Фильтр публикаций


ናታን አኬ ቀዶ ጥገና አድርጓል !

የማንችስተር ሲቲው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋቹ ናታን አኬ በጉዳቱ ምክንያት ቀዶ ጥገና ማድረጉን በማህበራዊ ትስስር ገፁ አሳውቋል።

ተጨዋቹ ማንችስተር ሲቲ ከቀናት በፊት ፕሌይ ማውዝን ባሸነፈበት ምሽት ጉዳት አስተናግዶ ተቀይሮ መውጣቱ አይዘነጋም።

አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ከጨዋታው በኋላ ናታን አኬ  ለረጅም ጊዜ ከሜዳ እንደሚርቅ ተናግረው ነበር።

አሁን ላይ ናታን አኬ ከጉዳቱ አገግሞ ወደ ሜዳ ለመመለስ ወራት እንደሚወስዱበት ተገልጿል።

@Tikvahethsport   @kidusyoftahe


አርሰናል ሀላፊ ለመሾም ተቃርቧል !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በኤዱ ጋስፐር ምትክ አዲስ ስፖርቲንግ ዳይሬክተር ለመሾም መቃረቡ ተገልጿል።

መድፈኞቹ የቀድሞውን የአትሌቲኮ ማድሪድ ስፖርቲንግ ዳይሬክተር አንድሬ ቤርታ ለመሾም መቃረባቸው ተነግሯል።

በአለም እግርኳስ ውስጥ ስማቸው በጉልህ የሚነሳው አንድሬ ቤርታ ከኤሲ ሚላን ጥያቄ ቀርቦላቸው ለአርሰናል ቅድሚያ መስጠታቸው ተገልጿል።

ጣልያናዊው ስፖርቲንግ ዳይሬክተር አንድሬ ቤርታ በአትሌቲኮ ማድሪድ ቤት ከአሰልጣኝ ዲያጎ ሲሞኒ ጋር ለአስራ ሁለት አመታት የሰሩ ናቸው።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


የማድሪድ የወሩ ምርጥ ተጨዋች ታውቋል !

በአሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ የሚሰለጥነው የላሊጋው ክለብ ሪያል ማድሪድ የወርሀ የካቲት የወሩ ምርጥ ተጨዋቻቸውን ይፋ አድርገዋል።

በዚህም መሰረት ሞሮኳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ብራሂም ዲያዝ የወርሀ የካቲት የሪያል ማድሪድ የወሩ ምርጥ ተጨዋች በመሆን መመረጥ ችሏል።

ብራሂም ዲያዝ በወሩ ባደረጋቸው ጨዋታዎች ሁለት ግቦችን አስቆጥሮ አንድ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።

@tikvahethsport              @kidusyoftahe


“ ዋንጫውን ከፈለግን ጠንካሮቹን መግጠም አለብን “ አንቾሎቲ

የሎስ ብላኮዎቹ ዋና አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ ከነገው የሻምፒየንስ ሊግ የማድሪድ ደርቢ ጨዋታ በፊት አሰተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አንቾሎቲ ካነሷቸው ሃሳቦች መካከልም :-

- " ማንችስተር ሲቲ ላይ በሜዳችን ያደረግነውን ነገር ነገ አትሌቲኮ ማድሪድ ላይ መድገም እንፈልጋለን የተለየ ነበር ያደረግነው።

- ፌዴሪኮ ቫልቬርዴ አብሮን ልምምድ ሰርቷል በጨዋታው መሰለፍ አለመሰለፉን አይተን የምንወስን ይሆናል።

- በመጨረሻው ጨዋታ እረፍት የተሰጣቸው አሴንስዮ እና ካማቪንጋ በነገው ጨዋታ የመጫወት እድል ይሰጣቸዋል።

- ፌዴ ቫልቬርዴ የማይጫወት ከሆነ ሉካስ ቫስኩዌስ የቀኝ መስመር ተጨዋች ቦታ ተሰልፎ ይጫወታል።

- በሻምፒየንስ ሊጉ ድልድል እድለኛ አልነበርንም ነገርግን ለዋንጫው መፎካከር ከፈለግክ ጠንካሮቹን መግጠም አለብህ።" ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ አርሰናልን የማሸነፍ ትልቅ እድል አለን “ ፔርሲች

