✞ ጋሜል - የመዝሙር ግጥሞች ✞


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


✟ የኦርቶዶክሳውያን መንፈሳዊ የምስጋና ቤት ✟
ቤተ ክርስቲያንን አንተውም ከቶ
የሰጠንን አምላክ በደሙ መስርቶ
የሰጠንን ጌታ በመስቀሉ ሞቶ
የአምላካችንን ቤት አንተውም ከቶ
ለማስታወቂያ ሥራ➠ @Naolviva
💿 የተዋሕዶ የመዝሙር ግጥሞች 💿
   ✍ / ትምህርቶችን ለማግኘት ✍
👇👇👇
https://t.me/maedot_ze_orthodox

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


ከ17 ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ




Репост из: ✞ ጋሜል - የመዝሙር ግጥሞች ✞
​​✝ ሰሙነ ሕማማት✝


ከማክሰኞ የቀጠለ

ረቡዕ፦

ረቡዕ ምክረ አይሁድ ይባላል፡፡ ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ  እንደሚገባቸው ምክር ያጠናቀቁበት ቀን ነውና፡፡

በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ቀን የተቃረበ በመሆኑ፣ ብዙው ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ፣ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለ ነበር ሁከት እንዳይፈጠር ነው፡፡

በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ፣ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡ ማቴ፳፮፥፩-፲፬፣ ማር ፲፬፥፩-፪፣ ቁ ፲ ,፲፩፣ ሉቃ ፳፪፥፩-፮ ፤ የሐዲስ ኪዳን ካህናትና ምእመናን በዚሁ ዕለት በቤተክርስቲያን ተሰብስበው መላ ሰውነታቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው የሞት ፍርዱን በማሰብና በማልቀስ፣ ሐዋርያት ከጌታችን መያዝ በኋላ በኀዘን በፍርሐት እንደነበሩ እያሰቡ መጻሕፍትን በማንበብ በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ተወስነው ይቆዩና ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡

ረቡዕ የመልካም መዓዛ ቀንም ይባላል። ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ፣ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት፣ /ባለሽቱዋ ማርያም/፤ "ከእንግዲህ ወዲህ በኃጢአት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ፣ ኃጢአትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ" ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ፣ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ፣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የተሞላ ሽቱ ይዛ በመሔድ በጠጉሩ /በራሱ/ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባችው ነው ረቡዕ የመዓዛ ቀን የተባለው፡፡

ረቡዕ የእንባ ቀንም ይባላል። ማርያም እንተ እፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ፣ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና፤ በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና፡፡ ማቴ ፳፮፥፮-፲፫፣ ማር ፲፬፥፱ ፣ ዮሐ ፲፪፥፰ ኃጢአትን በማሰብ ማልቀስና ራስን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ማቅረብን ከምታስተምረን ማርያም እንተ እፍረት እንባን ለንስሐ ሕይወት ልንጠቀምበት ይገባል፡፡

ሐሙስ፦

       ይቆየን፦

እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ያብጽሐነ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም
  ፦
ያለ ደዌ ያለ መከራ ያለ ድካም እግዚአብሔር በደስታና በሰላም ለብርሃነ ትንሳኤው ያድርሰን።
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
    @yemezmur_gexem
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈


Репост из: ✞ ጋሜል - የመዝሙር ግጥሞች ✞
​​✝ሰሙነ ሕማማት✝

    ከሰኞ የቀጠለ

ማክሰኞ፦
ሰኞ ባደረገው አንጽሖተ ቤተመቅደስ ምክንያት፣ ሹመትን ወይም ሥልጣንን ለሰው ልጅ የሰጠ ጌታችን፣ ስለ ሥልጣኑ በጸሐፍት ፈሪሳውያን ተጠይቋልና፤ የጥያቄ ቀን ይባላል፡፡

ጥያቄውም ከምድራውያን ነገሥታት፣ ከሌዋውያን ካህናት ያይደለህ ትምህርት ማስተማር፣ ተአምራት ማድረግ፣ ገበያ መፍታትን፣ በማን ሥልጣን ታደርጋለህ? ይህንንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ? የሚል ነበር፡፡ ማቴ ፳፩ ፥፳፫ - ፳፯፣ ማር ፲፩፥ ፯ -፴፫ ፣ ሉቃ ፳፩ ፥፳፫ ፴፯፣ ማር ፲፩ ፥ ፳፯ ፴፫፣ ሉቃ ፳ ፥ ፩ - ፰፤

እርሱም ሲመልስ፤ እኔም አንድ ነገር እጠይቃችኋለሁ፣ እናንተም ብትነግሩኝ በማን ሥልጣን እነዚህን እዳደርግ እነግራችኋለሁ፡፡ የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረ፣ ከሰማይ? ወይስ ከሰዉ? በእግዚአብሔር ፈቃድ፣ ወይስ በሰው ፈቃድ? አላቸው፡፡

እነርሱም ከሰማይ ብንል ለምን አልተቀበላችሁትም ይለናል፤ ከሰው ብንል ሕዝቡ ሁሉ ዮሐንስን እንደ አባት ያከብሩታል፣ እንደ መምህርነቱ ይፈሩታልና ሕዝቡን እንፈራለን፤ ተባብለው ከወዴት እንደሆነ አናውቅም ብለው መለሱለት፡፡

