Фильтр публикаций


" በዚህ አመት ዋንጫ ማሸነፍ ነው ምኞቴ " አርቴታ

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ በ 2025 ዋንጫ የማሸነፍ ምኞት እንዳላቸው በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል።

“ በዚህ አመት ዋንጫ ማሸነፍ እመኛለሁ “ ያሉት ሚኬል አርቴታ ካሳየነው ቀጣይነት ያለው አቋም እና ቁጥር አንፃር ማሸነፍ ይገባናል የተለመደም ነው ሲሉ ተናግረዋል።

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ አክለውም አርሰናል በዚህ አመት በእርግጠኝነት የሆነ ነገር ያሸንፋል ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe


“ ጨዋታውን ማሸነፍ እፈልጋለሁ “ አሞሪም

የማንቸስተር ዩናይትዱ ዋና አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የነገው የሳውዝሀምፕተን ጨዋታ ስለ ተጨዋቾቹ ብዙ የሚያስተምረኝ ነው በማለት ተናግረዋል።

ሩበን አሞሪም በአስተያየታቸውም “ ካለፉት ሁለት ጨዋታዎች ይልቅ የሳውዝሀምፕተን ጨዋታ ተጨዋቾቹን በደንብ የማውቅበት ነው “ ብለዋል።

“ ባለፉት ጨዋታዎች የሚጠበቅ ነገር አልነበረም በአርሰናል ጨዋታ አጋጣሚዎችን ስንጠብቅ ነበር ለወደፊቱ እንደዚህ መጫወት አንችልም “ሲሉ ሩበን አሞሪም አክለዋል።

ስለ ራሽፎርድ አዲስ ነገር የተጠየቁት ሩበን አሞሪም “ የነገውን ጨዋታ ማሸነፍ እፈልጋለሁ ፤ ጨዋታውን ለማሸነፍ ምርጡን ቡድን እመርጣለሁ “ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe


" ከሊቨርፑል ጋር ጥሩ ጨዋታ ይኖረናል " ኖርጋርድ

የብሬንትፎርዱ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ክርስቲያን ኖርጋርድ በሳምንቱ መጨረሻ ከሊቨርፑል ጋር ጥሩ ጨዋታ እንደሚኖራቸው ገልጿል።

“ በማንችስተር ሲቲ ጨዋታ ያደረግነውን የምናስቀጥለው ከሆነ ቅዳሜ ከሊቨርፑል ጋር ጥሩ ውጤት እንደምናገኝ እርግጠኛ ነኝ“ ሲል ክርስቲያን ኖርጋርድ ተናግሯል።

ክርስቲያን ኖርጋርድ ትላንት ምሽት ከማንችስተር ሲቲ በነበራቸው ጨዋታ የብሬንትፎርድን የአቻነት ግብ በመጨረሻ ሰዓት ማስቆጠሩ አይዘነጋም።

ብሬንትፎርድ በሜዳው ቅዳሜ ምሽት 12:00 ከሊቨርፑል ጋር የሊግ መርሐግብሩን ያደርጋል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe


#EthPL🇪🇹

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ አስራ አራተኛ ሳምንት መርሐግብር ሲዳማ ቡና ከመቐለ 70 እንደርታ
ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 0ለ0 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

7️⃣ ሲዳማ ቡና :- 18 ነጥብ
1️⃣4️⃣ መቐለ 70 እንደርታ :- 15 ነጥብ

ቀጣይ የሊጉ መርሐ ግብር ?

⏩ እሁድ - ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከ መቐለ 70 እንደርታ

⏩ እሁድ - ሲዳማ ቡና ከ ወላይታ ድቻ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ ፓልመር ሜሲን ያስታውሰኛል “ ጆ ኮል

የቀድሞ እንግሊዛዊ ተጨዋች ጆ ኮል ኮል ፓልመር አርጀንቲናዊውን የፊት መስመር ተጨዋች ሊዮኔል ሜሲ እንደሚመስለው ተናግሯል።

በቼልሲ እና ሊቨርፑል ተጫውቶ ያሳለፈው ጆ ኮል ሲናገርም “ ኮል ፓልመር ሲጫወት ስመለከተው ሊዮኔል ሜሲን ያስታውሰኛል “ ሲል ተደምጧል።

የቀድሞ ተጨዋቹ አክሎም ነገርግን በዚህ ንግግር ኮል ፓልመርን ጫና ላደርግበት አልፈልግም በማለት ተናግሯል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe


ቼልሲ ተጫዋቹን ከውሰት መልሶ ጠርቷል !

