💛 የ መዝሙር ግጥሞች 💛


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


🇪🇹 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ ቆየት ያሉና አዳዲስ👇👇
👏 የቸብቸቦ መዝሙራት 🎻 የበገና መዝሙራት  
👑 የቅዱሳ መዝሙራት ⛪️ የንግስ መዝሙራት
💍 የሠርግ መዝሙራት 🌦 ወቅታዊ መዝሙራት መገኛ

📢ለ ማስታወቂያ ስራዎች @Miki_Mako

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


✞የዓለም ጨለማ የጠፋብሽ✞

የዓለም ጨለማ የራቀብሽ ንጽሕት ብርሕት
የሞት ፀሐይ ማስፈራት የጠፋብሽ እመ ሕይወት
ቡርክት ነሽ በእውነት ክብርት ነሽ በእውነት ኪዳነምሕረት

በምሥራቅ በኩል ከተተከለች የኤደን ገነት
ሁለት እጽ ካሏት አንዱ የሕይወት
አንደኛው የሞት
አንቺ ትበልጫለሽ የሕይወት ፍሬን የተሸከምሽው
የሞትን ተክል ነቅሎ የጣለ ልጅ የወለድሽ
       አዝ= = = = =
የአምላክን ሕግ በመተላለፍ በመጣ መርገም
ክህደት ጨለማ አለማወቁ ሰፍኖ በዓለም
ስንደናገር ቀንዲሉ ጠፍቶ ፍጹም ታውረን
ሰጠችን ድንግል የሚያበራውን የሕይወት
ብርሃን
       አዝ= = = = =
ከምርጦቹ ጋር የሚያደርገውን የምሕረት ኪዳን
ለድንግል ሰጥቷል ከሁሉ የሚበልጥ የእናትነትዋን
ኪዳኗን አምኖ ስሟን ለጠራ ዝክርዋን ላረገ
በላይ ይኖራል በልጇ እልፍኝ እንደከበረ

መዝሙር
መምህር አቤል ተስፋዬ

​​"ከመረጥኩት ጋር ቃልኪዳኔን አደረግሁ"
              መዝ ፰፱፥፫
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


​​የዐቢይ ጾም ሰባተኛ ሳምንትኒቆዲሞስ)

ክፍል ሁለት

በሚታይ አገልግሎት የማይታይ ደጋፊ ከእግዚአብሔር ሲታደል ማንም አያየውምና።ዮሐ ፫፥፱ "ኒቆዲሞስም መልሶ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል አለው፡፡"

ኒቆዲሞስም በሚታይ አገልግሎት የማይታይ የልጅነት ደጋ የሚሰጥበትን ምሥጢር ጥምቀት በምሳሌ በነገረውም አልገባውም ነበር፡፡ ለዚህም ነው "ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል" ሲል የጠየቀው ዮሐ፫፥፲€
"ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ፬አንተ የእስራኤል መምህር ስትሆን ይህን
አታውቅምን"


እዚህ ላይ ሁለት ነገሮች ይነሳሉ
፩፦መምህር ብሎ፦ ማለምለም ማክበር በዚህ በጌታችን ንግግር መምህርንን ማክበር እንዳልከን ነው የምንረዳው፡፡
አንድም፦ የኒቆዲሞስን ማንነት ሲመሰክር ነው።
አንድም፦ አቅርቦ ማስተማር ለመምህራን ልማድ ነው ከዚያ አንጻር ሲያስተምረው ነው።
፪፦አታውቅም ማለቱ ተግሳጽን ያመለክታል ምንም እንኳን የአይሁድ መምህራቸው ብትሆንም ይህንን ለመሰለው ታላቅ ምሥጢር አላዋቂ ነህ ሲል ገሥጾታል፡፡
አንድም፦ ጌታችን የነቀፈው አለማወቁን እንጂ መምህርነቱን አይደለም፡፡
አንድም፦/ተግሳጹ ባለማወቁ ሳይሆን ክርክር በማብዛቱ ነው፡፡/
ዮሐ፫፥፲፩ "እውነት እውነት እልሃለው፡- የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውን እንመስክራለን ምስክራችንንም አትቀበሉም።"
ያስተማረውን የልጅነት ምሥጢር አይሁድ አምነው አይቀበሉትምና እንዲህ አለ፡፡
እውነት እውነት እልሃለሁ፦ አንድነቱን ተናገረ ያየነውን የሰማነውን እንመሰክራለን ሲል፦ ሶስትነቱን
የምናውቀውን እንናገራለን፦ ያየነውንም እንመሰክራለን ምስክራችንንም አትቀበሉም አለ፡፡

ራሱን ከመጥምቁ ከዮሐንስ ጋር ጀምሮ ኒቆዲሞስን ደግሞ ከአይሁዳ ጋር ቆጥሮ ሲናገር ነው።
አንድም፦ ራሱን ከባሕርይ አባቱ ከአብና ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ አድረጎ ሲናገር ኒቆዲሞስን ደግሞ በሃናና ቀያፋ መስሎ ነው፡፡ ሉቃ ፳፪፥፷፮፥፸፩

አንድም፦ ራሱን ከሐዋርያት ጀምሮ ኒቆዲሞስን በአይሁድ በአሕዛብ በነገስታት መስሎ ነው፡፡ ሐዋ ፫፥፲፫, ፬፥፬
አንድም፦ ራሱን በኋላ ዘመን መምህራን ጋር ቆጥሮ ኒቆዲሞስን በኋላ ዘመን መናፍቃን መስሎ ነው አንዲህ ያለው

ዮሐ ፫፥፲፪ "ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኳችሁ ጊዜ ካለመናችሁ ስለሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ"
በሚታይ አገልግሎት በጥምቀት የሚሰጣችሁን ልደታችሁን ካላመናችሁ ሰማያዊ ልደታችሁን ማለትም ከሙታን ተለይታችሁ ተነሥታችሁ መንግሥተ ሰማያት ትገባላችሁ ብዩ ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ ሲለው ነው።/ትንሳኤ ሙታን ሁለተኛው ሰማያዊ ልደት ይባላል/ ማቴ፲፱፥፳፰

አንድም፡- ስለ ምድራዊ ልደቴ ስነግራችሁ ካላመናችሁ ስለ ሰማያዊ ልደቴ ብነግራችሁ እንዴት ታምናላች ሲላቸው ነው፡፡

አንድም፡- የፊተኛው ልደት በኋላኛው ልደት ተገለጠ ተብሎ እንደተነገረ ምድራዊ ልደቱ ያመነ ሰማያዊ ልደቱንም ይቀበላል ሲል ነው፡፡

ዮሐ ፫፥፲፫ ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሠው ልጅ ነው።"

ወደ ሰማይ የወጣ የለም ወደ ሰማይ የወጣው ከሰማይ የወረደው ክርስቶስ ነው አንጂ ይህንስ ለምን ይለዋል ቢል ወንጌላዊው የመጣውም የወረደውም አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው ለማለት

