TIKVAH-MAGAZINE


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን +251913134524

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


#እንድታውቁት

ከነገ መጋቢት 24 ጀምሮ የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት በየአቅራቢያው በመታወቂያ አድራሻ ሳይገደብ እንዲሰጥ መፈቀዱን የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለሥልጣን አስታውቋል።

በዚህም ተገልጋዮች በሚቀርባቸው ቅርንጫፍ ፋይላቸው ያለበት ቅርንጫፍ ሳይጠየቅ የጤና ምርመራ ሰርተፊኬትን በመያዝ የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት እንዲያገኙ መወሰኑን አመልክቷል።

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot

20.4k 0 210 20 163

በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን ያሉ የጦር ትብብሮች ቀጠናው ላይ ምን ያስከትላል?

በሱዳን በቀጠለው የእርስ በእርስ ጦርነት እየተደረጉ ያሉ የጦር አጋርነቶች ሱዳንና ደቡብ ሱዳንን ብሎም ቀጣናውን ወደ አደገኛ ነገር እንደሚመራው ባለሙያዎች እያስጠነቀቁ ነው።

የኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ ባለሙያው አለን ቦስዌል በደቡብ ሱዳን ነገሮች በዚህ የሚቀጥሉ ከሆነ የደቡብ ሱዳንን ጦርነት ከሱዳን ጦርነት ለይተን ማየት ከባድ መሆኑን ተናግሯል።

ባለፈው የካቲት የሰሜን የሱዳን ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ(SPLM-N) እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ(RSF) መካከል ትብብር መፈጠሩ ይታወሳል።

የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ(RSF) ከ2023 ጀምሮ በጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን ከሚመራው የሱዳን ጦር ጋር ጦርነት ውስጥ ሲሆን በምስራቅ እና ማዕከላዊ ሱዳን ያለውን ቁጥጥር ማጠናከር ይፈልጋል።

የሰሜን የሱዳን ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ አብድላዚዝ አልሂሉ በሚባሉ ሰው ሲመራ ሱዳን ከደቡብ ሱዳን በምትዋሰንባቸው የብሉ ናይልና ደቡብ ኮርዶፋን አካባቢዎች እንቅስቃሴ የሚያደርግና ባለፉት 10 ዓመታት ከሱዳን ጦር ጋርም እየተዋጋ የሚገኝ ነው።

የሰሜን የሱዳን ህዝቦች ንቅናቄጰ(SPLM-N) ደቡብ ሱዳንን ከሱዳን የገነጠለውን እንቅስቃሴን የመራው የሱዳን ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ(SPLM) አካል የነበረ ሲሆን የሱዳን መንግስትም እነዚህን ታጣቂዎች ሲዋጋ ቆይቷል።

ደቡብ ሱዳን ተገንጥላ ስትወጣ የብሉ ናይል እና ደቡብ ኮርዶፋን አካባቢዎች በሱዳን ውስጥ የቀሩ ሲሆን ታጣቂዎቹ ከደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ድጋፍ እየተደረገላቸውም በዚህ አካባቢ ከሱዳን መንግስት ጋር ሲዋጉ ቆይተዋል።

በዚህ ታሪካዊ ትስስር የተነሳም ጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን ሳልቫ ኪር የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉንና የሰሜን የሱዳን ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄን ይደግፋሉ ብለው እንደሚያምኑ አለን ቦስዌል ይናገራል።

ታዲያ በሁለቱ ጦሮች መሃል ስምምነት ከተደረሰ በኋላ በምላሹ በጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን የሚመራው የሱዳን ጦር የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ሁለቱን ጦሮች እንዲዋጉለት እያስታጠቀ መሆኑ ተነግሯል።

ተንታኞች የሰሜን የሱዳን ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ ከፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ጋር የተጣመረው በአንድ ጊዜ ከሱዳን ጦር እና ከፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ጋር መዋጋት ስለማይችል ነው ብለዋል።

የአብድልአዚዝ ጦር የደበብ ኮርዶፋን እና ብሉ ናይል አካባቢዎችን የተቆጣጠረ ሲሆን የደቡብ ኮርዶፋ የሱዳንን ማዕከላዊ ቦታዎች ለመቆጣጠር ከሚያስችለው ኋይት ናይል ጋር ሲዋሰን ብሉ ናይል ደግሞ ከኢትዮጵያ ጋር ይዋሰናል፤ ይህም ቦታዎቹን ስትራቴጂካዊ አድርጎታል።

