“ ለባሎን ዶር ሽልማት ያልሄድኩት ክለቡ አትሂድ ስላለኝ ነው “ ቪንሰስ
⏩ “ የአመቱ ወሳኝ ወቅት ላይ ደርሰናል "
የሎስ ብላንኮዎቹ የፊት መስመር ተጨዋች ቪንሰስ ጁኒየር ከነገው የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ በፊት ከጋዜጠኞች ጋር ቆይታ አድርጓል።
ቪንሰስ ጁኒየር በቆይታው ወቅት " ወደፊት ከሪያል ማድሪድ ጋር ባሎን ዶር እንዲሁም በርካታ ዋንጫዎች የማሸነፍ እድሉ አለኝ “ ብሏል።
ቪንሰስ ጁኒየር ምን አለ ?
- " ሪያል ማድሪድ ውስጥ በርካታ ታሪኮችን መፃፍ እና የክለቡ ታሪካዊ ተጨዋች መሆን እፈልጋለሁ።
- በሪያል ማድሪድ ቤት ለተጨማሪ አመታት ውሌን እስከማራዝም በጉጉት እየጠበቅኩ ነው።
- ወደፊት ባሎን ዶር የማሸነፍ እድሎች ይኖረኛል ፤ ወደ ዝግጅቱ ያልሄድኩት ክለቤ እንዳልሄድ ስለጠየቀኝ ነው።
- ነገ ጥሩ ጨዋታ ለማድረግ ጓጉቻለሁ ፤ የውድድር ዘመኑ ወሳኝ ወቅት አሁን ጀምሯል ሁልጊዜም በተሻለ መመጫወት አለብን።
" ሁልጊዜም ብስጭት ውስጥ የምገባው ቅሬታ ሳቀርብ የማስጠንቀቂያ ካርድ ስመለከት ነው ማሻሻል አለብኝ ገና 24ዓመቴ ነው ብዙ ነገሮች መማር አለብኝ።" ብሏል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe