Фильтр публикаций


#እግዚአብሔር_ሆይ

እግዚአብሔር ሆይ እርዳኝ ቸርነት አድርገህ ፪
እድሜ ለንሰሃ እንደ ሕዝቅያስ ሰጥተህ
ጠማማውን ልቤ በቃልህ አቃኝተህ
           
አዝ =======

አላቀውም ብሎ ሲጠየቅ ያመጸው
ዶሮ እስኪጮህ ድረስ ሦስት ጊዜ የካደው
የጅረት ወንዝ ነው የሰጠኸው እንባ
ጴጥሮስ ተጸፅቶ ንስሃ እንዲገባ
         
አዝ =======
ፅዋው እንዳይደርሰኝ የይሁዳ እድል
ልጅህ ሆኖ ውሎ ኋላ መኮብለል
ጴጥሮስ እድለኛው አልቅሶ ተማረ
በትዕቢቱ ይሁዳ እንደወጣ ቀረ
         
አዝ =======
ዘመኗን በሙሉ በዝሙት አቃጥላ
ለንሰሐ ጠራት ጌታ በገሊላ
ታድሳ ተነሳች በእንባዋ ብዛት
እግሩ ሥር ተደፍታ ማርያም መግደላዊት
         
አዝ =======
አመጸኛው ልቤ ዛሬስ መች ይተኛል
በኃጢአት በዝሙት በስርቆት ይዋኛል
ወደ ቀድሞ ግብሩ እዳይመለስ
ፍቅርህ በእኔ ሰርጾ ኃጢአቴን ደምስስ
         
አዝ =======

በደላችንን ሁሉ ሳታስብ ትተህ
በምጽአት ሰዓት ከጻድቃን ቆጥረህ
ነጭ ልብስ ለብሰን ሆነን ከአንተ ጋራ
በሩ ሳይዘጋ አስገባን አደራ

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊
ሀሳብ አስተያየት ካለ @kingo08bot


የካቲት ፳፰ /28/


በዚች ዕለት በነገሥታት መክሲሞስና መክስምያኖስ ዘመን ሮማዊ ቅዱስ ቴዎድሮስ በሰማዕትነት አረፈ።

ይህንንም ቅዱስ ለጣዖቱ እንዲሰዋ ንጉሱ ሊደልለው ቢሞክር እንቢ አለው በመጨረሻም ንጉሱ ለመኮንኑ ሰጠው መኮንኑም ሊያሳምነው ባልቻለ ግዜ አንገቱን አነቀው እግዚአብሔርም ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ አዳነውና እየዞረ የሚያስተምርበትን መንፈሳዊ ፈረስ ሰጠውና ወደ እስያ ሔደ።

ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ የከበረ ቴዎድሮስን ከነፈረሱ እንዲይዙት በትምህርቱም የአመኑትን ሁሉ እንዲገድሉ መቶ ፈረሰኞች ወታደሮቹን ላከ። ከሴቶችና ከልጆች በቀር ስድስት ሺህ አርባ ስምንት ሰውን ገደሉ። ሊይዙትም ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ በደረሱ ጊዜ ፈረሱ በላያቸው ተወረወረ ከአፉም እሳትን አውጥቶ አመድ እስኪሆኑ አቃጠላቸው ነገር ግን ሌሎች አግኝተው ያዙትና ወደ ንጉሥ ወሰዱት እርሱም ወደ እሥር ቤት እንዲአስገቡት እንዳይበላና እንዳይጠጣም ደጃፎችን እንዲዘጉበት አዘዘ።

ጌታችንም ተገለጠለትና ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውንም ለሚያደርግ ገድሉንም ለሚጽፍ ዕድል ፈንታውን ከርሱ ጋር በመንግሥተ ሰማያት ያደርግ ዘንድ ቃል ኪዳንን ሰጠው።

ከዚህም በኋላ ቅዱስ ቴዎድሮስን ወደ ነደደ እሳት ወረወሩት ምስክርነቱንም ፈጸመ የመላእክት አለቆች ሚካኤልና ገብርኤል ነፍሱን ተቀበሉ በሦስት አክሊላትም አቀዳጁት ሥጋውንም አውሳብያ የተባለች የመኰንኑ ሚስት ወሰደች ዋጋው ብዙ በሆነ ሽቱም ገነዘችውና ወደ ገላትያ ወሰደችው በዕብነ በረድ ሣጥንም አድርጋ በዚያ ቀበረችው ቤተ ክርስቲያንም ሠራችለት ከሥጋውም ታላላቆች ድንቆች ተአምራቶች ተገለጹ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@sebhwo_leamlakne

🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋


#እግዚአብሔር_ስራው_ድንቅ_ነው

እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው
ለኔ ያደረገው ብዙ ነው
እግዚአብሔር ስራውን ድንቅ ነው
ለኔ ያደረገልኝ ብዙ ነው

እረዳቴ እሱ ነው ከሰማያት
እግዚአብሔር ጠባቂ ለኔ ህይወት ብርሀን በፊቴ የሚያበራ
አምላኬ ድንቅ ነው የሱ ስራ

በመንገዴ ሁሉ የሚመራኝ
ስነሳ ስወድቅ የሚያስበኝ
ማንም አልመጣል ከወገኔ
ከሁሉም ይበልጣል እርሱ ለኔ


የዳየ ደብዳቤ ውድቅ አድርጎ
ህይወቴን መራልኝ ወደ ጎን
ኧረ እግዚአብሔር ማን ይሆናል
እሱን ለሚፈሩት ይታመናል

አንድ ቀን አስቤ ተጨንቄ
ለመኖር አልቻልኩም ተጠንቅቄ
ሁሉን ነገር ለእርሱ ትቸዋለሁ
በምህረት ጥላ እኖራለሁ

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


የካቲት ፳፯ /27/

በዚች ቀን በታላቁ ንጉሥ በቈስጠንጢኖስ ዘመን የከበረ አባት የአንጾኪያ አገርሊቀ ጳጳሳት ትምህርቱ በዓለም የመላ አንስጣስዮስ አረፈ።

የከበሩ አባቶችም በኒቅያ ከተማ የአንድነት ስብሰባ በአደረጉ ጊዜ በዚህ ጉባኤ ከተሰበሰቡት ሊቃውንት አንዱ እርሱ ነው በዚህም ጉባኤ ተስማምተው አርዮስን ከባልንጀሮቹ ጋር አውግዘው ለይተውታል ባልንጀሮቹም የቂሣርያ አውሳብዮስ የኒቆምድያ አውሳብዮስና አርናሲስ ናቸው። እሊህም በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ታውቀዋል።

እሊህም የከበሩ አባቶች ሥርዓትን ሠርተው ወደየሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ እሊህ ከኤጲስቆጶስነት ሹመት የተሻሩት ወደ ኢየሩሳሌም የሚሔዱ መስለው ወጡ ወደ አንጾኪያም ከተማ ገብተው ከአንዲት አመንዝራ ሴት ዘንድ ተሰበሰቡ ብዙ ገንዘብም ሊሰጧት ቃል ገቡላት ወደ ቤተክርስቲያን እንድትገባ ይህ አባት ከእርሷ ጋር እንዳመነዘረ የወለደችውም ልጅ የእርሱ እንደሆነ በዚህ ቅዱስ አባት አንስጣስዮስ ላይ ለካህናቱና ለሕዝቡ እንድትናገር አስተማሩዋት።

ሕዝቡም እንዲህ አሏት አንቺ ሐሰተኛ ነሽ በዚህ ቅዱስ አባትም ላይ ሐሰትን ተናግረሻል በከበረ ወንጌል ካልማልሽ በቀር ቃልሽን አንቀበልም አሏት እርሷም ስለ ገንዘብ ፍቅር በሐሰት ማለች። ከዚህም በኋላ ለንጉሥ ነግረው ከመንበረ ሢመቱ ወደ አጥራክያ ደሴት አሳደዱት በስደትም ሳለ በርሷ አረፈ።

ከመንበረ ሢመቱ ለመሰደዱ ምክንያት የነበረችው ሴትም በቅዱሱ ላይ በሐሰት በመመስከሯ በጽኑ ደዌ ታመመች በመጨረሻም ያደረገችውን ሁሉ በአደባባይ ተናግራ የቅዱሱን ንፅህና መሰከረች።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@sebhwo_leamlakne

🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋


የካቲት_26
#አንድ_አምላክ_በሆነ_በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ_ስም
የካቲት ሀያ ስድስት በዚህች እለት ነቢይ_ሆሴዕ አረፈ፣ ለቅዱሳን_ሳዶቅና ከእርሱ ጋር ሰማዕትነት ለተቀበሉ ሁለት_ሺህ_ስምንት ሰዎች ለዕረፍታቸው በዓል መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።