እንደ አለን ቦስዌል ገለፃ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ከነፃነት ንቅናቄው ጋር መጣመሩ በቀላሉ መሳሪያዎችን ከደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ እንዲያስገባ ያግዘዋል።

አለን አክሎም ጦሩ ወደ ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ ድንበሮች ገብቶ እየወጣ የሱዳን ጦርን መዋጋት እንደሚችል ተናግሯል።

በደቡብ ሱዳን ደግሞ ከሰሞኑ በሁለቱ መሪዎች መካከል ግጭት ያለ ሲሆን የሁለቱ መሪዎች ግጭት ግን ደቡብ ሱዳን ነፃ ሃገር ከመሆኗ በፊት እንደሚጀምር ተነግሯል።

ደቡብ ሱዳን ነፃ ሳትሆን ሪክ ማቻር በወቅቱ የሱዳን ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄን ለመዋጋት እና የንቅናቄው መሪ የነበሩትን ጆን ካራንግን ለማስወገድ ከካርቱም መንግስት ድጋፍ የተቀበሉ ሲሆን በ2005 ካራንግ በሄሊኮፕተር አደጋ ሲሞቱ ሳልቫ ኪር የንቅናቄው መሪ ሆነው ብቅ አሉ።

የማቻር ጦር በአብዛኛው የኑዌር ጎሳ ሲሆን ሪሳቸውን በሳልቫ ኪር ከሚመራው ንቅናቄ ወይም SPLM ለመለየትም ስማቸው ላይ In Opposition የምትል ጨምረው SPLM-IO ብለው ስማቸውን ሰየሙት።

በአንፃሩ ሳልቫ ኪር የዲንካ ጎሳ ሲሆኑ በሁለቱ መካከልም ግጭት ተነስቶ ከ400,000 በላይ ሰዎች ህይወት አለፈ።

በዚህ ወርም በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉና በSPLM-IO መካከል ግጭት መነሳቱ ተዘግቦ የነበረ ሲሆን በብሉ ናይል ግዛቶችም ውጊያ ተደርገው እንደነበር ተዘግቧል።

አለን ቦሶዌል በደቡብ ሱዳን ያለው ውጥረት በዚሁ ከቀጠለ አብዛኞቹ ደቡብ ሱዳናዊያን የሱዳን ቅጥረኛ ተዋጊዎች እንደሚሆኑ ይናገራል። ለማሳያነትም የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ደቡብ ሱዳናዊያንን ለጦር እየመለመለ መሆኑን ተናግሯል።

አለን አክሎም ደቡብ ሱዳን ወደ እርስ በእርስ ጦርነት ከገባች ከሱዳን ጦር በላይ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ሊጠቀም እንደሚችል ተናግሯል።

ትንታኔው ሲጠቃለልም ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ እና የሰሜን የሱዳን ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄን እንደሚደግፉ ሲገመት የሱዳን ጦር በምላሹ የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎችን እያስታጠቀ ነው የሚል አንድምታ አለው።

ሱዳን ባለፉት ሁለት አመታት ከፍተኛ የተባለውን የሰብዓዊ ቀውስ ያስተናገደ የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ስትሆን ከሰሞኑ የሱዳን ጦር ዋና ከተማዋን መያዙ ሲታወስ የሱዳን የጦር አመራሮችም ደቡብ ሱዳን፣ ቻድና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉን ይደግፋሉ ብለው ሲከሱ ነበር።

በቀጣናው የሁለቱ ሃገራት የፖለቲካ ግጭቶች ውስጥ መግባት በአካባቢው ሌላ ቀውስን እንዳይፈጥርም ተሰግቷል።

Published On : Al Jazeera

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot


ትራምፕ የአሜሪካ ጦር በአፍሪካ የመኖሩ አስፈላጊነት ላይ ጥርጣሬ አላቸው ተባለ።

ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ አብዛኞቹ ሪፐብሊካን የአሜሪካ ጦር በአፍሪካ መኖርን እንደማይደግፉ እና ፔንታጎን ለምን በአፍሪካ ጦሩን እንዳሰፈረ ጥያቄ እንዳላቸው ተዘግቧል።

