Фильтр публикаций


የሱዳን ጦርነት በዋና ከተማዋ ካርቱም ያለውን ሁኔታ አስከፊ አድርጎታል ተባለ

ሁለት ዓመታትን ያስቆጠረው የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት በዋና ከተማዋ ካርቱም ያለውን ሁኔታ አስከፊ እንዳደረገው ተገልጿል፡፡

ዩኒሴፍ፤ ሰብዓዊ እርዳታዎች በመገደባቸው እና ተደራሽ ባለመሆናቸው ሁኔታው አሳሳቢ እንደሆነ ገልፆ ፍላጎቶች ብዙ ቢሆኑም አቅርቦቱ ግን በቂ አይደለም ብሏል፡፡

በሱዳን ጦር እና በፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ መካከል በተቀሰቀሰው ጦርነት ምንም እንኳን ቁጥሩን ለመገመት አዳጋች ቢሆንም ከ20ሺ በላይ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ ተነግሯል፡፡

የሱዳን ጦር ካርቱምን እንደተቆጣጠረ ቢነገርም የአከባቢውን ሰላም ወደ ነበረበት መመለስ አስቸጋሪ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ በተቀሰቀሰው ግጭት ብቻ ከ300 በላይ ንፁሃን ዜጎች መሞታቸውን አስታውቋል፡፡

የዓለም የምግብ ፕሮግራም እንደገለጸው፣ ከሱዳን ሕዝብ ግማሽ ያህሉ፣ ወደ 25 ሚሊዮን የሚጠጋው በአሁኑ ጊዜ ለከፍተኛ ረሃብ ተጋልጧል፡፡

እንደ ቻድ እና ግብፅ ባሉ አጎራባች ሀገራት ጥገኝነት በመጠየቅም ከሦስት ሚሊዮን በላይ ዜጎች ሀገሪቱን ለቀው ለመሰደድ ተገደዋል ተብሏል።

አፍሪካን ኒውስ

@Sheger_Press
@Sheger_Press


#የ“ሲኒሃ ድርየም” ሸንጎው ምክር

ዕለተ ረቡዕ አይሁድ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ይሙት ብለው የወሰኑበት ዕለት ነው። ዕለቱ “እለተ ምክር”፣ “እለተ መዓዛ” እና “እለተ አንብዕ” ይባላል፡፡ “እለተ ምክረ አይሁድ” ነው፡፡ ይህ ከሰኞው ምክር፣ ከማክሰኞውስ በምን ይለያል ቢሉ የአይሁድ አለቆች፣ ጸሐፍትና ፈሪሳውያን የተስማሙና እልባት ያገኙለት ዛሬ ነበር፡፡ ዛሬም ይሙት ብለው ወሰኑ፡፡ እዚህ መላ ላይ ለመድረስ ሦስት ቀን ፈጅቶባቸዋል፡፡ ምክንያቱም በመሃላቸው “ይህ ሰው ንጹሕ ነው፤ ሞት አይገባውም” የሚሉ ርቱዓን ነበሩ የሚበዙቱ ግን ይህን በክፋታቸው ብዛት አቸንፈው መገደሉ ላይ ተስማሙ፡፡ ሌላኛው ጭንቀታቸው “እንግደልስ ብንል ምን ምስክር አለን፤ ሰውየው ንጹሕ ነው፤ ተፈትኖም ሐሰት አልተገኘበትም፤ የሚሉቱ ነበሩ፡፡ ይህንንም የሐሰት እማኞችን ለማዘጋጀት ከወሰኑ በኋላ ወዲያውኑ ለዚህ ጉዳይ ይጠቅሙናል ያሏቸውን በር ማንኳኳት ጀምረዋል፡፡

ነገር ግን በዚህች እለት ሞቱ ላይ ቢስማሙም እንዴት እንደሚይዙት ቸግሯቸው ነበር እንጂ መላ አላገኙለትም፡፡ ወቅቱ “በዓለ ፋሲካ” ነበርና በበዓል ይህን ደባ እንዴት እንተገብራለን፤ ሕዝቡም እንዳይታወክ ብለው ሰግተው ነበር፡፡ በየአገሩ ተበትነው የሚገኙ በርካታ ቤተ እስራኤል በዓለ ስርየት፣ በዓለ ሰዊትን መጸለትን፣ ፋሲካን፣ በዓለ ሀምሳ ወይም በዓለ ጰንጤ ቆስጤን ከያሉበት ሀገር ወደ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ መጥተው ለሐምሳ ቀናት ሊያከብሩ የሚሰባሰቡበትና የሚሳለሙበት ሕግ ስላላቸው ከተማ የሚከርሙ ነበሩ፡፡ እኒህም ሁሉ በጌትነቱ እንዳመኑበት በሆሣዕና እለት በክብር ሲቀበሉት ወደቤተ መቅደስም ሲሸኙት አይተው ፈርተው ነበርና ስለዚህ እንዴት እንደሚይዙና እንደሚገድሉት ተጨነቁ፡፡

