Фильтр публикаций


የኬንያ መንግስት በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ 'ልዩ የፀጥታ ዘመቻ' መጀመሩን አስታወቀ

ዘመቻው የተጀመረው ባለፈው ወር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከዊሊያም ሩቶ ጋር በናይሮቢ ከተነጋገሩ በኋላ ነው።
የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ አገልግሎት በማርሳቢት እና ኢሲዮሎ ግዛቶች በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ 'ልዩ የፀጥታ ዘመቻ' መጀመሩን አስታወቀ።

አገልግሎቱ ትናንት ባወጣው መግለጫ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የሚጠቀምባቸውን መሸሸጊያዎች ለቆ እንዲወጣ ለማድረግ “ኦንዶአ ጃንጊሊ ኦፖሬሽን” የተባለ ዘመቻ ከትናንት ጥር 26 ቀን ጀምሮ እንደሚያካሄድ ገልጿል።

በከፍተኛ ደረጃ የሚካሄደው ዘመቻ ለኬንያ ብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ ስጋት የሚጥሉ እንደ የጦር መሳሪያ፣ የአደንዛዥ ዕፅ እና የሰዎች ዝውውር፣ ህገወጥ የማዕድን ማውጣት ያሉ ህገወጥ ስራዎችን የሚያከናውኑ ወንጀለኞችን ዒላማ ያደረገ ነው ተብሏል።

@sheger_press
@sheger_press


በሳባ ቦሩ ወረዳ በደረሰ በአፈር መደርመስ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ!

በጉጂ ዞን ሳባ ቦሩ ወረዳ በደረሰ የአፈር መደርመስ አደጋ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ላይ የነበሩ 8 ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡አደጋው በትናንናው ዕለት 9 ሰዓት ላይ የደረሰ ሲሆን፤ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ሥራ በተሰማሩ ዜጎች ላይ መድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎችን አስከሬን ከተደረመሰው አፈር ውስጥ የማውጣት ሥራ መከናወኑም ተገልጿል፡፡

Via Ahadu

@sheger_press
@sheger_press


በተለመዶ የጣራና ግድግዳ እየተባለ የሚጠራው የቤትና ቦታ ግብር ያለቅጣትና ወለድ የሚከፈልበት ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ ግብር ከፋዮች ከወዲሁ እንዲከፍሉ ተጠየቀ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተለመዶ የጣራና ግድግዳ እየተባለ የሚጠራ የቤትና ቦታ ግብር የሚከፍሉ ግብር ከፋዮች ግብሩ ያለቅጣትና ወለድ የሚከፈልበት ጊዜ እየተጠናቀቀ መሆኑን በመገንዘብ ከወዲሁ ግብራቸውን እንዲከፍሉ ተጠየቀ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የገቢ አወሳሰንና አሰባሰብ ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኝ ካሳዬ እንደገለፁት በመዲናዋ 429 ሺህ 829 ግብር ከፋዮች የቤትና ቦታ ግብር ክፍያ እንዲፈፅሙ ይጠበቃል፡፡

ይሁንና እስካሁን ባለው ሂደት 228 ሺህ 222 ግብር ከፋዮች የቤትና ቦታ ግብር መፈፀማቸውን በመግለፅ ይህም የዕቅዱ 51 በመቶ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አክለውም የቤትና ቦታ ግብራቸውን ከከፈሉ ግብር ከፋዮችም 2 ነጥብ 24 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡

የቤትና ቦታ ግብር በተለምዶ የአፈር፣ የቤትና ጣሪያ  በሚሉና መሰል ስያሜዎች እስከ የካቲት 30 ድረስ የሚሰበሰብ የግብር አይነት መሆኑ ተገልጿል።

@sheger_press
@sheger_press


#ቴምር ሪልስቴት
😱7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ ለሽያጭ ያወጣናቸው 3 ሳይቶች
🎯1,አያት ሳይታችን
        👉 2መኝታ 87ካሬ
        ሙሉ ክፍያ 4,976,400ብር
         👉 3መኝታ 107ካሬ
        ሙሉ ክፍያ 6.1ሚሊዮንብር
         👉 3 መኝታ 121ካሬ
        ሙሉ ክፍያ 6.9ሚሊዮን ብር
🎯2,ተክለሃይማኖት ሆስፒታል ፊት ለፊት
         👉3 መኝታ 113ካሬ
         10%ቅድመ ክፍያ 1ሚሊዮን ብር
          ሙሉ ክፍያ 10,961,000ብር
         👉3መኝታ 119ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 1.1ሚሊዮን ብር
        ሙሉ ክፍያ 11,543,000ብር
         👉ቀሪውን 90% በ15 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
🎯3,ፒያሳ (ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት) ጀርባ
         👉1 መኝታ 66ካሬ=
         10% ቅድመ ክፍያ 693,000ብር
         ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
         👉2መኝታ 71ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 745,000ብር
        ሙሉ ክፍያ 7,455,000ብር
         👉2መኝታ 93ካሬ=
       10% ቅድመ ክፍያ 1,044,000ብር
       ሙሉ ክፍያ 10,044,000ብር
        👉3መኝታ 130ካሬ
      10%ቅድመ ክፍያ 1,365,000ብር
      ሙሉ ክፍያ 13,650,000ብር
        👉ቀሪውን 90% በ17ዙር ከፍለው         የሚጨርሱት
        👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273


የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም ዛሬ ባደረጉት ንግግር የትራምፕን ውሳኔ ተችተዋል፡፡ ፕሬዘደንት ትራምፕ አሜሪካ ከጤና ድርጅቱ መውጣቷንና የምታደርገውን ድጋፍ ማቆሟን ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡

ዶክተር ቴዎድሮስ በድርጅቱ ስራ አስፈፃሚ ቦርድ ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር ‹‹በዚህ ውሳኔ እጅግ አዝነናል፡፡ አሜሪካ ይህንን መለስ ብላ እንደምታጤነው ተስፋ አለኝ›› ብለዋል፡፡ ትራምፕ በውሳኔያቸው ላይ የአለም ጤና ድርጅት ፈጣን የማሻሻያ እርምጃዎችን እንዳልወሰደ የጠቀሱ ቢሆንም ዶክተር ቴዎድሮስ ግን በዛሬ ንግግራቸው ‹‹የአለም ጤና ድርጅት ባለፉት ሰባት አመታት በታሪክ ውስጥ እጅግ ጥልቅና ሰፊ ማሻሻያዎችን አድርጓል›› ብለዋል፡፡

ትራምፕ ይህ ድርጅት ፍትሀዊ ባልሆነ ሁኔታ ከአሜሪካ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚፈልግ ገልፀው የነበረ ሲሆን ዶክተር ቴዎድሮስ በበኩላቸው በዛሬ ንግግራቸው ሌሎች የገንዘብ ምንጮችንና ለጋሾችን ሲፈልጉ መቆየታቸውን ገልፀዋል፡፡

የኮቪድ ወረርሽኝን በተመለከተም ድርጅቱ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰዱን ጠቅሰው በአሰራራቸው ላይ ፈተናዎችና ድክመቶች መኖራቸውን የገለፁት ዶክተር ቴዎድሮስ ድርጅታቸው ለሁሉም አገራት ያለማዳላት እንደሚሰራም መናገራቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡

Via : ዘ-ሐበሻ

@sheger_press
@sheger_press


#... ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ


በዕለተ ሥቅለተ ክርስቶስ ካሕናት አባቶቻችን የዘጠኝ ሰዓት ስግደት ሲሰገድ “ኦ ዘጥዕመ ሞተ በስጋ” “በስጋው ሞትን የቀመሰ ኢየሱስ ክርስቶስ” እያሉ ልብን በሚያሳዝን ዜማ ያዜማሉ፡፡ በመለኮቱ ሕያው ሲሆን በስጋው ግን ሞትን ቀመሰ፡፡ የአዳምን ሞት በሞቱ ሊሽር መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን በገዛ ፈቃዱ አሳልፎ ሰጠ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች ሲጽፍ  “ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን… አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን” ይላል፡፡


የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ቄርሎስም “ለቤተ ክርስቲያን ስትል በአደባባይ በጥፊ የተመታህ አቤቱ ይህን ማድረግህ እርስዋን በከበረ ደምህ ትቀድሳት ዘንድ ነው፡፡ ለእርስዋ ሲል ታሥሮ መጎተት የቻለ የበደለውም በደል ሳይኖር፣ ርኩስ ምራቅን ሲተፋበት የታገሠ መድኃኔ ዓለም በእንጨት መስቀል ላይ ተሰቀለ” በማለት ገለጸው፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ሰው ሆኖ እንደሚያድነን በመጀመሪያ ለአዳም ቃል ገባለት፡፡ ከዚያም በነቢያት ትንቢት አስነገረ፡፡ በስጋ በተገለጠ ጊዜም የሰቀሉትና የገደሉት አይሁድ ሳይቀሩ እንዲናገሩ አፋቸውን አስከፈታቸው፡፡ አልአዛርን ለአራት ቀናት በመቃብር ከቆየ በኋላ ከሙታን ሲያስነሳው ከአይሁድ ወገን ብዙዎች አመኑ፡፡ አንዳንዶች ግን ወደ ፈሪሳውያን ሄደው ኢየሱስ ያደረገውን ነገሯቸው፡፡