በአፍሪካ የአሜሪካ ጦር ማዘዣ(AFRICOM) እ.ኤ.አ በ2007 በጆርጅ ቡሽ አስተዳደር የተመሰረተ ሲሆን በአፍሪካ በተለይ በቀይ ባህር የአሜሪካን ጥቅም ለማስጠበቅ ሲሰራ ቆይቷል።

በአካባቢው የቻይናን ተፅዕኖ በመገደብ የተለያዩ የሽብር ድርጅቶችንም ላለፉት 18 አመታት ሲዋጋ መቆየቱ ይታወሳል።

አሁን ግን የAFRICOM አስፈላጊነት ላይ በፕሬዚዳንቱ ጭምር ጥያቄ መነሳቱ ምናልባት አሜሪካ በአፍሪካ ያላትን የጦር ሰራዊት እንዳታስወጣ ወይም እንዳትቀንስ የሚል ፍራቻን አዋልዷል።

ፕረዚዳንት ትራምፕ ወጪያቸውን መቀነስ እንደሚፈልጉ እና ትኩረታቸውን በኢንዶ ፓስፊክ ቀጣና ላይ ማድረግ እንደሚፈልጉ NBC የዘገበ ሲሆን በኢንዶ ፓስፊክ አካባቢ ያላቸውን ተፅዕኖ ለማሳደግም AFRICOMን በአውሮፓ ከሚገኘው የአሜሪካ ማዘዣ ጋር ሊቀላቅሉት እንደሚችሉ ተዘግቧል።

የAFRICOM ዋና አዛዥ ጀነራል ሚካኤል ላንግሊ ሃሙስ በሴኔት ፊት ቀርበው ማብራሪያ እንደሚሰጡ የሚጠበቅ ሲሆን ቀድሞ ይህ ዜና መሰማቱም ማብራሪያውን ተጠባቂ አድርጎታል ተብሏል።

በርካታ የሴኔት እና የኮንግረስ አባላት ግን ይህንን ሃሳብ እየተቃወሙ ሲሆን ሃሳቡ ወደ ውሳኔ ከተሸጋገረ ቻይና በአፍሪካ ያላትን ተፅዕኖ የምታሳድግበት ይሆናል ተብሎ ተገምቷል።

Source: The Africa Report

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot


"እናሙኛችሁ" ከሚሉ ተጠንቀቁ!

ዛሬ "አፕሪል ዘፉል" በሚል አንዳንድ ከመዝናኛነቱ ይልቅ ጉዳቱ የሚያመዝንበት ቀልድ የሚቀልዱ፤ በወላጅ ላይ ሳይቀር ይህንን ተግባር የሚፈጽሙ ሰዎች አሉ። እናንተም በዚህ ቀን "እናሞኛችሁ" በሚል ያልተገባ ቀልድ ከሚቀልዱ ትጠነቀቁ ዘንድ ይህንን መልዕክት አስተላለፍንላችሁ።

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot

27.4k 0 97 25 325

ትረፊ ያላት ነፍስ!

በማይናማር በተከሰተው በከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት ለ91 ሰዓታት በፍርስራሹ ውስጥ ተቀብራ የነበረች የ63 ዓመት ሴት ዛሬ ማለዳ ላይ በህይወት አድን ሰራተኞች ድጋፍ በህይወት ከነበረችበት ማውጣት ተችሏል።

Source: MHT

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot


በር ካልተከፈተልኝ ባለው ተሳፋሪ ምክነያት አውሮፕላኑ ወደ መነሻው ተመለሰ!

200 ሰዎችን ጭኖ ከኢንዶኔዥያ ወደ አውስትራሊያ ሲበር የነበረ አውሮፕላን ወደ መዳረሻው ሳይደርስ ተመልሷል።

አውሮፕላኑ ለመመለስ የተገደደበት ምክነንያትም ብዙዎቹን አስገርሟል።

ጀትስታር የሚባለው አየር መንገድ መነሻውን ከኢንዶኔዥያ ባሊ አድርጎ መዳረሻውን ሜልቦርን አውስትራሊያ አድርጎ ሲበር ነበር።

ታዲያ የህንድ ውቅያኖስ ላይ ሲደርስ በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበረ ተሳታፊ የአውሮፕላኑ በር ካልተከፈተ ብሎ በማስቸገሩ አውሮፕላኑ ወደ ኢንዶኔዥያ መመለሱ ተነግሯል።

