Фильтр публикаций


🌿️️️️🌿️️️️🌿️️️️✨✨✨🌿️️️️🌿️️️️🌿️️️️✨✨✨🌿️️️️🌿️️️️🌿️️️️✨✨✨

ኤፍታህ

አያድርገውና ጆሮዎቻችን ቢደነቁሩ እና ምላሳችን ቢተሳሰር ሰዎች በሦስት መንገድ ምላሽ ሊሰጡን ይችላሉ:: አንዱ ወገን "እንኳን እንዲህ ሆነበት" ብሎ መዘባበቻ የሚያደርገን ነው፡፡ ሌላው ወገን ደግሞ ክፉ ባይናገርም ለመርዳት ግን አይቀርበንም:: እንዲያው ከሩቅ ሆኖ "አይይ... የእገሌ ነገር እንዲህ ሆነ በቃ?" ብሎ ከንፈር የሚመጥ ይሆናል:: ሦስተኛው ወገን ግን ከደዌያችን የምንፈወስበት ቦታ ፈጥኖ ሊወስደን ይሞክራል:: በሁሉ ነገር ሊረዳንም ዝግጁ ነው፡፡ በወንጌል እንደምናነበው፤ በሦስተኛው ወገን የሚመደቡ መልካም ሰዎች አንድ ደንቆሮ እና ዲዳ የሆነን ሰው ወደ ጌታ ይፈውሰው ዘንድ አመጡት::

🌿️️️️✨✨
እነዚህ ሰዎች ወደ ጌታችን ያመጡትን ሰው ”እኛ አምጥተነዋል፤ ሌላውን እርሱ ይወጣው” ብለው ከፊት አሰልፈው ብቻ አልተውትም:: እንዲፈወስ ጥልቅ ፍላጎት ስለነበራቸው ጌታችን "እጁንም ይጭንበት ዘንድ ለመኑት" (ማር 7:33) ተብሎ ተጽፏል፡፡ እርሱም ይህንን ተመልክቶ ከሰዎች መካከል ለይቶ ወሰደው:: በቃሉ ብቻ መፈወስ የሚችል ጌታ ቢሆንም፤ እርሱ ግን "ጣቶቹንም በጆሮቹ አገባ እንትፍም ብሎ መላሱን ዳሰሰ፤ ወደ ሰማይም አሻቅቦ አይቶ ቃተተና፦ ኤፍታህ፡ አለው፥ እርሱም ተከፈት፡ ማለት ነው። ወዲያውም ጆሮቹ ተከፈቱ የመላሱም እስራት ተፈታ አጥርቶም ተናገረ።" (ማር 7:33-35) ይህ ሰው በእውነት እድለኛ ሰው ነበር:: መታመሙን አይተው ወደ ባለ መድኃኒቱ የሚያመጡ፣ ከዚያም አልፎ ይፈወስ ዘንድ የሚለምኑለት ወዳጆች ነበሩት:: የእኛስ ነገር እንዴት ይሆን? ቅዱስ ቃሉን ለመስማት የተሳነፉ ጆሮዎቻችንን ዓይቶ፣ ለክፋት እንጂ መልካም ለመናገር አልፈታ ያለውን አንደበታችንን ተመልክቶስ ማን መታመማችንን ይወቅልን? ታማችኋል፤ ወደ ባለ መድኃኒቱ ሂዱ ብሎ ማን ወደ ፈዋሹ ዘንድስ ያምጣን?

🌿️️️️✨✨
ጌታ ሆይ፤ እኛስ በብርቱ ታምመናል:: በጥበብህ መስማትን ይሰሙ ዘንድ ያበጀሃቸው ጆሮዎቻችን ክቡር ወንጌልህ ለመስማት ሲሆን ይደነቁራሉ፤ ለከንቱ ወሬ ሲሆን ግን ያለ እክል ይሠራሉ፡፡ ሐሜትን ለመቅዳት ወለል ብለው ይከፈታሉ፤ ተግሳጽህን ለመስማት ግን ይከረቸማሉ:: መልካምን ይናገሩ ዘንድ በጥበብ የፈጠርካቸው ምላሶቻችንም በከንቱ ልፍለፋ ሁሌም ይጠመዳሉ፤ ቅዱስ ቃልህን ለማካፈል ግን ይኮላተፋሉ:: ምላሶቻችን አንተን እንዲያመሰግኑ፣ ሰዎችንም በመልካም ቃላት እንዲያክሙ ብትፈጥርልንም፤ እኛ ግን ሰዎችን በሐሜት እያቆሰልንበት፤ በስድብም እያደማንበት እናሳዝንሃለን:: በንግግራችን አጥንት ማለምለም እንቢ ቢለን፤ ቅስም እየሰበርንበት አለን፡፡