#ቅዱስ_ሆሴዕ_ነቢይ
የካቲት ሀያ ስድስት በዚህች እለት ዖዝያ ይባል የነበረ እውነተኛ ነቢይ ሆሴእ አረፈ። ዳግመኛም ይህ ነቢይ በአራቱ የይሁዳ ነገስታት ዘመን ትንቢት ተናገረ። እሊህመ ዖዝያን ኢዮአታም አካዝ ህዝቅያስ ናቸው። በትንቢቱም ድንቆች ስራዎችን ተናገረ የእስራኤልንም ልጆች ብሎም ጠራቸው እግዚአብሔርም ቁጣውን ከእርሳቸው እንደማይመልስ አስረዳቸው።

እንዲህም አለ የእስራኤል ልጆች ቁጥራቸው እንደማይሰፈርና እንደማይቁጠር የባህር አሸዋ ቢሆን ከጥቂት በቀር አይተርፍም አለ። ስለ አህዛብም በ እግዚአብሔር ማመን ተናገረ እንዲህም አለ እኔ ወገኖቼ ያልሆኑትን እጠራቸዋለሁ እነርሱም ይሰሙኞል።

ዳገመኛም ስለ መድኃኒታችን መከራ መቀበልና በከበረ ደሙ ስለ መዳናችን ስለ ትንሳኤውም እንዲህ ብሎ ተናገረ። እሱ በመከራ ገርፎ ያድነናል እርሱም በመከራ አቁስሎ ይቅር ይለናል ሲያድነንም በሁለተኛው ቀን ነው ።

በሶስትኛውም ቀን ድነን በሱ ፊት እንነሳለን እግዚአብሔርንም አውቀን እንከተለው ዘንድ ስለ ሞት ስልጣን መሻር ስለ መቃብርም መሸነፍ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ ሞት ይዘህ ማስቀረትህ መቃብርስ ድል መንሳትህ ወዴት ነው ትንቢትን እየተናገረ ሰባ ዓመት ያህል ኑሮ በበጎ ሽምግልና አረፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በነብዩ ቅዱስ ሆሴዕ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
#ቅዱስ_ሳዶቅ
በዚህችም እለት የከበሩ ሳዶቅና ከእርሱ ጋር የሆኑ ሁለት ሺህ ስምንት ሰዎች በሰማእትነት አረፉ። ይህንንም የከበረ ሳዶቅን ለፀሀይ ይሰግድ ዘንድ የፋርስ ንጉስ ብርህም ፈለገው ቅዱሱም ለፈጣሪዋ እንጂ ለዚች ለምትታይ ፀሀይ ልሰግድ ከእናቴ ማህፀን አልወጣሁም ብሎ መለሰለት።
ብርህም ንጉስም መልሶ ለዚች ፀሀይ አምላክ አላትን አለው ቅዱስ ሳዶቅም አለሙን ሁሉ የፈጠረ ክርስቶስ አምላክ ነው አለው ። ንጉሱም የቅዱስ ሳዶቅን ራስ በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የከበረ ሳዶቅም ቁሞ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ከዚህም በኃላ ራሱን ዘንበል አድርጎ ቆረጡት።

ያን ጊዜ ከሰማይ ብርሀን በላዩ ወረደ ከዚያ ያሉትም ሁሉ አይተው እኛ ሁላችንም በቅዱስ ሳዶቅ አምላክ የምናምን ክርስቲያን ነን ብለው ጮኹ ንጉሱም ሁሉንም ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማእትነት አክሊልንም በመንግስተ ሰማያት ተቀበሉ ቊጥራቸውም ሁለት ሺህ ስምንት ነፍስ ናቸው።
††† "ኑ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንመለስ:: እርሱ ሰብሮናልና: እርሱም ይፈውሰናል:: እርሱ መትቶናል: እርሱም ይጠግነናል:: ከሁለት ቀን በሁዋላ ያድነናል:: በሦስተኛውም ቀን ያስነሳናል:: በፊቱም በሕይወት እንኖራለን:: እንወቅ:: እናውቀውም ዘንድ እንከተል . . . " ††† (ሆሴዕ 6:1-3)

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትሁን አሜን፡፡

@sebhwo_leamlakne


 ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞


የካቲት ፳፮ /26/


በዚች ዕለት ዖዝያ ይባል የነበረ ዕውነተኛ ነቢይ ሆሴዕ አረፈ። ዳግመኛም ይህ ነቢይ በአራቱ የይሁዳ ነገሥታት ዘመን ትንቢት ተናገረ። እሊህም ዖዝያን፡ ኢዮአታም፡ አካዝ፡ ሕዝቅያስ ናቸው።

