ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Транспорт


╔════◈◉◈════╗
                     أهل السنة والجماعة
            ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⚪️አህለሱና ወልጀመዓህ ስንል የሰለፎችንና የኸለፎችን የግንዛቤ ዘይቤ የሚከተሉ ማለት ነው።
🔴ይህ መንገድ ሌሎች የኢስላም አስተሳሰብ ተከታዮችን አያከፍርም
🔎አመላካች የሰሪን ምንዳ ያገኛልና ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩልን
╚════◈◉◈════╝

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Транспорт
Статистика
Фильтр публикаций


ፆም ግዴታ የሚሆንባቸው መስፈርቶች እና
ፆም ለመብቃት መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች እንደሚከተሉት  ናቸው፡

1) እስልምና
ካፊር በሆነ ሰው ላይ ረመዳን ግዴታ አይሆንበትም። በሌላ አነጋገር በዱኒያ ላይ እንዲፆም አይጠየቅም ምክንያቱም እስልምና ዉስጥ  መግባቱን ተከትሎ የሚመጣ ነገር ሰለሆነ ፣ እስልምና ዉስጥ እስካልገባ ድረስ መፆሙም ሆነ እንዲፆም መጠየቁ  ምንም አይነት ትርጉም የለውም ። አኺራ ላይ ካፊር የሆነ ሰው ካፊር በመሆኑም ባለመፆሙም ይቀጣልና።

2)ተክሊፍ

ተክሊፍ ሲባል ሙስሊም ፣ ለአቅም አዳም የደረሰ ወይም ለአቅመ ሄዋን የደረሰች ፣ ነገራቶችን የሚለይ መሆነ አለበት። ከነዚህ ባህሪያት አንዱ ከጎደለ ሙከለፍ አይደለም ማለት ነው። ይህም ከዲን ስራዎች በየትኛውም አይታዘዝም ሚለውን ያስይዘናል።
ሰይዱና ዐሊይ ረዲየሏሁ ዐንሁ ባስተላለፉት ሀዲስ የአሏህ መልክተኛ እንዲህ ብለዋል፡❝ ብዕር ከሶስት ሰዎች ላይ ተነስቷል ፡ የተኛ ሰው እስኪነቃ፣ ህፃን ልጅ እስኪ ጎረምስ ፣እብድ አእምሮዉ ጤነኛ እስኪሆን ድረስ ❞ ።
አቡ ዳውድ ዘግበዎታል

3)ፆምን ከሚከለክሉ ወይም ፆምን ማፍረስ ከሚያበቁ ምክንያቶች መንፃት

መፆምን የሚከለክሉ ምክንያቶች
♦️በቀኑ ክፍለ ጊዜ ውስጥ  የሀይድ ወይም የኒፋስ ደም መመልከት
♦️ቀኑን ሙሉ ራስን መሳት ወይም ማበድ ።ከቀኑ
ክፍለ ጊዜ ለአፍታ እንዃን ከነቃ ምክንያቱ ይወድቃል ፡ ከምግብ መቆጠብ ግድ ይሆንበታል።

ለማፍጠር የሚያስችሉ ምክንያቶች

1:በፇሚው ላይ ከባድ ችግርን ወይም ህመምን ወይም አለመርጋጋትን የሚያስከትል በሽታ

በሽታው ወይም ህመሙ ከመፆሙ ጋር ለሞት የሚዳርግ ጉዳት ያስከትልብኛል ብሎ ከፈራ የዚህን ጊዜ ማፍጠር ግዴታ ይሆንበታል።

2.ከ83 ኪሎሜትር የማያንስ ረጅም ጉዞ
መስፈርቱም ጉዞው የተፈቀደ  ( በሸሪአ ለተፈቀዱ ተግባራት ተብሎ የሚደረግ ) መሆን አለበት ቀኑን ሙሉ የሚፈጅ መሆነ አለበት

አከባቢዉ ላይ ባለበት ፆመኛ ሆኖ አንግቶ በቀኑ መሀከል ላይ ጉዞ ቢጀምር  ማፍጠር አይበቃለትም ።

የሁለቱ ምክንያቶች ማስረጃ

ومن كان مَّرِيضًا أَوْ عَلَىٰ سَفَرٍ فَعِدَّةٌ مِّنْ أَيَّامٍ أُخَرَ
البقرة ١٨٥
   ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጹመው፡፡ በሽተኛ ወይም በጉዞ ላይ የኾነም ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን (በልኩ) መጾም አለበት፡፡