አንድም፦ ሰማያዊ ሃብትን ሰማያዊ እውቀትን ገንዘብ ያደረገ የለም ሰማያዊ ሃብትን ሰማያዊ እውቀትን ገንዘብ ያደረገ ከሰማይ የወረደው ክርስቶስ ነው እንጂ ዮሐ ፮፥፴፰ ሉቃስ ፳፬፥፶-፶፪
ዮሐ ፬፥፲፭-፲፭ ሙሴም ከምድረ በዳ እባብን እንደሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘለዓለም ሕይወት እንዲኖረው እንጅ እንደይጠፋ የሠው ልጅ ይሰቀል ዘንድ ይገባዋል፡፡"
ለምሣሌ፦
አስቀድሞ ሙሴ በተረዳ ላይ እባቡን መስቀሉ ለክርስቶስ መስቀል ምሳሌ ነው ዘኁ ፳፩ ፥፬-፱ ከብረት የተሠራው እባብ የክርስቶስ የምድር እባቡ የዲያብሎስ በአርዌ (እባብ) ምድር መርዝ እንዳለበት በዲያብሎስም ፍዳ ኃጢአት አለበት በአርዌ (እባብ) ብርት መርዝ እንደሌለበት በጌታም ፍዳ ኃጢአት የለበትም ብረት ጽሩይ እንዲሆን ጌታም ጽሩዋ ባሕርይ ነው እስራኤል የምዕመናን የሠው ልጅ ምሣሌ አንድም፦ ተራዳው የመስቀል ብረት የወልድ እግዚአብሔር እባብ የዲያብሎስ ቀርሰሉ የኃጢአት መርዙ የመርገም ሥጋ የመርገመ ነፍስ በርኃው የጋሃነመ እሳት አምሳል ነው
ያን አይተው ሠምተው ይዳኑ አለስቀለት ክርስቶስን አይተው ያጤኑ ሐዋርያት ስምተው ያመኑ ምዕመናን የመኖራቸው ምሳሌ አንድም፦ መልኩን አይተው ድምጹን ሰምተው የዳኑ ከቃሉ ስምተው ያመኑ የዳኑ ድምፁን ብቻ ሠምተው የዳኑ ከርሱ በኋላ ከተነሡ መምህራን ሰምተው ያመኑ የዳኑ የምዕመናን ምሣሌ ያላመኑ ይፈፀሙ ማለቱ ስቅለተ ክርስቶስን አይተው ያላመኑ አይሁድ ስምተው ያላመኑ አሕዛብ ያለመዳናቸው ምሳሌ ነፍስ ያለው እባብ የገደላቸውን ሰዎች ነፍስ የሌለው ብረት እንዳዳናቸው በባሕርይው ሞት የሌለበት አምላክ ዲያብሎስ የሰራቸውን ነፍሳት ተስቅሎ ሞቶ የማዳኑ ምሣሌ ነው ስለምን እራሱን ለብረት መሰለው ቢሉ ብረት ከቆላም ከደጋም አጠረቃቅሞ ይሠሩታል የጌታችንም ልደቱ ከቤተ መንግስት ከቤተ ክህነት ነውና አንድም፦ ብረት አሩይ ነው ሲመቱት ከሩቅ ይሰማል የጌታም ልደቱ ጥምቀቱ ሞቱ ዕርገቱ እስከ ምጽአት ድረስ ሲነገር ይኖራልና ከብረት መስለው ትንቢቱን ያናገረ አምሳሉን ያደረገ እርሱ ባወቀ ነው፡፡

ዪሐ ፫፥፲፮ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘለዓለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለምን እንዲሁ ወዷልና።ዮሐ፬፥፱

አንድ ልጅ ለሁሉ ቤዛ አድርጎ እስከ መስጠት ደርሶ እግዚአብሔር ዓለሙን ወዶታልና ከመኩሉ ዘየአምን ቦቱ አይትኃጎል
በርሱ ያመነ ሁሉ እንዳይጎዳ የዘላለም ሕይወትን ያገኙ ዘንድ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ቤዛ አድርጎ ሠጠን ሲል
አንድም ትምርቱን ሰምተው ቃሉን አምነው ቢፈጽሙት ቢኖሩበት ሞትን አያዩምና ዓለም ያለው የሰውን ልጅ ነው
ዮሐ፫፥፲፯ ዓለም በልጁ እንዲድን እንጂ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አላከውምና

እግዚአብሔር ባለሙ ሊፈርድበት ልጁን ወደዚህ ዓለም አልሰደደውም እርሱስ ስለካሠለት ሊያድነው ዘንድ እንጂ
አንድም፦ አስቀድሞ ያለተፈረደበት ሆኖ ሊፈርድበት አልሠደደውም ተፈርዶበታልና ከተፈረደበት ፍርድ ሊያድነው ነው እንጂ አንድም፦ በሥጋው ሊፈርድበት አልላከውምና እጅ ለሌለው እጅ እግር ለሌለው እግር ዓይን ለሌለው ዓይን ሊሰጠው ነው እንጂ አንድም፦ በመንፈሳዊ ቅሉ ሊፈርድበት አልሰደደውም ተኃድግ ለኪ ኃጢአትን ሊሰጥ ነው እንጂ።ዮሐ፭፥፳፬

ዮሐ፫፥፲፰ በእርሱ የሚያምን
አይፈረድበትም በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል

በግርማ መንግሥቱ በመለኮታዊ ክብሩ በቅድሳን ታጅቦ ለፍርድ ይመጣል በእርሱ ያመነ አይፈረድበትም በእርሱ ባላመነ ግን ፈጽሞ ይፈረድበታል።

በአንድ በእግዚአብሔር ልጅ አላመነምና ተፈርዶበታል ይፈረድበታል።
ዮሐ፫፥፲፱"ብርሃንም ወደ ዓለም ስለመጣ ሰዎችም ስራቸው ክፋ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለወደዱ ፍርዱ ይህ ነው።"

ብርሃን ክርስቶስ ወደ ዓለም መጥቷልና ሰውም ከብርሃን ጨለማን ከእውቀት ድንቁርናን ከክርስቶስ ሠይጣንን ከወንጌል ኦሪትን ወዷልና፡፡
ዮሐ፫፥፳ "ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃን ይጣላልና ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም።

ምግባረ ክፉ የሆነ ሠው ብርሃንን ይጠላል ወደ ብርሃን አይመጣም ሥራው እንዳይገለጥበት ሥራው ሁሉ ክፉ ስለሆነ ኢዮ፳፬፥፲፫-፲፮

ወስብሐት ለእግዚአብሔር


✞ጌታ ሆይ ውለታህ✞

ጌታ ሆይ ውለታህ ተአምርህ ድንቅ ነው
አምላካዊ ቃልህ ስምህ ሕይወቴ ነው(፪)

በሐዋርያት አድረህ ብዙ መክረኸኛል
ስለ ኃጢአቴ ሞተህ ህይወት ሰጥተኸኛል
ጌታ ሆይ ውለታህ ተአምርህ ድንቅ ነው
አምላካዊ ቃልህ ስምህ ሕይወቴ ነው