አየር መንገዱ ለመንገደኞች ደህንነት ቅድሚያ ሰጣለሁ ሲል ድርጊቱን ተቀባይነት የሌለው ብሎታል።

Source: CNN‌‌

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot


#AddisAbaba

በመዲናችን አዲስ አበባ በኤሌክትሪክ የሚሠሩና የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ 100 አውቶብሶችን ወደ ሥራ መግባታቸው ተገልጿል።

በአሁኑ ጊዜ በከተማዋ በቀን ከ1ሺህ 170 በላይ የብዙሃን ትራንስፖርት አውቶብሶች አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot


ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የተውጣጡ አምራቾች እና አቅራቢዎች ምርቶቻቸውን የሚያሳዩበት የCanton Fair ፓኬጅ ይዘንላችሁ መጣን❎

ይህን Fair እንድትካፈሉ የሚረዳችሁን ፓኬጅ በ ❎❎2399 ብቻ!

ጥቅሉ
🛂የቻይና ቪዛን
🏝7 ቀን አዳር
✈️የደርሶ መልስ የጉዞ ቲኬት
🏨የባለ 5 ኮኮብ ሆቴል ማረፊያ ያጠቃልላል።

የሚደረገውም April 13 - April 22 2025 ድረስ ስለሆነ ሳትቀደሙ ቦታችሁን ያዙ።

ለበለጠ መረጃ 📞0935997964
/ 0946620169 / 0913203138 ደውለው ሊያገኙን ይችላሉ!


#ትኩረት 📣

በትግራይና በአማራ ክልል የዋግኽምራ ዞን አዋሳኝ ተራራ በሆነው "እምባነዋይ ተራራ" ላይ ከቀኑ 7:00 ጀምሮ እስከ አሁን ያልጠፋ እሳት መከሰቱን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ  ገልጸዋል።

በዚህ ተራራ ተራራ ከዛሬ በፊት ተደጋጋሚ ቃጠሎ ቢያጋጥም የዛሬው ቀን ሃይለኛ እና ለረጅም ሰዓታት የቆየ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ነዋሪዎቹ ቃጠሎው ለመቆጣጠር ከአቅማቸው በላይ መሆኑ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደርና የፌደራል መንግስት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

ተራራው ረጅም መሆኑንና ዙሪያው በጥቅጥቅ ደኖች የተሞላ ነው። ተራራው ከነብር ጀምሮ ሌሎች የዱር እንስሳት እንደሚገኙበት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

(ሁኔታውን ተከታትለን የምናሳውቃችሁ ይሆናል።)

#TikvahEthiopiaFamliyMekelle

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot


የኬንያ መንግስት በማይናማር እና ታይላንድ ለሚኖሩ ዜጎች ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

የኬንያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው በመሬት መንቀጥቀጡ ዜጎቻቸውን ካጡት ማይናማር እና ታይላንድ ጎን እንደሚቆም አስታውቋል።

ሚኒስቴሩ በማይናማር ያሉ የኬንያ ዜጎች ደህንነት እንዳሳሰበውም ገልጿል።

በመሬት መንቀጥቀጡ በተጠቁ አካባቢዎች የሚኖሩ የኬንያ ዜጎችም ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎችን በአግባቡ እንዲከታተሉ ከማሳሰቡ በተጨማሪ ኬንያ ለጊዜው ዜጎቿ አላስፈላጊ ጉዞዎችን እንዳያደርጉ አስጠንቅቃለች።

የኬንያ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ጨምሮም በሃገራቱ የሚኖሩ ዜጎቹ ካልተመዘገቡ በባንኮክ በሚገኘው የኬንያ ኤምባሲ እና የምስራቅ አፍሪካ ማዕበረሰብ ዲፕሎማቲክ ተልዕኮ መረጃቸውን ማስመዘገብ እንዳለባቸው ያሳሰበ ሲሆን ለዚህም የሚሆን የኢሜል እና የስልክ አድራሻን አስቀምጧል።

የኬንያ መንግስት አክሎም ዜጎች ከአመራሮች የሚሰጠውን መመሪያ እንዲተገብሩ አሳስቦ ለዜጎቹ እርስ በእርሳቸው በተለይም ተማሪዎችን እና አቅም የሌላቸውን የሃገራቸውን ሰዎች እንዲያዩ እና እንዲደጋገፉ ጥሪ አቅርቧል።

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot


በደቡብ ሱዳን የተከሰተው ግጭት እና ኮሌራ ምዕራብ ኢትዮጵያ ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ መሆኑ ተገለፀ።