በዮሐንስ 11 እንደተጻፈው ከተአምራቱና ከትምህርቱ የተነሳ ሕዝቡ ሁሉ ትቷቸው እንዳይሔድ የፈሩት አይሁድ ሲማከሩ “በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት የነበረ ቀያፋ የሚሉት ከእነርሱ አንዱ። እናንተ ምንም አታውቁም፤ ሕዝቡም ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ስለ ሕዝቡ ይሞት ዘንድ እንዲሻለን አታስቡም አላቸው። ይህንም የተናገረ ከራሱ አይደለም÷ ነገር ግን በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ነበረና ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ሊሞት እንዳለው ትንቢት ተናገረ፡፡ ስለ ሕዝቡም ሁሉ አይደለም÷ ነገር ግን የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች ደግሞ በአንድነት እንዲሰበስባቸው ነው እንጂ።” ተብሎ ተጽፏልና፡፡ የቀድሞው የግብጽ ኦርቶዶክሳውያን ሊቀ ጳጳስ አቡነ “ሺኖዳ እኛ ወደ እርሱ መውጣት ሲያቅተን መድኃኔ ዓለም ወደኛ ወረደ” በማለት ይገልጹታል፡፡


አምላክነትን ሲሻ የወደቀ የሰው ልጅን የወደደውን አምላክነት ያገኝ ዘንድ የሰውን ባሕርይ ተዋህዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ፡፡ ከኛ በነሳው ስጋም ወደ ሰማይ አረገ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይለናል፡፡ “ሔዋንን ዲያብሎስ አሳታት የሞት ምክንያት የሚሆን ቃልን ወለደች፡፡ ድንግል ማርያም ግን መልአክ በአበሠራት ጊዜ ሁሉን ወደ ዘለዓለም ሕይወት የሚመራ አካላዊ ቃልን በሥጋ ወለደች፡፡” በማዳኑ ስራ ውስጥ የቅድስት ድንግል ማርያም ድርሻ ታላቅ ነው፡፡ “የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ልጁን ላከ፡፡” ሲል ቅዱስ ጳውሎስም ለገላትያ ክርስቲያኖች ጽፏል፡፡ ገላ 4÷4 ስለፍጹም የሰው ልጆች ፍቅር መድኃኔ ዓለም “በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፣ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ” ፊልጵ 2÷8 ተብሎ እንደተጻፈ፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




የትግራይ ህዝብ ቁስሉ ሳይሽር በፍራቻ ውስጥ ገብቶ በጦርነት ወሬ ተከቦ እየኖረ ይገኛል - ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ

ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ በዛሬው ዕለት በተለይ ለትግራይ ህዝብና ለትግራይ ልሂቃን የተፃፈ ደብዳቤ አሰራጭተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስተሩ 'ምክር ለትግራይ ህዝብና ልሂቃን' በሚል ርእስ ባሰራጩት ዘለግ ያለ ፅሑፍ በተለያዩ አጋጣሚዎች እንደገለፅኩት የትግራይ መሬትና ህዝብ የስልጣኔ መሰረት ብሎም የሀገር ዋልታና መከታ ናቸው ከዚህ በላይ ግን ትግራይ በርካታ ሀገራቸውን የሚጠቅሙ ሊቆች፣ የሀይማኖት መሪዎች፣ ፖለቲከኞችና የሀገር ሽማግሌዎች ያፈራ ህዝብ ነው ብለዋል።

ዶ/ር አብይ በመግለጫቸው መጥፎ አጋጣሚ ሆኖ ባለፉት መቶ ዓመታት በተለያዩ አጋጣሚና ምክንያቶች በተለይ ደግሞ ከማእከላዊ መንግስት ጋር በሚፈጠሩ አለመግባባቶች ትግራይ የጦርነት አውድማ፣ የትግራይ ህዝብ ደግሞ የጦርነት ገፈጥ ቀማሽ ሆነዋል ብለዋል።

ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን መነሳት ያለበት ጥያቄ ባለፉት 100 ዓመታት የተደረጉ ጦርነቶች ለትግራይ ህዝብ ምን አይነት ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖምያዊና የፀጥታ ትርፍ አስገኙለት ምንስ አከሰሩት ብለን መጠየቅና ማስላት ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ በዚህ ሰዓት አንድ ልባም የትግራይ ልሂቅ ትግራይና ህዝቧ ከጦርነቶቹ ያገኙት ወይስ ያጦት ይበዛል ብሎ መጠየቅና መልስ ማግኘነት ይገባዋል ብለዋል። አክለውም ሁሉም የተደረጉ ጦርነቶች ብቸኛ የመፍትሄ አማራጮች ነበሩ ወይ ብሎም መጠየቅ ከዚህ በኃላስ ተመሳሳይ ጦርነት ውስጥ ላለመግባት ምን መደረግ አለበት የሚል ጥያቄ ተነስቶ ምላሽ መፈለግ ይገባል ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለው አሳዛኙ ነገር የትግራይ ህዝብ የትላንት ቁስሉ ሳይሽር አሁንም ሰላም አግኝቶ ሰርቶ እንዳይኖርና እንዳይለማ በፍራቻ ውስጥ ገብቶ በጦርነት ወሬ ተከቦ እየኖረ ይገኛል ያሉ ሲሆን ይህንን አይነቱ አደጋ እንዴት ማስቀረት እንደሚቻል ላይ በተረጋጋ መንፈስ መመካከር የሚገባው ጉዳይ ስለመሆኑ ግልፅ ነው ብለዋል።

