ሳሙኤል ተመስገን


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


ቤተክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ ።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


በዚህ ክረምት
      🌹፩ኛ ሃይማኖተ አበውን
      🌷፪ኛ ድርሳነ ቄርሎስን
እንማማራለን። አምስቱ አዕማደ ምሥጢር በስፋት የተገለጡ በእነዚህ መጻሕፍት ነው። ሰው ደግሞ ከምንም በፊት እነዚህን ማወቅ አለበት። ስለዚህ አንድምታውንም ዘሩንም እያነበባችሁ ግልጽ ያልሆነላችሁን በመጠየቅ እንማማራለን። ድርሳነ ቄርሎስ እና ሃይማኖተ አበው በክቡር መምህራችን የኔታ ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ የተዘጋጀ አለ። ያንን ገዝታችሁ ማንበብ ትችላላችሁ። በተጨማሪም ሃይማኖተ አበው በመጋቤ ሐዲስ ፍቅረማርያም ባዘዘው የተዘጋጀ አለ።

አንድምታ ትርጓሜ የቃሉን ትርጉም፣ የቃሉን ምክንያተ ጽሕፈት፣ ምሥጢሩን፣ ምሳሌውን ለይቶ የሚነግር ስለሆነ እጅግ በጣም ተወዳጅ ነው። ሐሳውያን መሰለኛቸውን እውነት አድርገው እንዳያቀርቡ አንድምታውን መማር መልካም ነው። ቃሉን መሸምደድ ብቻ ሳይሆን የነገሩን ፍሬ ሐሳብ መረዳት ትልቅ ጥቅም አለው። እንደ ከሓድያን ለቃሉ የራስን ትርጉም መስጠት ነውር ነው። እንደ መጽሐፉ ሐሳብና መጽሐፉ በተጻፈበት ዐውድ መረዳት ግን ለነፍስም መድኃኒት ነው።

ስለአምስቱ አዕማደ ምሥጢር ሃይማኖተ አበው ምን ይላል? ድርሳነ ቄርሎስ ምን ይላል? የሚለውን በጥልቀት እንመለከታለን። መማር ለሚፈልጉ ሼር አድርጉላቸው። ትምህርቱ በነጻ በዚሁ ፌስቡክና በቴሌግራም ይሰጣል። በነጻ ያገኘነውን በነጻ እንሰጣለን።

© መ/ር በትረማርያም አበባው (የመጻሕፍተ ብሉያት፣ የመጻሕፍተ ሊቃውንትና የመጻሕፍተ መነኮሳት ትርጓሜ መምህር)

🌹የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ @edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።




+ የተሠጠህን ቁጠር +

ሔዋን ከዕባብ ጋር እየተነጋገረች ነው። የመጀመሪያ ጥፋትዋ ካለደረጃዋ ወርዳ ከዕባብ ጋር ወዳጅነት መጀመርዋ ሳይሆን አይቀርም። ዕባብ ደግሞ የስይጣን አንደበት ነበረ።

ሰይጣን እንዲህ አላት:- በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን? አላት። ልብ አድርጉ እግዚአብሔር "ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ" አላለም። የከለከለው አንዲት ዛፍ ነው:: ሰይጣን ግን ሁሉን ተከልክላችሁዋል? ብሎ እንዳላዋቂ ጠየቀ። ሰይጣን በመጽሐፍ ቅዱስ ንግግሩን የከፈተው በውሸት ነበረ።

ዓላማው ከሔዋን መረጃ ለማግኘት አልነበረም። ሔዋን እስከዛሬ ያላሰበችውን ማሳሰብ ነበር። ብሉ ተብሎ ከተሠጣቸው ብዙ ሺህ ዛፍ ይልቅ የተከለከሉትን አንዲት ዛፍ አሳይቷት ሔደ። ከዚያች ደቂቃ ጀምሮ ስላልተሠጣት ማሰብ ጀምራ ደስታዋን አጣች። የተከለከለችውን በልታ የተሠጣትን ብዙ ሥጦታ ከነሠጪው አጣች።

ወዳጄ የቀደመው እባብ ዛሬም መርዙን ይረጫል

በሕይወታችን ከተሠጠን ብዙ ነገር ይልቅ ያልተሠጠንን ጥቂት ነገር እናስባለን። ገንዘብ እንደሌለህ እያሰብክ ጤና እንዳለህ ትረሳለህ። ጫማ እንደሌለህ እያሰብክ እግር እንዳለህ ትረሳለህ። አልጋ እንደሌለህ እያሰብክ እንቅልፍ እንዳለህ ትረሳለህ። ስለዚህ ውስጥህ ያለውን የዕባቡን ድምፅ  አትስማ ከሌለህ ይልቅ ያለህ ይበልጣልና የተሠጠህን ቁጠር።