በትንቢቱም ድንቆች ሥራዎችን ተናገረ የእስራኤልንም ልጆች ገሠጻቸው የአመንዝራ ልጆች ብሎም ጠራቸው እግዚአብሔርም ቍጣውን ከእርሳቸው እንደማይመልስ አስረዳቸው። እንዲህም አለ የእስራኤል ልጆች ቍጥራቸው እንደማይሠፈርና እንደማይቈጠር የባሕር አሸዋ ቢሆን ከጥቂት በቀር አይተርፍም አለ። ስለ አሕዛብም በእግዚአብሔር ማመን ተናገረ እንዲህም አለ እኔ ወገኖቼ ያልሆኑትን እጠራቸዋለሁ እነርሱም ይሰሙኛል።

ዳግመኛም ስለ መድኃኒታችን መከራ መቀበልና በከበረ ደሙ ስለ መዳናችን ስለ ትንሣኤውም እንዲህ ብሎ ተናገረ። እሱ በመከራ ገርፎ ያድነናል እርሱም በመከራ አቍስሎ ይቅር ይለናል ሲያድነንም በሁለተኛው ቀን ነው በሦስተኛውም ቀን ድነን በሱ ፊት እንነሣለን እግዚአብሔርንም አውቀን እንከተለው ዘንድ ስለ ሞት ሥልጣን መሻር ስለ መቃብርም መሸነፍ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ ሞት ይዘህ ማስቀረትህ መቃብርስ ድል መንሳትህ ወዴት ነው ትንቢትን እየተናገረ ሰባ ዓመት ያህል ኑሮ በበጎ ሽምግልና አረፈ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑርለዘላለሙ አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@sebhwo_leamlakne

🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋


በእግዚአብሔር የሚያምኑ ሰዎች መደሰት የማይገባቸው በምንድን ነው?
Опрос
  •   በጭፈራና በዘፈን
  •   በእግዚአብሔር
  •   ወደ እግዚአብሔር ቤት በመሄድ
  •   ለ እና ሐ
177 голосов


ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አብይ ፆምን የፆመው የት ሆኖ ነው ?
Опрос
  •   ገዳመ ቆሮንቶስ
  •   ደብረ ዘይት ተራራ
  •   ደብረታቦር
  •   ቀራኒዮ
240 голосов


የካቲት ፳፭ /25/


በዚች ቀን የከበሩ አውሳንዮስና ፊልሞና ስሟ ሉቅያ የሚባል አንዲት ድንግልም በሰማዕትነት ሞቱ።

እሊህ ቅዱሳንም በአፍራቅያ ሀገር ሳለ በከበረ ሐዋርያ ጳውሎስ ትምህርት ያመኑ ናቸው ከሀድያንም ዝሑራ በሚባል ኮከብ ስም ለሚጠሩት ለአርታዳሚ ጣዖት በዓልን በአደረጉ ጊዜ አይተው በስሕተታቸው ሊዘብቱ እሊህ ቅዱሳን ተሰብስበው ወደ ጣዖቱ ቤት ገቡ ሰዎችም ለጣዖቱ ሲሠዉና ከፍ ከፍ ሲያደርጉት በአዩአቸው ጊዜ በክብር ባለቤተ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር እሳትነት ልባቸው ነደደ ከጣዖቱም ቤት ወጥተው ወደ ክርስቶሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሔደው የክብር ባለቤት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብሩንና ልዕልናውን አብዝተው አመሰገኑ።

ከዚያ ካሉት አንድ ሰው በሰማቸው ጊዜ በጣዖታቸው ላይ እንደ ዘበቱ የተናገሩትን ልብ ብሎ በመኰንኑ ዘንድ ወነጀላቸው መኰንኑም በፈረስ ተቀምጦ ሔደ ከወታደሮቹም ጋር ቤተ ክርስቲያኒቱን ከበባት ከምእመናንም ሰዎች የሸሹ አሉ።

እሊህንም ሦስቱን ቅዱሳን ያዛቸው የብረት ዘንጎችን በእሳት አግለው በቅዱሳኑ ጐኖች ውስጥ አደረጉት ከዚህም በኋላ የከበረ አውሳንዮስን ወደ ጒድጓድ ወረወሩትና ነፍሱን እስከ ሰጠ ድረስ በደንጊይ ወገሩት።