ክቡር መድኃኔዓለም፤ ደንቆሮና ኮልታፋውን ሰው ወዳጆቹ አስበውለት ወደ አንተ አመጡት:: አንተም ጣቶችህን ወደ ጆሮዎቹ አስገባህ:: እንትፍ ብለህም ምላሱን ዳሰስክ:: በዚህም ቸርና ሰውን ወዳጅ መሆንህን አሳየኸን:: ከደጅህ የቆምነውን እኛን ከንቱዎቹን እንደ እርሱ ትፈውሰን ዘንድ ወደ አንተ መጥተናል:: እባክህ፤ ከዓለም ግርግር ለይተህ ውሰደን:: ጆሮዎቻችንን እና ምላሶቻችንንም ዳስስልንና ዝንት ዓለም አንተን እያወደስንህ የምንኖር እንሁን:: ፈዋሽ ቃላቶችህ ከንቱ የሆኑ ጆሮዎቻችንን ዘልቀው ወደ ልባችን እንዲገቡ አድርግልን፡፡ የደነደነ ልቤን አረሰረሰ፣ የተዘጉ ጆሮዎቼን ከፈተ፣ የተቆለፈ አንደበቴንም ፈታ ብለን እንዘምር::

ቸርና ሰውን ወዳጅ ሆይ፤ ለደንቆሮውና ለዲዳው ሰው "ኤፍታህ" ብለህ የተዘጉ ጆሮዎቹን ከፈትክለት፤ የምላሱንም እስራት ፈታህለት፡፡ለቃልህና ለተግሳጽህ ዝግ ሆኖ የቆየውን የእኛን ጆሮ "ኤፍታህ" ብለህ የምትከፍትልን መቼ ይሆን? ለወሬ እንጂ ለንስሃ አልፈታ ያለውን ምላሳችንን፤ ለሐሜት እንጂ ሥጋና ደምህን ለመቀበል አልከፈት ያለው አፋችንንስ "ኤፍታህ" ብለህ የምትከፍትልን መቼ ነው?

🌿️️️️✨✨
ጌታችን ሆይ፤ እኛ ልጆችህ ትፈውሰን ዘንድ አንተን ብለን መጥተናልና ተመልከተን:: እኛንም እዘንልን እና "ኤፍታህ" ብለህ መልካምን ሁሉ ለመስማት የሰነፉ ጆሮዎቻችንን ክፈትልን፤ ክፉን ሁሉ ለመናገር የፈጠነ አንደበታችንንም ለመልካም ፍታልን::

✨✨✨
✍️ መ/ር ፍሬሰንበት አድኃኖም
የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ
የዕብራይስጥ ቋንቋ መምህር

@sebhwo_leamlakne


🌿️️️️🌿️️️️🌿️️️️✨✨✨🌿️️️️🌿️️️️🌿️️️️✨✨✨🌿️️️️🌿️️️️🌿️️️️✨✨✨


➕ የሞትን ደብዳቤ ወደ ህይወት የቀየረው!
➕ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል!
➕ የኛንም ሕይወት ይቀይርልን!
የቅዱስ ሚካኤል ምልጃው ጥበቃው አይለየን፣ ጸሎታችሁን በእግዚአብሔር ፊት ያሳርግልን።


መልካም አዳር ውድ ቤተሰቦቻችን

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊



🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂
"ትጾማለኽ? ጾምኽ ፍጹም እንዲኾንልኽ የተራቡትን አብላ፥ ለተጠሙት አጠጣ፥ የታመሙ ወገኖችን ጎብኝ፥ የታሠሩ ወገኖችን መጠየቅ አትርሳ፥ የሚያለቅሱትንና የተበደሉ ወገኖችን አጽናና፥ ምሕረትን አድርግ፥ ትኹት ኹን፥ የተረጋጋኽ ኹን፥ ይቅር በል፥ እውነትን ተናገር፥ ሃይማኖተኛ ኹን። እንዲኽ ከኾነ እግዚአብሔር ጾምኽን ይቀበል ይኾናል። የንስሐን ፍሬም ገንዘብ ማድረግ ይቻልኻል። ጾም የነፍስ መድኃኒት ነውና።"

     ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

የተወደደ - በረከትን የሚያስገኝልን - ፍሬን የምናፈራበት ጾም  ይኹንልን!


