Фильтр публикаций


የተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በልዩ ልዩ የትምህርት መስኮች ያስተማሯቸውን ተማሪዎች የካቲት 15 እና 16/2017 ዓ.ም ያስመርቃሉ።

አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ፣ እና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በሳምንቱ መጨረሻ ተማሪዎቻቸውን ከሚያስመርቁ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል ይገኙበታል፡፡

ተቋማቱ በቅድመ-ምረቃ እና በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች ያስተምሯቸውን ተማሪዎች ያስመርቃሉ።

@tikvahuniversity

36.6k 0 13 111 189

ሚዛን ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ በሦስት ዙር ቴክኖሎጂ ነክ በሆኑ ኮርሶች ያሰለጠናቸውን 127 ተማሪዎች አስመርቋል።

ተመራቂዎቹ በዌብ ዲቨሎፕመንት፣ በሞባይል አፕ ዲቨሎፕመንት፣ በግራፊክስ ዲዛይን፣ በዲጂታል ማርኬቲንግ፣ በቪዲዮ ኤዲቲንግ፣ በቤዚክ ኮምፒውተር ስኪል እና በዳታ ሳይንስ መስኮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ተማሪዎቹም በመደበኛ፣ በማታ እና በእረፍት ቀናት በአካል እና በኦንላይን ትምህርታቸውን መከታተላቸውን የኢንስቲትዩቱ ሥራ አስኪያጅ አህመድ ሙሀመድ ገልፀዋል።

በ2014 ዓ.ም የተቋቋመው ኢንስቲትዩቱ እስካሁን ከ300 በላይ ተማሪዎችን ከ 2-9 ወር በሚሰጡ ኮርሶች በሰባት ዙር ማስመረቁን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።

@tikvahuniversity


20ኛ ዙር የድረ-ገጽ እና ሞባይል መተግበሪያ ማበልፀግ (Full-Stack Website and Mobile Application Development) ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ በምዝገባ ላይ ነን።   

👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 ፕሮግራሚንግ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 Front-end እና Back-end በአንድ ላይ እስከ Deployment ያካተተ
👉 በተግባር ድረ-ገጾች እና ሞባይል መተግበሪያዎችን እያበለፀጉ የሚሰለጥኑበት
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


የመውጫ ፈተና ውጤት መለቀቅን ተከትሎ በርካታ የኮምፕርሄንሲቭ ነርሲንግ ተፈታኞች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ልከዋል፡፡

"ፈተናው ከብሉ ፕሪንት ውጪ ነው የመጣው" የሚሉት ተፈታኞቹ፤ እርማቱ በድጋሜ ሊታይ ይገባል ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡

በጉዳዩ ላይ ትምህርት ሚኒስቴርን ያነጋገርን ሲሆን፤ ከኮምፕርሄንሲቭ ነርሲንግ ፈተና ጋር የተያያዘ ምንም አይነት ቅሬታ ለተቋሙ #አለመድረሱን ሚኒስቴሩ ጠቁሟል፡፡

በውጤታቸው ላይ ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ ለሚገኘው የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ማቅረብ እንደሚችሉም ተቋሙ ገልጿል፡፡

በሌላ በኩል ውጤታቸውን ለማየት የተቸገሩ የግል (በድጋሜ) ተፈታኞች፣ ውጤታቸው ወደተፈተኑበት ተቋም የተላከ በመሆኑ ወደተቋማቱ በመሔድ ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ አስረድቷል፡፡

@tikvahuniversity

54.5k 0 166 287 332

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በቅድመ-ምረቃ እና በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን 343 ተማሪዎች ዛሬ ያስመርቃል፡፡

ከተመራቂዎቹ 76ቱ በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም ትሀምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቀቁ ናቸው፡፡

@tikvahuniversity


የተባበሩት መንግሥታት የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት (SDSN) የአፍሪካ ማዕከል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከፍቷል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተከፈተው የጥምረቱ ማዕከል የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማከናወን ለፖሊሲ አውጪዎች ግብዓት የሚሆኑ ሳይንሳዊ መፍትሔዎችን ያቀርባል ተብሏል።

የማዕከሉ መከፈት ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥር እና በትብብር ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄዎችን ለመቅረፅ የራሱን አበርክቶ እንደሚወጣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

@tikvahuniversity


41ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ በምዝገባ ላይ ነን!

👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 Advanced Graphic + Video Editing + Motion Graphic + Digital Marketing በአንድ ላይ
👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


#Exit_Exam_Result

የ2017 አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ኦንላይን የመመልከቻ ሊንክ መስራት ጀምሯል።

https//:result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት ExitExam የሚለውን በመምረጥና የራስዎን User Name በማስገባት ውጤትዎን መመልከት ይችላሉ።

@tikvahuniversity

65.5k 2 1.5k 662 432

የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኢንስቲትዩት የመውጫ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎቹ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን አሳውቋል፡፡

በዚህም ኢንስቲትዩቱ ያስፈተናቸው የአንስቴዥያ፣ ሚድዋይፈሪ፣ ሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ እና ፋርማሲ ተፈታኞች በሙሉ የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን ግልጿል፡፡

@tikvahuniversity


ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ሥራ ያስጀመረው የመሀል-ሜዳ ካምፓስ ትምህርት መስጠት ጀምሯል፡፡