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ በውሰት ለክሪስታል ፓላስ የሰጠውን የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ትሮቮህ ቻሎባህ መልሶ መጥራቱ ተገልጿል።

የ 25ዓመቱ ተከላካይ ትሮቮህ ቻሎባህ ክሪስታል ፓላስ ዛሬ ምሽት ከሌስተር ሲቲ በሚያደርገው የሊግ ጨዋታ እንደማይሳተፍ ዘ አትሌቲክ አስነብቧል።

ውሳኔውን አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ መወሰናቸው የተገለፀ ሲሆን ተጨዋቹ በቀሪው የውድድር አመት በቡድን ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተነግሯል።

ቼልሲ የኋላ መስመሩ በጉዳት ምክንያት እንዲሁም የሚለቁ ተጨዋቾች በመኖራቸው መሳሳቱ ቻሎባህን እንዲጠራ እንዳሳሰበው ተዘግቧል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe


ቅቫራስኬሊያ በፒኤስጂ ስንት ይከፈለዋል ?

ጆርጂያዊው የፊት መስመር ተጨዋች ቅቫራስኬሊያ የፈረንሳዩን ክለብ ፒኤስጂ ለመቀላቀል ከስምምነት ደርሷል።

ፒኤስጂ ተጨዋቹን በ 70 ሚልዮን ፓውንድ በአምስት አመት ውል ለማስፈረም በዚህ ሳምንት የህክምና ምርመራ ያደርጉለታል።

የ 23ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ቅቫራስኬሊያ በፒኤስጂ ቤት በአመት 1️⃣1️⃣ ሚልዮን ዩሮ ደሞዝ እንደሚከፈለው ተገልጿል።

ተጨዋቹ በናፖሊ ቤት በአመት 1.8 ሚልዮን ዩሮ ይከፈለው እንደነበር ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


የሎስ አንጀለስ ስፖርት ቡድኖች ድጋፍ አድርገዋል !

በአሜሪካ ሎስ አንጀለስ ግዛት የሚገኙ አስራ ሁለት የስፖርት ቡድኖች በጋራ በአካባቢው በተከሰተው አስከፊ የሰደድ እሳት አደጋ ለተጎዱ ድጋፍ አድርገዋል።

ክለቦቹ በእሳት አደጋው ጉዳት ለደረሰባቸው እና እሳቱን ለማጥፋት ለተሰማሩ የሚውል 8️⃣ ሚልዮን ዶላር ድጋፍ ማድረጋቸው ተዘግቧል።

ከሰሞኑ በአሜሪካ ፤ ሎስ አንጀለስ ግዛት የተነሳው ከፍተኛ ሰደድ እሳት አሁንም መቆጣጠር እንዳልተቻለ ተገልጿል።

እስከ ትላንት ባለ መረጃ በሰደድ እሳቱ ምክንያት 2️⃣4️⃣ ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ 1️⃣6️⃣ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


Репост из: WANAW SPORT WEAR
#wanaw_8289⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️
ያዘዝከው የስፖርት ትጥቅ ከምን ደረሰልክ❓

ወደ 8️⃣2️⃣8️⃣9️⃣ ደውለው 3️⃣ቁጥርን ሲነኩ ያዘዙት ማሊያ ከምን እንደደረሰ ማወቅ ያስችልዎታል‼️

አዲስ የስፖርት ትጥቅ ለማዘዝ🔽
8️⃣2️⃣8️⃣9️⃣
+251901138283
+251910851535
+251913586742

🔗 ማህበራዊ ገጾቻችን🔗
Instagram|Facebook |TikTok |X|Youtube
😀በአፍሪካውያን የተመረተ 😀
⭐️ዋናው ወደፊት🔣🔣🔣


አንቾሎቲ የታክቲክ ለውጥ ሊያደርጉ ነው !

የሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ በትልቅ ጨዋታዎች ላይ የጨዋታ ታክቲካቸውን ለመቀየር በማሰብ ላይ መሆናቸውን ለክለቡ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ዘግበዋል።

አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ በትልቅ ጨዋታዎች ቪኒሰስ ጁኒየር ፣ ጁድ ቤሊንግሀም ፣ ሮድሪጎ እና ኪሊያን ምባፔን አንድ ላይ #ላለማሰለፍ ማሰባቸው ተነግሯል።

ሎስ ብላንኮዎቹ ተጭኖ የሚጫወት ቡድን ሲገጥማቸው የቡድኑን ሚዛን ለመጠበቅ አራቱን የማጥቃት ባህሪ ያላቸው ተጨዋቾች አንድ ላይ ላለማሰለፍ ማሰባቸው ተዘግቧል።

አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ እና አባላቶቻቸው እቅዳቸውን ለመቀየር ያሰቡት ባለፈው እሁድ በባርሴሎና ከደረሰባቸው የ 5ለ2 ሽንፈት በኋላ መሆኑ ተነግሯል።

በቀጣይ የአካዳሚው ውጤት አሴንሲዮ ተጨማሪ የጨዋታ ሰዓት ያገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተጠቁሟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ ሁሉም የሚደነግጥለትን ዩናይትድ መመለስ አለብን “ ፈርናንዴዝ

የቀያይ ሴጣኖቹ አምበል ብሩኖ ፈርናንዴዝ ሁሉም ቡድኖች የሚፈሩትን ማንችስተር ዩናይትድ መመለስ እንደሚፈልጉ ተናግሯል።

“ የድሮውን ማንችስተር ዩናይትድ መመለስ አለብን “ የሚለው ፈርናንዴዝ ሁሉም ቡድኖች የሚፈሩት እና የሚደነግጡለትን ቡድን መመለስ አለብን ብሏል።

ፈርናንዴዝ አክሎም ቡድኑ ሐሙስ ምሽት የሚገጥመው ሳውዝሀምፕተን ላለመውረድ የሚጫወት በመሆን ቀላል ግምት መስጠት እንደሌለበት አሳስቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


" ጥሩ የመጀመሪያ አጋማሽ አልነበረንም " አርኔ ስሎት

የሊቨርፑሉ ዋና አሰልጣኝ አርኔ ስሎት በምሽቱ ጨዋታ ቡድናቸው በመጀመሪያው አጋማሽ ጥሩ እንዳልነበረ ገልጸዋል።

“ በመጀመሪያው አጋማሽ ጥሩ አልነበርንም
ሁለተኛው አጋማሽ በነበረን እንቅስቃሴ ደስተኛ ነኝ ብዙ እድሎችን ፈጥረናል “ ሲሉ አርኔ ስሎት ተናግረዋል።

የኖቲንግሀም አሰልጣኝ ኑኖ እስፕሪቶ ሳንቶ በበኩላቸው “ በመጀመሪያው አጋማሽ የተደራጀን ነበርን ብዙ እድል እንዲፈጥሩ አልፈቀድንም በሁለተኛው አጋማሽ የጠረጴዛ ቴኒስ መስሎ ነበር “ ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


የዛሬ ተጠባቂ ጨዋታዎች !

9:00 ሲዳማ ቡና ከ መቐለ 70 እንደርታ

12:00 ወልዋሎ አዲግራት ዩ ከ ወላይታ ድቻ

4:30 ባየር ሙኒክ ከ ሆፌንሄም

4:30 ኤቨርተን ከ አስቶን ቪላ

4:30 ኒውካስል ከ ዎልቭስ

4:45 ኢንተር ሚላን ከ ቦሎኛ

5:00 ባርሴሎና ከ ሪያል ቤቲስ

5:00 ኤስፓሊ ከ ፒኤስጂ

5:00 አርሰናል ከ ቶተንሀም

🔴 የዛሬው የይግምቱ ሽልማታችን የአርሰናል እና ቶተንሀም ጨዋታ ነው።

🔴 የዛሬ ሽልማታችን 3:30 ሰዓት ላይ ወደ ቤተሰቦቻችን የሚደርስ ይሆናል።

🔴 መገመት የሚቻለው በተጠቀሰው ሰዓት ላይ ብቻ ነው።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