የካህናት አለቆችና የሕዝብ ሹማምት በጌታችን ላይ ይሙት በቃ ለመወሰን የሰበሰቡት ሸንጐ “ሲኒሃ ድርየም” ይባላል፡፡ በዚህ ሸንጐ ላይ በአብዛኛው የተሰየሙት ሰዱቃውያን ሲኾኑ ሌሎቹ ደግሞ ጸሐፍት ፈሪሳውያን ነበሩ፡፡ ሸንጐው በአጠቃላይ ሰባ ሁለት አባላት የነበሩት ሲኾን የሚመራውም በሊቀ ካህናቱ በቀያፋ ነበር፡፡ በዕለቱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዴት ይዘው እንደሚገድሉት አይሁድ በዚህ ሸንጎ መክረዋል፡፡ ከዳተኛው ይሁዳም ጸሐፍት ፈሪሳውያንና የካህናት አለቆች በጌታችን ላይ የነበራቸውን ጥላቻ ያውቅ ስለነበር “ምን ልትሰጡኝ ትወዳላችሁ? እኔም አሳልፌ እሰጣችኋለሁ፤” በማለት ጌታችንን አሳልፎ ሊሰጣቸው እንደሚችል ተስማቷል፡፡

ጌታችን ያስተምር በነበረበት ወቅት የአስቆሮቱ ይሁዳ ከምእመናን የሚገባውን ገንዘብ ሰብሳቢ ነበር፡፡ ከሚሰበሰበው ሙዳየ ምጽዋት ለግል ጥቅሙ እየቀረጠ የማስቀረት የእጅ አመል ነበረበት፡፡ ይሁዳ ፍቅረ ንዋይ እንደሚያጠቃው ድብቅ አመሉ ጎልቶ የወጣው ጌታችን በለምጻሙ በስምዖን ቤት ሳለ ማርያም እንተ እፍረት ባለሽቱዋ ማርያም ዋጋው ውድ የኾነ ሽቱ በቀባችው ጊዜ ይሁዳ “ይህ ሽቱ ተሽጦ ለድሆች ቢሰጥ መልካም ነበር፤” በማለት ያቀረበው አሳብ፣ ሽቱ ሲሸጥ የሚያገኘው ጥቅም ስላለ ነው፡፡ ሽቶው በጌታችን እግር ሥር ከፈሰሰ ለእርሱ የሚተርፈው የለም፡፡ ይሁዳ ተቆርቋሪ መስሎ ያቀረበው አሳብ ተቀባይነት በማጣቱም ማኩረፊያ ያገኘ መስሎት በቀጥታ ከካህናት አለቆች ዘንድ ሔዶ ጌታችንን በሠላሳ ብር ለመሸጥ ተዋዋለ፡፡ ጌታችን ሁሉን ቻይ እንደሆነ ከዋለበት ውሎ ካደረበት አደሮ ደቀ መዝሙሩ ሆኖ ቢመለከትም፣ ቢጠይቀው ሊሰጠው በሚችለው ሠላሳ ዲናር ሸጠው፡፡ ይህም ልቡ ከዳተኛ ስለሆነ ነው፡፡
    

በዚህ የጾም ወቅት በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን እየረዳንና በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


የኢትዮጵያ መምህራን የኅብረት ሥራ ባንክ በቀጣይ ዓመት ሥራ ሊጀመር ይችላል ተባለ

ባንኩ በመምህራን ላይ እየጨመረ ያለውን የገንዘብ ጫና ለማቃለል እና ተመጣጣኝ የብድር እና የቤት ድጋፍ ለመስጠት ያለመ ልዩ የፋይናንስ ተቋም መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለፓርላማ አባላት ተናግረዋል።

🗣 "የመምህራን የኅብረት ሥራ ባንኩ የአስተማሪዎቻችንን ኑሮ ለማሻሻል ትልቅ እርምጃ ይሆናል፡፡ የባንኩ መጀመር መምህራን የራሳቸውን ቤት ለመገንባት የሚያስችል መሬት መመደቡ ላይ የተመሠረተ ነው” ብለዋል።

መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ካደረገ ባንኩ በሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ ሥራ ሊጀምር እንደሚችል ጠቁመዋል።

@Sheger_Press
@Sheger_Press


ኤ.ቲ.ኤም ማሽን ያለባቸው ቦታዎች ላይ በመገኘት ገንዘብ ሊያወጡ የሚመጡ ግለሰቦችን የሚረዳ መስሎ ሚስጥር ቁጥራቸውን በማየትና ሌላ ካርድ በመቀየር የማጭበርበር ወንጀል ይፈፅም የነበረን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 08 ቀን 2017 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ተጠርጣሪው አለማየሁ የስጋት ይባላል፡፡ የወንጀል ድርጊቱን የሚፈፅመው ኤ.ቲ. ኤም ያለባቸው ቦታዎች በመገኘት ገንዘብ ሊያወጡ የሚመጡ በተለይም ደጋግመው የሚሞክሩ ሰዎችን ሲያይ የካርዳቸውን የሚስጥር ቁጥር በማየትና የሚረዳ በመምሰል ካርዳቸውን ወዲያው በሌላ በመቀየር እና ከአካባቢው በፍጥነት በመሰወር ከሌላ ማሽን ገንዘባቸውን አውጥቶ የሚሰወር ነው፡፡

