ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


ይህ ቻናል ዓላማው የሰው ልጆችን በተለይም የኢት.ኦ.ተዋህዶ እምነት ተከታዮችን የኢትዮጵያ ትንሳኤ እጅግ ቅርብ መሆኑን ለማሳውቅ፤ ዝግጅት እንዲያደርጉ እና ተደብቆ የቆየውን ''ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክታትን'' ለሰው ልጆች ማዳረስ ነው። መልእክቱን አዳምጡ።ለአዳም ዘር ሁሉ እንዲዳርስ የበኩሎዎን ይወጡ!!
ግሩፑ @yealemberhan
ለጥያቄ @etberhan

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


ከራእይ_ዮሐንስ_20_በተለያዩ_ጊዜያት_የተሰጡ_መግለጫ_፡_ትምህርትና_ማሳሰቢያዎች2_.pdf
7.2Мб
🟩 ከራዕይ ዮሐንስ 20 በተለያዩ ጊዜያት የተሰጡ
መግለጫዎች፣ትምህርቶችና ማሳሰቢያዎች
🟨 ሙሉ ክፍል

🟥 ከ2012-2016 ዓ.ም
ድረስ የወጡ

8/07/2017 ዓ.ም












ልዩ ማሳሰቢያ ከራዕይ ዮሐንስ 20

የካቲት - 28 - 2017 ዓ.ም




በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን እግዚአብሔር በዚ ዘመን ፈቃዱን የገለጸበት መልእክትና ከዘመኑም ጥፋት በሥጋም በነፍስም መትረፍያ ቃልኪዳን እንጂ ሃይማኖት አይደለም። ይሄ ለሚያምን ሰው የእግዚአብሔርን ቸርነት ማድነቂያ እንጂ መሰናከያ መሆን አልነበረበትም። እውነቱን በምን ልወቅ፣ በጥርጥርም ያለ በምን ልጽና ለሚል ሰው-
፩. በእምነት እግዚአብሔርን በመጠየቅ- ይሄ እግዚአብሔርን አባቱ ላደረገ፣ በንስሐ፣ በአቅሙ እንደፈቃዱ እየኖረ ላለ ሰው እርሱን መጠየቅ ድፍረትና ግብዝነት ሳይሆን የልጅነት ሥልጣኑ ነው። መጽሐፍ እንደሚል እግዚአብሔር የቅርብ አምላክ እንጂ የሩቅ ስላልሆነ በንስሐ፣ በጾም፣ በጸሎትና በዕንባ ለሚጠይቀው በሕልምም በራእይም በሕይወትም በሰውም ልቡናንም በመምራትና በማብራት እንዲሁም እንደየጸጋው ለጠየቀው ሰው እርሱ ባወቀ በተለያየ መንገድ መልስን ሊሰጥ የታመነ አምላክ ነው።
፪. መልእክቱን ከቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና አንፃር በመመርመር- ሁሉንም መልእክቶች ሆነ አባቶች ያስተላለፉትን ትምህርቶች በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ዶግማና ቀኖና መነጽርነት ብንመረምረው ከአዕማደ ምሥጢር፣ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን፣ ከነገረ ማርያም፣ ከነገረ ቅዱሳን፣ ከአበው ትውፊትና ወግ ያፈነገጠው የቱ ላይ ነው? ስለቃልኪዳኑ ሰንደቅ ዓላማና የተከበሩ ቃላት ብናነሳ ከመጽሐፍ ቅዱስ የነ ሊቀ ነቢያት ሙሴና እስራኤላውያን፣ ከቅዱሳን ታሪክ ደግሞ የነ ቅዱስ አንባ አብራም ግብጻዊ ምሥክር አለን። ስለውግዘትም ብናነሳ ከመጽሐፍ ቅዱስ የነ ነቢዩ ኤልያስ ከቅዱሳንም የነ ቅዱስ በጸሎተ ሚካኤል ምሥክር አለን። ስለጽዋም ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ከታሪክ፣ ከአበው ትውፊት ብዙ ምሥክር አለን። በእግዚአብሔር መንፈስቅዱስ መሪነት ብንመረምረው ስለእውነተኝነቱ እንጂ የምንነቅፍበትን ነገር አናገኝም።
፫. የሕሊናና የዘመኑ ምሥክርነት- ራሱን ለማያታልልና እምነት ላለው ሰው በሐገራችንም ሆነ በዓለም እየሆነ ያለው በእግዚአብሔር ቁጣ እንደሆነ ይረዳል። መልእክታቱም ገና ከዓመታት በፊት ስለመጻኢ ሁኔታ በርግጥ መናገራቸው ከእግዚአብሔር መንፈስቅዱስ ስለመሆናቸው ማስረጃ ነው። “ትንቢትን አትናቁ፤ ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ፤”— 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥20-21 እንደሚል መጽሐፍ ማነው ተናጋሪው በሚል የተላለፈውን መልእክት ሐሳብ ችላ ማለትና መናቅ ከጥፋት ይጥላል። ድምጹን ብቻ የሰሙት እነ አብርሃም እነ ኖኅ አንተ ማነህ ብለው እግዚአብሔር በክፉ ቢመራመሩት ዛሬ የእምነት አባቶቻችን አይሆኑም ነበር። የነነዌ ሰዎችም ከዛ በፊት ስለማያውቁት ስለነቢዩ ዮናስ ማንነት ቢመራመሩና ቢንቁ ንስሐም ባይገቡ በተቀጡ ነበር። ጃንደረባው ቅዱስ ባኮስ በፊት አይቶት ስለማያውቀው ስለቅዱስ ፊልጶስ ማንነት ቢመራመርና ቢንቅ ባልተጠመቀ ለኢትዮጵያም ምክንያት ባልሆነ ነበር። አሁንም እነማን ናቸው ሳይሆን መልእክቱ ምን ይላል ብለን በቅንነት እውነትን በመፈለግና በእግዚአብሔር መንፈስቅዱስ መሪነት እንፈትሸው። እኛም የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነታችን፣ በተስፋችነ በቃልኪዳናችን እንጽና። ጌታችን እንዳለው “ኢየሱስ ግን፦ ማንም ዕርፍ በእጁ ይዞ ወደ ኋላ የሚመለከት ለእግዚአብሔር መንግሥት የተገባ አይደለም አለው።” — ሉቃስ 9፥62 
ወደ ኋላ እንዳንመለከት ዕንቁአችን እንዳንጥል እንጽና እንበርታ !
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር!