(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ)
https://t.me/tsidq


አንዱ ለጓደኛው ስልክ ይደውልና "እባክህ እናቴ በጣም ታማ ሆስፒታል ገብታለች እናም አሁን 3ሺህ ብር ስለተባልኩኝ ከየትም ፈልገህ በፍጥነት ይዘህልኝ ና" ይለዋል። ጓደኛውም "እሺ 30 ደቂቃ ያህል ታገሰኝ" አለው እሺ ብሎ ሲጠብቀው 30 ደቂቃ አለፈ፡፡ ከዚያም ስልክ ሲደውልለት ስልኩ ጥሪ አይቀበልም ይላል ደጋግሞ ቢሞክርም ዝግ ነው በዚህ በጣም ይናደድና "እንዲያውም በቃ ተወው ያንተን ገንዘብ አልፈልግም ድሮም ጓደኛ አይወጣልኝም" ብሎ የጽሑፍ መልእክት ላከለት። ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ጓደኛው ሆስፒታል መጣ ገና እንዳየውም "ስማ ባታገኝ እንኳን ለምን ስልክህን ትዘጋለህ?" ብሎ ጮኸበት ጓደኛውም ረጋ ብሎ እንዲህ ሲል መለሰለት "ጓደኛዬ ስልኬን ዘግቼው አይደለም የማውቃቸውን ሰዎች ሁሉ ብድር ስጠይቅ የለንም አሉኝ ከዚያም አማራጭ ሳጣ ስልኬን ሽጬ ይኸው 3000 ብር ይዤልህ መጣሁ አለው" ከዚያም ጓደኛው አቅፎ ሳመው።

አንዳንዴ ሰዎች ለእኛ ብለው ደፋ ቀና እያሉ እና ዋጋ እየከፈሉ ነገር ግን ያሉበትን ሁኔታ ሳንረዳ እንዲሁ ነገሮች በምንፈልገው ፍጥነት ስላልሆኑ ብቻ ለንግግር አንቸኩል።

እግዚአብሔርም በችግር ቀን ደርሶ እንዲህ ከጎን የሚሆን፣ ሲኖር አብሮ በልቶ ሳይኖር የማይርቅ በመልካም ቀን ኖሮ በክፉ ቀን ጀርባ የማይሰጥ ሲሞላ ቀርቦ ሲጎድል የማይሸሽ ችግርን አብሮ የሚካፈል ቅን ወዳጅ ያድለን።

(ምንጩ ያልተወቀ)




ከሰይጣን በቀር ምንም ጠላት አይኑርህ፡፡የሰዎችን ስህተት አትመራመር፤ የባልንጀራህ ኃጢአት አትግለጥ፡፡ የባልጀራህ ውድቀት ደጋግመህ አታውራ፡፡ በራስህ ኃጢአት ላይ ፍረድ እንጂ በሌሎች ላይ አትፍረድ ገዢያቸው አይደለህምና፡፡ኃጢአትን በፈጸመ ሰው ላይ ወቀሳ አታብዛ አንተም ትበድላለህና፡፡ ነገር ግን ከኃጢአቱ ይመለስ ዘንድ ረዳትና መካሪ ሁነው፡፡ ከወደቀበትም የስህተት ሥራ እንዲወጣ አበርታው፡፡ ተስፋውን በእግዚአብሔር ላይ ቢያደርግ ኃጢአቱን ልክ በእሳት ፊት እንደወደቀ ገለባ ፈጥኖ እንደሚወገድለት ንገረው፡፡

ቅዱስ፣ ጥንቁቅ፣ ግልጽና ብልህ ሁን፡፡ እርጋታን የተላበሰ ሰብእና ይኑርህ፡፡ ደስተኛ ሁን፤ ሰላምታህ በፈገግታ የታጀበ ንጹህ ይሁን፡፡ ንግግርህ የታረመ አጭርና በጨው እንደተቀመመ ጣፋጭ ይሁን፡፡ ቃላቶችህ የተመጠኑ እና ጤናሞች ሁሉም የሚረዳቸው ይሁኑ፡፡የጓደኛህን ምስጢር አትግለጥ፤ ለሚወዱህ ሁሉ የታመንክ ሁን፡፡ ወደ ጭቅጭቅ እና ንትርክ ከመግባት ራህን ጠብቅ፡፡ የሚሰሙህ ሁሉ እንዳይጠሉህ ወደ ጠብ አትግባ፡፡

የምክር ቃል ከቅዱስ ኤፍሬም!!


+ ከሁሉ በኋላ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ታየኝ +

ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ምእመናን ስለ ጌታ ትንሣኤ ማስረጃ እያቀረበ ነው:: በዚያን ዘመን ለጌታ ትንሣኤ ማስረጃ ስትጠቅስ በማቴዎስ ወንጌል እንዲህ ይላል ብለህ እንዳትጠቅስ ገና ወንጌላት አልተጻፉም:: ቢጻፉም ማቴዎስ በሕይወት እያለ በቃሉ መመስከር ሲችል ጽሑፉን ማስረጃ ማድረግ አያስፈልግህም:: ስለዚህ ለመነሣቱ ማስረጃዎች ከተነሣ በኋላ ያዩት ሰዎች ነበሩ:: በሕይወት ያሉትን የዓይን ምስክሮችን መጥቀስ ይቻላል:: የዓይን እማኞች ምስክርነት ከጽሑፍ በላይ የታሪክ ማስረጃ ነው:: ስለዚህ ጳውሎስ ስለ ጌታ ትንሣኤ "እነ እገሌ አይተውታል" እያለ መዘርዘርን መረጠ::

ጌታ ከተነሣ በኋላ እንደ ቀድሞው ለሁሉ አልታየም:: እርሱን ለማየት የተገባቸው ጥቂት ወደ ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ነበሩ:: በማኅበር ያዩት አሉ:: በግል ያዩት አሉ::
ያዩት ነገር ወንጌል የሆነላቸው ብፁዓን ዓይኖች ያሏቸው እንዴት የታደሉ ናቸው? የተሰቀለውን ተነሥቶ ያዩት! ዳግም በሚመጣበት አካል የተገለጠላቸው ምንኛ የታደሉ ናቸው? ከመድኃኔ ዓለም አፍ ተቀብለው ኪዳን ያደረሱ! የጌታን ቅዳሴ ተቀብለው ያስቀደሱ! የትንሣኤው ማግስት ምስክሮች እንዴት ዕድለኞች ናቸው? ቢሞቱም እንኳን መነሣታቸውን በጌታ ትንሣኤ አይተው ደስ ብሎአቸው ያንቀላፉ እነርሱ ምንኛ የታደሉ ናቸው?