      
ለሐዘኔ ደርሰህ ፈጥነህ አረጋጋኸኝ
አይዞህ/ሽ/ ልጄ ብለህ ስወድቅ ያነሳኸኝ
ከማይጠፋው እሳት ከሞት ያወጣኸኝ
ላንተ የምከፍልህ ምን ስጦታ አለኝ
      
እውነተኛ ረዳት ወገኔ አንተ ነህ
ጌታዬ ከእናት ልጅ እጅግ ትበልጣለህ
መታመን ባንተ ነው ደግሞም መመካት
ወቅት የማይለውጥህ የማታውቅ ወረት
      

ስምህ ምግቤ ሆኖ ስጠራው እጠግባለሁ
ፍቅርህን ቀምሼ ፍፁም እረካለሁ
በሰማይም በምድር በነፍስም በሥጋ
በአንተ  እመካለሁ አልፋና ኦሜጋ

    መልአከ ሰላም ቀሲስ
     እንግዳወርቅ በቀለ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞በረቀቀው ፍቅርህ✞

በረቀቀው ፍቅርህ አንተ ብትጠራኝ ዛሬ
ይኸው ዳግመኛ መጣሁ በኃጢአት ዓለም ኖሬ(፪)

ከቤትህ ርቄ ብሄድ ለዓለም ተገዛሁ
አንተ ይቅር ትለኝ ዘንድ እንደገና መጣሁ(፪)


በቆረስከው ሥጋህ በአፈሰስከው ደምህ
ከዓለም ግዞት አውጥተህ አኑረኝ በቤትህ(፪)

ዳግመኛ እንዳልበድልህ በዓለም ተታልዬ
በቅዱሳንህ ምልጃ ጠብቀኝ ጌታዬ(፪)


በዓለም የሰራሁትን ያሳዘንኩህን ሁሉ
ይቅር በለኝ አምላኬ ስለ እግዝእትነ ኩሉ(፪)

በረቀቀው ፍቅርህ አንተ ብትጠራኝ ዛሬ
ይኸው ዳግመኛ መጣሁ በኃጢአት ዓለም ኖሬ(፪)


              መዝሙር
         በማኅበረ ቅዱሳን

"የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ።"

፩ጴጥ፩፥፲፮
  ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
     @yamazemur_getemoche
  ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


​​በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

የዐቢይ ጾም ሰባተኛ ሳምንት(ኒቆዲሞስ)
በዲያቆን ያሬድ መለሰ
ዮሐ፫፥፩ "ከፈሪሳውያን ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል ሠው ነበር።የኒቆዲሞስን ነገር ያነሳው ለምንድን ነው ቢሉ፦ በእምነት ጸንቶ እስከ መጨረሻው የሚከተለው ነውና፡፡ ሉቃ ፳፬፥፲፫ ፣ ዮሐ፲፱፥፴፱

አንድም ፦ በእርሱ አምኖ በኋላ የሚመሰክር ነውና፡፡ ዮሐ፯፥፶
አንድም፦ ያልተማሩ መጽሐፍት የማያውቁ ብቻ ሳይሆን ከተማሩ ከአዋቂዎች ከአለቆችና ከመምህራንም ወገን በእርሱ ያመኑ እንዳሉ ለመግለጥ

አንድ ሠው ነበር ያለው ታሪክ አያይዞ ነው ቢሉ፦ ብዙዎች በስሙ አመኑ ከተባሉት መካከል ነው ሲል ነው፡፡
ከምዕራፍ ፪ ጋር ሲያያዝን ነው፡፡ በፋሲካ በዓልም በኢየሩሳሌም ሳለ ያደረገውን ምልክት/ገቢረ ተአምራት/ ባየ ጊዜ ብዙ ሰዎች በስሙ አመኑ ብሎ ስለነበር፡፡

ከዚህ ጋር ሲያያዝ ነው ዮሐ፪፥፳፫ አመኑ ከተባሉ ሲደምረው ከፈሪሳውያን ወገን የሚሆን ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሠው ነበር አለ፡፡ ካመኑት መካከል አንዱ ኒቆዲሞስ ነውና
አንድም፦ ታሪክ አላያያዘም ቢሉ፦ የቃሉን ትምህርት ገቢረ ተአምራቱን ተመልክቶ በእርሱ ያመነ ከፊሪሳዊያን ወገን የሚሆን በትምህርቱ በሀብቱ በሹመቱ የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሠው ነበረ ሲል ነው፡፡

የአይሁድ አለቃቸው ሲል፦ አለቅነቱ በሶስት ወገን ነው በትምህርት/ሊቅ ኦሪት/በሹመት በባለፀግነት (በሀብት)
ዮሐ፫፥፪ "እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ መምህር ሆይ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርገውን እነዚህን ምልክቶችን ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን አለው።"በግዕዝ "ወውእቱ መድአ ሃበ እግዚአ ኢየሱስ ቀዲሙ ሌሊቱ።" ትርጉሙ "አስቀድሞ በሌሊት ወደ ጌታ የመጣ"
አማርኛው ከግዕዙ ጋር ሲነጻፀር ቀዲሙ /አስቀድሞ/ የሚለው ይገኝበታል ።"እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ አስቀድሞ መጥቶ
አስቀድሞ ወደ እርሱ የመጣ አለ ከምን አስቀድሞ?፦ ሲለው በስቅለት ጊዜ ሥጋውን ከመስቀል ከማወረዱ በፊት ለትምህርት በሌሊት መጣ ሲል ነው።

አስቀድሞ የሚለው ሥጋውን ከማውረዱ በፊት አስቀድሞ ለመማር መጣ ለማለት ነው፡፡ ዮሐ ፲፱
አንድም፦ ከመዓልት ከሚመጡት አስቀድሞ በሌሊት መጣ ሲል ነው
አንድም፦ ከማመን አስቀድሞ የመጣ ሲል ነው፡፡ ኒቆዲሞስ ኋላ ላይ አምኗል ከማመኑ በፊት ነው ለትምህርት የሚመጣ ነበር። ዮሐ ፯፥፵፱

በሌሊት ለምን መጣ?
በሌሊት ለምን መጣ ቢሉ ለወንጌል የተጋ የእግዚአብሔር በረከት እንዳይከፈልበት የሚፈልግ ነውና፡፡
አንድም፦ ውዳሴ ከንቱ ሽቶ መምህር ነኝ እያለ ገና ይማራል ብለው እንዳይንቁት ነው።
አንድም፦ ጨለማ የተባለ ድንቁርናን ይዞ አለማወቅንም ለብሶ ሲል ነው፡፡ ጨለማ የተባለች
አንድም፦ የቀን ልቡና ባካና ነው፡፡ የሌሊት ልቡና የተሰበሰበ ነውና፡፡ በተሰበሰበ አእምሮ ለመማር የሌሊቱ ጊዜ የተመቸ ነው፡፡
አንድም፡- አይሁድን ፈርቶ ነው፡፡ ዮሐ፱፥፳፫
በሌላ በኩል ኒቆዲሞስ የጌታን መምህርነት የመሰከረለት አምኖ ነው ወይስ ሳያምን ነው የሚለው መመልከት ይገባል።