ስለሆነም በትግራይ ፖለቲካ፣ ንግድ፣ ፀጥታ፣ አካዳሚና ሚድያ ብሎም በሌሎች ዘርፎች የምትሰሩ የትግራይ ልሂቃንና መላው የትግራይ ህዝብ የትግራይ ህዝብ እስካሁን የከፈለው ዋጋ ይበቃል፣ ከጦርነት የሚገኝ ትርፍ የለም በማለት በመጀመርያ ደረጃ በውስጣቹ ያለውን ክፍፍል ተነጋግራቹ ጉዳያቹ በሰላምና የትግራይን ህዝብ አንድነት በሚያረጋግጥ መንገድ እንድትፈቱ እጠይቃለው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ጥሪ አቅርበዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ከፌደራል መንግስትም ሆነ ከሌሎች ሀይሎች ጋር ያላቹን ልዩነት በሀገሪቱ ህገ መንግስትና በዴሞክራስያዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ እንደትሆኑ መልእክቴን አስታልፋለው ሲሉ አክለዋል። ጠቅላይ ሚኒስተሩ በመጨረሻም ለትግራይ ህዝብ ሰላም የተመኙ ሲሆን ቅራኔና ጦርነት ይበቃናል ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ትርጉም በሚሊዮን ሙሴ

@sheger_press
@sheger_press


ተፈታለች‼️

ገጣሚ ምሥራቅ ተረፈ ከ4 ቀናት እስር በኋላ ዛሬ፣ ሰኞ ጥር 26 ቀን 2017ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ተፈትታለቾ።

@sheger_press
@sheger_press


ፓርቲው የጣሪያ ግድግዳ/የንብረት ግብር መመሪያ እንዲቆም የመሰረተው ክስ በፍርድ ቤቱ ተቀባይነት ማግኘቱን አስታወቀ

እናት ፓርቲ የጣሪያ ግድግዳ/የንብረት ግብር መመሪያ እንዲቆም የአዲስ አበባ ከተማ ፋይናንስ ቢሮ ላይ ሐምሌ 17 ቀን 2015 የመሰረተው ክስ በፍርድ ቤቱ ተቀባይነት ማግኘቱን አስታወቀ።

ፓርቲው ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ በአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ አማካይነት ሚያዚያ 3 ቀን 2015 የተላለፈው የንብረት ግብር መመሪያ “ሕግን ባልተከተለ መንገድና የከተማ አስተዳደሩ ባልተሰጠው ስልጣን” የወጣ መመሪያ ነው ሲል መመሪያው እንዲሻር ክስ ማቅረቡን ገልጿል።

ተጠሪ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እናት ፓርቲ ለመሠረተው ክስ 1ኛ ፓርቲው የከስ ምክንያት የለውም፣ 2ኛ የቀረበው ክስ ፓርቲው መብትና ጥቅማቸው አረጋግጠው ያቀረቡት ክስ አይደለም፣ 3ኛ ክሱ በይርጋ የታገደ ነው በማለት ወደ ፍሬ ነገር ክርክር ሳይገባ ውድቅ ተደርጎ መዝገቡ ሊዘጋ ይገባል በማለት ሶስት የመጀመሪያ ደረጃ መቃዎሚያ በማቅረብ ተከራክረዋል።

ፍርድ ቤቱ ጥር 9 ቀን 2017 ዓ.ም. ባስቻለው ችሎት መመሪያ ተፈጻሚነት ሊኖረው አይገባም ተብሎ እንዲሻር በሙሉ ድምጽ ውሳኔ መስጠቱን እናት ፓርቲ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጿል።

ውሳኔው በተሰጠ የሰዓታት ልዩነት ተጠሪ የከተማ አስተዳደሩ ፋይናንስ ቢሮ በውሳኔው ለሚዲያ መግለጫ እንዳይሰጥ አቤቱታ በማቅረቡ ለ15 ቀን አፈፃፀሙ እንዲሁም ለሚዲያ መግለጫ እንዳይሰጥ የዕግድ ትዕዛዝ ተሰጥቷል ብሏል፡፡