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊
🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿
እንኳን ለተጋዳይ ለታላቁ አባት በቀንና በሌሊት ሰባት መቶ ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን ከስግደት ጋር እየጸለ ለአርባ ዓመት በገዳም ለኖረውና በኋላም ወደ በረሃ ከአንዲት ታናሽ ዋሻ ውስጥም ገብቶ እየተጋደለ ብቻውን ለኃምሳ ዓመት ለኖረ፤ ሁለት አንበሶች እንደሰው ለሚላኩለት ለባለ አንበሳው ለአባ አውሎግ ለዕረፍት በዓል፣ ለሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ለከበረ ለአባት ለአባ በላትያኖስ በንጉሥ ዳኬዎስ እጅ ለአንድ ዓመት ያህል ተሰቃይቶ ኋላም አንገቱን በመሰየፍ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና ለአባ ስልዋኖስ ረድእ ለአባ በትራ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከኤጲስቆጶስ ከአባ አብርሃም፣ ከመነኰስ ከአባ መቃቢስና ከኮንቲ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ  ረድኤትና በረከት ያሳትፈን።


@sebhwo_leamlakne


✨🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


ወደ መኝታህ ስትቀርብ እንዲህ አልጋህን በለው፦ “አልጋዬ ሆይ፣ ምናልባት በዚህች ሌሊት መቃብሬ ትሆኛለህ፤ ምክንያቱም በምትሃት እንቅልፍ ፈንታ፣ ወደፊት ያለው ዘላለማዊ እንቅልፍ የኔ ይሆን እንደሆነ አላውቅምና።” ስለዚህም ገና እግሮች እያሉህ፣ ፈጽሞ ሊበጠሱ በማይችሉ እስራት ከመታሰርህ በፊት የመስራትን መንገድ ተከተል። እጆች እያሉህ እስከ ሞት ድረስ በጸሎት እራስህን ስቀል። ገና አይኖች እያሉህ፣ በአፈር ከመሸፈናቸው በፊት በእንባ ሙላቸው። ጽጌረዳ በነፋስ ትንፋሽ እንደሚረግፍ፣ አንተም ከተፈጠርክባቸው ንጥረ ነገሮች በአንዲቱ ትንሽ ትንፋሽ ትሞታለህ። የፈጣን ሞት ሐሳብ በልብህ ውስጥ ይኑር፣ ሁልጊዜም ለራስህ እንዲህ በል፦ “እነሆ መልእክተኛው ሊወስደኝ በደጅ ነው የደረሰው። ለምን እዘገያለሁ? መነሳቴ ዘላለማዊ ነው፤ ወደ ኋላ መመለስም የለም።”

የቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊው


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁

እንኳን #ከዐሥራ_ሁለቱ_ሐዋርያት ለአንዱ ለእልፍዮስ ልጅ #ለከበረ_ሐዋርያ_ለቅዱስ_ያዕቆብ በንጉሥ ቀላውዴዎስ ዘመን በአይሁድ እጅ በድንጋይ ተወግሮ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል፣ #ለኢትዮያዊያኑ_ጻድቅ_ለአቡነ_እንድርያስ ኤርትራ አገር የሚገኘው ታላቁ ገዳም ደብረ ጽጌ ሰፍኣ ለመሰረቱ #ለዘጠኝ_መቶ_ዘጠና_ዘጠኝ_ደቀ_መዛሙርቶች በአረማውያን እጅ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል (ታሪካቸውን የካቲት1 ይመልከቱ)፣ ለንጉሥ ኑማርያኖስ ልጅ ለከበረ #ለቅዱስ_ዮስጦስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል፣ ፈርማ ከሚባል አገር በገድል ለተጠመደ ምሁር ለሆነ ዐሥራ ስምንት ሺህ መጽሐፍቶችን ተግሣጻትና ድርሳናት ለጻፈ ለዓለሙ ሁሉ #መምህር_ለአባ_ኤስድሮስ ለዕረፍት በዓልና ለፋርስ አገር ኤጲስቆጶስ #ለአባ_ፌሎ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ #ቅዱሳን_ከኒቅላዎስና_ከስምዖን ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