19/05/2017 ዓ.ም


መጨረስ በራሱ ታላቅ ነገር ነው ወገኖቼ!!
-----/////////-------/////////--
በሩጫ የሚሮጥ ሰው ውድድር ውስጥ የገባ ሰው፡፡42 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውስጥ ገብቶ ከሆነ ያን ለመጨረሽ ብዙ ይሮጣል ብዙ  ይደክማል ፡፡ብዙዎች አስር ሺሆች ሆነው ሲሮጡ አይታችኀችኀል፡፡
ወደ መጨረሻ የሚመጡት  መቶ ሰው ሁለት መቶ ሰው   ምናምን ነው ወደ መጨረሻ የሚመጣው፡፡
መጨረስ በራሱ ታላቅ ነገር ነው፡፡ወገኖቼ !!
በማረግ በአንደኝነት በሁለተኝነት በሥስተኝነት በዓራተኝነት በአምስተኝነት በአስረኝነት እያለ መውጣቱን ተውት፡፡መጨረስ በራሱ በጎዳናው ላይ በሩጫው ላይ ተገኝቶ እፍጻሜው ድረስ መሄድ   ትልቅ ነገር ነው ወገኖቼ !!
📌 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
እምነት  ፤ ተስፋ ፤ ፍቅር ትምህርት  ክፍል -3ቀ ላይ የተወሰደ፡፡


