#Premiereleague 🏴
በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐግብር ማንችስተር ሲቲ ፣ ቼልሲ እና ሊቨርፑል ጨዋታዎቻቸውን በአቻ ውጤት አጠናቀዋል።
የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ከኖቲንግሀም ፎረስት ጋር ያደረገውን ተጠባቂ የሊግ ጨዋታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቋል።
የኖቲንግሀምን ግብ ክሪስ ውድ ሲያስቆጥር ዲያጎ ጆታ ሊቨርፑልን አቻ አድርጓል።
ማንችስተር ሲቲ በበኩሉ ከብሬንትፎርድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2ለ2 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።
የማንችስተር ሲቲን ግቦች ፊል ፎደን 2x ሲያስቆጥር ለብሬንትፎርድ ዊሳ እና ኖርጋርድ ከመረብ አሳርፏል።
ቼልሲ ከበርንማውዝ ያደረገውን ጨዋታ 2ለ2 በሆነ አቻ ውጤት ማጠናቀቅ ችለዋል።
የሰማያዊዎቹን ግብ ኮል ፓልመር እና ሬስ ጄምስ ሲያስቆጥሩ ክላይቨርት እና ሴሜኒኖ ለበርንማዝ ከመረብ አሳርፈዋል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
1️⃣ ሊቨርፑል :- 47 ነጥብ
2️⃣ ኖቲንግሀም ፎረስት :- 41 ነጥብ
4️⃣ ቼልሲ :- 37 ነጥብ
6️⃣ ማንችስተር ሲቲ :- 35 ነጥብ
ቀጣይ መርሐግብር ?
⏩ ቅዳሜ - ብሬንትፎርድ ከ ሊቨርፑል
⏩ እሁድ - ኢፕስዊች ታውን ከ ማንችስተር ሲቲ
⏩ ሰኞ - ቼልሲ ከ ዎልቭስ
@tikvahethsport @kidusyoftahe