Tikvah-University


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


#AAU #UAT #Cutoff_Points

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመንግስት ስፖንሰርነት እና በግል የቅድመ ምረቃ አመልካቾች ለ2017 ዓ.ም የ UAT መቁረጫ ነጥብ ይፋ አድርጓል።

በዚህም በመንግስት ስፖንሰር ለተደረጉ የቅድመ ምረቃ አመልካቾች ለ2017 ዓ.ም የ UAT መቁረጫ ነጥብ ለተፈጥሮ ሳይንስ 64 እና ለማኅበራዊ ሳይንስ 51 መሆኑ ታውቋል።

በግል ለመማር ያመለከቱ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ለ2017 ዓ.ም የ UAT መቁረጫ ነጥብ ከ54-79 (እንደየትምህርት ክፍሉ) መሆኑ ተገልጿል።

በግል ለመማር ያመለከቱ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ከፍተኛ የመቁረጫ ያስቀመጡ ት/ት ክፍሎች፦
► ህክምና ትምህርት ክፍል - 79
► ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ እና ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ - 78
► ኮምፒውተር ሳይንስ ት/ት ክፍል - 77
► የጥርስ ህክምና ትምህርት ክፍል - 75
► ህግ ትምህርት ክፍል - 70

(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይፋ ያደረገው ለመንግስት እና የግል የቅድመ ምረቃ UAT አመልካቾች የመቁረጫ ነጥብ ከላይ ተያይዟል።)

በመንግስት ስፖንሰርነት እና በግል የቅድመ ምረቃ ትምህርታችሁን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለመከታተል የመግቢያ ፈተና (UAT) ወስዳችሁ ያለፋችሁ አመልካቾች፣ የምደባ ውጤታችሁን http://admission.aau.edu.et/login ላይ ገብታችሁ Username (email) እና Password በማስገባት መመልከት ትችላላችሁ።

@tikvahuniversity

23.5k 0 179 62 129

#EthiopianCivilServiceUniversity

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ ነባር ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚካሔደው መስከረም 20 እና 21/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

የተከታታታይ (የማታ እና የቅዳሜና እሑድ) ትምህርት ፕሮግራሞች ነባር ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 22 እና 23/2017 ዓ.ም የሚካሔድ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በሁሉም ፕሮግራሞች የዘገዩ ተማሪዎች ምዝገባ በቅጣት መስከረም 24/2017 ዓ.ም የሚከናወን ሲሆን፤ የሁሉም ትምህርት መርሐግብሮች ትምህርት መስከረም 24/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።

@tikvahuniversity


#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በጥራት፣ በብራንድ እና በባትሪ ቆይታ እጅግ አስተማማኝ የሆኑ ላፕቶፕች በተለያዩ ሞዴሎችና በፈለጉት ስክሪን መጠን ኮር እና ጀነሬሽን አሉን።

ላፕቶፕ ከመገዛትዎ በፊት ማወቅ ያለባቹሁን ወሳኝ ነገሮች እናስረዳዎታለን።

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለጌመሮች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ወ.ዘ.ተ ሁሉም አሉን! በላፕቶፖቻችን ጥራት አንደራደርም!

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራም ማየት ይችላሉ።

@sww2844
0928442662 / 0940141114

https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17


#AAU

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 2ኛ ዙር የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) የማመልከቻ ግዜን እስከ መስከረም 25/2017 ዓ.ም አራዝሟል፡፡

ለ GAT ፈተና ለማመልከት 👇
https://portal.aau.edu.et

ለማመልከት፦

https://Portal.aau.edu.et ይክፈቱ።
► Exam Application የሚለውን ይጫኑ።
► Test Taker Registration ቅፅን ይሙሉ።
► ፓስፖርት መጠን ያለው ፎቶዎን ያስገቡ።
► Submit የሚለውን ይጫኑ።
► ሲስተሙ የሚሰጥዎትን ቁጥር ኮፒ ያድርጉ።
► የGAT ፈተና ክፍያ ብር 1000 በቴሌብር ይክፈሉ።
► የክፍያ ቲኬትዎን አውርደው ፕሪንት ይበሉ። የፈተና ቀን ወደመፈተኛ አዳራሽ ለመግባት ያስፈልግዎታል።

@tikvahuniversity

33.2k 0 248 17 83

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለ2ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ መደበኛ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች እንዲሁም ለነባር የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች ጥሪ አለማድረጉን አረጋግጧል።

ወደፊት በ EBC እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ማኅበራዊ ሚዲያ ገፆች ጥሪ የሚደረግ መሆኑን የገለፀው ዩኒቨርሲቲው፤ እስከዛ ድረሰ ተማሪዎቹ በትዕግስት እንዲጠብቁ ጠይቋል።