በደቡብ ሱዳን የተከሰተው ግጭት፣ መፈናቀል እና የተስፋፋው የኮሌራ በሽታ በደቡብ ሱዳን እና ኢትዮጵያ ድንበር አካባቢዎች ከፍተኛ የሆነ የሰብዓዊ ቀውስ እያደረሰ እንደሆነ ድንበር የለሽ የሃኪሞች ቡድን(MSF)አስታውቋል።

ቡድኑ በጋምቤላ ክልል ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከመጋቢት ወር ጀምሮ ለ560 የኮሌራ በሽታ ተጠቂዎች ህክምና ማድረጉን አስታውቋል።

በደቡብ ሱዳን የላይኛው ናስር ክልል ግጭት መቀስቀሱ የሚታወስ ሲሆን የግጭቱ ዳፋ ለኢትዮጵያ መትረፉን አንስቷል።

ተመድ በደቡብ ሱዳን ግጭት ከተከሰተ በኋላ ከ10,000 በላይ ሰዎች ተፈናቅለው ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን አስታውቋል።

የቡድኑ የደቡብ ሱዳን ተልዕኮ መሪ ዛካሪያ ምዋቲያ ግጭቱ እንዴት ኮሌራን እንዳስፋፋው እየተመለከትን ነው ያሉ ሲሆን ግጭቱ ከቀጠለ ሃገሪቷን ወደለየለት የሰብዓዊ ቀውስ እንደሚከታት ተናግረዋል።

በላይኛው የናይል ግዛት የተቀሰቀሰው የኮሌራ በሽታ ወደ ደቡብ ሱዳን ሌሎች ግዛቶች እየተንሰራፋ ከመሆኑ በተጨማሪ ወደ ኢትዮጵያ ጋምቤላ ክልልም መግባቱ ተነግሯል።

ከመጋቢት ወር ጀምሮ የMSF አባላት ከ1000 በላይ የኮሌራ ተጠቂዎችን ያከሙ ሲሆን ከ30 በላይ በግጭቱ የተጎዱ ሰዎችንም በደቡብ ሱዳን አክመዋል።

በሁለቱ ሃገራት ድንበር ያጋጠመው ቀውስ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) የእርዳታ መቋረጥ ጨምሮ ከፍተኛ የእርዳታ ችግር እንዳጋጠመው ተዘግቧል።

የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) እርዳታውን ካቆመ በኋላ በርካታ ተንቀሳቃሽ ክሊኒኮች መዘጋታቸውንም ዛካሪያ ምዋቲያ ተናግረዋል።

ደቡብ ሱዳን ጠንካራ የጤና ስርዓት እንደሌላት የተነገረ ሲሆን ከሱዳን በጦርነቱ ምክንያት ተፈናቅለው የመጡ 1 ሚሊየን ሰዎች የጤና ሥርዓቷ ላይም ጫና መፍጠራቸው ተዘግቧል።

በደቡብ ሱዳን እና ኢትዮጵያ ለተከሰተው የጤና ቀውስ ለጋሾች አስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርጉም ቡድኑ ጠይቋል።

#MSF #Gambella #SouthSudan

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot


ግብፅ ከደቡብ ኮሪያ 100 FA-50 የተሰኙ የጦር አውሮፕላኖችን ልትገዛ ነው።

በሴኡል የግብፅ አምባሳደር የሆኑት ካሊድ አብድራህማን ሀገሪቱ ከደቡብ ኮሪያ ለምትገጻው የጦር አውሮፕላን ድርድሩ በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በዚህም ግብፅ በመጀመሪያው ዙርም 36 የጦር አውሮፕላኖችን እንደምትረከብ ይጠበቃል።

FA-50 የተሰኘው የጦር አውሮፕላን በሰዓት እስከ 1800 ኪሎሜትሮችን መጓዝ እንደሚችል የተነገረ ሲሆን ግዢው የግብፅን ወታደራዊ አቅም ለማሳደግ ታቅዶ እንደሆነ ተገልጿል።

Source: The Defense post

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot

20k 0 6 23 62

ሰርቢያ ከኬንያ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋረጠች።

የሰርቢያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ኬንያ ለኮሶቮ የሰጠችው የሃገር ዕውቅናን ተቃውሟል።