@sebhwo_leamlakne


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


ከመለሳችሁ በኋላ👍❤🥰አድርጉ ቅዱስ ቅባት በመቀባት ከሥጋም ከነፍስም ደዌ የምንድንብት ምሥጢር የትኛው ነው?
Опрос
  •   ምሥጢረ ሜሮን
  •   ምሥጢረ ቀንዲል
  •   ምሥጢረ ተክሊል
  •   ምሥጢረ ቁርባን
63 голосов

2.2k 0 18 10 175

#ቅኔ_ነሽ

ልጠራ ልሰየም ድንግል በስምሽ
ተሰጠኝ በመስቀል እናቴ አድርጎሽ
ግቢ ወደ ቤቴ ወደ ጎሰቆለው
ሃዘን በበዛበት ባይተዋር በሆነው-(2)
ግብሬ ክፉ ስራ መንገዴ የግፍ
ፅልመት ያጨለመኝ ከድካም አላርፍ
አንቺ ስትሰጪኝ ከመስቀል ግርጌ
እንዴት ላመስግንሽ እንዴትስ አድርጌ  
      ቅኔ ነሽ የማይቆም ዝማሬ
        ያፈልቃል ማወደስ ከንፈሬ
        ሞገስ ነሽ ለምስኪናን ሁሉ
        ማርያም ምሊተ ኩሉ    
 
                    
አቡጊዳዬ ነሽ ጽድቅ የተማርኩብሽ
የፊደል ገበታ ጌታን ያወኩብሽ
የህይወት መገኛ ቤተልሄም ለህብስቱ
ተቀዳ ከሆድሽ ህይወት ለፍጥረቱ       
ርግብዬ ንኢ ሰናይትየ              
        ልቤ አያርፍ ልጅሽን ካላየ
        መገኛ የሰላሜ ረፍቱ
        ላመነሽ ቅጥር ነሽ ርስቱ
                    
ምዕልይተ ጸጋ የንጉስ ሙሽራ
ለተጠማ ውሻ ልብሽ የሚራራ
ሸልሞ ከሰጠኝ አንቺን ለእናትነት
በሰሽ ልጠራ እንድታወቅበት 
ጣፋጭ ነሽ ከማር ከወለላ
  ምስጋናሽ በአንደበቴ ይሙላ
  ለንጉስ ኪሩብ ለመንግስቱ
  ማረፊያ ድንግል ለፍጥረቱ
   
ዘማሪት እፀገነት ከበደ


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ትወልዳለች ኃጢአት ካደገች በኋላ____ትወልዳለች?
Опрос
  •   ተንኮል
  •   ጥላቻ
  •   ሞት
  •   ንቀት

3.3k 25 19 22 120

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁

እንኳን #ለእስክንድርያ_አገር አርባ ሦስተኛ ሊቀ ጳጳስ በአገሩ የነገሡ የተለያዩ አሕዛብ ነገሥታት በጽኑ ሥቃይ ላሠቃዩት ለከበረ አባት #ለአባ_እለስክድሮስና ለአርባ አምስተኛ ሊቀ ጳጳስ ለከበረ አባት #ለአባ_ቴዎድሮስ ለዕረፍታቸው በዓል፣ የሰውን ፊት ሳያይ በበረሀ ለሰባ ዓመት ለኖረ አባ ዕብሎይን ላረጋጋ ለገዳማዊው አባት #ለአባ_አብዱልማስ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ #ከአብራቅያ_ከአባዲር፣ #ከአባርያኖስና ከዕረፍታቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


@sebhwo_leamlakne

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


☝️☝️
[ አጋዝዕተ ዓለም ሥላሴ፣ ስዕለተ ማርያም፣ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣ ቅድስት እኅተ ጴጥሮስ]