ይሁንና እስከ ዛሬ ጥር 26 ቀን ድረስ ቢሮው ያቀረበዉ ይግባኝ ባለመኖሩና የእግድ ትእዛዙ የጊዜ ገደብም ያበቃ በመሆኑ ፓርቲው የፍርድ አፈፃፀም ስልጣን ላለዉ የአፈፃፀም ፍርድ ቤት ፋይል ለመክፈት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡

የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንትም ለ15 ቀናት የሰጡት የአፈፃፀምና ለሚዲያ መግለጫ እንዳይሰጥ የእግድ ትዕዛዝ ቀነ ገደብ ያበቃ በመሆኑ ይህንን ጋዜጣዊ መግለጫ በዛሬው ዕለት ልንሰጥ ችለናል ብሏል፡፡

እናት ፓርቲ በመግለጫው በቀጣይም "በህዝቡ ላይ ከሕግ አግባብ ውጪ የሚጫኑበትን ሸክሞች ወደ ፍርድ ቤት እያቀረበና በሕግ እየሞገተ የሚያስወግድ መሆኑንና ለዚህም በቁርጠኝነት እንደሚሰራ” ገልጿል ሲል አዲስ ስታንዳርድ ዘገባ ተመልክተናል።

@sheger_press
@sheger_press


45 የብልጽግና ሥራ አስፈጻሚ አባላት
========
#ኦሮሚያ_ክልል

1. ዶር ዐቢይ አህመድ
2. ኦቦ ሽመልስ አብዲሳ
3. ኦቦ አወሉ አብዲ
4. ኦቦ ፍቃዱ ተሰማ
5. አዴ አዳነች አቤቤ
6. አዴ ጫልቱ ሳኒ
7. ኦቦ ሳዳት ነሻ
8. ኦቦ ከፍያለው ተፈራ
9. ዶር ተሾመ አዱኛ
10. ዶር እዮብ ተካልኝ

#አማራ_ክልል

11. አቶ ተመስገን ጥሩነህ
12. አቶ መላኩ አለበል
13. ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ
14. አቶ አረጋ ከበደ
15. አቶ ይርጋ ሲሳይ
16. ዶክተር አብዱ ሁሴን
17. አቶ ጃንጥራር አባይ
18. ዶክተር ሙሉነሽ ደሴ

#ሶማሌ_ክልል

19. አቶ አደም ፋራህ
20. አቶ ሙስጠፌ መሃመድ
21. አቶ አህመድ ሺዴ
22. ወ/ሮ ሃሊማ ዋሽራፍ

#ትግራይ_ክልል

23. ዶክተር አብርሃም በላይ
24. አቶ ታዜር ገብረ እግዚአብሔር

#ሀረሪ_ክልል

25. አቶ ኦርዲን በድሪ
26. ወ/ሮ አሚና አብዱልከሪም

#አፋር_ክልል

27. ሀጂ አወል አርባ
28. መሀመድ ሁሴን አሊሳ
29. መሀመድ አህመድ አሊ

#ደቡብ_ምዕራብ_ኢትዮጵያ_ክልል

30. ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ
31. አቶ ፍቅሬ አማን

#ሲዳማ_ክልል

32. አቶ ደስታ ሌዳሞ
33. አቶ አብርሃም ማርሻሎ
34. ዶ/ር ፍፁም አሰፋ

#ጋምቤላ_ክልል

35. ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ
36. ዶ/ር ካትሏክ ሩን ናቸው።

#ቤኒሻንጉል_ጉሙዝ_ክልል

37. አቶ አሻድሊ ሀሰን
38. አቶ ጌታሁን አብዲሳ

#ማዕከላዊ_ኢትዮጵያ_ክልል

39. አቶ እንዳሻው ጣሰው
40. ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል
41. ዶ/ር ዴላሞ ዶቶሬ

#ደቡብ_ኢትዮጵያ_ክልል

42. አቶ ጥላሁን ከበደ
43. ወ/ሮ ⁠ሸዊት ሻንካ
44. ዶ/ር ተስፋዬ ቤልጅጌ
45. ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ

@sheger_press
@sheger_press


መረጃ‼️

የጅቡቲ መከላከያ ሚንስቴር፣ "አሸባሪ" ባለው ቡድን ላይ ባለፈው ሳምንት የድሮን ጥቃት የፈጸመው በጅቡቲ ውስጥ እንጂ በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ እንዳልኾነ ማስተባበሉን የፈረንሳዩ ዜና ወኪል ዘግቧል።

መከላከያ ሚንስቴሩ፣ በድሮን ጥቃቱ ስምንት የቡድኑ አባላት እንደተገደሉ ማስታወቁን ዘገባው ጠቅሷል።

በጥቃቱ ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ሰላማዊ ሰዎች ጭምር እንደተገደሉ የገለጠው ሚንስቴሩ፣ በክስተቱ ዙሪያ ምርመራ መጀመሩን ማስታወቁም ተገልጧል።