3)መፆም አለመቻል

በእድሜ መግፋት እንዲሁም መዳኑ ተስፋ በሌለው በሽታ መፆም ያልቻለ ሰው ፡ ፆም ግዴታ አይሆንበትም። ምክንያቱም ፆም ግዴታ ሚሆነው በሚችል ሰው ላይ ነውና።

አሏህ እንዲህ ይላል፥

وَعَلَى الَّذِينَ يُطِيقُونَهُ فِدْيَةٌ طَعَامُ مِسْكِينٍ
البقرة١٨٤
በእነዚያም ጾምን በማይችሉት ላይ ቤዛ ድኻን ማብላት አለባቸው፡፡

❝ዩጢቀነሁ❞ የሚለው በሌላ አቀራር “ ዩጠወቁነሁ “ በሚል ተቀርቷል ፡ ❝ዩከለፋነሁ❞ ማለት ።ትርጉሙም ❮የማይችሉ❯ ማለት ነው።

እንዲህ አይነት ሰዎችን በተመለከተ ኢብኑ አባስ እንዲህ ብለዋል  ❝በእድሜ የገፋ ሽማግሌና  አሮጊት ሆነው መፆም የማይችሉ ሰዎች ለእያንዳንዱ ቀን አንዳንድ ምስኪን ያበላሉ❞
                     ቡኻሪ ዘግበውታል

ፆም የመብቃቱ መስፈርቶች

ፆም ለመብቃቱ ቀጥለው የሚመጡ መስፈርቶች መሟላት አለባቸው።

ሙስሊም መሆን ፡ በትኛውም ሁኔታ የካፊር ፆም አይበቃም
አል ዐቅል (መለየት መቻል)
የእብድና የማይለይ ህፃን ልጅ ፆም አይበቃም።
የሚለይ ልጅ ፆም ይበቃል ፡ ህፃን ልጅ ሰባት አመት የሞላዉ ጊዜ የመፆም አቅም ካለው እንዲፆም ይታዘዛል ፡ አስር አመት  ሲሞላው ባለመፆሙ ይመታል ልክ እንደ ሰላት።

ፆምን ከሚከለክሉና ማፍጠርን ከሚያበቁ ምክንያቶች መጥራት እነርሱም ከላይ እንደተገለፀው የሀይድና የኒፋስ ደምን መመልከት  እንዲሁም ቀኑን ሙሉ የሚቆይ እብደት ወይም አውድቅ መከሰት ናቸው።

የፆም መስፈርት
የመብቃት።።።።።።።።።።።። ግዴታ የመሆን
ኢስላም ፣ አቅል።።።።።።።።።ኢስላም -ተክሊፍ
ፆምን ከሚከለክሉ ነገራቶች
መጥራት።።።።።።።።።።።።።።።

ዘ.ሐ &ፈቂር


የሀኪም ስህተት መሬት ውስጥ ይቀበራል ፡ የመሀንዲስ ስህተት መሬት ይከሰታል ፡ የአስተማሪ ስህተት ግን ምድር ላይ ይጏዛል


💎ዐቂዳ ደርስ - 44💎

💢 ለነቢያቶች የሚያስመቹ ( ጃኢዛት) እና በፍፁም የማይገቡ ( ሙስተሂላት )) ባህሪያት

     🎤 በኡስታዝ ዒሳ አብራር
          ( ሀፊዘሁሏሁ ተዐላ )


💎ዐቂዳ ደርስ - 43💎

💢 ነቢያቶች ዘንድ በፍፁም ሊታጡ ከማይገባቸው ባህሪያት መካከል አንዱ ስለሆነው “ አል ዒስማህ “ ( ፍፁም ከወንጀል ጥቡቅነት ወይም መፅዳት ) በሰፊው የተዳሰሰበት

👉 ዒስማህ ወይም ነቢያቶች ከወንጀል የፀዱ ናቸው ወይስ አይደሉም በሚለው ጉዳይ የአህለሱና እንዲሁም የሌሎች የስሜት ባለቤቶች አቋምም ተዳስሷል

