#AAU #UAT #Cutoff_Points አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመንግስት ስፖንሰርነት እና በግል የቅድመ ምረቃ አመልካቾች ለ2017 ዓ.ም የ UAT መቁረጫ ነጥብ ይፋ አድርጓል።
በዚህም በመንግስት ስፖንሰር ለተደረጉ የቅድመ ምረቃ አመልካቾች ለ2017 ዓ.ም የ UAT መቁረጫ ነጥብ ለተፈጥሮ ሳይንስ
64 እና ለማኅበራዊ ሳይንስ
51 መሆኑ ታውቋል።
በግል ለመማር ያመለከቱ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ለ2017 ዓ.ም የ UAT መቁረጫ ነጥብ ከ
54-79 (እንደየትምህርት ክፍሉ) መሆኑ ተገልጿል።
በግል ለመማር ያመለከቱ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ከፍተኛ የመቁረጫ ያስቀመጡ ት/ት ክፍሎች፦
► ህክምና ትምህርት ክፍል -
79► ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ እና ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ -
78► ኮምፒውተር ሳይንስ ት/ት ክፍል -
77► የጥርስ ህክምና ትምህርት ክፍል -
75► ህግ ትምህርት ክፍል -
70(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይፋ ያደረገው ለመንግስት እና የግል የቅድመ ምረቃ UAT አመልካቾች የመቁረጫ ነጥብ ከላይ ተያይዟል።)
በመንግስት ስፖንሰርነት እና በግል የቅድመ ምረቃ ትምህርታችሁን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለመከታተል የመግቢያ ፈተና (UAT) ወስዳችሁ ያለፋችሁ አመልካቾች፣ የምደባ ውጤታችሁን
http://admission.aau.edu.et/login ላይ ገብታችሁ Username (email) እና Password በማስገባት መመልከት ትችላላችሁ።
@tikvahuniversity