የፒኤስቪው የፊት መስመር ተጨዋች ኢቫን ፔርሲች ቡድናቸው ነገ አርሰናልን የማሸነፍ እድል እንዳለው ገልጿል።

ነገ ምሽት “ አርሰናልን የማሸነፍ ትልቅ እድል እንዳለን አውቃለሁ “ ሲል ኢቫን ፔርሲች ከጨዋታው በፊት በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።

“ አርሰናል ምርጥ ቡድን ነው “ የሚለው ፔርሲች ወጣት ቡድን ነው ምርጥ አሰልጣኝም አላቸው ነገርግን ባለፉት አመታት ዋንጫ ለማንሳት የሚረዳቸው ነገር አጥተው ነበር ብሏል።

ፒኤስቪ ነገ ምሽት 5:00 ሰዓት የመጀመሪያ ዙር የሻምፒየንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ጨዋታውን ከአርሰናል ጋር በሜዳው ያደርጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ ለባሎን ዶር ሽልማት ያልሄድኩት ክለቡ አትሂድ ስላለኝ ነው “ ቪንሰስ

⏩ “ የአመቱ ወሳኝ ወቅት ላይ ደርሰናል "

የሎስ ብላንኮዎቹ የፊት መስመር ተጨዋች ቪንሰስ ጁኒየር ከነገው የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ በፊት ከጋዜጠኞች ጋር ቆይታ አድርጓል።

ቪንሰስ ጁኒየር በቆይታው ወቅት " ወደፊት ከሪያል ማድሪድ ጋር ባሎን ዶር እንዲሁም በርካታ ዋንጫዎች የማሸነፍ እድሉ አለኝ “ ብሏል።

ቪንሰስ ጁኒየር ምን አለ ?

- " ሪያል ማድሪድ ውስጥ በርካታ ታሪኮችን መፃፍ እና የክለቡ ታሪካዊ ተጨዋች መሆን እፈልጋለሁ።

- በሪያል ማድሪድ ቤት ለተጨማሪ አመታት ውሌን እስከማራዝም በጉጉት እየጠበቅኩ ነው።

- ወደፊት ባሎን ዶር የማሸነፍ እድሎች ይኖረኛል ፤ ወደ ዝግጅቱ ያልሄድኩት ክለቤ እንዳልሄድ ስለጠየቀኝ ነው።

- ነገ ጥሩ ጨዋታ ለማድረግ ጓጉቻለሁ ፤ የውድድር ዘመኑ ወሳኝ ወቅት አሁን ጀምሯል ሁልጊዜም በተሻለ መመጫወት አለብን።

" ሁልጊዜም ብስጭት ውስጥ የምገባው ቅሬታ ሳቀርብ የማስጠንቀቂያ ካርድ ስመለከት ነው ማሻሻል አለብኝ ገና 24ዓመቴ ነው ብዙ ነገሮች መማር አለብኝ።" ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


አርሰናል ከሩዋንዳ ጋር ያለውን ውል ያራዝማል ?

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ከሩዋንዳ ጋር ያለው የማልያ ላይ አጋርነት ውል ስምምነት በአመቱ መጨረሻ ሲጠናቀቅ ላለማራዘም በማሰብ ላይ መሆናቸው ተገልጿል።

መድፈኞቹ ከ “ Visit Rwanda “ ጋር ለአመታት የዘለቀ የቱሪዝም አጋርነት እንደነበራቸው ይታወቃል።

አርሰናል የውል ስምምነቱን ላለማራዘም ካሳሰባቸው ምክንያቶች ኮንጎ በቅርቡ ከስምምነቱ ጋር በተያያዘ ያቀረበችው ቅሬታ አንዱ መሆኑ ተገልጿል።

ዲሞክራቲክ ኮንጎ በቅርቡ በሩዋንዳ የሚደገፉ ታጣቂዎች በሀገሪቱ ግጭት በመቀስቀስ ለበርካቶች መሞት ምክንያት ሆነዋል በሚል ነው ቅሬታ ያቀረበችው።

ዲሞክራቲክ ኮንጎ ለአርሰናል እና ክለቡ ባለቤቶች በላከችው ደብዳቤም “ ይህንን በደም የጨቀየ ስምምነት ቅደዱ “ ብላ ነበር።

መድፈኞቹ አሁን ላይ የተሻለ ገንዘብ የሚያስገኝላቸውን እና ቅሬታ የማያስነሱ ስምምነቶችን ለመፈፀም በማፈላለግ ላይ መሆናቸውን ዴይሊ ሜል ዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


Репост из: Betika Ethiopia Official Channel
አሸናፊዎች እነሆ!
እንደተለመደው ደንበኞቻችን ማሸነፋቸውን ቀጥለዋል።
ተራው የእርስዎ ነው !
አሁኑኑ Betika.et ላይ ይወራረዱ!
ቤቲካ የአሸናፊዎች ቤት!