ሁሉም ሰው ሁሉንም አያውቅም።
===================
ለነቢዩ ኢሳይያስ የተገለጸለት
ለነቢዩ ኤርምያስ የተገለጸለት
ለነቢዩ ሕዝቅኤል የተገለጸለት
እንዲሁም ለሁሉም ነቢያቶች የተገለጸላቸው ይለያያል።
ነገር ግን አንዱ ነቢይ ሁሉንም እኔ ብቻ ነው የማውቅ ብሎ ሌላውን ነቢይ ሲነቅፍ ሲተች አልታየም።
ለምሳሌ ድንግል በድንግልና ጸንሳ በድንግልና እንደምትወልድ ስሙንም አማኑኤል እንደምትለው ለነቢዩ ኢሳይያስ ተገልጾለት።ተናገረ።
ለነቢዩ ኤርምያስ ደግሞ በሠላሳ ብር እንደሚሸጥና ክርስቶስ እንሚባልም ተገልጾለት ተናገረ።
ነቢዩ ሚክያስም ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም እንደሚወለድ ተገልጾለት ተናገረ።
ሁሉም እግዚአብሔር የገለጸላቸውን ተናገሩ።
እግዚአብሔር እኮ ሁሉንም ለነቢዩ ኢሳይያስ  ገልጾለት ሁሉንም መናገር ይችል ነበር የሁሉም ክብር ይገለጽ ዘንድ እንጂ።
እናም ነቢዩ ኢሳይያስ  ሁሉንም አውቃለሁ ብሎ ነቢዩ ሚክያስ የተናገረውን ውሸት ነው ክርስቶስ በቤተልሔም አይወለድም አላለም።
ስለዚህ ሁሉም ሰው ሁሉንም አያውቅምና
ሁሉን አውቃለሁ ብሎ ምሥጢሩን ሁሉ ሳይመረምር ዝም ብሎ ከሚናገር ሰው በዚህ ዘመን መራቅ ብልህነት ነው።

ማቴዎስ 11፥6 ላይ እንደተጻፈው።ጌታ
ለድሆችም ወንጌል ይሰበካል፤ በእኔም የማይሰናከለው ሁሉ ብፁዕ ነው።

ሲል ተናገረ።እውነት በዚህ ዘመን በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት የማይሰናከል ምንኛ ብጹዕ ነው።

ኢየሱስ ክርስቶስ ሰማይና ምድርን አሳልፎ ለፍርድ የሚመጣው እኮ ቀድሞ መጥቶ ተወልዶ ተጠምቆ ተርቦ ተጠምቶ ንስሓ ግቡ ብሎ የታመሙትን ፈውሶ ለምጻሞችን አንጽቶ ወንጌልን አስተምሮ ተሰቅሎ ሙቶ ተነስቶ አርጎ ይህንን ሁሉ አድርጎ ቃሉን በናቁት እና ባቃለሉት ላይ ነው የሚፈርደው።ይህንን ሁሉ ባያደርግ ኑሮ ለፍርድ ባልመጣም ነበር።
ታድያ ዛሬስ በዚህ አመጸኛ ትውልድ ላይ ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን የተሠጠው ንጉስ ቴዎድሮስስ ቀድሞ ሳያስተምር የሚገሰጸውን ሳይገስጽ ሳያስጠነቅቅ እንዴት ይመጣል?
የሚፈርደው እኮ በዚህ መልእክቴ እንዲህ አላልኩህም ነበር?ለምን ቃሉን ሰምተህ ንስሓ አልገባህም ብሎ እኮ ነው?

እናም ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃንን መልእክትን  አጣጥሎ ልክ አዲስ እምነት እንደሆነ አድርጎ ህዝቡን ማሰናከል እጅግ ከባድ ፍርድ ውስጥ መግባት ነውና።
ሁሉም ሰው ሁሉን እንደማያውቅ ተረድተን መልእክቱ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን አምነን እስከ መጨረሻው ድረስ መጽናት ከመታደልም በላይ መታደል ነው።
የእግዚአብሔር እውነት ሁሌም አያዳላም።
ዲያቆን ቄስ ጳጳስ መነኩሴ መምህር ብሎ አያዳላም ካጠፋ አጠፋ ነው ንስሓ እንዲገባ ይገስጻል።ያማ ካልሆነ ምኑን እውነት ሆነ ታድያ?
ሁሉም ሰው ሁሉንም አያውቅምና በማንኛውም ሰው መሰናከል ከእውነት ፈቀቅ ማለት እውነትን አለማወቅ ነውና እስከ ሞት ድረስ የታመንን እንሁን
እውነት አርነት ያወጣናል እና።
ሁሉም ሰው ሁሉንም አያውቅም። አራት ነጥብ።
17/5/2017