የድሮን ጥቃቱ የተፈጸመው፣ ከኢትዮጵያ ድንበር ስድስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ አዶርታ በተባለ አካባቢ ነበር ተብሏል።

የፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌህ አማካሪ፣ የጥቃቱ ዒላማ የጅቡቲ አፋሮች አማጺ ቡድን መኾኑን ማረጋገጣቸውንም የዜና ምንጩ ዘገባ ያመለክታል።

@sheger_press
@sheger_press


#ባለጸጋ ያደረጉን ድሆች፣ የደስታችን ምንጭ የሆኑ ሀዘንተኞች 

በዓለት መሀል የሚገኝ በመነኮሳት ፀሎት ብቻ እየተቆረጠ ለፀበልተኞች የሚሰጥ የማር እምነት መገኛ፣ ድውያንን ከመፈወስ አልፎ ሙት ያስነሳ ድንቅ የሚያደርግ ጸበል ያለበት፤ ከዘጠና በላይ መናንያን ዓለምን ንቀው የተጠለሉበት ነገር ግን ስለ ዓለምና ስለ ሀገራችን ሌት ተቀን የሚጸልዩበት ቅዱስ ስፍራ፤ ሙትአንሳ  ማር  ቅዱስ ሚካኤል አድነት  ገዳም።

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ በለሳ ወረዳ የሚገኘው ይህ ገዳም ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በ2ኛ ቆሮንቶስ 6÷10 “ኀዘንተኞች ስንሆን ዘወትር ደስ ይለናል፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው።” ያለው ሕያው ቃል በዘመናችን በተግባር የሚታይበት ቦታ ነው፡፡

ምንም እንኳን መነኮሳቱና ገዳማውያኑ አሁንም ድረስ መንፈሳዊ ግዴታቸውን እየተወጡ በጽናት ቢቆዩም ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች እየተፈታተኗቸው ነው፡፡ ይህ ድንቅ ተአምር ያለበት ታሪካዊ የአንድነት ገዳም በአንድ በኩል አከባቢው ተፈጥሮ ፊቷን አዙራበት በድርቅ ምክንያት ምንም ዓይነት አዝርእት ያልበቀለበት በመሆኑ ጭው ያለ ምድረ በዳ ሆናል። ወዲህ ደግሞ በአካባቢው ያለው ጦርነት በየጊዜው ይጎበኟቸው የነበሩ ፀበልተኞች ፈጽመው እንዲሸሹና ገዳማውያኑ ያለምንም ጠያቂ በትልቅ ችግርና ፈተና ውስጥ እንዲገኙ አድርጓቸዋል፡፡

ረሀብ፣ እርዛት፣ የማረፊያ ቦታ ችግር እጅግ ቢፈታተናቸውም፣ በአንድ በዓት ለሶስት ለአራት ለማደር ቢገደዱም ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው የራሳቸውን ስጋዊ መከራ ችለው፤ ሌት ተቀን ስለ ሀገር ደህንነት፣ ስለ አሐቲ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ሰው ልጅ ሰላምና ጤንነት ሳያቋርጡ በጽናት የሚፀልዩ ናቸው።

ዙሪያችንን የከበበንና በእሳት ውስጥ ያሳለፈን መከራ ያልጣለን፣ በተገፋነው እጥፍ ጸንተን የቆምነው በእነዚህና በሌሎችም ገዳማውያን አባቶቻችን የማያቋርጥ የሕብረት ጸሎት ነው፡፡ የገዳማት መፈታት የመነኮሳት ከበዓታቸው መውጣት ይህን የሕብረት ጸሎት ያስተጓጉለዋል፡፡

ድውያነ ስጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የሚፈውሰውን ስፍራና ገዳማውያኑን ዛሬ ካልታደግን ዳሩ ሲወረር መሀሉ ዳር ይሆናል የሚለው ይፈጸምብናል፡፡ የተወረወረብን ጦር፣ የተመከረብን ክፉ ምክር በግላጭ ያገኙናል፡፡ በግንብ የታጠረ ቤታችን አቅበን የያዝነው ንብረታችን አይታደጉንም፡፡

ከፀሎትና ከድካም መልስ የሚጠለሉበትን፣ ከፆም መልስ የሚቀምሱትን ነገር ልናቀርብላቸው ይገባል። ለሰማያዊ ህይወታችን ስንቅ ይሆነናል ከመነኮሳቱ ፀሎት የበረከት ተካፋይ እንሆናለን፥ ለህሊናችንም እረፍት እናገኝበታለን።
 