👉 ነቢያችን ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም “ መዕሲያ ሀቂቂያ “ ( ትክክለኛ ወንጀል ) ሰርተዋል ለሚሉ የሀረሪያ ጀመዐዎችም ምላሽ ተሰጥቷል


     🎤 በኡስታዝ ዒሳ አብራር
          ( ሀፊዘሁሏሁ ተዐላ )


የረመዳን ወር መግባት የሚረጋገጥባቸዉ መንገዶች

የረመዳን ወር መግባት በሁለት ነገራቶች ይረጋገጣል።

1) የሻእባን ወር ሰላሳኛዉ ለሊት ( በነጋታዉ 30ኛው ሻእባን ሊሆንባት የምትችለዋ ምሽት ) ላይ  ጨረቃ መታየት ።

ይህም አዲል የሆነ መስካሪ ቃዲ ፊት ቀርቦ ጨረቃን በእርግጥ እንደተመለከተ ሲመሰክር ነው።

2) የሻእባን ወር ሰላሳ ቀን የሞላ እንደሆነ ።

ይህም በደመና ምክንያት ጨረቃን ማየት ያስቸገረ ወይም ጨረቃን እንደተመለከተ የሚመስክር አዲል የሆነ ሰው ያልተገኘ እንደሆነ ሻእባንን ሰላሳ ቀን እንሞላለን ። ይህን የሚቃረን ነገር እስካልመጣ ድረስ መሰረቱ ይህ (ሻእባን ሰላሳ ቀን መሙላቱ) ስለሆነ ።

የነዚህ የሁለቱ ነገራቶች ማስረጃቸው :

1/ ነቢዩ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል :-
❝ጨረቃን አይታችሁ  ፁሙ፤ እርሷኑ አይታችሁ ፆማችሁን  ፍቱ ፤ ደመና ከሸፈናችሁ ሻእባንን ሰላሳ ቀን ሙሉ❞።
ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል

2/ ኢብኑ አባስ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንዳስተላለፉት ፦አንድ የገጠር ሰው ወደ አሏህ መልክተኛﷺ  መጣና እንዲህ አላቸው ❝እኔ የጨረቃን የመጀመሪያ ውልደት ( መውጣት) ተመለከትኩ❞ አላቸው።
እርሳቸውም❝ላኢላሀ ኢለላህ❞ ብለሀል አሉት ?
❝ አው❞አላቸው።
እርሳቸውም፡❝የአሏህ መልክተኛ መሆኔን ትመሰክራለህ?❞ አሉት። አዎ አላቸው ፣ እርሳቸዉም : ❝ ቢላል ሆይ  ! ሰዎችን ተጣራ ነገ ይፁሙ❞ አሉ።
ኢብኑ ሂባን ሰሂህ ነው ብለዉታል።

⭕️የፀሀይ መውጫ ልዩነቶችን ከግምት ውስጥ ማስገባት

አንድ ሀገር ላይ ጨረቃ ከታየ ቅርብ የሆኑ አካባቢዎችም ላይ መፆም ግዴታ ይሆንባቸዋል። ምክንያቱም ቅርብ የሆኑ እንደ ዲመሽቅ ፣ ሂምስ፣ ሀለብ ያሉ ከተማዎች እንደ አንድ ሀገር ነው የሚቆጠሩት ።ሩቅ የሆኑ ከተማዎች እንደ ዲመሽቅ ፣ቃሂራ እና መካ ያሉት እንደ አንድ ሀገር አይቆጠሩም ስለዚህ በአንዱ ሀገር ቢታይ በሌላው ሀገር ላይ ግዴታ አይሆንም።