ቅዱስ ጳውሎስ በወንጌል ከተጠቀሱት ከነ ኬፋ በተጨማሪ ለይቶ ጌታ ለማን ለማን እንደታየ ገለጸ:: ለያዕቆብ ታየ ብሎ የእልፍዮስን ልጅ ለይቶ ጠቀሰው:: የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፍት እንደሚሉት ይህ ሐዋርያ ከሌሎች በተለየ የጌታን ትንሣኤ ሳላይ እህል አልቀምስም ብሎ የተሳለና አክፍሎትን የጀመረ ነበርና ጌታ ለይቶ ክብሩን አሳይቶታል:: ከዚያም ለዐሥራ ሁለቱ ታየ ብሎ የጌታን ድኅረ ትንሣኤ አስተርእዮ ዘረዘረ:: እኔ ማለትን የማይወደው ትሑት ቅዱስ ጳውሎስ "ከሁሉ በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ አለ::

ጭንጋፍ ምንድር ነው? ጭንጋፍ (ጸዕጻዕ/ ተውራድ) ለፅንስ የሚነገር ቃል ነው:: መወለድ ያለበትን ጊዜ ያልጠበቀ ያለ ጊዜው የተወለደ ፅንስ ነው:: በመጠኑ ከሌላው ጊዜውን ከጠበቀ ፅንስ የሚያንስ ሲሆን ዕድገቱን በተገቢው ጊዜ ከሚወለድ ልጅ ጋር ለማስተካከል ሲባል በሙቀት ማቆያ ክፍል እንዲቆይ ይደረጋል:: ይህ ፅንስ ሲወለድ በሕመም ውስጥ ሆኖ ተሰቃይቶ ተጨንቆ ነው::

ቅዱስ ጳውሎስ ራሱን ለመግለጽ የተጠቀመበት ይህ አንድ ቃል የሕይወት ታሪኩን ጠቅልሎ የያዘ ድንቅ ቃል ነበር::
ቅዱስ ጳውሎስ ምንም እንኳን የቤተ ክርስቲያን ብርሃን የሆነ ሐዋርያ ቢሆንም እንደ ዓሥራ ሁለቱ ሐዋርያት በጊዜው የተጠራ አልነበረም:: እርሱ ከሐዋርያት ጋር አብሮ በዳግም ልደት የተወለደ ሳይሆን ያለ ጊዜው ክርስቶስ ባረገ በስምንተኛው ዓመት የተጠራ ነበረና ራሱን ካለ ጊዜው ከተወለደው ፅንስ ጋር አመሳስሎ እንደ ጭንጋፍ የምሆን ብሎ ጠራ::

ጭንጋፍ ሲወለድ በመጠኑ ከሌላው ፅንስ ያነሰ ይሆናል::
ቅዱስ ጳውሎስም ራሱን ጭንጋፍ ካለ በኋላ "እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ስላሳደድሁ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ" ብሎ አብራርቶታል:: (1ቆሮ 15:9)

ልጅ ጭንጋፍ ሆኖ ሲወለድ በሥቃይ ነው:: ጤና ያጣል ይታመማል:: እናቲቱም ትታወካለች በድብታ በጭንቀት ትቸገራለች:: ባለሙያዎቹ እንደሚሉት እናት ያለ ጊዜው ከተወለደ ልጅዋ ጋር እናታዊ ትስስር ለመፍጠርና የእናትነት ፍቅርዋን ለመሥጠት ባልጠበቀችው ጊዜ የመጣ በመሆኑ ምክንያት ለጥቂት ጊዜ ትቸገራለች:: በአጭሩ ጭንጋፍ ሆኖ ሲወለድ እሱም ይሰቃያል እናቱንም ያስጨንቃል:: ወዲያው እንደሌላ ሕፃን በሰው እጅ አይታቀፍም:: ከተፈጥሮአዊ እስከ ሰው ሠራሽ እንደየጊዜው እየዘመነ በሔደው የልጅ ሙቀት መስጫ መንገድ እየታገዘ የሰውነት አካሎቹ በአግባቡ መሥራት እስከሚችሉና በሽታ መቋቋም እስከሚችል ይቆያል::

ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ጭንጋፍ ነበርኩ ያለው ለዚህ ነው:: በዳግም ልደት የተወለደው በደማስቆ መንገድ ወድቆ ሊቋቋመው ባልቻለው ብርሃን ተመትቶ ነበር:: "ሳውል ሳውል ስለምን ታሳድደኛለህ?" የሚል ድምፅ ሲሰማ ፅንስ ነውና ዓይኑን እንኳን መግለጥ አልቻለም ነበር::
ከተወለደ በኋላም ወዲያው ወደ ቤተ ክርስቲያን እቅፍ ወደ ሐዋርያት ማኅበር አልገባም:: እንደ ጭንጋፍ የምሆን እንዳለ ሙቀት ያስፈልገው ነበርና የሰው እጅ ሳያቅፈው ሦስት ዓመት በሱባኤ ቆይቶ በመንፈስ ቅዱስ ተማወቀ::

"ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም፥ ከእኔም በፊት ሐዋርያት ወደ ነበሩት ወደ ኢየሩሳሌም አልወጣሁም፥ ነገር ግን ወደ ዓረብ አገር ሄድሁ እንደ ገናም ወደ ደማስቆ ተመለስሁ። ከሦስት ዓመት በኁዋላ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣሁ" ብሎ ስለ መንፈሳዊ ኃይል መልበሱ ይናገራል:: (ገላ 1:15-18)

ጭንጋፍ ሆኖ የተወለደ ልጅ የሚገጥመው ችግር ከወላጆቹ ጋር በሥነ ልቡና ለመተሳሰር መቸገሩ ነው::
ቅዱስ ጳውሎስን ለማመንና እንደ ልጅ ለመቀበል የቤተ ክርስቲያን ማኅበርም ተቸግራ ነበር::
"ሳውልም ወደ ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ ከደቀ መዛሙርት ጋር ይተባበር ዘንድ ሞከረ፤ ሁሉም ደቀ መዝሙር እንደ ሆነ ስላላመኑ ፈሩት" ሐዋ 9:26 ስለዚህ ሐዋርያው እንደ ጭንጋፍ ነኝ አለ::

ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ጌታ መነሣት ምስክሮች ብሎ ሌሎችን ከዘረዘረ በኋላ "ከሁሉ በኋላ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ታየኝ" ብሎ ተናገረ:: ክርስቶስ ተነሥቶአል ወይ ብለው ሲጠይቁህ አዎ ተነሥቶአል እነ እገሌ አይተውታል ብለህ ዘርዝረህ
"ከሁሉ በኁዋላ ለእኔም ታየኝ" ብለህ መናገር መቻል እንዴት መታደል ነው!?

ወዳጄ ክርስቶስ መነሣቱን ታምናለህ:: ልክ ነህ ለብዙዎች ታይቶአል:: አንተስ ከሁሉ በኁዋላ ለእኔም ታየኝ ማለት ትችል ይሆን? ጌታ ከተነሣ በኁዋላ ላለፉት ሁለት ሺህ ዓመታት ለብዙዎች ታይቶአል:: ብዙዎቹ ቅዱሳን አይተውታል:: ቅዱስ እስጢፋኖስ አይቶታል : ቅድስት አርሴማ አይታዋለች : አቡነ ተክለ ሃይማኖት አይተውታል : አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ተመልክተውታል:: አባ ጳኩሚስ በዕንባ ተመልክቶታል : ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ አይታዋለች::

ሁሉም ቅዱሳን ብዕር ቢሠጣቸው ከዕንባ ጋር
"ከሁሉ በኁዋላ ለእኔም ታየኝ" ብለው የትንሣኤውን ማስረጃ ዝርዝር ይቀጥላሉ:: ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ በበረሃ ሲጸልይ አይቶት ነበርና ሰው ባገኘ ቁጥር
ወቅቱ የፋሲካ ሰሞን ባይሆንም እንኳን በፈገግታ ተሞልቶ
"ክርስቶስ ተነሥቶአል!" ብሎ ያበሥርና ሰላምታ ይሠጥ ነበር::

ጌታ ሆይ ለእኔ ለኃጢአተኛው የምትታየኝ መቼ ይሆን? ቸርነትህን አይቻለሁ! ፍቅርህን አይቻለሁ! ብሩሕ ገጽህን የማየው መቼ ይሆን? መች እደርሳለሁ የአምላኬንስ ፊት መቼ አየዋለሁ? እኔም እንደ ቅዱሳንህ "ከሁሉ በኁዋላ ለእኔ ታየኝ" ብዬ የተቀመጠውን ብዕር አንሥቼ የምጽፈው መቼ ይሆን? አቤቱ ፊትህን እሻለሁ! አቤቱ ፊትህን ከእኔ አትመልስ! አቤቱ ፊትህን እሻለሁ!

"ኢየሱስ ክርስቶስ በግዕ ዘቀራንዮ
ለላሕይከ ንትሜነይ ከመ ንርአዮ"
"የቀራንዮው በግ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ
ውበትህን ልናየው እንመኛለን"

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ማዕዶት 2012 ዓ ም
አዲስ አበባ
https://t.me/tsidq




አንድ መነኩሴ አባ እንጦርጦስን እንዲህ አለው አባቴ ባህታዊ ሆኜ በበረሐ ብቻዬን ድንጋይ ተንተርሼ ጤዛ ልሼ ድምፀ አራዊቱን ፀባዐ አጋንንቱ ታግሼ በብትውና መኖር ያምረኛል
አንድዳንድ ጊዜ ደግሞ ገዳም ገብቼ በበዓላት ተከትቼ  አጎውን ረድቼ አበውን አገልግዬ በፍቅር በማኅበር በገዳም መኖርም ያሻኛል