ግለሰቡ በተመሳሳይ የወንጀል አፈፃፀም ሚያዚያ 7 ቀን 2017 ዓ/ም በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው ፈረንሳይ ማዞሪያ አካባቢ ከሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቀኑ7:30 ሠዓት በመገኘት አንዲት ግለሰብ ገንዘብ ለማውጣት ሲሞክሩ ከኋላቸው ሆኖ የካርዱን ሚስጥር ቁጥር ካየ በኋላ የሚረዳ መስሎ በመቅረብ ማሽኑ እምቢ ብሏል እስኪ በሌላ ይሞክሩ በማለት ካርዳቸውን ይዞ ይሄዳል፡፡ ግለሰቧም እውነት መስሏቸው ካርዱን ተቀብለው ደጋግመው ሲሞክሩ የተመለከታቸው የባንኩ ማናጀር ካርዳቸውን ተቀብሎ ሲያረጋግጥ የግል ተበዳይ አለመሆኑን በማወቁ ተከሳሹ ከአካባቢው ሳይርቅ በፖሊስ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል።

ተከሳሹ ኪሱ ሲፈተሽም 4 የንግድ ባንክና 3 የአቢሲኒያ ባንኮች ኤ.ቲ.ኤም ካርዶች ከኪሱ የተገኘ ሲሆን ተጠርጣሪው ከ6 ወራት በፊት መርካቶ አካባቢ ከሚገኝ አንድ ባንክ በተመሳሳይ የማጭበርበር ወንጀል 7ሺህ ብር እንዳወጣም በምርመራ የተረጋገጠ ሲሆን ምርመራውም ቀጥሏል።

በተለያዩ ቦታዎች ተመሳሳይ ወንጀል የተፈፀመባቸው ግለሰቦች ካሉ የካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመቅረብ ለፖሊስ ተጨማሪ መረጃ እንዲሰጡ እያሳሰበ ህብረተሰቡ ገንዘብ ለማውጣት በተለይም በባንኮችና የገንዘብ ማውጫ ማሽኖች በሚገኙባቸው ቦታዎች ሲገኝ የሚረዱ ወይም የባንክ ሠራተኛ በመምሰል የሰዎችን የኤ.ቲ.ኤም ካርድ የሚስጥር ቁጥራቸውን በማየት የማጭበርበር ወንጀል በሚፈጽሙ ግለሰቦች ሠለባ እንዳይሆን ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግና አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙም በአቅራቢያ ለሚገኝ ፖሊስ መረጃ በመስጠት ተባባሪ መሆን እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።

@Sheger_Press
@Sheger_Press




የአካባቢ ስብሰባ አልተሰበሰባችሁም በማለት የጸጉር ቤት ባለቤትን ከነደንበኛው የገደለው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

በአርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ አለጋ ዱሬታ ቀበሌ አዲሱ ገበያ ሐሠን ኑር የተባለ   25 ዓመት ወጣት የወንዶች ፀጉር ቤት ከፍቶ በመስራት ይተዳደር እንደነበረ ተገልጿል ።ታሕሣስ  14 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ አራት ሠዓት ላይ የነዋሪዎች ስብሠባ ነበር፡፡ በርካቶች ስራቸውን አቁመው ስብሰባው ወደተዘጋጀበት ስፍራ እንዲሔዱ የቀበሌው ፅ/ቤት ሠራተኞች በየአቅጣጫው እየቀሠቀሱ እንደነበር  የአርሲ ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የወንጀል ምርመራ የተለያዪ ወንጀሎች ምርመራ ንኡስ ክፍል ሃላፊ ኢንስፔክተር አሸናፊ እንዳለ በተለይ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።
   
በዚሕ ግዜ በሐሠን ኑር ፀጉር ቤት  የ 35  ዓመት እና የሑለት ልጆች አባት የሆነ ደንበኛ ፀጉሩን እየተስተካከለ ነበር። ታድያ መሐመድ አሚን የተባለ ታጣቂ  ሐሠን ፀጉር ቤቱን ዘግቶ ወደ ስብሠባ ቦታ እንዲሔድ ትዕዛዝ ሰጥቶ ለተመሣሣይ ስራ ወደ ሌላ ቦታ ይሄዳል። ከግማሽ ሠዓት በሗላ መሐመድ አሚን  ሲመለስ ሐሠን በፀጉር ማስተካከሉ ስራ ላይ ሲያገኘው  ትዕዛዝ የማታከብሩት ንቀት ነው በሚል በመካካለቸው ግጭት ይፈጠራል።

በዚህም መሐመድ የታጠቀውን መሣርያ በማቀባበል ሶስት ጥይት ሲተኩስ የፀጉር ቤት ባለቤቱን የተተኮሠው አንድ ጥይት ደረቱን በመምታት  ወዲያውኑ ህይወቱ ሲያልፍ ፀጉር የሚስተካከለው ሠው ጉዳት ደርሶበት  ሆስፒታል ገብቶ ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም  ሕይወቱ አልፏል።ፖሊስ በወቅቱ በስፍራው ደርሶ መሐመድ አሚን  ከታጠቀው የጦር መሣርያ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎት የምርመራ ስራውን ሲያጠናክር የድርጊቱ ፈፃሚ  አሚን ከድር በሠጠው ቃል በወቅቱ ልቋቋመው የማልችለዉ ፀያፍ ነገር ተናገሩኝ ስሜቴን መቆጣጠር አቃተኝ መሣርያው አውቶማቲክ ላይ ነበረ ሁለቱንም መታኃቸው በማለት ቃሉን ይሰጣል። ፖሊስም የሟቾችን አስክሬን በማስመርመር በተገኘው የአስክሬን ምርመራ ውጤት እና በተለያዩ ማስረጃዎች በተከሳሽ የእምነት ቃል በማጠናከር የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለአቃቢ ሕግ ይልካል።