⭕️ርቀቱ የሚታየው በፀሀይ መውጫ መለያየት ነው

ኩረይብ እንዳስተላለፈው ❝ ሻም እያለሁ ሰይዱና ዐልይ ረዲየሏሁ ዐንሁ ረመዳንን አስጀመሩ ፡ የጁሙዐ ቀን ጨረቃን ተመለከትኩ.. በወሩ መጨረሻ ወደ መዲና መጣሁ ፡ ኢብኑ ዐብባስም መች ነበር ጨረቃን ያያችሁት አሉ ? እኔም ፡የጁሙዐ ለሊት ነበር ያየነው አልኩኝ ፡ አንተ በትክክል አይተሀልን ? አሉኝ ፡ እኔም ፡ አዎ !  ሰዎችም አይተውት ፆመዋል ፡ ሙአውያም ፆመዋል አልኳቸዉ ፡ እርሳቸዉም “  ሁላችንም ያየነው የቅዳሜ ለሊት ነው ፡ ሰላሳ ቀን እስኪሞላ ወይም ጨረቃን እስክናይ ከመፆም አንወገድም አሉኝ ። በሙዐዊያ እይታና ፆም አትብቃቁምን ? አልኳቸዉ ፡  አልብቃቃም ፡ የአሏህ መልክተኛ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም እንደዚህ ነው ያዘዙን❞ አሉኝ።
ሙስሊም ዘግበውታል

ከዚህ ሀዲስ ተነስተው ኡለማዎች እንዲህ ብለዋል :


አንድ ሰው ጨረቃ ከታየበት ሀገር ሌላ ሩቅ ወደሆነ ረመዷን ወዳልገባበት ሀገር ቢጓዝ ፣ እዚያች ሀገር በመግባቱ ምክንያት የዚያች ሀገር አንደኛው ነዋሪ ስለሚሆን ወደ አዲሱ ሀገር ከመምጣቱ በፊት የፆመው ሰላሳ ቀን ቢሆንም እንኳ የአዲሱን ሀገር ሰዎች በፆም ይገጥማቸዋል ወይም እነርሱ እስከፆሙ ድረስ እርሱም አብሯቸው ይፆማል

ጨረቃ ካልታየበት ሀገር ጨረቃ ወደ ታየበት ሀገር የተጓዘ ሰው እነርሱ ፆም ሲፈቱ እርሱም አብሯቸዉ ይፈታል ፣ ነገር ግን የፆመው ቀን ሲደመር ሀያ ስምንት ቀን ከሆነ አንድ ቀን ቀዷእ ያወጣል ምክንያቱም በአረብኛ አቆጣጠር አንድ ወር ሀያ ስምንት ቀን ስለማይሆን ፣ የፆመው ቀን ሲደመር ሀያ ዘጠኝ ከሆነ ግን ምንም የለበትም ።

ነገ ዒድ ነው የተባለበት ሀገር ላይ ካነጋ በኃላ የሀገሪቷ ነዋሪዎች ፆመኛ ወደሆኑበት ሀገር የተጓዘ እንደሆነ እነርሱን ለመግጠም ሲል የተቀረውን የቀን ክፍል ፆምን ከሚያበላሹ ተግባራት መቆጠብ አለበት

ዘ.ሐ& ፈቂር


ከማወቁ ጋር ታጋሽ በመሆኑ ፣ ከቻይነቱ ጋር ደግሞ በዚህች ሀገር / ዱንያ/ ይቅርታን ስለለገሰን አሏህን እናመሰግነዋለን ፤ በቀጣዩ ሀገርም ይህን ይቅርታውን በድጋሚ እንዲለግሰን እንለምነዋለን።

አባዬ ሾንኬ / አል-በድዐት አስሰኒያህ/


ስለ አጥቢ እናት እና ነፍሰ- ጡር ሴት ተጨማሪ ማብራሪያ
—————————

💢 በሻፊዒይ እና ሀንበሊይ መዝሀብ አጥቢ እና ነፍሰ-ጡር ሴቶች ቀዷእ ብቻ የሚወጅብባቸው መፆማቸው እነርሱ ላይ ጉዳት ያስከትላል ወይም አንችልም ብለው የፈሩ ወይም ለራሳቸው ለልጁም ጉዳት የፈሩ ጊዜ ነው ።

💢 የመፆም አቅም ኖሯቸው ነገር ግን ልጁ ይግጎዳል ብለው ለልጁ ብቻ የፈሩ እንደሆነ ከቀዷእ ጋር ለእያንዳንዱ ቀን አንድ ሚስኪን መመገብ አለባቸው።