አንዳንድ ጊዜ በዓለም ትዳር መስርቼ ንስሓ ገብቼ በፈቃደ ካህን በምክር ፀንቼ ዐሥራቱ በኩራቱን አውጥቼ ሥጋውን ደሙን ተቀብዬ እንግዳ አስተናግጄ የታመመ ጠይቄ የታሰረ አስፈትቼ የተራበ አብልቼ  የተጠማ አጠጥቼ የታረዘ አልብሼ በሕግ በትዳር ፀንቼ ልጅ አሳድጌ መኖርም ያምረኛል ምከረኝ ምን ይሻለኛል ብሎ ጠየቀው
     አባ እንጦስም ሁሉንም ለእግዚአብሔር ብለህ ከሠራኸው ትድናለህ ብሎ መለሰለት
                እኛስ በምንሠራው ሥራ ውለን በምናድርበት ቦታ  እግዚአብሔር የሚከብርበት የሚመሰገንበት ይሆን  የምንሰራቸው ሥራዎችስ ማንን ደስ ለማሰኘት ይሁን ?
            ሳሙኤል ተመስጌን
              ቡሌ ሆራ(ሀገረ ማረያም)
               30/10/1014 ዓ/ም
https://t.me/tsidq




★ መረቡን ከታንኳይቱ በስተቀኝ ጣሉ ★

ስምዖንና ጓደኞቹ ዓሣ አጥማጆች ናቸው። ሌሊቱን ሙሉ ሲያጠምዱ አድረው አንድ ዓሣ እንኳን ሳይይዙ ነጋባቸው። ባዶ መረባቸውን እያጠቡ እያለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እነርሱ መጣ። አስተምሮ ከጨረሰ በኋላ ስምዖንን : "ወደ ጥልቁ ፈቀቅ በል መረቦቻችሁንም ለማጥመድ ጣሉ" አለው።
@deaqonhanok
ስምዖን ከአምስት ዓመቱ ጀምሮ ዓሣ ሲያጠምድ ያደገ የሃምሳ አምስት ዓመት ጎልማሳ ነው። ሆኖም "ጥርሴን የነቀልኩበት ሙያ ነው" ብሎ ሳይመፃደቅ "አቤቱ ሌሊቱን ሁሉ አድረን ስንደክም ምንም አልያዝንም።

ነገር ግን በቃልህ መረቦቹ እጥላለሁ" አለ። የጌታን ትእዛዝ አክብረው ወደ ጥልቁ ፈቀቅ ብለው መረባቸውን ሲጥሉ እጅግ ብዙ ዓሣ ያዙ ፣ መረቦቻቸውም ተቀደዱ። በሌላ ታንኳ የነበሩት ጓደኞቻቸውን እንዲያግዙአቸው ጠሩአቸው። ታንኳው እስኪሠጥም ድረስ መረቡ በዓሣ ተሞላ።
ይህንን ተአምር ያዩ ሁሉ ሲደነቁ ስምዖን ጴጥሮስ ግን ጌታችንን ፈራው። በዚህ ትልቅ ባሕር ውስጥ ያለውን መርምሮ ካወቀ በእኔ ልብ ውስጥ ያለውን ኃጢአትማ እንዴት ያውቅብኝ ይሆን? ብሎ ተጨነቀ ፣ የረከሰ ሕይወቱን አስቦ ራሱን ተፀየፈ።

ከኢየሱስ ጉልበት ላይ ወድቆ "ጌታ ሆይ እኔ ኃጢአተኛ ነኝና ከኔ ተለይ" አለው። ጌታ ግን "አትፍራ ከእንግዲህ ወዲህ ሰውን የምታጠምድ ትሆናለህ" አለው።

ያቺ ዕለት ስምዖን ጴጥሮስና ጓደኞቹ ጌታ ባዘዛቸው መሠረት መረብ እየጣሉ ዓሣ ማጥመድ የጀመሩባት ዕለት ሆነች። (ሉቃ 5:3)
ይህ ከተፈፀመ ከሦስት ዓመታት በኋላ ጌታችን በመስቀል ተሰቅሎ ሞቶ ከተነሣ በኋላ ትንሣኤውን ሙሉ በሙሉ ያላመኑት ስምዖን ጴጥሮስና ጓደኞቹ ዓሣ ለማጥመድ ወደ ባሕር ሔደው ነበር።

ጌታችን በዚህ ጊዜ ከመካከላቸው ተገኝቶ "አንዳች የሚበላ አላችሁ?" አላቸው። እነርሱም የለንም አሉት። ይህን ጊዜ "መረቡን በታንኳይቱ በስተቀኝ ጣሉት ታገኙማላችሁ" አላቸው።
@deaqonhanok
መረቡን ሲጥሉ ከዓሣው ብዛት የተነሣ ሊጎትቱት አቃታቸው። (ዮሐ 21:6)
በጌታ ትእዛዝ ዓሣ ሁለት ጊዜ የሚጠመድባት ይህች መረብ በዓሣ የተመሰልን እኛን የሰበሰበች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት።
በመጀመሪያው ዙር ዓሣ የማጥመድ ሥራ የተካሔደው "ወደ ጥልቁ በመሔድ ነበር" ቤተ ክርስቲያን ከዚህች ዓለም ባሕር ውስጥ ብዙዎችን አጥምዳለች። በዚህ ዓለም በኃጢአት ዐዘቅት ውስጥ ጠልቀው የገቡትን ሰዎች ሳይቀር መረብዋ ቤተ ክርስቲያን ወደ ጥልቁ ፈቀቅ ብላ አጥምዳ ሰብስባለች። በዚህ ነፍሳትን የማጥመድና ወደ መረቡ የማስገባት ሥራ ላይ የተመደቡት እነቅዱስ ጴጥሮስ ቢሆኑም ከዓሣዎቹ ብዛት የተነሣ ለብቻቸው ሊወጡት አልቻሉም።