@tikvahuniversity


በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ የቻሉ ትምህርት ቤቶች ሰባት ብቻ ናቸው።

ከነዚህ ጥቂት ስኬታማ ትምህርት ቤቶች መካከል በጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው The Spark Academy አንዱ ነው።

ትምህርት ቤቱ ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸውን 35 ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ ችሏል። ሁለት ተማሪዎች ደግሞ ከ500 በላይ ውጤት አስመዝግበዋል።

የተገኘው ውጤት የት/ቤቱ ማኅበረሰብ የተቀናጀ ጥረት ፍሬ መሆኑን የአካዳሚው ባለቤት ክፍለገብርኤል ወ/ተንሳይ ለ SRTV አማርኛ ተናግረዋል።

አካዳሚው በ2017 ዓ.ም 25 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እንደሚያስፈትን የገለፁት ባለቤቱ፤ ሁሉንም ተማሪዎች ለማሳለፍና የሀገሪቱ ከፍተኛ ውጤት በትምህርት ቤቱ እንዲመዘገበ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።

@tikvahuniversity


በሦስቱም ቅርንጫፎቻችን (መገናኛ፣ ሜክሲኮ እና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸው  ስልጠናዎች ባሉን ውስን ቦታዎች አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለውጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ!

ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕውቅና ካለው ሰርተፊኬት ጋር! የብዙ ዓመት ልምድና ብቃት ባላቸው አሰልጣኞች ይማሩ!

🌼 Graphics Design
🌼 Video Editing
🌼 Digital Marketing
🌼 Adobe Photoshop
🌼 English Language
🌼 Website Design
🌼 Programming
🌼 Interior Design
🌼 Database
🌼 Basic Computer
🌼 Accounting Softwares
🌼 SPSS & STAΤΑ
🌼 MS-Project
🌼 Foreign & Local Languages

አድራሻ፦
ቁ.1:
መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 419 (ሊፍት ይጠቀሙ)
ቁ.2: ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 639 (ሊፍት ይጠቀሙ) (ትንሹ ኬኬር)
ቁ.3: ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ

☎️    0991929303 / 0991929304 /
         0991926707


Telegram: https://t.me/topinstitutes


#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ
#Lorcan_Medical_College

የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ጀምሯል❗️

BSc fields of study:
→ Doctor of Medicine
→ Doctor of Dental Medicine
→ Bachelor of Dental Science
→ Nursing

TVET Programs:
→ Dental Therapy
→ Nursing
→ Medical Laboratory
→ Pharmacy
→ Radiography

የ CPD ማዕከል አገልግሎት!

☎️ 0913398780 / 0911596059

አድራሻ፦
CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ

📍 Addis Ababa, CMC Square, behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital

Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege


#AAU

የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የወሰዳቹ ተፈታኞች ውጤታችሁን ኦንላይን ማየት እንደምትችሁ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

ውጤት ለማየት 👇
https://portal.aau.edu.et/Web/ApplyForAdmission/TestingStatus

በተመሳሳይ በመንግስት ስፖንሰር ተደርጋችሁ የቅድመ ምረቃ ትምህርታችሁን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለመከታተል ፈተና የወሰዳችሁ አመልካቾች፣ ውጤታችሁን https://portal.aau.edu.et/ ላይ ገብታችሁ Username (email) እና Password በማስገባት መመልከት ትችላላችሁ።

ዩኒቨርሲቲው ሦስተኛ ዙር የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) በቅርቡ ይሰጣል ማለቱ አይዘነጋም።

@tikvahuniversity

34.4k 0 126 42 79

የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት መለቀቅን ተከትሎ በርካታ ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ የድኅረ ምረቃ አመልካቾችን ለመቀበል ማስታወቂያ እያወጡ ይገኛሉ።

አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠውን የመግቢያ ፈተና (NGAT) ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡

(የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች ያወጧቸው የጥሪ ማስታወቂያዎች ከላይ ተያይዘዋል፡፡)

@tikvahuniversity


ራያ ዩኒቨርሲቲ 59 የተቋሙ መምህራንን በከፍተኛ ዲፕሎማ መርሐግብር (HDP) አስመርቋል።

ስልጠናውን ተከታትለው ከተመረቁ መመህራን ውስጥ 11 ሴት መምህራን ይገኙበታል።

ራያ ዩኒቨርሲቲ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ የመምህራን አቅም ለማሳደግና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ መምህራኖቹን በከፍተኛ ዲፕሎማ መርሃሐግብር (HDP) እያሰለጠነ እንደሚገኝ ተገልጿል።

@tikvahuniversity


ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታይ ቤተሰቦቻችን በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ!