👆በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
እንዴትሰነበታችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንዴትሰነበታችሁ በየአላችሁበት የእግዚአብሔር ሠላም ከእናንተ ጋር ይሁን። እግዚአብሔር ፈቃዱ ይሁንልና ሰሞኑንን አንድ የዩቲዩብ ቻናል ላይ የተለቀቀ የሚዘዋወር ቪዲዮ አለ ስለኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ተናገሩ ከበረሃ አባቶች የሚል ነገር እየተዘዋወረ ነው ግን ይኼን መልዕክት በደንብ ከሰማችሁት መልካም የሚመስል ነገር ግን በማር የተለወሰ መርዝ ስለሆነ ባታጋሩ መልካም ነው።እስኪ አንዳንድ ነገሮችን እናንሳ የሊቀ ሊቃውንት አለቃ አያሌው ውግዘት ውግዘቱ የተካሄደው በአባ ጳውሎስና በሊቀ ሊቃውንት አለቃ አያሌው መካከል ብቻ እንደሆነ ይናገሩ ።ግን ውግዘቱ እንደዚያ ነው የሚለው? አይደለም በተዋረድ ከሲኖዶስ ጀምሮ እስከ ምዕመን የሚመጣ ነው እናንተም እንደምታውቁት በድምጽ አለ ተመልሳችሁ ስሙት ለማስታወስ ያክል በራሳችሁ በሊቀ ሊቃውንት አያሌው አንደበት ።
ሁለተኛ ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ገና አልተቀባም አሉ ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ከተቀባ ሌሎች በንጉሥ ማዕረግ ያሉ ሁሉ አብረው ያሉ እንደተሾሙ ነው እኛ ከእግዚአብሔር በእግዚአብሔር ባሮች በራሳቸው አንደበት የተነገረን ወደዱም ጠሉም ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ከተቀቡ ቆዩ ጊዜያትም አልፈዋል። እነዚህ ሰዎች አሁን ካለው ከአጥፊው ከቤተክህነት መዋቅር ያልተላቀቁ ናቸው ብዙ ነገር ስለአለው ጥንቃቄ ብናደርግና አዲስ ነገር በመጣ ቁጥር ስለኢትዮጵያ ትንሳኤ የተናገረ ሁሉ እውነተኛ አይደለምና ጥንቃቄ አድርጉ።በአደባባይ ይውጡ እንወቃቸው ይላሉ እንነጋገር ይላሉ እኛ በአባቶች በኩል የተነገረን የክርክር ጊዜ እንዳበቃ ነው። ስለዚህ እባካችሁ ሁሌም አንድ ሰው እየመጣ ስለኢትዮጵያ ትንሳኤ እየመጡ በተናገሩ ቁጥር የነሱን ንግግር የምናስተጋ አንሁን።ስለኢትዮጵያ ትንሳኤ እነ መምህር ዶ/ር ዘበነ ፣እነ መምህር መስፍን፣ይኼ ዘመድኩን  የሚባል የኢትዮጵያ ትንሳኤ በ2015 ዓ.ም ይሆናል ንጉሡ በ2015 ይመጣል እያለ ብዙውን ሰው ጊዜ እየገደበ ሲያሰናክል የቆየ ፣ይቺ ስንዱ የምትባል ሳይቀር የዛር መንፈስ የሚጫወትባት ጭምር ፣ባህታዊ ነኝ የሚሉ መምህር ገብረ መስቀል የሚባሉት ፣ ሌሎችም ስለኢትዮጵያ ትንሳኤ ይናገራሉ ዳር ዳር ይዞራሉ ግን እውነተኛ አይደሉም በጎን የእግዚአብሔርን እውነት ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክትን የሚነቅፉ የሚተቹ በተቃራኒ የቆሙ ናቸው።ስለዚህ እነዚህ ትምህርት ሊሆኑን ይገባል አብዛኛዎቹ የራሳቸውን ፈቃድ እንጅ  የእግዚአብሔርን ፈቃድ አይደለም የሚናገሩት። የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ስለኢትዮጵያ ትንሳኤ ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች ከእናንተ የበለጠ እግዚአብሔር ስለሚያደርገው ነገር በአባቶች በባሮቹ በኩል ምስጢር የገለጸለት እንዲያውቅም ያደረገው የለም።