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ስለ አይነላህ ምርጥ ማብራሪያ


Репост из: ሱና የእውቀት ማዕከል
ማ‌‌ስ‌‌ታ‌‌ወ‌‌ሻ‌‌
ሸ‌ዕ‌ባ‌ን‌ ከ‌መ‌ው‌ጣ‌ቱ‌ በ‌ፊ‌ት‌
:
የቀደመ የረመዳን ቀዷ ያለበት መጪው #ረመዳን ሳይገባበት ቀዷውን አውጥቶ ይጨርስ። ቀዷ ማውጣት እየቻለ ሳያወጣው ተከታዩ ረመዳን የገባበት ሰው: ‐
⚀ ኃጢኣተኛ ይሆናል፤
⚁ ቀዷእ ማውጣቱ አይቀርለትም፤
⚂ ፊድያ (ቤዛ) ማውጣት ግዴታ ይሆንበታል። ፊድያው ለአንድ ቀን አንድ እፍኝ ነው። አመቱ በጨመረ ቁጥርም ፊድያው ለአንድ አመት አንድ እፍኝ እየጨመረ ይመጣል።
:
በህመም፣ በማጥባት፣ በእርግዝና ወይም በሌላ ሸሪዓዊ ምክንያት ቀዷውን መክፈል ያልቻለ ሰው ግን በተመቸው ጊዜ ብቻ ቀዷ ማውጣት ይበቃዋል።
ይህ የሻፊዒዮች እና የአብዝሃኛዎቹ ልሂቃን ሃሳብ ነው!
ረመዷን ሊገባ ነውና እንተዋወስ!
መልካም አዲስ የሥራ ሳምንት ይሁንልን!
✏️ኡስታዝ_ቶፊቅ_ባሕሩ (ሐፊዘሁላህ)


እንዃን እኛን "ከኔ የሆነን ውዴታና አደረኩብህ" የተባሉትም ነቢላሂ ሙሳ ዓለይሂ ሰላም ሁሉም አልወድዳቸውም።


" በአሁን ጊዜ ለአላህ ብሎ ሚወድህም ሚጠላህም የለም" አትጨነቅ


ዘ.ሐ


አንድ ሙስሊም ይህን ካደረገ በኃላ ፆምም ይሁን ሌሎች የፈጣሪ ትእዛዛት ውስጥ የሚገኙ መለኮታዊ ጥበቦችንና ሚስጥራትን ለማወቅ ጥረት ቢያደርግ ምንም ከልካይ የለም ።
ሁሉም የአሏህ ህግጋት ለባሪያዎቹ የሚበጁ ጥበቦች፣ ሚስጥራትና ጥቅሞች ላይ እንደተመሰረቱ ምንም ጥርጥር የለውም ነገር ግን ባሮቹ ይህን ማወቃቸው መስፈርት አይደለም ።

👉 የረመዷን ፆምም  የራሱ የሆኑ ብዙ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን ፡ ከፊል ጥቅሞቹን ሙስሊም የሆነ ሰው ሊደርስባቸው ይችላል ፡ ከጥቅሞቹ መካከል :-

1/ ከፆም ባህሪ መካከል የሙስሊምን ልብ የአሏህ ቁጥጥር ( ሙራቀባ) አለብኝ ብሎ እንዲነቃ ማድረግ ነው ፡ ይህም አንድ ፆመኛ የሆነ ሰው ትንሽ የቀኑን ክፍለ ጊዜ እምደገፋ የረሀብ ስሜት ይሰማዋል ፡ ነፍሱ ወደ ምግብና መጠጥ ትጓጓለች ፡ ነገር ግን ፆመኛ እንደሆነ ማሰቡ የአሏህን ትእዛዝ ለመጠበቅ ሲል ይህን ፍላጎቱን እንዳያሳካ ያግደዋል ፡ በዚህ ግብግብ መሀከል ልቡ ይነቃል ፣ አሏህ እየተቆጣጠረኝ ነው የሚለው ስሜት እያደገ ይመጣል ፡ የአሏህን ጌትነትና የስልጣኑን ታላቅነት ከማስታወስ ፡ እርሱ ( ፆመኛው ) ደግሞ ለአሏህ ትእዛዝ የተዋረደና ለአሏህ ፍላጎት እጅ የሰጠ ባሪያ መሆኑን ከማስታወስ አይወገድም ።