ስለዚህ በሌላ ታንኳ የነበሩ ጓደኞቻቸውን ጠርተው መረቡን በዓሣ ሞሉት። እነዚህ በረዳትነት የተጠሩት የሐዋርያት ጓደኞች ምእመናንን ከዓለም ጥልቅ ውስጥ በትምህርት እየሳቡ ወደ መረቧ ቤተ ክርስቲያን ሲያስገቡ የኖሩ አርድእት ፣ ሐዋርያውያን አበው ፣ ሊቃውንትና ካህናት ናቸው። በጴጥሮስና በመሰሎቹ ትጋት ዛሬ ቤተ ክርስቲያን በብዙ ዓሣዎች ተሞልታለች። ዓሣዎቹ በበዙ ጊዜ መረቡ ተቀድዶ ነበር። እንደዚሁም ኃጢአተኛውን ከጻድቁ ክፉውን ከደጉ ሳትለይ ከሁሉም ዓይነት የሰበሰበችው ቤተ ክርስቲያን በየጊዜው በዓሣዎቿ ብዛት ብዙ የመቀደድ ፈተና ገጥሟታል።

አንዳንድ ዓሣዎች ከባሕር ከወጡ በኋላ ወደ ባሕር ለመመለስ ሲታገሉ ፣ አንዳንዶቹ ባሕር ውስጥ እያሉ እንደሚዋኙት ሊዋኙ ሲሞክሩ ፣ አንዳንድ ዓሣዎች መረብ ውስጥ ገብተው ሲፋለሙ መረቡን ቀድደውት ነበር። የእኛዋ መረብ ቤተ ክርስቲያንም ይህ ዓይነቱ በዓሣዎቿ ጦስ የመቀደድ ችግር ሁሌ እንደገጠማት እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ትቆያለች።

ይህ ሁሉ ችግር ግን ጌታችን ዳግም እስኪመጣ ድረስ ነው። ወደነ ቅዱስ ጴጥሮስ ድጋሚ መጥቶ መረቡን ጣሉ ያለው ጌታ ስለ ቤተ ክርስቲያንም ይህን ማለቱ አይቀርም። እስቲ ሁለተኛውን የዓሣ ማጥመድ ሥራ አስተውለን እናንብበው።

መጀመሪያ "ወደ ጥልቁ ጣሉ" ያለው ጌታ ከትንሣኤ በኋላ ግን "በስተቀኝ ጣሉ" ብሏል። ከጥልቁ ብዙ ዓሣዎች የሰበሰበችው መረብ ቤተ ክርስቲያን ጌታ ዳግም ሲመጣ ድጋሚ ዓሣ ትሰበስባለች።
@deaqonhanok
ያን ጊዜ ግን የምትሰበስበው "በስተቀኝ" ብቻ ነው። በዓሣዎችዋ ብዛት ስትቀደድ የኖረችው ቤተ ክርስቲያን ከትንሣኤ በኋላ ግን ዓሣዎችዋ ብዙ ቢሆኑም እንኳን አትቀደድም።
ምክንያቱም ጌታ "በስተቀኝ ጣሉ" እንዳለው ከትንሣኤ በኋላ ወደ መረቡ የሚገቡት ጌታ አስቀድሞ በቀኙ ያቆማቸው ቅዱሳን ሰማዕታት ምእመናን ናቸው። ቅዱሳን ደግሞ የቱንም ያህል በቁጥር ቢበዙ መረብዋ እንድትቀደድ አያደርጉም።

ጌታችን ዳግም መጥቶ መረብዋን ቤተ ክርስቲያን በሚያስጥልበት ጊዜ በስተቀኝ ሆነው ከሚገቡት ከነቅዱስ እስጢፋኖስ ፣ ከመጥምቁ ዮሐንስ ጋር ፣ ከሁሉም ቅዱሳን ሰማዕታት ጋር ለመገኘት ያብቃን።

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ




+ እኔ ግን እኔ አይደለሁም +

አውግስጢኖስ ፈጣሪ የለም ባይ እና በዝሙት የተበላሸ ሕይወት ይኖር የነበረ ሰው ነው:: በቅዱስ አምብሮስ ስብከት ከተመለሰ በኁዋላ ግን ይህ ሰው ፍጹም በንስሓ ተለውጦ በምንኩስና መንገድ ሔዶ እስከ ጵጵስና ደረሰ:: ይህንን የንስሓ ሕይወት መኖር ከጀመረ በኁዋላ ቀድሞ በአመንዝራነት ሕይወት ሲኖር ወዳጁ የነበረች አንዲት ሴት መንገድ ላይ ከሩቅ አይታ ተከትላ ጠራችው::
ወደ ቀድሞ ትዝታውና ኃጢአቱ መመለስ ያልፈለገው ይህ አባትም ጥሪዋን እንዳልሰማ ሆኖ በፍጥነት መሔድ ጀመረ::
ይህች ሴትም እየሳቀች :-
አውግስጢኖስ እኔ እኮ ነኝ! ብላ ጮኸች

እርሱም ወደ እርስዋ ዞሮ :- "እኔ ግን እኔ አይደለሁም" አላት::

ክርስትና የወደቀ የሚነሣበት የረከሰው የሚነጻበት ሕይወት ነው:: በዚህ መስመር ያለፉ ሁሉ ትናንትን እየተዉ ሌላ ማንነትን ይለብሳሉ:: ትልቁ ፈተና ሰዎች ተነሥተህ እያዩህም እንኩዋን መውደቅህን አለመርሳታቸው ነው:: ፈጣሪ "ከእንግዲህ አትበድል" ብሎ ይቅር ቢልህም ሰዎች ግን ይቅር አይሉህም:: "ድመት መንኩሳ ዓመልዋን አትረሳ" እያሉ እየተረቱ ወደ ነበርክበት እንድትመለስ ይገፉሃል እንጂ እንድትለወጥ አይፈቅዱልህም::