ፍጽም አምኗል ቢሉ፦ አምኖ ነው ቢሉ፦ በህልውና በባሕርይ በመለኮት በሥልጣን ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ከሆነ በቀር ማንም ሰው ይህንን ሥራ ሊሠራው አይችልም ሲል ነው፡፡ ዮሐ፩፥፶
ፍጹም አላመነም ቢሉ፦ እግዚአብሔር ያደረበት ሠው ካልሆነ በቀር ይህንን ተዓምራት ማንም ሊሰራው አይችልም ሲል ነው፡፡

ዮሐ፫፥፫ "ኢየሱስም መልሶ እውነት እውነት እልሃለሁ ሠው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔር
መንግስት ሊያይ አይችልም አለው፡፡"


የእግዚአብሔር መንግስት ያለው፦ ሃይማኖትን ነው፡፡ መንግስተ ሰማያት ሃይማኖት ትባላለች ለምን መንግስት ሰማያት በሃይማኖት ነውና የምትወረሰው ደግሞ ወልድ ዋሕድ በምትባል ሃይማኖት የምትወረስ ናትና፡፡

አንድም፦ መንግስተ ሰማያትን ነው
ጻድቃን ከረፍታቸው በኋላ እንደ ከዋክብት ብርሃናዊያን ሆነው ይወርሷታል፡፡
ሠው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግስት አይወርስም ሲል ያልተጠመቀ ርኩስ ነው የረከሠ ያልተጠመቀ ሁሉ መንግስተ ሰማያትን አይገባባትም፡፡ አይወርሳትም አያያትም።

ሰው በጥምቀት ዳግም ካልተወለደ በቀር መንግሥተ ሰማያትን አይወርሳትም ሲል ነው፡፡ ዮሐ፩፥፲፩-፲፫

ዳግም ልደት ያለው ጥምቀት ነው፡፡
ለልደት ሥጋ ነው ቢሉ፦ ከእናት ከአባት የምንወለደው አንድ ልደት ሲሆን በጥምቀት ከእግዚአብሔር ሲወለዱ (የምንወለደው) ዳግም ልደት ነው፡፡/ያልተካከለ ንጽጽር/
ለልደት ነፍስ ቢሉ፦ ሰው ሁለተኛ በጥምቀት ከእግዚአብሔር የሚወለደውን ነውና።/የተሰተካከለ ንጽጽር/ ዮሐ፩፥፲፩-፲፫

ጥቅል ትርጉም፦ ያልተጠመቀ/ዳግም ያልተወለደ/ ወልድ ዋሕድ የምትለውን ሃይማኖት አያውቃትም፡፡ መንግስት ሰማያትን አይወርስም ሲል ነው፡፡

ዮሐ፫፥፬ "ኒቆዲሞስም ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል ዳግመኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው።"
ሰው ወደ እናቱ ማኅፀን ወደ አባቱ አብራክ ተመልሶ ዳግም ሥጋዊውን ልደት ይወለድ ዘንድ እንዴት ይችላል? ሲል ነው፡፡
አንድም፦ ዳግም ካልተወለደ ክብር አብራክ ተመልሶ ዳግም ሥጋዊውን ልደት ይወለድ ይገባዋል ሲል ነው
ዮሐ ፫፥፭ "ኢየሱስም መልሶ እንዲህ ሲል እውነት እውነት እልሃለሁ ሠው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡"
ኒቆዲሞስ ጌታን ዳግም መወለድ ይቻላል ግዴታ ነው ብሎ ጠይቆ ነበርና ለጠየቀው መልስ ሲሰጥ ነው፡፡
ይቻላልን፦ ብሎ ለጠየቀው ልደቱን ነገሮች መወለጃውን አልነገረውም ነበርና ሁለተኛ ከአብራከ መንፈስቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ካልተወለደ መንግሥተ ሰማያት መግባት አይችልም የሚለውን የመወለጃውን መንገድ ሲገልጥ ነው።
ይገባዋል፦ ላለው ደግሞ የሚያሰጠውን ክብር ነገረው ሲል ነው።
ዮሐ፫፥፮ "ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው፡፡
በሥጋዊ ግብር የሚወለድ ግዙፍ ሥጋ ነው ልደቱም ሥጋዊ ነው ከረቂቅ መንፈስቅዱስ የምትወለድ ነፍስ ግን ረቂቅ ናት፡፡
አንድም፦ ከሥጋ የተወለደ ሥጋዊውን ክብር ያገኛል ከመንፈስ የተወለደ ግን መንፈሳዊውን ክብር ያገኛል ሲል ነው።
ዮሐ፫፥፯ "ዳግመኛ ልትወለድ ያስፈልጋችኋል ስላልሁህ አታድንቅ፡፡
ዳግመኛ መወለድ ይገባል ግዴታ ነው ሲለው ነው።
አንድም፦ የምትወለድበት መንገድ ይሄ ነው ብዬ ስለነገርኩህ ቃል አታድንቅ ሲለው ነው፡፡
ዮሐ፫፥፰ "ነፋስ ወደ ወደደው ይነፍሳል ድምጹንም ትሰማለህ ነገር ግን ከወዴት እንደመጣ ወዴትም እንዲሄድ አታውቅምን ከመንፈስ የተወለደ ሁሉ እንዲሁ ነው፡፡"
ንፋስ ወደ ወደደው ይነፍሳል ከወዴት እንደመጣ ወዴትም እንደሚሄድ ግን አይታወቅም የንፋስ መኖር ባህር ሲገሥጽ ዛፍ ሲያናውጽ ይታወቃል፡፡ ከመንፈስቅዱስ የሚወለዱትም ልደት የማይታይ በሥራቸው የሚታወቅ ሲል ነው እንዲሁ በእምነት ተቀብለውት በሚሠራው ሥራ ይታወቃል፡፡




✞ኒቆዲሞስ✞

ሥውር ወዳጅ ምሁረ ኦሪት
ኒቆዲሞስ ክቡር ኒቆዲሞስ ትሑት
ባለጸጋ ሳለ በበጎ ሕሊና
ዝቅ ብሎ ተማረ በሚደንቅ ትሕትና(፪)