2) ረመዷን ከአመቱ ወራቶች መካከል የተቀደሰ ወር ነው ፡ ባሮች ይህን ወር ወደ አሏህ በሚያቃርቡ ተግባራትና አምልኮዎች እንዲያሳልፋት አሏህ ይፈልጋል ፡ የላቁ የባርነት መገለጫዎችንም እንዲላበሱ ይፈልጋል። ይህ ደግሞ በምግብ ማእዶችና በመጠጥ ስብስቦች በመገኘት ብቻ ሊገኝ አይችልም ።

3) የጥጋብ ስሜት(ሁኔታ ) በሙስሊም ህይወት ውሰጥ መቀጠሉ ስሜቱን ጭካኔን በሚያስከትሉ ምክንያቶች  ሊሞላው እና በነፍሱ ውስጥ የጭቆና ምክንያቶችን ሊያዳብር ይችላል ፡ እኚህ ሁለቱም ባህሪያት ደግሞ ከሙስሊም ባህሪ ጋር የማይጣጣሙ ናቸው። ስለዚህ የፆም ህግ የሙስሊሙን ነፍስ የማግራትና  ስሜቱን የማለዘብ ጥበብን  ይዟል።

4) ኢስላማዊ ማህበረሰብ ከተመሰረተባቸው መሰረታዊ መርሆች አንዱ የሙስሊሞች መተዛዘን እና ርህራሄ ነው። ባለፀጋ የሆነ ሰው  የድህነት ስቃይና አስከፊነት፣ የረሃብ ምሬትና ጭካኔ ሳይሰማው ለድሆች ልባዊ ርኅራኄ ማሳየት አይቻለውም።

ባለፀጎች የድሆች ስሜት እንዲሰማቸውና በሥቃያቸውና በእጦት አብረው እንዲኖሩ የሚያደርጋቸው የጾም ወር ከሁሉ የተሻለው መንገድ ነው። ስለዚህ ጾም በሀብታሞች ነፍስ ውስጥ የርኅራኄ፣ የምሕረትና የመጽናናት መነሳሳትን ለመቀስቀስ ከሁሉ የተሻለው መንገድ ነው።

ዘ.ሐ& አብዱል ፈቂር


⇣【ፆም】⇣

ምንነቱ/ድንጋጌው /ሚስጥሩ
                  ــــــــــــــــــــــــ❀•▣ ▣•❀ــــــــــــــــــــــــ

በቋንቋ ደረጃ❩:- ከአንዳች ነገር  ከንግግርም ይሁን ከምግብ  መቆጠብ ማለት ነው።

ለዚህም ማስረጃ አሏህ ስለ መርየም ሲተርክልን እንዲህ ይላል፡

       قوله تعالى:﴿۝إِنِّي نَذَرْتُ لِلرَّحْمَنِ صَوْمًا۝﴾
ለአዛኙ አምላኬ ፆምን ተስያለሁ
ሱራ አል-መርየም :26

❨ሸሪዐዊ ትርጓሜው❩፡ ከጎህ መቅደድ ጀምሮ ፀሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ከማሰብ ❪ከኒያ❫ ጋር ፆምን ከሚያስፈቱ ነገራቶች መቆጠብ የሚለውን ያስይዛል ።

           ፆም የተደነገገበት ጊዜ
                          ـــــــــــــــــــ❀•▣ ▣•❀ـــــــــــــــــــ

የረመዷን ፆም በሁለተኛው አመተ - ሂጅራ በሻእባን ወር ላይ ተደነገገ።ፆም ከኛ በፊት የነበሩ ህዝቦች ዘንድ እንዲሁም በነብዩﷺ ዘመን ይኖሩ የነበሩ አህለል ኪታቦች ዘንድ ይታወቅ ነበር።
አሏህ እንዲህ ይላል:-
قوله تعالى:﴿۝يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُتِبَ عَلَيْكُمُ الصِّيَامُ كَمَا كُتِبَ عَلَى الَّذِينَ مِن
قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ۝﴾ البقرة: ۱۸۳.