የከበረ ፊልሞናንና የከበረች ሉቅያን ግን ብዙ ጊዜ በጸና ሥቃይ ያሠቃዩአቸው ጀመር ነፍሳቸውንም ይወስድ ዘንድ እግዚአብሔርን ለመኑት እርሱም ልመናቸውን ተቀብሎ ነፍሳቸውን ወሰደ።

በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነሆ የምስክርነታቸውና የሃይማኖታቸው መታሰቢያ ተጽፎአል ። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@ney_ney_emye_maryam
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


እንኳን ለከበሩ #በቅዱስ_ጳውሎስ ትምህርት ላመኑ #ለቅዱሳን_አውሳንዮስ_ፊልሞ፣ ለድንግል #ቅድስት_ሉቅያ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለከበረ #ሐዲስ_አባ_እንጦኒ ይህም ረውሕ ለሚባለው ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና ከግብጽ አገር ከእስሙናይን አውራጃ ለሆነ ዐሥራ ስምንቱ ዓመት ቆሞ ሳይቀመጥ ለጸለየ #ለአባ_አቡፋ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሮሜ አገር #ከዲያቆን_ቶና ከአገረ ቊስ #ሚናስ_ከጋዛ_ይልማድዮስ በሰማዕትነት ከዐረፉ፣ #ከደማይልናልና_ከርጊኖስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ  ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

@sebhwo_leamlakne


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


ጌታዬና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ
✍️✍️✍️✍️✍️
በዚያ በምኩራብ ስታሰተምር ሳለ ፲፰ አመት ጀምሮ የድካም መንፈስ ያደረባትንንና ቀና ብላ ትቆም ዘንድ የማትችለውን ሴት ከድካምሽ ተፈትተሻል ባልካት ጊዜ ቀጥ ብላ እንደቆመች፤ እኔም የኃጢአቴ ብዛት እንደ ሸክም ከብዶኝ ጎብጫለሁና አቤቱ መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ሸክሜን አንሳልኝ፤ ቀና ብዬ እንድሄድ እርዳኝ።

አሜን 🙏🙏
እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


#አማኑኤል_ይቅር_ባይነዉ

አማኑኤል ይቅር ባይነዉ ፍቅር
ምህረት ከቦት በሰማያት ሚኖር
እያመመው አባቱን እየጠራ
አይቻለው ለሚገድሉት ሲራራ

#አዝ

አይምረኝም አትበሉ ጨካኝ ንጉስ አይደለም
ደሙ ብቻ ያነፃናል ከሀጢአታችን ዘለዓለም
እንደሞላ ጅረት ፈሶ ምድራችንን አጥለቅልቋል
የእሱ ምህረት ሀይል ሆኖት ስንቱ ከሞት አፈትልኳል

#አዝ

የጨለመው እየነጋ የተሻለ ቀን ይመጣል
በፍቅሩ ጦር ሳይወጋ ማን ከሞት እሮጦ ያመልጣል
ያን ክፉ ቀንበድል አልፈን እንደ ዋርካ የሰፋነው
ነውርን ሁሉ በሚከድን በሞተልን በኢየሱስ ነው

#አዝ

የእሱን ፍቅር የሚያሸንፍ አንዳች ሀጢአት የለምና
ወደጌታ ለመመለስ አንዳች እንኳን እዳትፈራ
ሀገራችን በሰማያት ነው የሚወድቅ የለም የሚረሳ
ሰማያትን እንወርሳለን ከቤቱ ደም የተነሳ

#አዝ

ወዳጅ አለን አንድ ብቻ በሰማያት የምድርም
ስሙ ኢየሱስ የተባለ ሰውን ሁሉ የሚያፈቅር
ከመቃብር በላይ ሆኖ ፍቅሩ አለምን አስገረመ
እሄን ሁሉ ጎስቋላ ሰው በትክሻው ተሸከመ

ዘማሪ ዕዝራ ኃ/ሚካኤል


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


ይህንን checklist ይጠቀሙ።


የሳምንት 2 ቅድስት ቻሌንጅ

ዳሩ ግን፦እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ኹኑ ተብሎ ስለ፡ ተጻፈ የጠራችኹ ቅዱስ እንደ ኾነ፡ እናንተ ደግሞ በኑሯችኹ ዅሉ ቅዱሳን ኹኑ።
-1ኛ ጴጥ 1:15-16