ኬንያ በይፋ አሰልጣኝ ሾመች !

የኬንያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞውን የማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ቡድን አባል ቤኒ ማካርቲ በሀላፊነት መሾሙን በይፋ አስታውቋል።

ደቡብ አፍሪካዊው አሰልጣኝ ቤኒ ማካርቲ የሀራምቤ ኮከቦቹን ከደቂቃዎች በፊት በይፋ ተረክበዋል።

አሰልጣኝ ቤኒ ማካርቲ ኬንያን እየመሩ ከሶስት ሳምንታት በኋላ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ከጋምቢያ ጋር የሚያደርጉ ይሆናል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe


“ ያለንን ጥንካሬ እናውቃለን “ ዲያጎ ሲሞኒ

የአትሌቲኮ ማድሪዱ ዋና አሰልጣኝ ዲያጎ ሲሞኒ በነገው የሪያል ማድሪድ የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ የማሸነፍ እድል ይኖረናል በማለት ተናግረዋል።

“ አስቸጋሪ ቡድን እንደምንገጥም እናውቃለን “ የሚሉት ዲያጎ ሲሞኒ ነገርግን እኛም ያለንን ጥንካሬ እናውቃለን ነገ በምርጥ አቋማችን እንፋለማለን “ ብለዋል።

“ ሪያል ማድሪድ በሻምፒየንስ ሊግ ያለው ታሪክ የሚደንቅ ነበር ነገርግን ነገ በእርግጠኝነት እድሉ ይኖረናል ፤  ጨዋታውን እነሱን ወደምንጎዳበት ቦታ መውሰድ እንፈልጋለን።“ ዲያጎ ሲሞኒ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ የራሽፎርድ ችሎታ የተለየ ነው " ኡናይ ኤምሬ

የአስቶን ቪላው ዋና አሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ ማርከስ ራሽፎርድ አሁንም ድንቅ የሚባል ብቃት እንዳለው ገልፀዋል።

“ ራሽፎርድ ማንችስተር ዩናይትድን ለምን እንደለቀቀ ማወቅ አልፈልግም ነገርግን እሱ እዚህ በመሆኑ በጣም ደስተኛ ነኝ “ ሲሉ ኡናይ ኤምሬ ተናግረዋል።

አሰልጣኙ አክለውም “ ማርከስ ራሽፎርድ ያለው አቅም እና ችሎታ አሁንም ልዩ ነው “ ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


ኢንተር ሚላን ተጫዋቹን በጉዳት አጣ !

ኢንተር ሚላን ወሳኝ የግራ መስመር ተጨዋቹ ፌዴሪኮ ዲማርኮን በጡንቻ ጉዳት ምክንያት ማጣታቸው ተገልጿል።

ጣልያናዊው ሁለገብ ተጨዋች ፌዴሪኮ ዲማርኮ ኢንተር ሚላን ከናፖሊ አቻ በተለያዩበት ጨዋታ በጉዳት ተቀይሮ መውጣቱ አይዘነጋም።

አሁን ላይ ፌዴሪኮ ዲማርኮ ኢንተር ሚላን በሳምንቱ አጋማሽ ከፌይኖርድ ጋር ከሚያደርገው የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ውጪ መሆኑ ተገልጿል።

በተጨማሪ ተጨዋቹ ለሚቀጥሉት ሶስት ሳምንታት ለቡድኑ ግልጋሎት መስጠት እንደማይችል ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ ለፔሬዝ ቅርብ መሆን እፈልጋለሁ “ ቤንዜማ

ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ካሪም ቤንዜማ ጫማውን ከሰቀለ በኋላ ለሪያል ማድሪዱ ፕሬዝዳንት ፍሎራንቲኖ ፔሬዝ ቅርብ መሆን እንደሚፈልግ ተናግሯል።