አክብረን እና አስበን እንውላለን።

(#ዕለት:- ዓርብ
      #ቀን:- የካቲት ፯ ፳፻፲፯ ዓ.ም)


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


በዚህ ሁሉ በወደደን በእርሱ ከምን እንበልጣለን ይላል?
Опрос
  •   ከሰይጣን
  •   ከዓለም
  •   ከአሸናፊዎች
  •   ሁሉም
171 голосов


እግዚአብሔር ቋንቋን የደበላለቀባቸው ህዝቡ ምን በማድረጋቸው ነው?
Опрос
  •   ልጆቻቸውን መስዋዕት በማድረጋቸው
  •   እግዚአብሔርን በመሳደባቸው
  •   ለእግዚአብሔር መስዋዕት ባለማቅረባቸው
  •   ባቢሎንን በመስራታቸው
331 голосов


ኦዛ ታቦተ እግዚአብሔር ስታጋድል እርሷን ለመያዝ እጁን ቢዘረጋ ተቀሰፈ ኦዛ የሞተበት ያቦታ ማን ተብሎ ተጠራ?
Опрос
  •   አቤንኤዘር
  •   ቤቴል
  •   የኦዛን ስብራት
  •   ሰማርያ
263 голосов


#ይተካል_እግዚአብሔር

ይተካል እግዚአብሔር አገልጋይ ለቤቱ
ከዛሬው የሚልቅ የማይዝል ጉልበቱ
አይሰስትምና ፀጋን በማካፈል
ብርቱውን ያስነሳል ከትውልዱ መሃል (፪)

የሙሴ በረከት ደርሶዋል ለኢያሱ
አምላክ በቃ ብሎ ሊጠራው ወደርሱ
ኢያሱን አቆመው በበረታ ጸጋ
የነገሥታት ንጉሥ አልፋና ኦሜጋ (፪)

መጎናጸፊያውን ለኤልሳ ትቶለት
ኤሊያስ ቢሄድም ቢነጠቅ በእሳት
እጥፍ ድርብ ጸጋ ከሁሉ የሚልቅ
አምላክ ስለሰጠው ፈጽሟል ድንቃድንቅ (፪)

ከእኔ ብቻ በቀር ማነው ያለው ሌላ
ትጉን ለአገልግሎት ዝናሩ ያልላላ
እንዲህ አትበሉ እግዚአብሔር ዘገየ
ይሾማል ለቤቱ ጠላት ዓይኑ እያየ (፪)

ቀድሰን ዘምረን ወንጌሉን መስክረን
ወደ ሰማዩ ቤት ደሞ እንሄዳለን
እግዚአብሔር ያስነሣል ዳግም እንደገና
ዘመኑ የዋጀ እጅጉን የጸና (፪)

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


☝️☝️
[ግዝረተ ኢየሱስ፣ ቁስቋም ማርያም፣ ነቢዩ ኢያሱ፣ቅድስት አርሴማ፣ አባ ጰንጠሌዎን፣ ቅዱስ ቴዎዶስዮስ፣ አቡነተጠምቀመድኅን]

አክብረን እና አስበን እንውላለን።

(#ዕለት:- ሀሙስ
      #ቀን:- የካቲት ፮ ፳፻፲፯ ዓ.ም)


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


እሰይ ነጋ - ቅዱስ ኃያል፣ የድንግል ልጅ ልዑል እግዚአብሔር ክበር ተመስገንልን።
በፍቅር ዋሉ ክርስቲያኖች!