ዓቃቢ ሕግም ከፖሊስ የቀረበውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በወንጀል ሕግ ቁጥር  539-1 መሰረት በከባድ የሠው መግደል ወንጀል ክስ ይመሠርታል። ክሱን ሲከታተል የቆየው የአርሲ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት መጋቢት 28 ቀን 2017  ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሣሽ በከባድ የሠው መግደል ወንጀል ተከሶ  በ 21  ዓመት እስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን ኢንስፔክተር አሸናፊ እንዳለ  ለብስራት ተናግረዋል፡፡

@Sheger_Press
@Sheger_Press


#የ“ሲኒሃ ድርየም” ሸንጎው ምክር

ዕለተ ረቡዕ አይሁድ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ይሙት ብለው የወሰኑበት ዕለት ነው። ዕለቱ “እለተ ምክር”፣ “እለተ መዓዛ” እና “እለተ አንብዕ” ይባላል፡፡ “እለተ ምክረ አይሁድ” ነው፡፡ ይህ ከሰኞው ምክር፣ ከማክሰኞውስ በምን ይለያል ቢሉ የአይሁድ አለቆች፣ ጸሐፍትና ፈሪሳውያን የተስማሙና እልባት ያገኙለት ዛሬ ነበር፡፡ ዛሬም ይሙት ብለው ወሰኑ፡፡ እዚህ መላ ላይ ለመድረስ ሦስት ቀን ፈጅቶባቸዋል፡፡ ምክንያቱም በመሃላቸው “ይህ ሰው ንጹሕ ነው፤ ሞት አይገባውም” የሚሉ ርቱዓን ነበሩ የሚበዙቱ ግን ይህን በክፋታቸው ብዛት አቸንፈው መገደሉ ላይ ተስማሙ፡፡ ሌላኛው ጭንቀታቸው “እንግደልስ ብንል ምን ምስክር አለን፤ ሰውየው ንጹሕ ነው፤ ተፈትኖም ሐሰት አልተገኘበትም፤ የሚሉቱ ነበሩ፡፡ ይህንንም የሐሰት እማኞችን ለማዘጋጀት ከወሰኑ በኋላ ወዲያውኑ ለዚህ ጉዳይ ይጠቅሙናል ያሏቸውን በር ማንኳኳት ጀምረዋል፡፡

ነገር ግን በዚህች እለት ሞቱ ላይ ቢስማሙም እንዴት እንደሚይዙት ቸግሯቸው ነበር እንጂ መላ አላገኙለትም፡፡ ወቅቱ “በዓለ ፋሲካ” ነበርና በበዓል ይህን ደባ እንዴት እንተገብራለን፤ ሕዝቡም እንዳይታወክ ብለው ሰግተው ነበር፡፡ በየአገሩ ተበትነው የሚገኙ በርካታ ቤተ እስራኤል በዓለ ስርየት፣ በዓለ ሰዊትን መጸለትን፣ ፋሲካን፣ በዓለ ሀምሳ ወይም በዓለ ጰንጤ ቆስጤን ከያሉበት ሀገር ወደ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ መጥተው ለሐምሳ ቀናት ሊያከብሩ የሚሰባሰቡበትና የሚሳለሙበት ሕግ ስላላቸው ከተማ የሚከርሙ ነበሩ፡፡ እኒህም ሁሉ በጌትነቱ እንዳመኑበት በሆሣዕና እለት በክብር ሲቀበሉት ወደቤተ መቅደስም ሲሸኙት አይተው ፈርተው ነበርና ስለዚህ እንዴት እንደሚይዙና እንደሚገድሉት ተጨነቁ፡፡

የካህናት አለቆችና የሕዝብ ሹማምት በጌታችን ላይ ይሙት በቃ ለመወሰን የሰበሰቡት ሸንጐ “ሲኒሃ ድርየም” ይባላል፡፡ በዚህ ሸንጐ ላይ በአብዛኛው የተሰየሙት ሰዱቃውያን ሲኾኑ ሌሎቹ ደግሞ ጸሐፍት ፈሪሳውያን ነበሩ፡፡ ሸንጐው በአጠቃላይ ሰባ ሁለት አባላት የነበሩት ሲኾን የሚመራውም በሊቀ ካህናቱ በቀያፋ ነበር፡፡ በዕለቱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዴት ይዘው እንደሚገድሉት አይሁድ በዚህ ሸንጎ መክረዋል፡፡ ከዳተኛው ይሁዳም ጸሐፍት ፈሪሳውያንና የካህናት አለቆች በጌታችን ላይ የነበራቸውን ጥላቻ ያውቅ ስለነበር “ምን ልትሰጡኝ ትወዳላችሁ? እኔም አሳልፌ እሰጣችኋለሁ፤” በማለት ጌታችንን አሳልፎ ሊሰጣቸው እንደሚችል ተስማቷል፡፡