ሳውል አሳዳጅ ነበረ ዛሬ ግን ሐዋርያ ነው:: ብዙ ክርስቲያኖች ግን እርሱን ለማመን ተቸግረው ነበር:: ከመመረጡ ጀምሮ "ኸረ እርሱ አይሆንም" ብለው ለፈጣሪ ምክር የሠጡም ነበሩ:: ከተመረጠ በኁዋላም ለመቀበል ተቸግረው ከሐዋርያት አሳንሰው ያዩት አልጠፉም:: እርሱም በትሕትና "ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ" ቢልም : "ጭንጋፍ" ብሎ ራሱን ያለ ጊዜው ከሚወለድ ጽንስ ጋር አነጻጽሮ ዘግይቶ የተጠራ መሆኑን ቢናገርም ከሐዋርያት በምንም የማያንስ ሐዋርያ ነበረ:: እነርሱ በትናንት ማንነቱ ሊያዩት ቢሹም እርሱ ግን "እርሱ አልነበረም" እርሱ መኖር አቁሞ በእርሱ ይኖር የነበረው ክርስቶስ ነበረ::

አንዳንድ ሰዎች የማያምኑህ ከክፋት ተመልሰህ መልካም ስትሆን ብቻ አይደለም:: በጣም መልካም ስትሆንላቸውም አያምኑህም:: ስታከብራቸው ምን አስቦ ነው? ብለው ይጠራጠራሉ:: መልካም ስታደርግላቸው "ምነው ደግነት አበዛሽ? ተንኮል አሰብሽ እንዴ? "ይህቺ ጠጋ ጠጋ ዕቃ ለማንሳት ነው" "there is no free lunch” ብለው ሊሰጉ ይችላሉ:: መልካም የሚያደርግላቸውን ሁሉ ሊያርድ የሚያሰባቸው የሚመስላቸው ሰዎች አሉ:: ፍቅር የትግል ስልት የሚመስላቸው ጨብጠውህ ጣታቸው እንዳልጎደለ የሚቆጥሩ ዓይነት ተጠራጣሪ ሰዎች አሉ::

ዮሴፍ የገጠመው ይህ ነበር:: በሃያ ብር ሸጠው ግብፅ ያወረዱት ወንድሞቹን ይቅር ብሎ በፍቅር ተቀበላቸው:: አባታቸውን ያዕቆብን አስመጥቶ በክብር በግብፅ እንዲኖሩ አደረጋቸው:: ከዓመታት በኁዋላ አረጋዊው ያዕቆብ ሞተ::
ይሄን ጊዜ የዮሴፍ ወንድሞች ድንገት ስብሰባ አደረጉ: "አባታችን ከሞተ በኁዋላ ቢበቀለንስ?!" ብለው ስጋታቸውን ተመካከሩ::
ስለዚህ ዶልተው መጡና እንዲህ አሉት :-
አባታችን ከመሞቱ በፊት እንዲህ ሲል ተናዝዞ ነበር:: እባክህን የወንድሞችህን በደል ይቅር በል:: (ዘፍ 50:15-21) ዮሴፍ ይኼን ሲሰማ አለቀሰ:: ይቅርታን አድርጎም አለመታመኑ አመመው::

እርሱ ለእነርሱ ድሮም ክፉ አልነበረም:: አሁን ደግሞ ላደረሱበት በደል እንኩዋን ፈጣሪውን የሚያመሰግን ሆኖአል:: "እናንተ ክፉ ነገርን አሰባችሁብኝ፤ እግዚአብሔር ግን ዛሬ እንደ ሆነው ብዙ ሕዝብ እንዲድን ለማድረግ ለመልካም አሰበው" ነበር ያለው:: ምንም በደል ቢደርስበት እነርሱ አልተለወጡ ይሆናል እንጂ እርሱ ግን ትናንት የሚያውቁት ዮሴፍ አይደለም:: "እኔ ግን እኔ አይደለሁም" አላቸው::

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ታኅሣሥ 30 2012 ዓ ም
አዲስ አበባ

https://t.me/tsidq




+ አባቶቻችን እንዲህ አሉ +

"ለምድር የሕይወት ዘመንህን ሁሉ ብትሠጣት በመጨረሻ የምትሠጥህ መቃብር ብቻ ነው:: ለሰማይ ግን ራስህን ብትሠጥ በመጨረሻ የምትሠጥህ ዙፋንን ነው" ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

"እግዚአብሔር ከኃጢአተኛ ይርቃል ብሎ ማሰብ ፀሐይ ከዓይነ ሥውር [ስላላያት] ትርቀዋለች ብሎ እንደማሰብ ነው" ቅዱስ እንጦንስ

"እግዚአብሔር ለአንተ ሲል ራሱን ዝቅ አደረገ:: አንተ ግን ለራስህ እንኳን ስትል ራስህን ዝቅ ማድረግ እንዴት ያቅትሃል?" ቅዱስ መቃርዮስ

"ለሰውነትህ ያሰኘውን ነገር ሁሉ ከሠጠኸው ሰውነትህ የማትፈልገውን ነገር ሁሉ ይሠጥሃል:: ሰውነትህን ሠልጥንበት እንጂ አንተ ለሰውነትህ አትገዛ" አቡነ ካራስ