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




ጅቡቲ አመነች‼️

ከትናንት በስተያ በአፋር ክልል የተፈፀመውን የድሮን ጥቃት አስመልክቶ የጅቡቲ መከላከያ ሚኒስትር መግለጫ ያወጣ ሲሆን የድሮን ጥቃቱን  መፈፀሙን አምኖ 8 ሰው መግደሉን ገልጿል።
የድሮን ጥቃት የተፈፀመው በራሳችን ግዛት ውስጥ ነው ያለ ሲሆን አሸባሪዎችን ለመምታት ነው ብሏል። ለተጎጂዎች እገዛ እናደርጋለን ብሏል።

የጅቡቲ መንግሥት መከላከያ ሚኒስቴር ይሄን ማስተባበያ ቢሰጥም የድሮን ጥቃቱ የተፈፀመው በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ በአፋር ክልል ኢልዳዓር ወረዳ ሲያሩ ቀበሌ ሲሆን የድሮን ጥቃት የተፈፀመው ሁለት ጊዜ ነው።

በዚህ ጥቃት በቀብር ስነስርዓት ላይ የነበሩ ሰዎችን ጨምሮ አጠቃላይ 14 ሰዎች መሞታቸውን እንዲሁም ሶስት ሰዎች መቁሰላቸውን የአፋር የመረጃ ምንጮች ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በዚህ ዙሪያ ላይ እስካሁን ያለው ነገር የለም።

@sheger_press
@sheger_press


በአዲስአበባ ተገቢ ባልሆነ ቦታ የሚደረጉ ሐይማኖታዊ ስብከቶችን ለማስቀረት መመሪያ እየተዘጋጀ ነዉ ተባለ

በየመንገዱ የሚደረጉ ሐይማኖታዊ ስብከቶችን መቀነስ ተችሏልም ተብሏል

በአዲስ አበባ ተገቢ ባልሆኑ ቦታዎች ላይ የሚደረጉ ሐይማኖታዊ ስብከቶችን መቀነስ እንደተቻለ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ገለጸ።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።

የቢሮ አማካሪ አቶ ገብሬ ዳኘው በወቅቱ እንደተናገሩት በሜክሲኮና በመገናኛ አደባባዮች የሚደረጉ ስብከቶች ላይ በተከታታይ የግንዛቤ በመፍጠር እንዲሁም መታረም የሚገባቸውን በማረም የችግሩን መጠን ከነበረበት መቀነስ ተችሏል።

የአደባባይ ስብከቶችን በሚገባቸው ሐይማኖታዊ ቦታዎች እንዲደረጉ ከሐይማኖት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ሐይማኖታዊ ነጻነትን በማይጋፋ እና ህገ ወጥነትን መከላከል በሚያስችል መልኩ በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

እንደሀገር ተገቢ ባልሆነ ቦታ ላይ የሚደረጉ ሐይማኖታዊ ስብከቶችን ለማስተካከል እና ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑንም ገልጸዋል።

በመመሪያ ማውጣቱ ሂደት ቢሮውን ጨምሮ የሐይማኖት፣ የተለያዩ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት እንደሚገኙበት አስረድተዋል።
#EPA

@sheger_press
@sheger_press


ተፈቷል‼️

ሰመረ ካሳዬ (ሰመረ ባርያው) በዛሬው እለት መፈታቱን መሠረት ሚድያ አረጋግጧል

@sheger_press


የባንኮች ብድር ጉዳይ

ባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው የብድር ጣሪያ መስከረም ላይ ይነሳል

ካለፈው ነሀሴ 2015 ዓ.ም. አንስቶ ተጥሎ የነበረው ባንኮች መስጠት የሚችሉት አዲስ ብድር ገደብ ሙሉ ለሙሉ ሊነሳ መሆኑን ተሰምቷል።

የአለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅትን (IMF) መረጃ እንደሚጠቁመው ባንኮች የሚችሉት የብድር መጠን ላይ ተጥሎ የቆየው ጣሪያ በቀጣይ መስከረም ይነሳል።

በነሀሴ 2015ዓም ወደ ስራ የገባው የብድር ጣሪያ ባንኮች አመታዊ የብድር እድገታቸው ከቀደመው የብድር ክምችት  መጠን በ14 በመቶ ብቻ እንዲያድግ የሚያደርግ ነው።

ባለፈው ወር መጨረሻ እድገቱ ወደ 18 በመቶ እንዲሆን በብሄራዊ ባንክ ተወስኖ ነበር። ሆኖም ውሳኔው በባንኮች በአወንታዊ የታየ አልነበረም።