ጌታችን ያስተምር በነበረበት ወቅት የአስቆሮቱ ይሁዳ ከምእመናን የሚገባውን ገንዘብ ሰብሳቢ ነበር፡፡ ከሚሰበሰበው ሙዳየ ምጽዋት ለግል ጥቅሙ እየቀረጠ የማስቀረት የእጅ አመል ነበረበት፡፡ ይሁዳ ፍቅረ ንዋይ እንደሚያጠቃው ድብቅ አመሉ ጎልቶ የወጣው ጌታችን በለምጻሙ በስምዖን ቤት ሳለ ማርያም እንተ እፍረት ባለሽቱዋ ማርያም ዋጋው ውድ የኾነ ሽቱ በቀባችው ጊዜ ይሁዳ “ይህ ሽቱ ተሽጦ ለድሆች ቢሰጥ መልካም ነበር፤” በማለት ያቀረበው አሳብ፣ ሽቱ ሲሸጥ የሚያገኘው ጥቅም ስላለ ነው፡፡ ሽቶው በጌታችን እግር ሥር ከፈሰሰ ለእርሱ የሚተርፈው የለም፡፡ ይሁዳ ተቆርቋሪ መስሎ ያቀረበው አሳብ ተቀባይነት በማጣቱም ማኩረፊያ ያገኘ መስሎት በቀጥታ ከካህናት አለቆች ዘንድ ሔዶ ጌታችንን በሠላሳ ብር ለመሸጥ ተዋዋለ፡፡ ጌታችን ሁሉን ቻይ እንደሆነ ከዋለበት ውሎ ካደረበት አደሮ ደቀ መዝሙሩ ሆኖ ቢመለከትም፣ ቢጠይቀው ሊሰጠው በሚችለው ሠላሳ ዲናር ሸጠው፡፡ ይህም ልቡ ከዳተኛ ስለሆነ ነው፡፡
    

በዚህ የጾም ወቅት በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን እየረዳንና በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




የትግራይ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአስተማሪዎች የ17 ወራት ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈል ወሰነ

የትግራይ ክልል አስተማሪዎች በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ያልተከፈላቸው ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈላቸው ጉዳያቸውን ወደ ፍርድ ቤት ወስደው እንደነበር የሚታወስ ሲሆን፤ ጉዳዩን ተከሳሾቹ የትግራይ ትምህርት ቢሮ፣ የፋይናንስ ቢሮና ጊዜያዊ አስተዳደሩ በሌሉበት ሲከታተል የቆየው የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ሚያዝያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም ውሳኔ መስጠቱን ብስራት ሬዲዮ ዘግቧል፡፡

ፍርድ ቤቱ በውሳኔውም ተከሳሾች የአስተማሪዎችን ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፍሉ በመወሰን የክስ መዝገቡ እንዲዘጋ ወስኗል። የፍርድ ሂደቱ 1ኛ ተከሳሽ የትግራይ ትምህርት ቢሮ፣ 2ኛ ተከሳሽ የትግራይ ፋይናንስ ቢሮ፣ 3ኛ ተከሳሽ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርና 4ኛ ተከሳሽ የገንዘብ ሚኒስቴር ባልተገኙበት የተደረገ ነው ተብሏል።

@Sheger_Press
@Sheger_Press


ተመዘገቡ‼️

ጽናጽል ከበሮና መቋሚያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ንብረት ሆኖ ተመዘገበ‼️

"ጸናጽል፣ ከበሮና መቋሚያ ከሌሎች ከ10 በላይ ቅዱሳት መጽሃፍት ጋር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዐዕምሮአዊ ንብረት መሆናቸው ተረጋግጦ ከሚያዝያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን በቅጂና ተዛማች መብቶች ሥራ ተመዘግበዋል፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ በአእምሯዊ ንብረት ዐቢይ ኮሚቴ አማካኝነት በርካታ የቤተክርስቲያን ንብረቶች ተመዝግበው እውቅና አግኝተዋል"

Via የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን ህዝብ ግንኙነት

@Sheger_Press
@Sheger_Press


መንገድ ላይ ሽንት የሸኑ ግለሰቦች 100,000 ብር ተቀጡ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በመርካቶ እና በመሳለሚያ አካባቢ በመንገድ ሽንት በመሽናት ደንብ ቁጥር 167/2016 የተላለፉ 50 ግለሰቦች እየዳዳቸው 2000 ብር በድምሩ 100,000 /አንድ መቶ ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ አዲስ አበባን ውብና ፅዱ ለማድረግ ቀንና ማታ እየሰራ ባለበት ወቅት አንዳንድ ሀላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የተማውን ፅዳት ሲያበላሹ ህብረተሰቡ አካባቢውን ሊጠብቅ እንደሚገባ ተገልፃል።

ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 167/2016 ላይ ለህብረተሰቡ በተለያዩ አግባቦች ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱ የገለጸ ሲሆን ደንብ በሚተላለፉ ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።

