፨ ብጣሽ፨
ብጣሽ ቃል ብጣሽ ጨርቅ ብጣሽ እንጀራ
ብጣሽ ሃሳብ... ብጣሽ... ብጣሻም ፤ ብጣሽ ስንጠላ ደሞ... ካልተቀደደ ሙሉ ጨርቅ የተሰራ ይመስል... እድሜ ልክ አዲስ ማይበጠቅ ይመስል... መጣፊያ የሚሆን ብጣሽ አንፈልግ ይመስል... ባንፀባራቂው በቀለማችን በጥንካሬው ስንመካ
አይቀደድ ይመስል... ስናዳላ
የጉድ ቀን አይመጣ ይመስል ፣ ሰው በተሰበሰበት ከወደመቀመጫው አይተረተር ይመስል... ያ ብጣሽ ጨርቅ አያስፈልግ ይመስል
ከ ክር ያልተሰራ ይመስል... እንደመሰሎቹ... ፤ በክር ይሰፋ ዘንድ የክር ክምር በዛፍ ቅርንጫፍ መሬቱን እየጫረ ተክዞ አንዴ በልቡ እንደው ፈጣሪዬ መች ነው እኔም ከጨርቅ እኩል ምሆነው መች ነው እኔም ብጥቅ የምሸፍን መች ነው ሰው( ጨርቅ) የምሆነው ብሎ እየፀለየ... ስራ ፈቱ እንዲጣፍ ተመኘ... በሌላ ጨርቅ መቀደድ ላይ የህይወቱ ትርጉም ተንጠልጥላ እያያት ነይ ውረጅ ክር ሁሉ እኩል ነው አላላትም... መንጠልጠል መቀጠል ይቀላላ
ስወጣ አስፍቶ ሞልቶ ነው የሰጠኝ ቀለሜም ሚወይብ አይመስል ሲል ሲመካ ይቆይና... እህም የቅዱ ቀን ሲመጣ... ኪሮሽ ቅድ ሲያደርጉት ይተርፍና... ሸሚዝ ሊሰሩበት ይተርፍና... በ አጋጣሚ መጣፊያ ሆኖ ይቀራል... ከልባሽነት መደ መጠገኛ ሲዞር ትምክህቱ ውሃ ሲበላው( ጨርቁ ሲታጠብ በሉ ከተመቻችሁ) እንደ አዲስ መፈጠር እንዳ... እንዳዲስ... ሌላ ምኞት ይወለዳል... ክር
ክር ክርን ልትሰፋ በመርፌ አይን አልፋ
ክር እኔ እሻል ብላ ተደርባ ከ ወደታች ተጠምጥማ ታስራ ሌላ የክር ክምር ልታገናኝ... ሰብ(ፍ) ብላ ትመጣለች... ባለ ተራ እድለኛ ከ ኩራት ከፍታ የወደቀ ቀኑን ጠብቆ ይቀላቀላል በክር ጉልበት ( እሱም በሆነበት) ምናል ደና ቦታ ቢሆን
ሰፍቶኝ ከተቦተረፈው ከ ወደመቀመጫው ጣፍኩት
እኔ ስለቦታ ስለተፈጥሮ እሷ ስለ ክር ስለ ጥለት ስታወራ የተጋመድንበትን ተፈጥሮ ካድን
( የገባው ገብቶታል)
ውሃ
@wuhachilema
ብጣሽ ቃል ብጣሽ ጨርቅ ብጣሽ እንጀራ
ብጣሽ ሃሳብ... ብጣሽ... ብጣሻም ፤ ብጣሽ ስንጠላ ደሞ... ካልተቀደደ ሙሉ ጨርቅ የተሰራ ይመስል... እድሜ ልክ አዲስ ማይበጠቅ ይመስል... መጣፊያ የሚሆን ብጣሽ አንፈልግ ይመስል... ባንፀባራቂው በቀለማችን በጥንካሬው ስንመካ
አይቀደድ ይመስል... ስናዳላ
የጉድ ቀን አይመጣ ይመስል ፣ ሰው በተሰበሰበት ከወደመቀመጫው አይተረተር ይመስል... ያ ብጣሽ ጨርቅ አያስፈልግ ይመስል
ከ ክር ያልተሰራ ይመስል... እንደመሰሎቹ... ፤ በክር ይሰፋ ዘንድ የክር ክምር በዛፍ ቅርንጫፍ መሬቱን እየጫረ ተክዞ አንዴ በልቡ እንደው ፈጣሪዬ መች ነው እኔም ከጨርቅ እኩል ምሆነው መች ነው እኔም ብጥቅ የምሸፍን መች ነው ሰው( ጨርቅ) የምሆነው ብሎ እየፀለየ... ስራ ፈቱ እንዲጣፍ ተመኘ... በሌላ ጨርቅ መቀደድ ላይ የህይወቱ ትርጉም ተንጠልጥላ እያያት ነይ ውረጅ ክር ሁሉ እኩል ነው አላላትም... መንጠልጠል መቀጠል ይቀላላ
ስወጣ አስፍቶ ሞልቶ ነው የሰጠኝ ቀለሜም ሚወይብ አይመስል ሲል ሲመካ ይቆይና... እህም የቅዱ ቀን ሲመጣ... ኪሮሽ ቅድ ሲያደርጉት ይተርፍና... ሸሚዝ ሊሰሩበት ይተርፍና... በ አጋጣሚ መጣፊያ ሆኖ ይቀራል... ከልባሽነት መደ መጠገኛ ሲዞር ትምክህቱ ውሃ ሲበላው( ጨርቁ ሲታጠብ በሉ ከተመቻችሁ) እንደ አዲስ መፈጠር እንዳ... እንዳዲስ... ሌላ ምኞት ይወለዳል... ክር
ክር ክርን ልትሰፋ በመርፌ አይን አልፋ
ክር እኔ እሻል ብላ ተደርባ ከ ወደታች ተጠምጥማ ታስራ ሌላ የክር ክምር ልታገናኝ... ሰብ(ፍ) ብላ ትመጣለች... ባለ ተራ እድለኛ ከ ኩራት ከፍታ የወደቀ ቀኑን ጠብቆ ይቀላቀላል በክር ጉልበት ( እሱም በሆነበት) ምናል ደና ቦታ ቢሆን
ሰፍቶኝ ከተቦተረፈው ከ ወደመቀመጫው ጣፍኩት
እኔ ስለቦታ ስለተፈጥሮ እሷ ስለ ክር ስለ ጥለት ስታወራ የተጋመድንበትን ተፈጥሮ ካድን
( የገባው ገብቶታል)
ውሃ
@wuhachilema