በቅርቡ ተማሪዎችን የተቀበለው ካምፓሱ፤ የመጀመሪያ ቀን የመጀመሪያ የትምህርት ክፍለ-ጊዜ ዛሬ አካሒዷል።

@tikvahuniversity


ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ በ2017 አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው የሕክምና ተማሪዎች መካከል 98 በመቶ ተፈታኞች የማለፊይ ውጤት ማምጣታቸውን ገልጿል።

@tikvahuniversity

52.1k 0 15 143 199

#TVTI_Exit_Exam

የመውጫ ፈተና የምትወስዱ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ሰልጣኞች በኦንላይን የምዝገባ ጊዜ ዛሬ ያበቃል።

ተከታዩን ማስፈንጠሪያ በመጫን የምታገኙትን ቅፅ በመሙላት ምዝገባ ያድርጉ 👇
https://forms.office.com/r/3KgnK1esuc

ኦንላይን መመዝገብ የማትችሉ አመልካቾች በኢንስቲትዩቱ ዋናው ግቢ በመገኘት በየትምህርት ክፍላችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል።

🔔 የምዝገባ ጊዜው ዛሬ የካቲት 10/2017 ዓ.ም ያበቃል።

የመውጫ ፈተናውን #በድጋሜ ለምትወስዱ ተፈታኞች ፈተናው በኢንስቲትዩቱ ዋና ግቢ እና በአዲስ አበባ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።

የመዝገባ ብር 500 በኢንስቲትዩቱ የንግድ ባንክ አካውንት በማስገባት ክፍያ በመፈፀም ደረሰኝ መያዝ ይጠበቅባችኋል።

✍ የምዝገባ ጥሪው በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የጋርመንት ቴክኖሎጂ ሰልጣኞችንም ይመለከታል።

የመውጫ ፈተናው ከመጋቢት 6-11/2017 ዓ.ም ባለው ጊዜ እንደሚሰጥ ኢንስቲትዩቱ ገልጿል።

@tikvahuniversity


21ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Modern Accountancy) ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ ምዝገባ ላይ ነን። 

👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute

47k 0 15 4 38

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ በመደበኛ እና በተከታታይ የትምህርት ፕሮግራም በመጀመሪያ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 395 ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል።

በዱራሜ ካምፓስ በመደበኛ እና በተከታታይ የትምህርት መርሐግብር በተሰጠው የመውጫ ፈተና 79 በመቶ ተፈታኞች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን የዱራሜ ካምፓስ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዘውዱ ክፍሌ ገልፀዋል።

@tikvahuniversity

54.5k 0 11 37 201

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 2,717 ተማሪዎች አስመርቋል።

የተቋሙ 19ኛ ዙር ተመራቂዎች በመደበኛ እና በተከታተይ የትምህርት መርሐግብር በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ ዲግሪ እና በሦስተኛ ዲግሪ በተቋሙ ሦስት ካምፓሶች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል።

@tikvahuniversity


ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 394 ተማሪዎች አስመርቋል።

የተቋሙ 17ኛ ዙር ተመራቂዎች በቅድመ-ምረቃ እና በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ከፍተኛ ውጤት አምጥተው የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ለሆኑ አንድ ወንድ እና አንድ ሴት ተማሪዎች የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን በተቋሙ እንዲቀጥሉ ነጻ የትምህርት ዕድል እንደተሰጣቸው ተገልጿል።

@tikvahuniversity


ክፍያቸውን ለፈፀሙ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ውጤት ዛሬ ተለቋል።

በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ2017 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተፈታኞች ውጤት ሳይለቀቅ መዘግየቱይታወቃል።

ለመጀመሪያ ጊዜ የመውጫ ፈተና የሚወስዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተፈታኞችን ክፍያ የሚፈፅሙት ተቋማት ክፍያቸውን ሳያደርጉ በመዘግየታቸው የተፈታኞቹ ውጤት ሳይለቀቅ ቆይቷል።

ተቋማቱ ክፍያውን በመፈፀማቸው የተማሪዎቹ ውጤት ዛሬ ለየተቋማቱ መለቀቁን የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት እና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ማህበር ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል።

@tikvahuniversity

72.4k 0 657 371 562

ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የመጀመሪያ ባች ተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት አካሒዷል።

ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ያስመረቃቸው የጤና ተማሪዎች ባለፈው ሳምንት የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ወስደው ሙሉ በሙሉ ያለፉ መሆናቸው ተገልጿል።

@tikvahuniversity


ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በጤናው ዘርፍ በመጀመሪያ እና ማስተርስ ዲግሪ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን 339 ተማሪዎች አስመርቋል።

ተመራቂዎቹ 232 በሁለተኛ ዲግሪ እና 107 በመጀመሪያ ዲግሪ በጤና ሳይንስ መስክ መሆናቸው ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው በተጨማሪም በ Higher Diploma Program ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 28 መምህራን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

@tikvahuniversity


ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 1,513 ተማሪዎችን ዛሬአስመረቀ።

የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እንዲሁም በተከታታይ መርሐግብር የቅድመ-ምረቃ እና የድኅረ-ምረቃ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ባከናወነው 14ኛ ዙር የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት መመረቃቸው ተገልጿል።

@tikvahuniversity

Показано 20 последних публикаций.