@sheger_press
@sheger_press


#ትጥቁንና ልብሱን አውጥቶ በንጉሱ ፊት ወረወረው

ሮማዊ ነው፤ ቤተሰቦቹ አረማውያን ሲሆኑ ከአምልኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር የተመለሱ ናቸው፡፡ አባቱ ፊታቸው የውሻ የሆነ፣ የአውሬነት ጸባይ ያላቸው በእግዚአብሔር ኃይል የሚታዘዙት ሁለት አገልጋዮች ነበሩት፡፡ በመርዶሳውያን ሀገር ተማርኮ የሔደው አባቱ ጸጋ እግዚአብሔር በዝቶለት በዚያ ሹመት አጊቷል፡፡ አባትና እናቱ ሲያርፉም ልጃቸው ስልጣኑን ተረክቧል፡፡ በክርስትናው ዓለም በዓለም አቀፍ ደረጃ ታሪካቸው ከሚነገርላቸው ሰማዕታት አንዱ በሀገራችን በኢትዮጵያም በአማላጅነቱ የሚታወቀው ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ፡፡ መርቆሬዎስ ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው። በሁለተኛ ትርጉሙ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው። በሀገራችን በኢትዮጵያም በበርካቶች ዘንድ በፈጣን ተራዲኢነቱ ይታወቃል፡፡

ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስ፣ ቅዱስ መርቆሬዎስ የአባቱን ስልጣን ወርሶ በንጉስ ዳኪዮስ ስር በመርዶሳውያን አገር ላይ ተሾመ፡፡ መርቆሬዎስ መኰንንነት በተሾመም ጊዜ ገጸ ከለባቱ አብሮት ነበር፤ ለመዋጋትም በወጣ ጊዜ የቀድሞው የአራዊት የሆነ ተፈጥሮውን እግዚአብሔር ይመልስለት ስለነበር ማንም አይቋቋመውም ነበር፡፡ ለቅዱስ መርቆሬዎስ ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠውና ዜናው በሁሉም ሀገሮች ተሰማ፤ በሮሜ ሀገር ጣዖትን የሚያመልከው ዳኬዎስ የተባለውም ንጉሥ የበርበር ሰዎች ጋር ጦርነት ሊገጥም በወጣ ጊዜ እጅግ ሲበዙበት ፈራ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስ ግን በጦሩ መካከል የተሳለ ሰይፍ የያዘ የእግዚአብሔርን መልአክ ስላየ ንጉሡን “እግዚአብሔር ያጠፋቸዋልና አትፍራ” አለው፤ ከዚያም ሰይፉን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ሰጠውና “ጦርነቱን ድል ባደረግህ ጊዜ እግዚአብሔርን አስበው” አለው፡፡

ጦርነቱ በንጉሱ ዳኪዮስ ወገን አሸናፊነት ተጠናቀቀ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስ በድሉ ውስጥ ትልቅ ድርሻ ነበረው፡፡ ድል አድርጎ ሲጨርስም መልአኩ ድጋሚ ተገልጦለት “ለምን የፈጣሪህን ስም መጥራት ረሳህ” አለው፡፡

ንጉሥ ዳኬዎስ ግን ከጦርነቱም በኋላ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን አደረገ፡፡ በዚህ ያዘነው ቅዱስ መርቆሬዎስ ግን በበዓሉ ላይ አልተገኘም፡፡ ንጉሡ ይህንን ሲያውቅ መልእክተኞችን ልኮ አስመጣውና “ከእኔ ጋር ለምን አታጥንም?” አለው፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስ ትጥቁንና ልብሱን አውልቆ ከወረወረለት በኋላ “ክብር ይግባውና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጽሞ አልክደውም፤ ለረከሱ ጣዖቶችህም አልሰግድም” አለው፡፡ ከዚህ በኋላ ነበር ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ በክርስትናው የተፈተነው፡፡

ንጉሡ አብሮት በጣኦት አምልኮው ስላልተሳተፈ በልዩ ልዩ ሥቃዮችም እጅግ አሠቃየው፡፡ ንጉሡም ስለ መርቆሬዎስ ብለው የሀገሩ ሰዎች እንዳይነሡበት ፈርቶ በብረት ችንካር ቸንክሮ የቀጵዶቅያና የእስያ ክፍል ወደ ሆነች ወደ ቂሳርያ ከደብዳቤ ጋር ላከው፡፡

በዚያም እጅግ ካሠቃዩት በኋላ በንጉሥ ዳኬዎስ ትዕዛዝ አንገቱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ተጋድሎውን ፈጸመ፤ የሕይወትንም አክሊል ተቀዳጀ፤ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነጹለት፡፡

እግዚአብሔርም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም አደረገ፡፡ በየወሩ በ25 ቀንም መታሰቢያው ነው፡፡ ገዳማውያን አባቶችና እናቶች ዓለም የምትሰጣቸውን ምቾት ትተው ክርስቶስን ብለው ወጥተዋል፡፡

ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡      


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

Показано 19 последних публикаций.