@Sheger_Press
@Sheger_Press


ባለፉት 6 ወራት ብቻ ከ38 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ መሰረተ ልማቶች መውደማቸውን የትግራይ ክልል ፖሊስ አስታወቀ፡፡

በዚህም መንገዶች፣ መብራት፣ የቴሌኮምና ውሀ መስመሮች ጭምር መቋረጣቸውን አስረድቷል፡፡

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር ሀፍቱ ሚካኤል ሲናገሩ ‹‹በመሰረተ ልማቶች ላይ እየደረሰ ያለው ጉዳት የሰላማዊ ሰዎችን ህይወት አደጋ ላይ ጥሏል›› ያሉ ሲሆን ለዚህም በቅርቡ ለመቀሌ ውሀ ያቀርብ በነበረው ትራንስፎርመር ላይ የደረሰውን አደጋ እንደምሳሌ አንስተዋል፡፡

ይህ ወደአምስት መቶ ሺህ ለሚቆጠሩ የመቀሌ ነዋሪዎች በሚቀርበው ውሀ ላይ ተፅእኖ መፍጠሩን ገልፀውም ስርቆት የሚፈፅሙት ሰዎች በክልሉ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት እንደመልካም አጋጣሚ መጠቀማቸውን አስረድተዋል፡፡

ኮሚሽኑ ትናንት ባዘጋጀው ፎረም ላይ ማብራሪያ የሰጡት ኮማንደር ወርቄ ገብረህይወት በበኩላቸው ‹‹እንዲህ አይነቱ ድርጊት ተራ የወንጀል ባህርይ የሌለው ነው፡፡

ውድመቱ የሚፈፀመው ሆነ ተብሎ ለሰዎች የእለት ተእለት ህይወት አስፈላጊ በሆኑ መሰረተ ልማቶችን ኢላማ አድርጎ ነው፡፡ ስለዚህም ከስርቆት ወይንም ከሌብነት የበለጠ ፖለቲካዊ አጀንዳ ያለው ነው›› ማለታቸውን ወጋህታ ፋክትስ ዘግቧል፡፡

@Sheger_Press
@Sheger_Press


ከሩሲያ ጋር ጦርነቱን የጀመረው ዘለንስኪ ነዉ - ዶናልድ ትራምፕ

ትራምፕ ከሩሲያ ከፍተኛ ጥቃት በኋላ ጦርነት በመጀመሩ ዘሌንስኪን ተጠያቂ አድርገዋል፡፡

በዩክሬን በደረሰ እና ከባድ ነዉ በተባለ የሩሲያ ጥቃት 35 ሰዎች ሲሞቱ 1መቶ17 ሌሎች ቆስለዋል።

በሶስት ሰዎች ምክንያት በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወታቸዉ አልፏል ያሉት ትራምፕ፤ ለዚህ ጦርነት ምክንያት ፑቲን የመጀመሪያዉን ሃላፊነት ይወስዳል፣ ሁለተኛዉ ምን እንደሚያደርግ እንኳን የማያዉቅ የነበረዉ ጆ ባይደን እና ሶስተኛዉ ደግሞ ዘለንስኪ ናቸዉ ብለዋል፡፡

የትራምፕ አስተያየት ሩሲያ እሁድ እለት በዩክሬኗ ሱሚ ከተማ ላይ ባደረሰችው ጥቃት ከፍተኛ ቁጣን መቀስቀሱን ተከትሎ የመጣ ሲሆን፤ ይህም በዚህ ዓመት ሩሲያ በሰላማዊ ዜጎች ላይ ያደረሰችዉ እጅግ የከፋ ጉዳት ነዉ ሲል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

@Sheger_Press
@Sheger_Press


#ሰባት ጊዜ ሙቶ ሰባት ጊዜ ተነስቷል

የቅዱሳኑ ተጋድሎ በዋነኝነት ከ2 አካላት ጋር ነው፡፡ በመጀመሪያ በስጋ ፍላጎትና በኃጢአት ከሚፈትኑ አጋንንት ጋር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ "ሃይማኖቸታችሁን ካዱ፣ ለጣዖትም ስገዱ" ከሚሉ ከሃድያን መሪዎችና ነገስታት ጋር የሚደረግ ነው፡፡ በተለይ 2ኛው እስከ ሞት የሚያደርስ ውሳኔ ይጠይቃል፡፡ ታላቁ አባ ባውላ ገዳማዊ ጻድቅ ሲሆን ትግሉ የነበረው ከአጋንንት ጋር ነው፡፡ ቅዱሳኑ ሁሌም አንድ ነገርን እያሰቡ ይኖራሉ፡፡ ይኸውም ሰማያዊው አምላክ ከዙፋኑ ወርዶ በተዋሐደው ሥጋ በቃል ሊገለጽ የማይችል መከራን ስለ እኛ መቀበሉ ነው፡፡ ክርስትና ማለት ቀራንዮን በልብ ውስጥ መሳል ነው፡፡ ፍቅረ መስቀሉን፣ የጌታንም ውለታ የሚያስብ ማንኛውም ሰው የትኛውም ዓይነት መከራ ቢመጣበት አይታወክም፡፡ ቅዱሳኑም የፍቅራቸውና የትእግስታቸው ምሥጢር ይኼው ነው፡፡