ጫማውን ከሰቀለ በኋላ ወደ አሰልጣኝነት ይመጣ እንደሆነ የተጠየቀው ቤንዜማ “ አሰልጣኝ መሆን ተጨዋች ከመሆን የበለጠ አስቸጋሪ ነው አላውቅም “ ብሏል።

ለሪያል ማድሪዱ ፕሬዝዳንት ፍሎራንቲኖ ፔሬዝ ትልቅ ቦታ እንዳለው የገለፀው ቤንዘማ “ ጫማዬን ስሰቅል ለፔሬዝ ቅርብ መሆን እፈልጋለሁ “ ሲል ተደምጧል።

“ ማድሪድን ለመልቀቅ ስወስን መጀመሪያ የደወልኩት ለፔሬዝ ነው እሱ በውሳኔው ደስተኛ አልነበረም ነገርግን ቪኒሰስ እና ሮድሪጎ ዝግጁ መሆናቸውን ነግሬ አስረድቼዋለሁ “ ቤንዜማ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


Репост из: WANAW SPORT WEAR
#wanaw_x_Tigray_Football_Federation🏆

1️⃣2️⃣2️⃣ ቡድኖች!2️⃣7️⃣9️⃣! ግጥሚያዎች:: አጎጊ ፍልሚያዎች! የመላው ትግራይ እግር ኳስ ዋንጫ እና የአንበሳ እግር ኳስ ዋንጫ እንደገና ተመልሷል! ሁሌም እንደተለመደው ዋናው የስፖርት አልባሳት ብራንድም ለጨዋታው የጀርባ አጥንት ነው::

⚡️በልዩ ጥራት ለክለቦች ከቅናሽ ጋር ተዘጋጅቷል!
ለመላው የትግራይ ዋንጫ እና አንበሳ ዋንጫ እግር ኳስ ክለቦች በሚቀጥሉት 15 ቀናት ውስጥ የስፖርት ትጥቃቸውን እና የዋናውን ምርቶች ከዋናው ሲያዙ የ5⃣% ቅናሽ ያገኛሉ! እንዳያመልጥዎት።
⭐️⭐️⭐️
ዋናው ስፖርትም የዚህ ታላቅ ዝግጅት የመጀመሪያ ደረጃ ስፖንሰር ስለሆነ ክብር ይሰማዋል!
🔥🔥🔥🔥ዋናው ንቕድሚት🔥🔥🔥🔥

📞 አሁን ይዘዙ እና 5% ወጪዎትን ይቆጥቡ
8️⃣2️⃣8️⃣9️⃣
+251901138283

🔗 ማህበራዊ ገጾቻችን🔗
Instagram|Facebook |TikTok |X|Youtube
🌎በአፍሪካውያን የተመረተ 🌎


Can PlayStation

PlayStation 4 Slim Packed በ 39,000ብር ብቻ

ብዛት አቅርበናል
ለክፍለ ሀገር እናቀርባለን ይደውሉ

1  jestic
Packed Brand New
Full accessories
1 year warranty without Power supply

🤝Tanks for choice

አድራሻ፦
ቁጥር 1  መገናኛ ሱቅ የአድራሻ ለውጥ በቅርቡ ስለምናደርግ ከመምጣቶ በፊት አስቀድመው ይደውሉ
   
ቁጥር 2   ቦሌ Celavi burger አጠገብ ዘንባባ ህንፃ  ምድር ላይ


ስልክ፦ 0910529770 ወይም                  0977349492
0914646972  ይደውሉ

ለአዳዲስ መረጃ Telegram channel join ይበሉ ፦
https://t.me/CanPlaystation

                       👍Update Your Life


“ እኔ የዋህ አይደለሁም “ ሩበን አሞሪም

የማንችስተር ዩናይትዱ ዋና አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም “ እኔ የዋህ አይደለሁም “ ሲሉ ዋይን ሩኒ ለሰጠው አስተያየት ምላሽ ሰጥተዋል።

ዋይን ሩኒ ከምሽቱ ጨዋታ በኋላ ሩበን አሞሪም ዋናው አላማችን ሊጉን ማሸነፍ ነው ማለታቸውን በዚህ ሁኔታ ይሄን ማሰብ የዋህነት ነው ሲል ገልፆ ነበር።