የአይሁድ አለቃ ኒቆዲሞስ ምሁር
ጌታችን እንዳለ የእስራኤል መምህር
ከፈሪሳውያን ልቡ የቀናለት
በሌሊቱ ሲጓዝ ብርሀን በራለት(፪)
በመቅደስህ ቆሜ ስምህን ላሞግስ
መንገዴን አብራልኝ በሌሊት ልገስግስ(፪)
አዝ= = = = =
እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነለት በቀር
ማንም አያደርግም የእጅህን ተአምር
ብሎ ባንደበቱ እንደመሰከረ
ከመስቀል አውርዶ ጌታውን ቀበረ(፪)
በመቅደስህ ቆሜ ስምህን ላሞግስ
መንገዴን አብራልኝ በሌሊት ልገስግስ(፪)
አዝ= = = = =
ዳግማዊ ልደትን ከጌታ ተማረ
ከምድራዊ እውቀት ሰማይ ተሻገረ
በምሽት ጨረቃ በመመላለሱ
ይበራለት ነበር ከፀሐይ ከራሱ(፪)
በመቅደስህ ቆሜ ስምህን ላሞግስ
መንገዴን አብራልኝ በሌሊት ልገስግስ(፪)
አዝ= = = = =    
ኒቆዲሞስ ልሁን ሌሊት የማይፈራ
ሠላሳና ስልሳ መቶ የሚያፈራ
እንቅልፍ አርቅልኝ በጽናት ልበርታ
እግሮቼን ታቅናልኝ ትእዛዝህ አብርታ(፪)
በመቅደስህ ቆሜ ስምህን ላሞግስ
መንገዴን አብራልኝ በሌሊት ልገስግስ(፪)
  አዝ= = = = =      
ጎጆዬ ሲጨልም ሰማይ ሲደፋብኝ
ውስጤ ብርሀን ሲያጣ ተስፋ ሲርቅብኝ
በልቤ ላይ ውረድ በብሩህ ደመና
ጨለማው ያላንተ አይገፋምና(፪)
በመቅደስህ ቆሜ ስምህን ላሞግስ
መንገዴን አብራልኝ በሌሊት ልገስግስ(፪)

መዝሙር
ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ


ከፈሪሳውያን ወገን፣ ከአይሁድ አለቆች አንዱ የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ ሰው ነበረ፤

ዮሐንስ ፫:፩
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯


✞ ኒቆዲሞስ ✞

ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስ ክቡር
ሌሊቱን በብርሃን የሚማር መምህር(፪)

በጨለማው ግርማ ኮከብ የደመቀ
በመከራው ፅናት ይህን ዓለም ናቀ
መምሕር ሆኖ ሳለ ከመማር ያልራቀ
የትዕቢትን ጅረት በትሕትና ተዋርዶ አደረቀ
ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ
አኮኑ አጽባዕት እምነ አጽባዕት የአቢ
ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ


ፍርሃትን በሚጥል ፍፁም ፍቅር ያደረ
ከመስቀል አውርዶ ጌታውን ቀበረ
የመግነዙን በፍታ በሽቱ ያከበረ
ከመቅደሱ አንቀጽ ላይረሳ አምድ ሆኖ ታጠረ
ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ
አኮኑ አጽባዕት እምነ አጽባዕት የአቢ
ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ


ሌሊትም ለሌሊት እውቀትን ነገረች
ህጉን ለሚያስበው ምክር አለኝ እያለች
ከጨለማው ኃጢአት ነቅታ ብርሃን ካየች
እንደ ኒቆዲሞስ ነፍስህም ተምራ ተመለሰች
ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ
አኮኑ አጽባዕት እምነ አጽባዕት የአቢ
ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ


በሌሊት አጋማሽ መምህር ለመምህር ሰገደ፤ ጣትስ ከጣት ይልቅ አይደለምን?

መዝሙር
ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ


"ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ"

ዮሐ፫፥፩-፴፮
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯




✞መቼ ነው ጌታ✞

መቼ ነው ጌታ መቼ ነው
ልቤ ለቃልህ የሚገዛው
መቼ ነው ጌታ መቼ ነው
አንተን በፍርሃት የማመልከው

ያ የቀደመው ኑሮ ለቤትህ ያለኝ ናፍቆት
ዛሬ ከልቤ ጠፍቷል አንቆታል የዓለም ፍትወት
አመጸኛ ሆኛለሁ አንዷን መክሊት ቀብሬ
እንዳነበረ ሆኗል ያ የቀድሞ ፍቅሬ
    አምልኮቴ እንዲሆን በእውነት እና በመንፈስ
    እርዳኝ አግዘኝ አባቴ ወደ ኋላ አልመለስ
       አዝ= = = = =
ቃልህን መመስከሬ በአደባባይ መጥራቴ
እኔን መቼ ሰበረኝ ጠዋት ማታ ስግደቴ
በበረሃ እንደሚዞር እንደተጠማ ዋልያ
ናፍቆቴ ጥማት ሆኗል ለማረፍ በአንተ ጥላ
    አምልኮቴ እንዲሆን በእውነት እና በመንፈስ
    እርዳኝ አግዘኝ አባቴ ወደ ኋላ አልመለስ
       አዝ= = = = =
በክፉ ሰዎች ምክር በአመጸኞች ጎዳና
በኃጢአተኞች ወንበር ተመኝቼ ልጽናና
ነፋስ እንደሚወስደው እንደሚበተን ትቢያ
መደፊያ አጣሁኝ ለነፍሴ ማሳረፊያ
    አምልኮቴ እንዲሆን በእውነት እና በመንፈስ
    እርዳኝ አግዘኝ አባቴ ወደ ኋላ አልመለስ

        መዝሙር
     መቅደስ ማርዬ

"እግዚአብሔር ጻድቅንና ኅጥእን ይመረምራል፤ ዓመፃን የወደዳት ግን ነፍሱን ጠልቶአል።"
                   መዝ፲፩፥፭
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞ሁሉም ያልፋል✞

ሁሉም ያልፋል እግዚአብሔር ያሳልፋል(፪)
ልጆቹን መቼ ይረሳል

ብርሃን ይመጣል ጨለማው ተገፎ
ደስታ ይሆናል መከራው አልፎ
/የምስራች ቃል ይሞላል በአፋችን
ሐዘናችን ጠፍቶ ይፈካል ፊታችን/(፪)
አዝ= = = = =
በትር ነው ምርኩዝ እሱን ላመኑበት
ባህር ውቅያኖሱን ከፍለው የሚያልፉበት
/በእሳት መካከል በግፍ ለተጣሉ
ውሃ አየሆናቸው በድል ይወጣሉ/(፪)
       አዝ= = = = =
ማስተዋል ጥሩ ነው ትዕዛዛቱን ማክበር
ያኖራል በሕይወት በሰማይ በምድር
/የማያልፍ ቀን የለም ታሪክ የማይሆን
በአምላክ አንድ ቀን ነው አንድ ሺ ዘመን/(፪)
       አዝ= = = = =
ይቅርታ እንዲሰጠን በደልን ሳይቆጥር
ማረን እንበለው ስለሆነ ፍቅር
/ነገ ቀን ሲመጣ ብርሀኑ ሲያበራ
ፊታችን እንዳይዞር ወደ ክፉ ስራ/(፪)

             መዝሙር
   ዲያቆን አቤል መክብብ

"እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ጥሩ፥"
               መዝሙር ፻፭፥፩
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞አምላኬ እግዚአብሔር✞

እግዚአብሔር አይተወኝም
ወድቄም አልቀርም

ለመንገዴ ብርሃን ለእግሬ መብራት
እረኛዬ እርሱ ነው አምላክ ምህረት
ጠርቶ ያሣደረኝ በለመለመ መስክ
አምላኬ እግዚአብሔር መንግሥቱ ትባረክ
       አዝ= = = = =
በእረፍት ውሃ ዘንድ ነፍሴን የሚመራ
ያድነኛል እርሱ ከጭንቅ ከመከራ
መታመኛዬ ነው የሚያሣጣኝ የለም
እርሱ ከእኔ ጋር ነው ወድቄ አልቀርም
       አዝ= = = = =
በትርና ምርኩዙ እኔን ያፅናኑኛል
ምህረት ቸርነቱ ሁሌ ይከተሉኛል
ኃጢአት ከፍቶብኝ ሰዎች ቢጠሉኝም
አምላኬ አይተወኝም ወድቄ አልቀርም
    