❝እናንተ ያመናቹ ሠዎች ሆይ!..ፆም ለእነዚያ ከእናንተ በፊት ለነበሩት ❨ህዝቦች በግዴታነት❩ እንደተደነገገ ሁሉ በእናንተም ላይ ተደንግጓል..ጥንቅቆች ትሆኑ ዘንድ❞
          ሱራ አልበቀራ 183

👉ይህም ማለት ይህ አንቀፅ ከመውረዱ በፊት የረመዳን ፆም ግዴታነት አልተደነገገም ነበር።

⚜የነብዩﷺ ኡመት ከሌሎች ኡመቶች ጋር በፆም ድንጋጌ ላይ ቢጋሩም የረመዳን ፆም ግዴታ በመሆኑ ላይ ግን ከሌሎች ኡመቶች ጋር ይለያያሉ።

     የረመዳን ፆም ግዴታ ለመሆኑ ማስረጃ
           ــــــــــــــــــــــــــ❀•▣ ▣•❀ــــــــــــــــــــــــ

የረመዳን ፆም ግዴታ መሆኑ ማስረጃው የአሏህ ንግግር ነው፦

قوله تعالى: ﴿۝شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَى وَالْفُرْقَانِ فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ۝﴾ البقرة: ١٨٥

❨አሏህ ትፆሙት ዘንድ የወሰነው❩ የረመዷን ወር ለሰው ዘር መመሪያ የሆነው ❨መለኮታዊ❩ አመራር እና ❨እውነት ከ ሀሠት❩ ለመለየት የሚያስችሉ ግልፅ አናቅፅ የሠፈሩበት ቁርዐን የወረደበት ወር ነው። ከመካከላቹ በዚህ ወር የተገኘ ወሩን በፆም ማሳለፍ አለበት❞
        ሱራ አል-በቀራ 185

የአሏህ መልክተኛﷺ እንዲህ ይላሉ፡ ❝እስልምና የተገነባው በአምስት ነገራቶች ነው ሸሀደተይን፣ ሰላትን ደንቡን ጠብቆ መስገድ፣ ዘካን መስጠት፣ ሀጅ ና ረመዳንን መፆም ናቸው ❞።

📜 ቡኻሪና ሙስሊም ሌሎችም ዘግበውታል።

በአንድ ወቅት አንድ በደዊ❨የገጠር ሠው❩ ወደ አሏህ መልክተኛﷺ ዘንድ መጣና ፡ ❝ አንቱ የአሏህ ነቢይﷺ ሆይ!.. አሏህ በእኔ ላይ ግዴታ ያደረገው ፆም ምንድነው?❞ ብሎ ጠየቃቸው ።
እሳቸውም ﷺ፡❝ የረመዷን ፆም❞ በማለት መለሡለት።

📜 ቡኻሪ ሙስሊም ዘግበውታል።

    የረመዳንን ፆምያለ ምክንያት የተወ ሰው ፍርድ
          ـــــــــــــــــــــ❀•▣ ▣•❀ــــــــــــــــــــــ

ረመዳን ከኢስላም መሰረቶች አንዱና በኢስላም ግዴታ እንደሆኑ ሁሉም ሰው ከሚያቃቸ
ግዴታዎች መካከል አንዱ ነው። ፆም የለም ብሎ የካደ ሰው ይከፍራል። ይከፍራል ማለት እንደ ሙርተድ ይሰተናገዳል ፡ ተውበት ያስደርጉታል ፡ ተውበት ካደረገ ይቀበሉታል ተውበት አላደርግም ካለም  ይገደላል።

⛔️ይህም የሚሆነው ❨የሚገደለው❩ ወደ እስልምና ቅርብ ጊዜ የገባና ከኡለማ ርቆ የሚኖር ሰው ካልሆነ ነው።

የፆምን ግዴታነት ሳይክድ ያለምንም ምክንያት የረመዳን ፆምን የተወ  ሰው ፡  ለምሳሌ :- “ ፆም ግዴታ ነው ግና አልፆምም  “ ያለ ሰው  ፋሲቅ ❨አመፀኛ❩ ይሆናል። ነገር ግን ካፊር አይሆንም።ሙስሊም በሆነ መሪ ላይ አስሮት ምግብና መጠጥን በቀኑ ክፍለ ጊዜ ሊከለክለው  ግዴታ ይሆንበታል። ፆም ሚመስል ነገር  እንኳን እንዲገኝለት( ተገዶ ሲፆም ኒያ ላይገኝ ስለሚችል) ።