በ2008 ከሰርቢያ ነፃ የወጣችው ኮሶቮ አሜሪካን ጨምሮ በብዙ ሃገራት ዕውቅናን ያገኘች ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጨምሮ በሃያላኑ ሩሲያ እና ቻይና ዕውቅናን አላገኘችም።

የሰርቢያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር በጉዳዩ ላይ መግለጫ ያወጣ ሲሆን የዊሊያም ሩቶ መንግስት የግዛት አንድነትን የሚደግፈውን የተመድ ቻርተር ጥሰዋል ያለ ሲሆን ሰርቢያ ከኬንያ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማቋረጧንም አስታውቀዋል።

ሰርቢያ ጨምራም ኬንያ የአለም አቀፍን ህግ ጥሳለች ያለች ሲሆን ተገቢው የፖለቲካ እና ዲፕሎማሲ እርምጃም እወስዳለሁ ብላለች። በተጨማሪ የግዛት አንድነቷን ለመጠበቅ ማንኛውንም ነገር እንደምታደርግ አስታውቃለች።

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot


#Update 🇸🇸

የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር የሆኑት መሐመድ ዩሱፍ የደቡብ ሱዳንን ውጥረት ለማርገብ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ከፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ጋር ተወያይተዋል።

የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበሩ በቀጣይ ለሰላም ተልዕኮ ከህብረቱ ተወካዮች የተወጣጣ ከፍተኛ ቡድን ወደ ጁባ እንደሚልኩ የገለፁ ሲሆን እነማን እንደሚላኩ ግን ይፋ አልሆነም።

የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር መሐመድ ዩሱፍ ከሳልቫ ኪር ጋር  በደቡብ ሱዳን ያለውን ውጥረት ለማርገብ የውይይት አስፈላጊነት ላይ መምከራቸውም ተነግሯል።

የህብረቱ ሊቀመንበር እና ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ውይይት የተደረገው ለሰላም ተልዕኮ ወደ ጁባ አምርተው የነበሩት ራይላ ኦዲንጋ ከሪክ ማቻር ጋር ተገናኝተው እንዳያወሩ መከልከላቸውን ካሳወቁ በኋላ ነው ተብሏል።

ራይላ ኦዲንጋ ሪክ ማቻር ከከፍተኛ የጦር መሪ ግድያ ጋር በተያያዘ ምርመራ ላይ እንደሆኑ በደቡብ ሱዳን የመንግስት አካላት እንደተነገራቸው አሳውቀው ነበር።

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot


"ከሰኞ ጀምሮ የተሰበሰበ በእጄ ያለው 40 ሺ ብር ነው፤ እነሱ የጠየቁኝ 1 ሚሊየን 275ሺሕ ብር ነው"- ወንድሙ በሊቢያ ታግቶ ያለ ቤተሰብ

በወላይታ ዞን ኪንዶ ዳዳዬ ወረዳ ቦሳ ማንከራ ቀበሌ ተወልዶ ያደገ የ19 አመት ወጣት ነው፤ በደላሎች የማይጨበጥ ተስፋ ተታሎ ካደገበት ቀዬ ጥር ወር 2017ዓ/ም በሱዳን በረሀ አቋርጦ የተሰደደው።

የታጋች ወንድም  " በሕገ-ወጥ ደላላዎች ነው የሄደው፣ ከሀገር ከወጣችሁ በኋላ የ3 ወር ደመወዛችሁን በኛ አካውንት ይገባል፤ ከዛ በኋላ ለእናንተ ትሰራላችሁ ተብሎ ነው የሄድነው" ሲል ስለ ሁኔታው ይናገራል።

"ቤተሰቦቻችንም የተጠየቅነው ገንዘብ ከአቅማቸው በላይ ስለሆነ ለፈጣሪ ሰጥው እያለቀሱ ነው" ያለው ወንድሙ አብሮት የተጓዙ 17 ኢትዮጵያያን ወጣቶችም አብረውት እንደሚገኙ እንደነገረውና አሁን ያሉትም በሊቢያ በረሃ መሆኑን ገልጾልናል።

" በየቀኑ በኢሞ እና ቁጥሩ በማይታይ ስልክ ይደውሉልኛል፣ ቶሎ ብሩን አስገቡ የሉኛል፣ ከየት ላምጣው እኔ፣ ወንድሜም ሳልሞት አድነኝ ታላቄ እያለ ያለቅሳል፣ እኔም አልቻልኩም ይላል" በተሰበረ ልብ በእንባ ታጅቦ።