     መዝሙር
  ተስፋዬ ኢዶ
መዝሙር ፳፫፥፩-፬
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞ንስሐ እንግባ✞

ንስሐ እንግባ(፪)
ንስሐ እንግባ  ሲኦል እንዳንገባ

የበደልነው በደል ያጠፋነው ጥፋት(፪)
ይወገድልናል ንስሐ በመግባት
ተመርምሮ እራስን ነግሮ ለካህኑ(፪)
ነገ ዛሬ ሳንል መቅረብ አሁኑኑ
       አዝ= = = = =
ለኛ የነገረን ጌታችን በወንጌል (፪)
ይቅር ብዬሀለው ከእንግዲህ አትበድል
ይህንኑ ቃሉን አምነን ብንቀበል(፪)
ይሰጠናል እና ሰማያዊ አክሊል
       አዝ= = = = =
ሞት እንደው አይቀርም ዙሮ ተዟዙሮ(፪)
ሲመጣ መጓዝ ነው የለውም ቀጠሮ
እድፋችን ይታጠብ በንስሐ ውሃ(፪)
ንዑ እና  ሑሩ ሲል ለመዳን አሜሃ
                    
          ሊቀ መዘምራን
     ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ

"መንግስተ ሰማያት ቀርባለችና
ንስሐ ግቡ"

                   ማቴ ፫፥፪
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


መቼስ በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ የ ኖት ኮይንን ዜና ሰምታችሁ ምነው ታብ ታብ ባደረግኩኝ እንዳላችሁ አልጠራጠርም:: ያኔ በሚሊዮን ቤት ታብ ታብ አድርገን የሰበሰብንውን ኮይን የመጨረሻዎቹን ሶስት ዜሮዎችን ዲጂት አጥፍቶ በኖት አስቀምጦልናል:: ማለትም ያኔ 5.000.000 ኮይን ሰብስበን ከነበር ሶስቱን ዜሮዎች አጥፍቶ አሁን ላይ በ 5000not አስቀምጦልናል::
መነሻ ተብሎ የታሰበው የ 1$not ዋጋ 0.012 Ton ነው:: ያ ማለት ደግሞ

5000 ኖት * 0.012 Ton = 60 Ton ይሆናል ማለት ነው:: 1 Ton ደግሞ 7 ዶላር ነው :: እንግዲህ ወደ ቶን የቀየረላችሁን Amount  በ 7 አባዙት😋 ወደ ዶላር መቀየር ምትችሉት April 20 ነው::

   እና በ ኖት ኮይን የተቆጫችሁ በ Tap swap ራሳችሁን ካሱት:: ልክ እንደ not coin ታብ ታብ በማድረግ ኮይን መሰብሰብ ነው.. ከ ኖት ኮይን በፊት የነበረ የኮይን ሲስተም ስለሆነ እና ማብቂያው  እየተቃረበ ስለሆነ እታች በማስቀምጥላችሁ ሊንክ ቴሌግራም ላይ እየገባችሁ ታብ ታብ በማድረግ ኮይን ሰብስቡ :: ባይሳካም ምንም ምትከስሩት ነገር አይኖርም :: እውን ሲሆን ግን አስቡት😋

https://t.me/tapswap_bot?start=r_259635251

🎁 +2.5k Shares as a first-time gift


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

በአንድነቱ በሦስትነቱ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብሎ የሚመሰገን እግዚአብሔር በባሕሪው ንጉሥ ሲሆን እንደ ባሪያ ሆኖ ትሕትናውን አሳየን  ስለዚህ ጌታ ሆይ እናመሰግንሃለን ።

     ✞ሥላሴ አምባዬ✞

ሥላሴ አምላኬ ብዬ እዘምራለሁ
ሥላሴ እምባዬ ብዬ እቀኛለሁ
ሰማይና ምድር ደመና ሳይቀሩ
አእዋፍ አዝርዕት በሱ ተፈጠሩ

ብርሃን ጨለማ እንዲሆን በተራ
በዓለሙ ሁሉ ፀሐይ እንዲያበራ
እንድትሰለጥን ጨረቃ በለሊት
ሥላሴ አስውቦ ፈጠረ ከዋክብት
       አዝ= = = = =
በእግር የሚሄዱ በክንፍ የሚበሩ
በምድር ላይ ያሉ በጥልቅ የሚኖሩ
በሥላሴ ዘንድ ውላቸው ታውቀዋል
በከሃሊነቱ ፍጥረት ተፈጥረዋል
       አዝ= = = = =
አስቀድሞ ያለ ዓለም ሳይፈጠር
ሥላሴ ነበረ ዘመን ሳይቆጠር
ዘመን አሳልፎ ዘመን የሚያመጣ
ልክፉው ለደጉ ፀሐይ የሚያወጣ

             መዝሙር
          አቤል ተስፋዬ

"የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች
በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ
ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ"


           መዝ ፴፫ ፥፭-፮
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞ገብር ኄር✞

እግዚአብሔር የሰጠህ መክሊትህ የታለ
ድንገት ቢመጣብህ ምን ታሳየዋለህ
አንድ ከተሰጠው ያንን ከቀበረው
አንተ ከገብረ ሐካይ ብልጫህ ምንድን ነው

አደራ ጠባቂው የጸና በእምነቱ
ታማኙ ገብር ኄር ባለ አምስት መክሊቱ
ወጣ ወረደና ረርቶ አተረፈበት
ጌታው በመጣ ቀን በእጥፍ መለሰለት
    ወደ ደስታው ገባ ክብርን ተሸለመ
    በጥቂቱ ታምኖ በብዙ ተሾመ
       አዝ= = = = =
ሊሠራ እንዳቅሙ ሁለት የተሰጠው
ሌላ ሁለት አትርፎ ጌታውን ጠበቀው
ሊቆጣጠራቸው ዳግመኛ ሲመጣ
የመክሊቱን ዋጋ ከነትርፉ አመጣ
    ወደ ደስታው ገባ ክብርን ተሸለመ
    በጥቂቱ ታምኖ በብዙ ተሾመ
       አዝ= = = = =
አንድ መክሊት ብቻ የተሰጠው ሐካይ
ምድር ሥር ደበቀው አኖረበት ድንጋይ 
የአደራ መክሊቱን መቅበሩ ሳያንሰው
ጨካኝ ክፉ ብሎ ጌታውን ሰደበው
    መክሊቱን ተቀማ አሥር ላለው ሰጡት
    ለቅሶ ወዳለበት ጨለማ ስር ጣሉት

መዝሙር
ሲስተር ሕይወት ተፈሪ

ማቴ ፳፭፥፲፬-፴
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

መዝ፲፬፥፩-፭

✞የዳዊትን ገርነቱን✞

የጎልያድ ትምክህት
በዳዊት ወንጭፍ ተመታ
አንገቱን ቆርጦ አነሳው
የእግዚአብሔርን እጅ እረዳው
       አዝ= = = = =
ቀድሞ በነቢያት ትንቢት መነገሩ
ወልደ ዳዊት ተብለህ ስትገኝ ከዘሩ
ብዙ አንስቶችን በዙሪያው ሰብስቦ
ድንግሊቱን ዳዊት ሊያገኛት አስቦ
       አዝ= = = = =
ለጽዮን ሲዘምር ዳዊትን የናቀች
ሜሊኮል ንግሥቲቱ መካን ሆና ቀረች
የዋህ ስለሆነ ዳዊት በሕይወቱ
ከዙፋኑ ወርዶ ሰግዷል ለታቦቱ
       አዝ= = = = =
የዝሙት እንግዳ ቢመጣ ከቤቱ
ከዙፋኑ ቆሞ ከቤተ መንግሥቱ
መቶ በግ እያለው እንዳይጎድሉ ሳስቶ
አንዷን የኦሪዮን አስገባት ጎትቶ

ጸሐፌ ትዕዛዝ
  ዲያቆን ታዴዎስ ግርማ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


የዐቢይ ጾም ፮ኛ ሳምንት #ዘገብር_ኄር #ሰንበት በቅዳሴ ጊዜ

   #ምንባባት
፪ጢሞ ም ፪÷፩-፲፯
፩ጴጥ ም ፭÷፩-፲፪
ግብ ሐዋ ም ፩÷፮-፱

    #ምስባክ
መዝ ፴፱÷፰
ከመ እንግር ፈቃደከ መከርኩ አምላኪየ
ወሕግከኒ በማዕከለ ከርሥየ
ዜኖኩ ጽድቀከ በማኅበር ዐቢይ
     #ትርጉም
አምላኬ ሆይ፥ ፈቃድህን ለማድረግ ወደድሁ፥ ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው።
በታላቅ ጉባኤ ጽድቅን አወራለሁ።

      #ወንጌል
የማቴዎስ ወንጌል ም ፳፭፥፲፬-፴፩
      #ቅዳሴ
ቅዳሴ ባስልዮስ

╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


Репост из: 💛 የ መዝሙር ግጥሞች 💛
​​"ጌታውን ደስ ያሰኘ ታማኝና ቸር አገልጋይ ማነው?"ቅዱስ ያሬድ

በዲያቆን ግዛው ቸኮል
መጋቢት ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም

ክፍል ሁለት
በዚህ ዘመን ለምንኖር አገልጋዮች አገልግሎታችንን የሚያዳክሙ ነገሮች ምንድን ናቸው?

፩.የመንፈሳዊ ሕይወታችን መዛል፡-

መንፈሳዊ ዝለት በሁለት መንገድ ሊፈጠር ይችላል፡፡ አንደኛው ያለ አቅም የተጀመረን መንፈሳዊ ተግባር ቀስ በቀስ ማቋረጥና ወደቀድሞው ሥጋዊ ሕይወት መመለስ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ቀስ በቀስ ያደገን መንፈሳዊ ሕይወት የሚጠይቀውን መንፈሳዊ አኗኗር ከመሰልቸት የሚመጣ ነው፡፡

በሁለቱም መንገድ በሕይወቱ ወደኋላ የተመለሰ ሰው ለአገልግሎት (ለመታዘዝና ለመታመን) የነበረው ፍቅር ይቀንስና ሁልጊዜ መጸጸትን ብቻ ሥራው ያደርጋል፤ "የነበርኩ" ሕይወትንም ይለማመዳል፡፡

፪.ምቹ ሁኔታዎችን መሻት፡-

ሰዎችን መርጦ መታዘዝና ማገልገል ቀላል ነው፤ሰው ሲመቸው ማገልገል ሳይመቸው ከቤተክርስቲያን መቅረትንም ገንዘቡ ያደረጋል፡፡

ነገር ግን እስከ መጨረሻው ጸንቶ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ ደግሞ በየትኛውም ጊዜና ቦታ ሁሉ ሰማዕትነትን መክፈል ያስፈልጋል፡፡

ካልሆነ የአገልግሎትን ጣዕም አንረዳውም፡፡"በዝግታ ቆመህ በጊዜውም ያለጊዜውም ቃሉን ስበክ፤ በሁሉም እየታገሥህና እያስተማርህ፥ ገሥጽ፤ ዝለፍ፤ ፈጽመህ አጽናና፤" ያለውን የሐዋርያውን ቃል ማሰብ ጠቃሚ ነዉ፡፡ ፪ኛ ጢሞ. ፬፥፪

፫.ዓላማን መርሳት፡-

መታዘዝም ሆነ መታመን ትርጒም የሚኖረው በዓላማ ሲፈጸም ነው፡፡ ኃላፊነትን መርሳት ከመስመር ያርቀናልና ሁልጊዜ የመጣንበትን ዓላማ ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ነገር ግን ከተመሠረተው በቀር ሌላ መሠረት ሊመሠርት የሚችል የለምብሎ እንደተናገረው መሰባሰባችንን ለሌላ ዓላማ መጠቀምም ሆነ ማሰብ ተገቢ አለመሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ፩ኛ ቆሮ. ፫፥፲፩

፬.ባላገለግልም እጸድቃለሁ ብሎ ማሰብ፡-

በእርግጥ ለጽድቅ የሚያበቃን የእግዚአብሔር ቸርነት እንጂ የእኛ በጎ ምግባር ብቻ እንዳልሆነ እናውቃለን፡፡ ነቢዩ ኤርምያስም ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምናበማለት ተናግሯል፡፡ ባላገለግልም እጸድቃለሁ ብሎ ማሰብ ራስ ወዳድነት ከመሆኑም በላይ ድርሻንም አለመገንዘብና አለማወቅም ጭምር ነው፡፡

ባለአንዱ መክሊት ድርሻውን ስላልተወጣ የተፈረደበት ለዚህ ነው፡፡ "በብዙ ድካምና መከራ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንገባ ዘንድ ይገባናል" በማለት መጽሐፍም ያስረዳናል፡፡
ሰቈ ኤ. ፫፥፳፪፣ ሐዋ ፲፬፥፳፪

በጎ አገልጋይ ለመሆን ምን እናድርግ?