ጌታ በማቴዎስ 16÷24 "የሚወደኝ ቢኖር የሞቱን መስቀል ተሸክሞ ይከተለኝ" እንዳለው ቅዱሳኑ ይህንን ቃል በተግባር ፈጽመውታል፡፡ ታላቁ አባ ባውላ በላይኛው ግብጽ አካባቢ በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን ተወለደ፡፡ ከክርስቲያን ወላጆቹ መንፈሳዊ ነገሮችን ተምሮ በወጣትነቱ መንኗል፡፡ ያ ዘመን እልፍ አእላፍ ቅዱሳን የነበሩበት ነውና ወደ ጠመው አካባቢ ሔዶ ምናኔን ተምሯል፡፡ ሥርዓተ ገዳምን፣ አገልግሎትን፣ ፍቅርን፣ ተጋድሎንና የመሳሰሉትን ከተማረ በሁዋላም ደቀ መዝሙሩን አባ ሕዝቅኤልን አስከትሎ ለዋናው የተጋድሎ ሕይወት ወደ በርሃ ወጣ፡፡ አባ ባውላ ዘወትር በፍቅረ ክርስቶስ ይመሰጥ ነበርና "ጌታ ሆይ! አንተ ለእኛ ለኃጥአን ኃፍረተ መስቀልን ታግሠህ ከሞትክልን እኛ ደግሞ ስለ ንጹሑ አምላክነትህ ስንል እልፍ ሞትን መታገስ አለብን::" ብሎም ዘወትር ያስብ ነበር፡፡ ተጋድሎውም በዚህ የተቃኘ ነበር፡፡

በዚህ እጅግ የጸና ተጋድሎው ምክንያትም 7 ጊዜ ሙቶ 7 ጊዜ ተነስቷል፡፡ እግሩን ከረዥም ዛፍ ላይ አስሮ፣ ወደ ታች ተዘቅዝቆ እህል ሳይቀምስ እንቅልፍና ዕረፍት ሳይሻ ሲጸልይ፤ ደሙ በአፍ በአፍንጫው ፈሶ አለቀ፡፡ በ40ኛው ቀንም ሲሞት መልአከ እግዚአብሔር ከሞት አስነሳው፡፡ ጥልቅ ባሕር ውስጥ ሰጥሞ ለ40 ቀናት ሲጸልይም በ40ኛው ቀን ለ2ኛ ጊዜ ሞቶ ቅዱስ መልአክ ከሞት አስነሳው፡፡ በሚኖርበት ጠመው አካባቢ ወደሚገኝ ረዥም ተራራ ጫፍ ወጥቶ፤ የተጠራረቡ ድንጋዮች ተመለከተ በቅጽበት የጌታ ኅማማት ከፊቱ ቢደቀንበት ከላይ ወደ ታች ተወርውረ፣ ጥርብ ድንጋዮቹም እየተቀባበሉት አካሉ እየተነከፈና እየተቆራረጠ በየመንገዱ ቀርቶ ሲሞት አሁንም ፈጣሪው ከሞት አስነሳው፡፡

ከዚህ በኋላም ሁለት ጊዜ ሞቶ ተነስቷል፡፡ በመጨረሻም የጌታን ሕማማት እያሰበ ወደ ጽኑ ቆላ ወረደ፡፡ አሸዋ በሞላው ስፍራ ቆሞ ሲጸልይም አሸዋው ውጦ ደፈነውና ለ7ኛ ጊዜ ሞተ፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ሊያስነሳው የመጣው እንደ ወትሮው ቅዱስ መልአክ ሳይሆን ራሱ የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ ነበር፡፡ ጌታችን አባ ባውላን ከሞተበት አስነስቶ "ወዳጄ ባውላ! ስለ እኔ ፍቅር እጅግ ተሰቃየህ አሁንም ይበቃሃል፡፡ መጥቼ እስክወስድህ ድረስ ከአባ ብሶይ ጋር ቆይ" ብሎት ባርኮት ዐረገ፡፡ አባ ባውላም እንደ ታዘዘው በአባ ብሶይ ገዳም ከቅዱስ ብሶይ ጋር ቆይቶ ሚያዝ 7 ቀን ለ8ኛ ጊዜ ዐርፏል፡፡ በረከተቱ ትደርብን፡፡


በዚህ የጾም ወቅት በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን እየረዳንና በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


7 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ኾነዋል‼️

ትምህርት ሚኒስቴር በ6ተኛው የህዝብ ተወካዮች 4ተኛ ዓመት የስራ ዘመን 24ተኛ መደበኛ ስብሰባ የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርቧል፡፡

በሪፖርቱም በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋዎች 7.2 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

በተለያዩ ክስተቶች ከ5 ሺህ 300 በላይ ትምህርት ቤቶቸ መውደማቸውን ተከትሎ ነው ተማሪዎቹ ከትምህርት ገበታቸው እንደራቁ የተገለጸው፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር በ9ወራት እቅድ አፈጻጸሙ ከተነሱ ጉዳዮች መካከልም የትምህረትን ጥራት ለማረጋገጥ የመምህራን ብሎም የትምህርት አስተዳደሩ አቅምን ማሳደግ ላይ እየተሰራ መሆኑ ተጠቁማሉ፡፡