"ሰይጣን ሊያስመስለው የማይችለው ተግባር ትሕትና ብቻ ነው" ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው

"ሰሎሞን 'ዝም ለማለት ጊዜ አለው ለመናገርም ጊዜ አለው' አለ:: ዝምታን ያስቀደመው በዝምታችን ወቅት የመናገርን ጥበብ ስለምንማር ነው" ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ

"ቁጣ በሕይወት እስካለች ድረስ የብዙ ደስታ አልባ ልጆች እናት ሆና ትቀጥላለች" ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ግንቦት 28 2013 ዓ ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
https://t.me/tsidq




+ የተሠጠህን ቁጠር +

ሔዋን ከዕባብ ጋር እየተነጋገረች ነው:: የመጀመሪያ ጥፋትዋ ካለደረጃዋ ወርዳ ከዕባብ ጋር ወዳጅነት መጀመርዋ ሳይሆን አይቀርም:: ዕባብ ደግሞ የስይጣን አንደበት ነበረ::

ሰይጣን እንዲህ አላት :- በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን? አላት።
ልብ አድርጉ እግዚአብሔር "ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ" አላለም:: የከለከለው አንዲት ዛፍ ነው:: ሰይጣን ግን ሁሉን ተከልክላችሁዋል? ብሎ እንዳላዋቂ ጠየቀ:: ሰይጣን በመጽሐፍ ቅዱስ ንግግሩን የከፈተው በውሸት ነበረ::

ዓላማው ከሔዋን መረጃ ለማግኘት አልነበረም:: ሔዋን እስከዛሬ ያላሰበችውን ማሳሰብ ነበር:: ብሉ ተብሎ ከተሠጣቸው ብዙ ሺህ ዛፍ ይልቅ የተከለከሉትን አንዲት ዛፍ አሳይቶአት ሔደ:: ከዚያች ደቂቃ ጀምሮ ስላልተሠጣት ማሰብ ጀምራ ደስታዋን አጣች:: የተከለከለችውን በልታ የተሠጣትን ብዙ ሥጦታ ከነሠጪው አጣች::

ወዳጄ የቀደመው እባብ ዛሬም መርዙን ይረጫል

በሕይወታችን ከተሠጠን ብዙ ነገር ይልቅ ያልተሠጠንን ጥቂት ነገር እናስባለን:: ገንዘብ እንደሌለህ እያሰብክ ጤና እንዳለህ ትረሳለህ:: ጫማ እንደሌለህ እያሰብክ እግር እንዳለህ ትረሳለህ:: አልጋ እንደሌለህ እያሰብክ እንቅልፍ እንዳለህ ትረሳለህ::
ስለዚህ ውስጥህ ያለውን የዕባቡን ድምፅ አትስማ ከሌለህ ይልቅ ያለህ ይበልጣልና የተሠጠህን ቁጠር::

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሰኔ 9 2012 ዓ ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ! በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)

ሌሎች እንዲያነቡትም Share ያድርጉ :
https://t.me/tsidq




እግዚአብሔር የሁከትና የግጭት አምላክ አይደለም። ስለዚህ አንተም በእግዚአብሔርና በባልንጀራህ ላይ የምታደርገውን ሁከትንና ግጭትን አቁም። እግዚአብሔር እንደ ምን ባለ ባሕርዩ እንደ አዳነህ በማስተዋል ከሰው ኹሉ ጋር በሰላም ኑር። ለምን መሰለህ? "የሚያስተራርቁ ንዑዳን ክቡራን ናቸው፤ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉ" ነው የሚለው (ማቴ. 5:9)። እንደዚህ ያሉ ሰዎች ናቸው ወልደ እግዚአብሔርን የሚመስሉት፤ አንተም ይህን ብታደርግ እርሱን ትመስለዋለህና ከኹሉ ጋር በሰላም ኑር (ተራረቅ)።

ባልንጀራህ ጎድቶህ ይኾናል። ዳሩ ልንገርህ፥ አንተም ስማኝ! ወዳጄ የምትለው ሰው ሳይቀር በጎዳህ መጠን፥ ምንዳህም የዚያኑ ያህል ብዙ ነው። ክቡር ዳዊት ይህን አስመልክቶ ሲናገር አልሰማኸውምን? “ሰላምን ከሚጠሉ ጋር ነፍሴ ብዙ ጊዜ ኖረች” ነው ያለው (መዝ.119፥6)። ይህ ፍቅር ነው፤ ይህ ፍቅርም ከሰዎች አስተሳሰብ የራቀ የመጠቀ ነው፤ ቅሩባነ እግዚአብሔር የሚያደርገንም እርሱ ነው። ክፋትን ካለማሰብ በላይ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝው ምንም ምን የለምና። እውነቱን ልንገርህ! ለበደልህ ኹሉ ሥርየትን የሚሰጥህ ይህ ነው፤ ከእስራትህ ኹሉ የሚፈታህ ይህ ነው። ግጭትንና አታካሮን የምንፈጥር ከኾንን ግን ከእግዚአብሔር እንርቃለን። ከግጭትና ከአታካሮ ጥላቻ፥ ከጥላቻም ተዘክሮተ እኪት ይከተላልና።

[ቅ. ዮሐንስ አፈ ወርቅ፥ ፊልጵስ. ድር. ፲፬ ]
https://t.me/tsidq



Показано 20 последних публикаций.