“ እኔ የዋህ አይደለሁም “ ሲሉ ምላሽ የሰጡት ሩበን አሞሪም ለዚህም ነው በ 40ዓመቴ ማንችስተር ዩናይትድን የማሰለጥነው ብለዋል።

“ አላማችን ሊጉ ነው ምናልባት ከእኔ ጋርም ላይሆን ይችላል ፤ የክለቡም ሆነ ቦርዱ አላማ የቀድሞው የዋንጫ አሸናፊነት መመለስ ነው “ አሞሪም

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


ሮድሪ መቼ ወደ ሜዳ ይመለሳል ?

የማንችስተር ሲቲው ወሳኝ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሮድሪ በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አረጋግጠዋል።

“ ሮድሪ በጥሩ ሁኔታ ላይ ነው “ ያሉት ፔፕ ጋርዲዮላ በፍጥነት ያገግማል ብለው እንዳልጠበቁ ገልጸዋል።

ምናልባት የውድድር አመቱ ሳይጠናቀቅ ወደ ሜዳ ሊመለስ እንደሚችል ያስረዱት ጋርዲዮላ “ በአለም ክለቦች ዋንጫ ከእኛ ጋር ይጫወታል “ ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ ሊጉን ለማሸነፍ ጥሩ የፋይናንስ ሁኔታ ያስፈልጋል “ ሩኒ

⏩ “ ተጨዋች ብሆን ለዩናይትድ አልፈርምም “

የቀድሞ የቀያይ ሴጣኖቹ ተጨዋች ዋይን ሩኒ ማንችስተር ዩናይትድ ሊጉን ለማሸነፍ ጥሩ ተጨዋቾች ማስፈረም እንደሚያስፈልገው ገልጿል።

“ ፕርሚየር ሊጉን ማሸነፍ ከፈለግክ ምርጥ ተጨዋቾችን ማምጣት በሚያስችል የፋይናንሻል ፌር ፕሌይ ቁመና ላይ መሆን ያስፈልጋል “ ሲል ሩኒ ተናግሯል።

በተንታኝነት እያገለገለ የሚገኘው ሩኒ አክሎም “ አሁን እኔ በሌላ ሀገር የምጫወት ምርጥ ተጨዋች ብሆን እና ዩናይትድ ሊያስፈርመኝ ቢመጣ መፈረሜን እግጠኛ አይደለሁም “ ብሏል።

“ በጣም ያበሳጫል በርካታ ትልቅ ቡድኖች ከኤፌ ካፑ መውጣታቸው ለማንችስተር ዩናይትድ ጥሩ እድል ሰጥቶት ነበር ሊጠቀምበት አልቻለም።" ዋይን ሩኒ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ አላማችን ፕርሚየር ሊጉን ማሸነፍ ነው “ አሞሪም

የቀያይ ሴጣኖቹ ዋና አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የቡድናቸው አላማ ሊጉን ማሸነፍ መሆኑን ከኤፌ ካፕ ስንብታቸው በኋላ ገልጸዋል።

“ የረጅም ጊዜ እቅዳችን ፕርሚየር ሊጉን ማሸነፍ ነው “ ያሉት ሩበን አሞሪም “ ምን ያህል ጊዜ እንደሚወስድ አላውቅም ኢላማችን ግን ሊጉ ነው ብለዋል።

ምንም ቢፈጠር ወደ ፊት መራመዳቸውን እንደሚቀጥሉ አሰልጣኙ ጨምረው ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

55.3k 0 66 130 1.3k

የኤፌ ካፕ ተጋጣሚዎች ተለይተዋል !

የእንግሊዝ ኤፌ ካፕ ሩብ ፍፃሜ ተጋጣሚዎች ከደቂቃዎች በፊት በተደረገ የእጣ ማውጣት ስነስርዓት ይፋ ተደርገዋል።

በዚህም መሰረት :-

- ፉልሀም ከ ክሪስታል ፓላስ

- ፕሪስተን ከ አስቶን ቪላ

- በርንማውዝ ከ ማንችስተር ሲቲ

- ብራይተን ከ ኖቲንግሃም / ኢፕስዊች ጋር ተደልድለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

Показано 20 последних публикаций.