የካቲት ፳፬ /24/


በዚች ቀን የከበረ አባት ኤጲስቆጶስ አጋቢጦስ አረፈ።

ይህም አባት በከሀድያን ነገሥታት በዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ ዘመን ነበር። ወላጆቹም ደጎች ምእመናን ነበሩ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተምረውት ዲቁና ተሾመ።

ከዚህም በኋላ እናትና አባቱን ትቶ ወደ አንድ ገዳም ሔዶ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደለ የሸመገሉ መነኰሳትን አገለገለ። የተጋድሎውና የኃይሉ ጽናት ወሬው በተሰማ ጊዜ ስሙ ሉክያኖስ የሚባል መኰንን ወደርሱ ልኮ አስመጥቶ ያለ ውዴታው በግድ የጭፍራ አለቃ አድርጎ ሾመው።

ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እጅግ የሚወደው መልከ መልካም የሆነ ወጣት ብላቴና ነበር ክፉ ጋኔንም ያሰቃየው ነበር። ከዚህ ከአስጨናቂ ደዌ ያድነኝ ዘንድ የወታደሩ አለቃ አጋቢጦስን ፈጥናችሁ አምጡልኝ አለ።

ቅዱሱም በእግዚአብሔር ኃይል አዳነው በመጨረሻም ንጉሡን ከወታደርነት ውስጥ አሰናብተኝ አለውና አሰናበተው አስቀድሞ ወደ ነበረባትም ቦታው ተመለሰ ብዙ ዘመናትም እጅግ እየተጋደለ ኖረ። በዚያችም አገር በኤጲስቆጶስነት ተሹሞ በዙ ተአምራትን እያደረገ የክርስቶስን መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቃቸው።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለም አሜን።

@sebhwo_leamlakne


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን ለከበረ አባት ለንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ወታደር አለቃ ለነበረው ብዙ ተአምራትን ላደረገ፤ ብዙ ሰዎችን ያጠፋውን ታላቅ ከይሲ በጸሎቱ ለገደለው ለኤጲስቆጶስ ቅዱስ አጋቢጦስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ በጋዛ ሰማዕት ከሆኑ ከጢሞቴዎስ፣ ከቆጵሮስ ከአገረ ከሚናስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


@sebhwo_leamlakne


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


አንተ ሰይፍና ጦር ጭሬም ይዘህ ትመጣብኛለህ እኔ ግን ዛሬ በተገዳደርኸው አምላክ ስም በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ስም እመጣብሃለሁ።
1ኛ ሳሙ 17፡45

ዐድዋ - ቅዱስ ጊዮርጊስ ገበዘ ኢትዮጵያ


የካቲት ❷❸

እንኳን ለኢትዮጵያ ገበዝ (ጠባቂ) ለአድዋው አርበኛ፣ ለፍጡነ ረድኤት፣ ለገባሬ ተአምር ሊቀ ሰማዕታት ለቅዱስ ጊዮርጊስ በ1888ዓ.ም በአድዋ ጦርነት ንጉሠ ነገሥትን ምኒልክና ሰራዊቱ ለረዳበት፤ ኢትዮጵያ በሮማውያንን (ጣልያንን) ድል ለተቀዳጀችበት ለ129 (ለአንድ መቶ ሃያ ዘጠነኛው ) ለአድዋ በዓል በሰላም አደረሰን።

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


[ቅዱስ ጊዮርጊስ (ዓመታዊ)
ልበ አምላክ ዳዊት፣ ጠቢቡሰለሞን፣ሰማዕቱ ቅዱስ ቤድራቶስ]

አክብረን እና አስበን እንውላለን።

(#ዕለት:- እሁድ
      #ቀን:- የካቲት ፳፫ ፰፳፻፲፯ ዓ.ም)


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨

ጊዮርጊስ ሆይ፤ ለክብርት ክንድህና ተባባሪዋ ለሆነችው መዳፍህም ሰላም እላለሁ። እንዲሁም ለጣቶችህና እንደ ዕንቍ ፊርጥ ለሚያበሩ የእጆችህም አጽፋር ሰላም እላለሁ።

ተአምር ሠሪው ሰማዕት ሆይ፤ የሰማዕታትና የጭፍሮቻቸው ሁሉ አለቃ ነህና አቤቱ በጥበብህ ከባሕረ ኅዘን አሻግረን በባሕር ላይ መሄድ ያልለመደ የባሕርን ጠባይ ሊያውቅ አይችልምና።

#መልከአ ጊዮርጊስ

@sebhwo_leamlakne

🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨

Показано 20 последних публикаций.