"#የእግዚአብሔር ስም የጸና ግንብ ነው፤ #ጻድቅ ወደ ርሱ ሮጦ ከፍ ከፍ ይላል።" ምሳ. ፲፰፥፲

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁

እንኳን አስቀድሞ ራሱን በኃጢአት አስገዝቶ ለነበረ ለጽኑዕ ተጋዳይ #ለአባ_ዕብሎይ ለዕረፍት በዓል፣ ለተጋዳይ ለሆነ #አባት_ጴጥሮስ_ለተባለው አስቀድሞ በድሎት ብቻ ይኖር ለነበረውና በኋላም ነፍሱ ተነጥቃ ሲኦልን አይቶ ከተመለሰ በኋላ በታላቅ መንፈሳዊ ተጋድሎ ሠላሳ ስምንት ዓመት ለኖረው #ለአባ_ብሶይ ለዕረፍት በዓል፣ መነሳንሱ የወርቅ ለሆነ ለጻድቅ #አባ_ኖብ ለዕረፍት በዓልና ለእስክድርያ አገር ዐሥረኛ ሊቀ ጳጳሳት ለከበረ አባት #ለአባ_አክርጵዮስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ በአስቄጥስ ገዳም በሰማዕትነት ከሞቱ #ከአባ_ዘጠኝ_መነኰሳት፣ ከሮሜ ሊቀ ጳጳሳት #ከአባ_አቡሊዲስ_ከቡላ_ከአሞኒ_ከዕብሎይ_እናት_ከአበያ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

@sebhwo_leamlakne


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


🍁️️🍁️️🍁️️✨✨✨🍁️️🍁️️🍁️️✨✨✨🍁️️🍁️️🍁️️

"ጸሎት በሕይወት ማዕበል ውስጥ መጠጊያ ወደብ ማእበል ለሚያንገላታቸው መልሕቅ የድሃው ሐብት የባለጸጋው ደህንነት የታማሚው መዳኛ ወይም ጤና ማግኛ ነው ጸሎት መጥፎ ነገሮችን ያስወግዳል መልካሙን ይጠብቃል።"

                              🍁️️✨✨ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

"ከንቱ ውዳሴ በመንገድ ሁሉ የሚከተልህ የተሸሸገና ጭንብል ያጠለቀ ሌባ ነው። አሳዳጅ በመሆኑ በጣም ደኅንነት በሚሰማህ አሳቻ ሰዓት ሳታውቀው ይዘርፈሀል፤ ይገድልህማል። "

                             🍁️️✨✨ቅዱስ ጎርጎርዮስ

"ብርሃን ወደ አንድ ቤት ውስጥ ሲገባ ጨለማን እንደሚያስወግድ ሁሉ፤ እግዚአብሔርን መፍራት ወደ አንድ ሰው ልብ ሲገባም አለማወቅን (በኃጢአት የሚወድቅባትን) ያስወግዳል።"

                           🍁️️✨✨አባ እንጦንስ

"ካህኑን እንደ መንፈሳዊ አባትነቱ እየው፤ ልክ በሽተኛ የተሸፈኑ ቁስሎችን ለሐኪም እንደሚያሳይና እንደሚፈውስ ምስጢሮችህን በግልጽ ንገረው”

                         🍁️️✨✨ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ።


"ሰይጣን ክርስቶስ በልብህ ውስጥ ያለ መሆን አለመሆኑን ያውቃል፡፡ ይኸውም ስትቆጣ ወይም ስትጮህ ወይም የማይረቡ ከንቱ ነገሮችን ስትናገር ሲያይህ ጠላት በአንተ ዘንድ እግዚአብሔር እንደሌለ ያውቃል ያን ጊዜ በውስጥህም በውጭህም ያለውን ሳይቀር ይገዛል ፤ መዝጊያ እንደሌለው ቤት እንደ ክፉ ሌባ ይገባና ውስጥህን ይበረብረዋል፡፡"

                          🍁️️✨✨ ቅዱስ ባስልዮስ


"ጥላቻን በልቡ ውስጥ የሚሸሽግ ሰው እባብን በጭኑ ላይ የሚያስቀምጥን ሰውን ይመስላል።
ጭስ ንቦችን እንደሚያባርር ሁሉ ጥላቻም በልብ ውስጥ የተቀመጠን እውቀት ያጠፋል፡፡"

                        🍁️️✨✨ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ


ሰው ሆይ! ጻድቅ መሆንን ትወዳለህን? አዎን ትለኝ እንደሆነ፥ እንግዲያውስ ለራስህ ንፉግ ለሌላው ግን ቸር ሁን፡፡

                     🍁️️✨✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ


@sebhwo_leamlakne

🍁️️🍁️️🍁️️✨✨✨🍁️️🍁️️🍁️️✨✨✨🍁️️🍁️️🍁️️


ኖህ ውሃውን መቅለሉን ለማረጋገጥ በመጀመሪያ መስኮቱን ከፍቶ የላከው ምንን ነው?
Опрос
  •   ንስርን
  •   እርግብን
  •   ቁራን
  •   ወፍን
144 голосов

Показано 20 последних публикаций.