መልካም በዓል!

የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥

 ☎️    0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1:
ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: @sage_training_institute' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


📢 ሐዋሳ፣ ወደ እናንተም እየመጣን ነው!

በቴሌግራም ቦት በኩል የምንሰጠው ስልጠና ሙያችሁን ለማሳደግ እንዴት እንደሚረዳችሁ ለማወቅ ተሳተፉ! 🚀

🗓 መስከረም 20/2017 ዓ.ም
🕒 ከቀኑ 7:30 እስከ 11:00 ሰዓት
📍 ሳውዝ ስታር ሆቴል (South Star Hotel)፣ ሐዋሳ

ቁልፍ ርዕሶች፦
🔹የመስራት ፕሮጀክት አጠቃላይ ዕይታ እና ግቦቹ 
🔹የመስራት የሙያ ማጎልበት ፕሮግራም እና ጥቅሞቹ
🔹በመስራት ቴሌግራም ቦት እንዴት እንደምትመዘገቡ እና ለየት ባሉ ስልጠናዎቻችንን እንዴት እንደምትካፈሉ

https://forms.gle/TemQSkS6k7rPLNa57 ተመዝገቡ!

#GigEconomy #Mesirat #Upskilling #CareerBoost #Hawassa


እንኳን አደረሳችሁ!


ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ለክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የመስቀል በዓል ይመኛል።

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምትገኙና በዓሉን ከቤተሰቦቻችሁ ርቃችሁ እያከበራችሁ ላላችሁ ተማሪዎች መልካም የመስቀል በዓል እንመኛለን።

@tikvahuniversity


#SalaleUniversity

በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርታችሁን በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ፤ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ ከታወቀ በኋላ የሚገለፅ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

1ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ የሆናችሁ ነባር የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ ቀናት ከዚህ በፊት በተገለፀው መሰረት መስከረም 20 እና 21/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tikvahuniversity

41.7k 0 152 49 151

#WoldiaUniversity

ወልድያ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል እና የአዲስ ገቢ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜን አራዝሟል።

በዚህም በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርታችሁን በወልድያ ዩኒቨርሲቲ ተምራችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እና በ2017 ዓ.ም ወልድያ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለምትመደቡ ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 27 እና 28/2017 ዓ.ም ይከናወናል ተብሎ ጥሪ የተላለፈ ቢሆንም፤ ምዝገባው በተለያዩ ምክንያቶች የተራዘመ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

Note:
የሌሎች ነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከዚህ ቀደም በተገለፀው መሰረት መስከረም 27 እና 28/2017 ዓ.ም ይከናወናል ተብሏል።

@tikvahuniversity

42k 0 56 19 120

#WolaitaSodoUniversity

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ ነባር መደበኛ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን የመግቢያ ጊዜ መስከረም 20 እና 21/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

ትምህርት መስከረም 22/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።

Note:
ለአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ወደፊት ጥሪ እንደሚደረግ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tikvahuniversity


የኦሮሚያ ክልል በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የክልሉ ተማሪዎች ዕውቅና ሰጥቷል።

በክልሉ የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ከ241,000 በላይ ተማሪዎች መካከል 8,520 ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ማምጣታቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) ገልፀዋል።

ከእነዚህ ተማሪዎች ውስጥ 305 የሚሆኑ ተማሪዎች ከፍተኛ ነጥብ ማምጣታቸውን ተናግረዋል።

ከፍተኛ ውጤት ካመጡ ተማሪዎች ውስጥ ለ77 ተማሪዎች የላፕቶፕ፣ የገንዘብ እና የሜዳልያ ሽልማት ተበርክቷል።

በክልሉ የሚገኙ ሞዴል እና ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸውን ጠቅሰዋል።

@tikvahuniversity

31k 0 32 6 119

💨 ⚡ቅመም MIFIን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም! ለ90 ቀን ከሚቆይ ነጻ 100ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር! ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት⚡
  
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom #SafaricomEthiopia #1Wedefit #Furtheraheadtogether


#DebreBerhanUniversity

በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የርቀት እና ተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም ማስተባበሪያ በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለነባር የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ከመስከረም 27 እስከ 29/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የነባር የሁለተኛ ዲግሪ የርቀት እና ተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ ከጥቅምት 4 እስከ 6/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

(የዩኒቨርሲቲው መልዕክት ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity

Показано 20 последних публикаций.