Репост из: Betika Ethiopia Official Channel
ይቅናዎት!
ኦዶች ከመቼውም ጊዜ በላይ ከፍ ተደርገዋል።
ታዲያ ምን ይጠብቃሉ? ለማሸነፍ በተመቻቹ ኦዶች ይወራረዱ!
አሁኑኑ Betika.et ላይ ብቻ!
ቤቲካ የአሸናፊዎች ቤት!


#Premiereleague 🏴󠁧󠁢󠁥󠁮󠁧󠁿

በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐግብር ማንችስተር ሲቲ ፣ ቼልሲ እና ሊቨርፑል ጨዋታዎቻቸውን በአቻ ውጤት አጠናቀዋል።

የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ከኖቲንግሀም ፎረስት ጋር  ያደረገውን ተጠባቂ የሊግ ጨዋታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቋል።

የኖቲንግሀምን ግብ ክሪስ ውድ ሲያስቆጥር ዲያጎ ጆታ ሊቨርፑልን አቻ አድርጓል።

ማንችስተር ሲቲ በበኩሉ ከብሬንትፎርድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2ለ2 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።

የማንችስተር ሲቲን ግቦች ፊል ፎደን 2x ሲያስቆጥር ለብሬንትፎርድ ዊሳ እና ኖርጋርድ ከመረብ አሳርፏል።

ቼልሲ ከበርንማውዝ ያደረገውን ጨዋታ 2ለ2 በሆነ አቻ ውጤት ማጠናቀቅ ችለዋል።

የሰማያዊዎቹን ግብ ኮል ፓልመር እና ሬስ ጄምስ ሲያስቆጥሩ ክላይቨርት እና ሴሜኒኖ ለበርንማዝ ከመረብ አሳርፈዋል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

1️⃣ ሊቨርፑል :- 47 ነጥብ
2️⃣ ኖቲንግሀም ፎረስት :- 41 ነጥብ
4️⃣ ቼልሲ :- 37 ነጥብ
6️⃣ ማንችስተር ሲቲ :- 35 ነጥብ

ቀጣይ መርሐግብር ?

⏩ ቅዳሜ - ብሬንትፎርድ ከ ሊቨርፑል

⏩ እሁድ - ኢፕስዊች ታውን ከ ማንችስተር ሲቲ

⏩ ሰኞ - ቼልሲ ከ ዎልቭስ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


80'

ኖቲንግሀም ፎረስት 1-1 ሊቨርፑል

⚽ ዉድ              ⚽ ጆታ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


#ተጠናቀቀ

ቼልሲ 2-2 በርንማውዝ

⚽ ፓልመር      ⚽ ክላይቨርት
⚽ ጄምስ        ⚽ ሴሜኒዮ

ብሬንትፎርድ 2-2 ማንችስተር ሲቲ

⚽ ዊሳ                     ⚽⚽ ፎደን
⚽ ኖርጋርድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


90+4'

ቼልሲ 2-2 በርንማውዝ

⚽ ፓልመር      ⚽ ክላይቨርት
⚽ ጄምስ        ⚽ ሴሜኒዮ

ብሬንትፎርድ 2-2 ማንችስተር ሲቲ

⚽ ዊሳ                     ⚽⚽ ፎደን
⚽ ኖርጋርድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


67 '

ኖቲንግሀም ፎረስት 1-1 ሊቨርፑል

⚽ ዉድ ⚽ ጆታ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


90'

ብሬንትፎርድ 2-2 ማንችስተር ሲቲ

⚽ ዊሳ                     ⚽⚽ ፎደን
⚽ ኖርጋርድ

ቼልሲ 1-2 በርንማውዝ

⚽ ፓልመር      ⚽ ክላይቨርት
                        ⚽ ሴሜኒዮ

66 ' ኖቲንግሀም ፎረስት 1-0 ሊቨርፑል

⚽ ዉድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

Показано 20 последних публикаций.