በ2017 ክረምት መርሃግብርም 84 ሺህ ለሚሆኑ የሁለተኛ ደረጃ መምህራንና አስተዳደሮችን ስልጠና ለመስጠት ታቅዷል ተብሏል፡፡

(ሰላም ይልማ - NBC)

@Sheger_Press
@Sheger_Press


ባለፉት 9 ወራት ከ600 ሚሊየን ብር በላይ ከትራፊክ ቅጣት መሰብሰቡን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣናት ተናገረ።

ባለስልጣን መ/ቤቱ ባለፉት 9 ወራት ከትራፊክ እና ከመሰል ቅጣቶች በአጠቃላይ ከ700ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ተናግሯል።

በከተማዋ ከሚስተዋለው የትራፊክ ደንብ ጥሰት ውስጥ 40 በመቶው የፍጥነት ወሰን ህግን አለማክበር ነው ተብሏል።

የትራፊክ ቁጥጥሩን ለማዘመን፣ የሙስና ተጋላጭነትን እና የደንብ ጥሰትን ለመቀነስ፣ የተገልጋዮችን እንግልት ለማስቀረት እንዲሁም መሰል የአሰራር ስርአትን ለማሻሻል ዲጂታል አሰራርን እየተገበርኩ ነው ሲል ባለስልጣን መ/ቤቱ ተናግሯል።

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ክበበው ሚዴቅሳ በትራፊክ ደንብ እና በመሰል ጥሰቶች ቅጣት የምንጥለው ገቢ ለመሰብሰብ ሳይሆን ህግን ለማስከበር ነው ብለዋል።(ሸገር )

@Sheger_Press
@Sheger_Press


#MoE

" ከ2019 ጀምሮ 3ኛ ዓመት የጨረሱ ተማሪዎች 4ኛ አመት ከመግባታቸው በፊት የ1 ዓመት አገልግሎት እንዲሰጡ ይደረጋል " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)

በዩኒቨርሲቲ የሚማሩ 3ኛ ዓመት የጨረሱ ተማሪዎች 4ኛ ዓመት ሳይገቡ በፊት የአንድ ዓመት አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ የተጀመረው እንቅስቃሴ ከ2019 ዓ/ም ጀምሮ ተግባር ላይ እንደሚውል የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ጠቁመዋል።

ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ፤ " በሚቀጥለው ዓመት ላይደርስልን ይችላል ግን ህጋዊ ስርዓቱን በሙሉ ጨርሰን በ2019 ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚማሩ 3ኛ ዓመት የጨረሱ ተማሪዎች ከ2019 ጀምሮ 4ኛ አመት ከመግባታቸው በፊት የ1 ዓመት አገልግሎት እንዲሰጡ ይድረጋል " ብለዋል።

" ከዚህ በፊት የነበረ ነው አዲስ አይደለም በጃንሆይ ጊዜ (በአጼ ኃይለስላሴ ጊዜ ማለታቸው ነው) የነበረ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ሁለት ጥቅም አለው ብለን ነው ይሄን የምናደርገው አንደኛ ልጆቹ ዝም ብሎ የቀለም ትምህርት ብቻ ተምረው ሳይሆን ተግባራዊ የሆነ ትምህርትም ለአንድ ዓመት ሄደው የሚሰሩበት ከማህበረሰቡ ጋር የሚተዋወቁበት ነው። ሁለተኛ የአስተማሪዎች እጥረትም ስላለ ልጆችን ወደ አስተማሪነት ለአንድ አመት ቢሆንም ለማስገባት ነው " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
@Sheger_Press
@Sheger_Press


ዶ/ር ደብረጺዮን ስለ ፕሪቶሪያው ስምምነት ምን አሉ⁉️

የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ ከፍተኛ ቡድን በፍጥነት በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ እንዲወያይ መጠየቃቸውን የትግራይ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ደብረጺዮን ይህን የጠየቁት፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ፣ አረጋጋጭና ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ከፍተኛ ሃላፊ ኾነው አዲስ ከተሾሙት ሜጀር ጀኔራል ሳማድ አላዴ አሶዴ ጋር ዛሬ መቀሌ ውስጥ በተወያዩበት ወቅት ነው።

ሕወሓት እና መንግሥት በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት እስካሁን የፖለቲካ ውይይት እንዳልጀመሩና የፓርቲው ሕጋዊ እውቅና እንዳልተመለሰለት ደብረጺዮን መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል።

አፍሪካ ኅብረት ጀኔራል ሳማድን የሾመው፣ የሥራ ጊዜያቸውን ባጠናቀቁት ጀኔራል እስጢፋኖስ ራዲናን ምትክ ነው። ሕወሓት ከኮሚቴው ጋር በትብብር እንደሚሠራ ያረጋገጡት ደብረጺዮን፣ ኮሚቴው መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ኹኔታ በግልጽ በመለየት ሪፖርት እንዲያቀርብ ጠይቀዋል ተብሏል።

@Sheger_Press
@Sheger_Press

Показано 20 последних публикаций.