በወላይታ ዞን ካኦ ኮይሻ ወረዳ ግብርና ቢሮ ውስጥ የሳይት ባለሙያ ነኝ የሚለው ወንድሙ "በሚከፈለኝ ደመወዝ ወንድሜን ከአጋቾቹ ማስለቀቅ አልችልም፣ በየቀኑ እኔን ነው ብር፣ ብር የሚሉኝ፣ ቤተሰቦቻችን አዘነው ከመቀመጥ ውጭ ምንም ማድረግ አልቻሉም።" ይላል።

አብረውት የተሰደዱት 17 ኢትዮጵያዊያን መታገታቸው ነግሮኛል፣ ሁሉም በተመሳሳይ ሲቃይ ውስጥ ናቸው፣ ምግብ አይሰጡንም ይለኛል በየቀኑ፣ የሚላክልኝ ቪዲዮ አሸዋ ላይ አድርገው እየገረፉ ነው፣ ብቻ ማልቀስ ነው ሲል ተናግሯል።

"ወንድሜን ደላሎች አታለው ነው የወሰዱት፣ በየሰዓቱ ይደውሉ እና ስንት ብር ሰበሰባችሁ ይሉኛል፣ ለምኑ እና ላኩ ይላሉ፣ የደወሉበትን ስልክ አይታይም፣ የሚያወሩትም በአማረኛ ነው፣ የደወሉበትን ስልክ ለቴሌ ሳሳያቸው ማን እንደሆኑ ማወቅ አንችልም ይሉኛል፣ ምን እንደማደርግ ግራ ገብቶኛል" ይላል ለመግለጽ እንባ እየተናነቀው።

እኔ የምሰሪው በመንግስት ቢሮ ውስጥ ነው፣ አሁን ስራየን አቁሜ የወንድሜን ህይወት ለማትረፍ የኢትዮጵያን ህዝብ እየለመንኩ ነው የሚለው ወንድሙ ነገር ግን ከተጠየቀው ብር መሰብሰብ የቻለው 40 ሺ ብር እንደሆነ ይጠቅሳል።

መርዳት ለምትሹ 1000265370024 አቶ አብርሃም አካንቴ ጉተማ የንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር ነው። አቶ አብርሃምን በዚህ ስልክ 0987343207 ማግኘት ይቻላል።

(📹 18.2 MB )

#ConceptHubEthiopia

@Tikvahethmagazine @Concepthubeth


በማይናማር ብሔራዊ የኃዘን ቀን ታወጀ!

በማይናሜር በአደጋው ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር ከ2000 ተሻግሯል። 3,900 የሚሆኑት ደግሞ ጉዳት እንደደረሰባቸው ሪፖርት ተደርጓል።

የማይናሜር ወታደራዊ አገዛዝ ከዛሬ ጀምሮ በሀገሪቱ ለሳምንት የሚቆይ የብሔራዊ የሃዘን ቀን አውጇል።

የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች አሁንም የነፍስ አድን ሥራውን የቀጠሉ ሲሆን የመሬት መንቀጥቀጡ ከተከሰተ 60 ሰዓታት በኋላ አንዲት ሴት ከፍርስራሽ ውስጥ በህይወት መገኘት ችላለች።

ሴትየዋን በህይወት ያወጡት የቻይና የነፍስ አድን ሰራተኞች ሲሆኑ ፍለጋውም 5 ሰዓታትን የፈጀ ነበር ተብሏል።

ቻይና፣ ራሺያ፣ ህንድ፣ ማሌዥያ፣ ፊሊፒንስ፣ ታይላንድ፣ ቬትናም፣ ታይዋን እስካሁን የነፍስ አድን ሰራተኞቻቸውን ወደ ማይናማር የላኩ ሀገራት ናቸው።

የመሬት መንቀጥቀጡ ጉዳት ያደረሰባት ሌላኛዋ ታይላንድ ደግሞ በአደጋው 19 ዜጎቿን ህይወት አጥታለች።

📹 ከላይ የተያያዙት ቪዲዮዎች የመሬት መንቀጥቀጡ ያደረሰውን ጉዳት የሚያሳዩ ናቸው። በተጨማሪም አደጋው ከመድረሱ በፊትና በኋላ ያለውን ልዩነት የሚያሳዩ ናቸው።

@Tikvahethmagazine @tikvahmagbot

Показано 16 последних публикаций.