       የረመዳን ወር ፆም ያለ ምክንያት የተወ ሰው
      ــــــــــــــــــــــــــ❀•▣ ▣•❀ــــــــــــــــــــــــ

💢ግዴታ መሆኑን ያልካደ

ፋሲቅ ወይም አመፀኛ ነው ፡ አይከፍርም በሙስሊም መሪ ላይ በቀኑ ክፈለ ጊዜ ሊያስረው ምግብ ሊከለክለው ግዴታ ይሆንበታል።

💢ግዴታ መሆኑን የካደ

ካፊር ይሆናል፤ እንደ ሙርተድ ይስተናገዳል ፤
ተውበት ያስደርገዋል..ተውበት ካደረገ ይቀበሉታል ያለበለዚያ ይገደላል።

             የፆም ጥበቡ ፣ሚስጥሩና ጥቅሙ
       ــــــــــــــــــــــــــ❀•▣ ▣•❀ــــــــــــــــــــــــ

♦️አንድ አማኝ የረመዷን ወር  ፆም አሏህ ግዴታ ያደረገው ኢባዳ እንደሆነ ከሁሉም ነገር በፊት ሊያውቅ ይገባዋል። ኢባዳ ነው ሲባል ከፆም የሚገኙ የትኛውንም  አይነት ጥቅሞችን ሳይመለከት የአሏህን ትእዛዝ ተቀብሎ መተግበር ማለት ነው።

꧁°•.❃_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_- ❃.•°꧂     ገፅ 1


ረመዳንን አቀባበል ከምናደርግበት ትልቁ መቀበያ ንፁህ ልብ ነው


ሀላል ኒካህ አገናኝ

አዲስ ስራ በቅርቡ 😂😂😂😂 ለመመዘገብ
እናትህን አማክር ለእህት ለሚስትነተ ያሰብካትን ሴት አሳያት ለሚስትነት ያሰብካትን ሴት እናት ተመልከት ዱአ አድርግ......... እዚህ የማይነገሩ ማጣራት የሚገባህን ጉዳይ ሁሉ አጣራ ከዚህ በኃላ ወደ ኒካህ ። ኮምሽኑን ካገቡ በኃላ ይልካሉ አያሳስብም ‼️

ማሳሰቢያ
ሚስት ከራስህ ነው እኛ የለንበትም




ዘ.ሐ


አሻዒራ ወይስ ወሀብያ ሰለፎችን ሚከተለው?

(አስሳቅ)(الساق ) ሰለፎች እንዴት ተረዱት "

ማን ለመወያየት ዝግጁ ነው?


"ውብ ሁን ፍጥረቱን ውብ ሆኖ ታየዋለህ"


አሏህ ሱብሀነሁ ወተዐላ ከእርሱ ውጪ ካለ ከየትኛውም ነገር ጋር የተዋሀደ አይደለም

አል-ዐቂደቱል ውስጣ


ዘመናዊ ሸክዋ(ስሞታ)


"አልሃምዱሊላህ እንጂ ምን አልደረሰብኝ "ችግር ከኔ ውጪ የሚሄድበት ያለው አይመስልም እኮ ዱኒያ ፊቷን አዙራለች መኖር አልተቻለም......ግን አልሃምዱሊላህ ስንቱን ቻልነውን።‼️ ይህ ደግሞ በነሺዳ ሲሆን አስበው እግር ባይኖርህ መሄጃ .....እኔና ኢትዮጵያን ቸግሮናል የአላህ ፈሪጅና

ዘ.ሐ


ምግብ ልሰራ ብዬ ምን መጣልኝ መሰላችሁ ፤ ስጋ ወጥ በቱና መስራት ፤ እስካሁን የሞከረው አለ ? ልስራው ወይስ?


ይህ ፅሁፍ ቡሉገል መራም እና ኡምደቱል - አህካምን በአማርኛ ትርጉም አንብበው መዝሀብ ተከታይ ሸይኾቻችንን ሲከራከሩ የነበሩ ቀርቀቦችን አስታወሰኝ ፡ እንዲህ አይነት ሰዎች አላጋጠሟችሁም ⁉️

Показано 20 последних публикаций.