ትናንት ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የሚባል የለም የጅል ስብስብ ነው እያሉ የዓለም ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ሲሉ የነበሩ እኛ ቸሩ መድኃኔዓለም  ክብር ይግባናው የዓለም ብርሃን አይደለም ያልን ይመስል ለምን እንዲህ እንደተባለ ሳይረዱ በራሳቸው በሥጋ ስሜት እየተነዱ የፈለጋቸውን እየተናገሩ ሲያስቱ ቆዩ ዛሬ ያኔ የተናገሩትን እያስተጋቡ እንደ አዲስ ያሉ አሉ።አንዳንዶች ደግሞ ዛሬ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ልክ ነው እያሉ መጠዋል ግን ደግሞ እኛን የሚተች ነገር  በአባቶቻችንን  እውነተኛዎቹ የዚህ መልዕክት አስተላላፊ አይደሉም የማለት ያክል የሚመስል ንግግር እየተናገሩ ነው።ልብ በሉ በፊት መልእክቱን አዲስ ሃይማኖት :አሁን ደግሞ  መልዕክት እንደሆነ እና ትክክል እንደሆነ ግን አስተላላፊዎች ትክክለኛ እንዳልሆኑ የሚመስል እየተናገሩ ነው ።አንዱ አልሳካ ሲል ሌላ ሊበሏት ያሰቧትን ምን እንደሚባለው...
የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አባቶቻችን ማስተላለፍ የጀመሩት በ1998 ዓ.ም ነው  የተላለፈውም ለአዳም ዘር በሙሉ ነው ዛሬ አዲስ የመጣ ይመስል ሥራቻችን አጓተቱ ይላሉ።እኛ ዛሬ ሰምተን እንዲህ የገረመን ቀዳይ የሥላሴ ባሮች ምን ይሰማቸው ይሆን እጅግ የሚገርም እኮ ነው።
ስለዚህ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች አዲስ ነገር በመጣ ቁጥር የምንሮጥ አንሁን።ይሄን የምለው በየማህበራዊ ሚዲያው ስታጋሩ ስታሸራሽሩ ስለምናይ ነው።
ልታውቁት የሚገባ ነገር እዚህ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ገጽ ላይ ተሰግስገው ተደብቀው የሚሰሙና እዚህ እየወሰዱ የሚመቻቸውን ብቻ እየወሰዱ የሚናገሩ አሉ ።እኛ የምንጠቀምባቸው ምስሎች ሁሉ እየወሰዱ የሚጠቀሙ አሉ። ወደ ፊት የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክትን በገሃድ እየተናገሩ የሚመጡ ይኖራሉ ጥንቃቄ አድርጉ። አንዳንዶች ደግሞ ተሰንገው ተገደው የሚናገሩ ይመጣሉ አምነውበት አይደለም ተገደው በየሚያዲያ ጣቢያው ሁሉ ይለፈልፋሉ ያን ካላደረጉ እረፍት እንቅልፍ ስለማያገኙ ይኼ ደግሞ በመልዕክታቱ ተነግሯል ይሄን ከወዲሁ ተረዱ።የሚገርመው ደግሞ የእግዚአብሔር ፍርድ ሲጀምር ሁሉ በየአፉ ብለን ነበር ተናገረን ነበር ማለት ጀምሯል መናፍቃን እንኳ ሳይቀር ተናግረን ነበር እያሉ ማለት ጀምረዋል እነሱን ብሎ ትንቢት ተናጋሪ።
