሰጠንን ስፍራ በሚገባ ካልተገነዘብን ትንሽ እንደሆንን የሚያሳየን ሁኔታ ብዙ ነው፡፡

ከትንሽነት አመለካከት የመውጣትን መጽሐፍ ቅዱሳዊና ሚዛናዊ ምልከታ ካላዳበርን ሁሉም ነገር ሙሉ ሆኖልን ሳለ እንኳን፣ አንዲትን የጎደለች ነገር በመጠቆም ትንሽነትን የሚሰብከን ዓለም ውስጥ እንኖራለን፡፡

ዓለም በትልቁና በትንሹ፣ በአዋቂውና በማያውቀው፣ በሃብታሙና በድሃው … ከፋፍላና አንዱ ጋር መድባ ማስቀመጥ ትችልበታለች፡፡ እኛም ብንሆን አምላካዊውን አስተሳሰብ ካላዳበርንና እግዚአብሔር እንደሚያስብ ማሰብ ካልጀመርን ይህንን ቀውስ ማሸነፍ አንችልም፡፡

እንደ ዳዊት ያሉ የአሮጌው ኪዳን ሰዎች እንኳን የትንሽነትን አመለካከት አሸንፈው የወጡ ሰዎች ነበሩ፡፡

በአጭሩ ሲተረጎም፣ ከትንሽነት አመለካከት መውጣት ማለት ስለማንነቴ ከሌሎች ምንጮች የምሰማውን ችላ በማለት ጌታ የሚለኝን ብቻ ወደ ማመን መሸጋገር ማለት ነው፡፡

ይህንን እውነታ ለመለማመድ ደግሞ ማስታወስ የሚኖርብኝ እውነታዎች አሉ፡፡

1. ሰዎች አይገድቡህ

“ወጣትነትህን ማንም አይናቅ” (1ጢሞ. 4:11)፡፡

ሰዎች ስለአንተ ምንም ማሰብ መብት አላቸው፡፡ ሰዎች አንተን መናቅ መብታቸው ነው፡፡ ሆኖም አንተ እስካልፈቀድክላቸው ድረስ ማንነትህን ሊቀናንሰው አይችልም፡፡ የአንተን ትልቅነትና ትንሽነት የሚወስነው ጌታ የሰጠህን ስፍራና ማንነት የመቀበልህና ያለመቀበልህን ሁኔታ መሆኑን አትዘንጋ፡፡

2. ራስህን አትገድበው

“ገና ህጻን ልጅ ነኝ አትበል” (ኤር. 1፡7)፡፡

አንዳንድ ሰዎች ሌሎች የሚሰጧቸውን ስፍራ ያለመቀበል ችግር የለባቸውም፡፡ ሆኖም ግን በራሳቸው ላይ ይህ ነው የማይባል የወረደ አመለካከት አላቸው፡፡ ትንሽ እንሆኑ፣ በኣካባቢያቸው ካለው ሰውና ሁኔታ ጋር የማይመጥን ማንነት እንዳላቸውና ገና ብዙ እንደሚቀራቸው ካለማቋረጥ ለራሳቸው ይሰብኩታል፡፡ እውነታው ግን “ገና ህጻን ልጅ ነኝ አትበል” ተብለን ታዘናል፡፡

3. ራስህን በሁኔታህ መነጽር አትመልከተው

“ጠላቴ ሆይ፤ በእኔ ላይ በደረሰው ደስ አይበልሽ! ብወድቅም እንኳ እነሣለሁ፤ በጨለማ ብቀመጥ እንኳ፣ እግዚአብሔር ብርሃኔ ይሆናል” (ሚክ. 7፡8)፡፡

ሰዎች በግል ሕይወታቸው አንዳንድ ያልጠበቁት ሁኔታ ሲገጥማቸው ውስጣቸው ሙግት ውስጥ ይገባል፡፡ “ይህ ሁኔታ የደረሰብኝ ለምንድን ነው?” የሚለውና የመሳሰሉት ሃሳቦች የዚህ ሙግት ምልክቶች ናቸው፡፡ ጠላታችንም ቢሆን በሆነብን ክፉ ነገርና ባልሆነልን መልካም ነገር አማካኝነት ኮቴ ኮቴያችንን እየተከታተለ አስቀያሚ ጥርሱን ማሳየቱ አይቀርም፡፡ ጌታ ስለእኛ በተናገረውና በወሰነልን ማንነት ከተደላደልን ግን ይህ የጠላት ሁኔታ ከምንም አይቆጠርም፡፡

የሚቀጥለው ትምህርት፡ “ከትንንሽ ንግግሮች መላቀቅ”


ከትንሽነት አመለካከት መውጣት

Показано 20 последних публикаций.