፩. መታዘዝ፡-

የሰው ልጅ በፈጣሪው አርአያና አምሳል ሲፈጠር የሚያዝም የሚታዘዝም ሆኖ ነው፡፡

አገልግሎት (መንፈሳዊነት) መታዘዝ ነው ስንል እንደ ባለአምስቱና ባለሁለቱ አገልጋዮች ያለምንም ማጉረምረም ከኃጢአት በስተቀር ሁሉንም ተቀብሎ ማከናወን ማለት ነው፡፡

አብርሃም "ልጅህን ሠዋልኝ" የሚለውን የእግዚአብሔርን ጥያቄና ትእዛዝ የተቀበለው በጸጋም በደስታም ነው፡፡

ነቢያት፣ ሐዋርያት ኃላፊውን ዓለም በማይታየው ዓለም ለውጠው መንፈሳዊ ተልእኮን እንዲወጡ ለእግዚአብሔር ቃል ሲታዘዙ በደስታ ነበር፡፡ ስለዚህ እኛም የአባቶቻችንን መታዘዝ መታዘዛችን ልናደርግ ይገባናል፡፡

፪.በትጋት ማገልገል፡-

ከዘመነ አበው ጀምሮ የእግዚአብሔር ወዳጆች እየተባሉ የሚጠሩ ሁሉ የፍቅረ እግዚአብሔር መገለጫቸው ትጋታቸው ነበር፡፡

መንፈሳዊ ሕይወት ከትጋት ውጭ መለኪያ የለውም፡፡ ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል አገልግሎት የተመረጡት ከሥራ ቦታቸው ነው፡፡

ጌታችን ሲመርጣቸውም እጅግ በጣም ትጋትን ለሚጠይቅ ተልእኮ ነበር፡፡ ዋጋን ለመቀበል ከጠዋት እስከ ማታ በአገልግሎት መትጋት ያስፈልጋል፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞንም በምሳሌ "በሥራው ታካች የሚሆን የሀብት አጥፊ ወንድም ነው"በማለት ትጋት የመንፈሳዊ ዋጋ መጠበቂያ መሆኑን አስረድቷል፡፡
ማቴ. ፲፥፩-፲፬፣፳፥፩-፲፪፣ ምሳ.፲፰፥፱

፫. በተስፋ የተመላ ትጉህ አገልጋይ መሆን፡-

የሰው ልጅን በተለይም በመንፈሳዊ ሕይወት የሚመሩ የእግዚአብሔር ወዳጆችን ከሌላው ሥነ-ፍጥረታት የተለዩ የሚያደርጋቸው ተስፋ ነው፡፡

የተወለደው የማደግ ተስፋ፣ ያደገው የመኖር ተስፋ፣ በኃጢአት የወደቀው በንስሓ የመነሣት ተስፋ፣ ቤተክርስቲያንን የማገልገል ተስፋ፣ መንግሥተ ሰማያትን የመውረስ ተስፋ ለሰው ልጆች በተለይም ለእኛ ለክርስቲያኖች የተሰጠን ተስፋችን ነው፡፡

ነቢያትን በትንቢት ያጸናና መከራውን እንዲታገሡ ያደረጋቸው፣ ሐዋርያትን በሐዋርያነት ያጸናና በሰማዕትነት ያጠነከራቸው፣ ከዘመነ አበው እስከ ዕለተ ምጽአት ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር አስተሳስሮ የሚኖር ኅቡእ ሰንሰለት ተስፋ ነው፡፡አባቶቻችን "የሙታንንም መነሣት ተስፋ እናደርጋለን" ሆኖ መገኘት የግድ ነው፡፡

በአጠቃላይ እኛም ኦርቶዶክሳውያን በመንፈሳዊ አገልግሎት ነግደን እንድናተርፍበት ከጌታችን የተሰጠንን መክሊት በግዴልሽነት፣ በትዳር፣ በትምህርት እና በቦታ ርቀት ምክንያት አንዳችን ካንዳችን ባለመስማማት ለራሳችን ሰበብ እየፈጠርን እንደ ባለአንዱ አገልጋይ ከቀበርነው ቆይተናል፡፡

ጌታችንም የሚመጣበትን ቀንና ሰዓት ስለማናውቅ ከቀበርንበት አውጥተን ልናተርፍበት ይገባናል።

"እነሆ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ የመዳን ቀን ዛሬ ነው"እንዳለ ሐዋርያው አትርፎ መገኘት ለእኛ ለክርስቲያኖች የግድ ያስፈልገናል፡፡
፩ኛ ቆሮ. ፮፥፪

ሊቁ ቅዱስ ያሬድም "መኑ ውእቱ ገብር ኄር ወምእመን ዘይረክቦ እግዚኡ በምግባረ ሠናይ፤ በጎ ሥራ እየሠራ ጌታው ያገኘው ቸርና ታማኝ አገልጋይ ማነው?"እንዳለ ታማኝነት እና መታዘዝ ከሌለን፣ ከመንፈሳዊ አገልግሎት ከራቅን፣ በጌታችንም ፊት መሾም መሸለም፣ ወደ ዘለዓለማዊ ደስታ መግባት አይኖረንም፡፡

ስለዚህ በተሰጠን ስጦታ፣ ሀብት፣ አቅም፣ ጊዜ፣ ቦታና ዕድሜ ሥጦታውን ለሰጠን እግዚአብሔር ታምነንና በአገልግሎት ጸንተን ወጥተው ወርደው አትርፈው ከተሾሙት ወገን እንዲደምረን አምላካችን እግዚአብሔር በቸርነቱ ይፍቀድልን፤
አሜን።

ቃለሕይወት ያሰማልን
~ተፈጸመ~
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯


✞የማይሻር ሥልጣን✞

የማይሻር ሥልጣን ከአምላክ የተሰጠው ገብረ መንፈስቅዱስ መፍቀሬ አምላክ ነው
የምሕረትን ጠል ከሰማይ ያወርዳል
ሕያው ቃልኪዳኑ ዓለምን ያድናል የአምላክ ባለሟል ዝናው የገዘፈ
በሰማያት መዝገብ ስሙ የተጻፈ

ቅሩበ ሥላሴ ርዕሰ ባሕታዊ ገብረ መንፈስቅዱስ ጻድቅ ሰማያዊ የማይሻር ሥልጣን ከአምላክ የተሰጠው
ገብረ መንፈስቅዱስ መፍቀሬ አምላክ ነው


የኃጥአን ተስፋ ጌታ ያከበረው የነፍስ ደስታዋ ለአጋንንት ፍርሃት ነው
የጻድቃን ነቢያት የሐዋርያት ዘመድ
የሰው ልጆች ወዳጅ ከአምላክ የሚማልድ

ቅሩበ ሥላሴ ርዕሰ ባሕታዊ ገብረ መንፈስቅዱስ ጻድቅ ሰማያዊ የማይሻር ሥልጣን ከአምላክ የተሰጠው
ገብረ መንፈስቅዱስ መፍቀሬ አምላክ ነው


የመላእክት ወዳጅ ዕጹብ ባሕታዊ
በተጋድሎ ጽናት ሆነ ሰማያዊ
የበረሃው መናኝ ወንጌልን የኖረ
ገብረ መንፈስቅዱስ ሰይጣን ያሳፈረ

ቅሩበ ሥላሴ ርዕሰ ባሕታዊ
ገብረ መንፈስቅዱስ ጻድቅ ሰማያዊ
የማይሻር ሥልጣን ከአምላክ የተሰጠው
ገብረ መንፈስቅዱስ መፍቀሬ አምላክ ነው


            መዝሙር
         ፍስሐጽዮን ካሳ

"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው"
              ምሳ፲፥፱
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯

Показано 20 последних публикаций.