ስለዚህ ወገኖቼ ጊዜ ካላችሁ የማንም ነገር እያያችሁ ጊዜ ከምታጠፉ የእግዚአብሔርን እውነት ተመልሳችሁ ስሙ እራሳችሁን ለእግዚአብሔር አገልግሎት አዘጋጁ ለዚያ የሚገባ ሰው እንድትሆኑ እግዚአብሔርን ጠይቁ እንጠይቅ እንለምን።ወርቅ እጃችን ላይ እያለ ሌላ ፍለጋ አንሂድ የእግዚአብሔር እውነት አንድ የቤተ-ክህነት ሰው ነኝ ባይ ስለተናገረ ስለአልተናገረ አይደለም እውነትነቱ የሚጸናው የእግዚአብሔር እውነት እውነት ነው ማንም ሊቀይረው አይችልምና ነው።
ቀዳማዊ የእግዚአብሔር ባሮችና እኛም የመንፈስ ልጆቻቸው ቤተሰቦቼ የሚሉን በስሜታዊነት ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ በገሃድ እንድንገለጥና ለማወቅ የሚደረግ ጥረት ይመስላልና ጥንቃቄ አድርጉ በገሃድ ራሳችሁን ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ አታጋልጡ ።
"ጥንቃቄ ይጠብቅሃል ማስተዋል ይጋርድሃል ይላል የእግዚአብሔር ቃል " ይሄን ደግሞ አስተምረውናል የእግዚአብሔር ባሮች።
ስለዚህ ከእኛ የሚጠበቀው የነገሩንን መታዘዝና ወደ ተግባር መለወጥ ነው።
ሌላው ከላይ በፎቶ የተጠቀሱትን የእግዚአብሔር ቃሎች እዩአቸው።
ከእኛ የሚለዩም ካሉ አትገረሙ የተጠራው ሁሉ የተመረጠ አይደለምና።ስለዚህ "ከእኛ ዘንድ ወጡ  ዳሩ ግን ከእኛ ወገን አልነበሩም፤ ከእኛ ወገንስ ቢኾኑ አለ አያችሁ ከእኛ ጋራ ጸንተው በኖሩ ነበር፤ ነግር ግን አለ ተመልከቱ ኹሉ ከእኛ ወገን እንዳልኾነ ይገለጡ ዘንድ ወጡ።ይላል የእግዚአብሔር ቃል በ1ኛ ዮሐንስ መልእክት ምዕ 2:19 ላይ ስለዚህ አብረውን የነበሩ የሚመስሉ ግን ያልነበሩ ሲወጡ ይሄን የእግዚአብሔር ቃል ማሰብ ነው።እንደ አንድ መንፈሳዊ ቤተሰብ እግዚአብሔር ሁሉን ይችላልና በጸሎት ማሰብ ነው።ከዚህ ውጪ ምን ማድረግ ይቻላል እንደ ፈቃድህ ይሁን ብቻ ነው።
ይቺን ለማስተላለፍ ነው ስለዚህ ዝምብላችሁ የአገኛችሁት ሁሉ ከማጋራትና ከመስማት ይልቅ የያዛችሁን ጠበቅ አድርጋችሁ ያዙ ተረዱት ገና አልተረዳነውም።ቀዳማዊ የሥላሴ ባሪያ አባታችን ገብረ መድህንም እንዲገባችሁ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በጸሎት እየጠየቅን እንድናነበው እንድንሰማው መክረውናል።
ሠላም እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን መልካም ጊዜ ይሁንላችሁ።
ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመስገኛ ምድር።
ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም።
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን።
ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ።
አሜን!
15/05/2017












ማሳሰቢያ ከራዕይ ዮሐንስ 20
15/04/2017 ዓ.ም



Показано 20 последних публикаций.