እርሱም "እኔም በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ አልነግራችሁም አላቸው" ይህንንም መጠየቃቸው እርሱ የሚያደርጋቸውን ሁሉ በራሱ ሥልጣን እንዲያደርግ አጥተውት አልነበረም፣ ልቡናቸው በክፋትና በጥርጥር ስለተሞላ እንጂ፡፡

በማቴ ፳፩ ፥፳፰ ፣ ምዕ ፳፭፥፵፮ ፣ ማር፲፪፥ ፪ ፣ ምዕ ፲፫፥ ፴፯ ፣ ሉቃ ፳ ፥፱ ፤ ምዕ ፳፩ ፥ ፴፰  የሚገኙት ትምህርቶች ሁሉም የማክሰኞ ትምህርት ይባላሉ፡፡

በዚህ ዕለት በቤተ መቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረ፣የትምህርት ቀንም ይባላል።

ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ከሥጋዊ ነገር ርቆ በዚህ ሰሞን የሃይማኖት ትምህርት ሲማር ሲጠይቅ መሰንበቱ መጽሐፋዊ ሥርዓት ነው፡፡

ረቡዕ፦

   ይቆየን፦

እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ያብጽሐነ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም
  ፦
ያለ ደዌ ያለ መከራ ያለ ድካም እግዚአብሔር በደስታና በሰላም ለብርሃነ ትንሳኤው ያድርሰን።  
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
    @yemezmur_gexem
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈


Репост из: ✞ ጋሜል - የመዝሙር ግጥሞች ✞
​​✝ሰሙነ ሕማማት✝ 

በነቢዩ ኢሳይያስ ነስአ ደዌነ ወፆረ ሕማመነ፤ በእውነት ደዌአችንን ተቀበለ፣ ሕመማችንንም ተሸከመ፣ እኛ ግን እንደተመታ፣ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሰፈ፣ እንደተቸገረም ቆጠርነው፡፡ እርሱ ግን ስለመተላለፋችን ቆሰለ፣ ስለ በደላችንም ደቀቀ፣ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፣ በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን፡፡"ኢሳ ፶፫ ፥፬-፯
ተብሎ የተነገረው ቃል ተፈጽሞ፣ ጌታችን ለድኅነተ ዓለም ሲል በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ የተቀበለው ጸዋትወ መከራ የሚዘከርበት ሳምንት ነው፡፡

ከሆሣዕና ማግስት እስከ ትንሣኤ ያለው የጾመ እግዚእነ መዝጊያ ሳምንት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡

በሰሙነ ሕማማት ካህናትና ምእመናን በአጸደ ቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው፣ ከሐሜት፣ ከነገርና ከኃጢአት ርቀው፤ የሕማሙን ነገር የሚያወሳውን ዜማ ሲያዜሙ፣ ግብረ ሕማም በመባል የሚታወቀውን መጽሐፍ ሲያነቡ፣ ሲሰሙ፣ ሲሰግዱና ሲጸልዩ ይሰነብታሉ፡፡

ካህናትና ምእመናን በቤተ ክርስቲያን ተገኝተው ወዛቸው ጠብ እስኪል ድረስ በነግህ፣ በሠለስት፣ በስድስት፣ በተሰዓት /በዘጠኝ/ ሰዓት፣ በሰርክ /በዐሥራ አንድ/ ሰዓት መላልሰው ሲሰግዱና ሲጸልዩ ይሰነብታሉ፣

በተለይም ካህናት በማንኛውም አገልግሎት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፣ ምክንያቱም ጌታችን የደረሰበትን መከራ ሥቃይን እና 5ሺ 5መቶ ዘመን የሰው ልጅ በጨለማ ግዞት ይኖር እንደነበር ለማዘከር ነው፡፡

ሰሙነ ሕማማት የጌታችንን ሕማማት ከማሰብ ጋር በርካታ ድርጊቶች መፈ ጸማቸውንም የምናስታውስበት ሳም ንት ነው፡፡በዕለት በዕለት ከፍለን በየትኛው ቀን ምን ተደረገ እያልን እንጠይቅ?

ሰኞ
ጌታችን የሆሣዕና ዕለት ቢታንያ በምትባል መንደር ያድራል በማግስቱም ከቢታንያ ሲወጣ ተራበ ።ማር ፲፩፥፲፩-፲፬ ቅጠል ያላትን በለስ ከሩቅ አይቶ ወደ በለሲቱ ቀረበ፣ ነገር ግን ከቅጠል በቀር አንዳች ፍሬ አላገኘባትም፡፡

ከአሁን ጀምሮ ማንም ከአንቺ ፍሬ አይብላ ብሎ ረገማት፡፡ በዚህ ምክንያት ይህ ዕለት መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ ይባላል፡፡

ትርጓሜ፦ በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ናት፤ፍሬ የተባለች፣ ሃይማኖትና ምግባር ናት፡፡ ከእስራኤል ፍቅርን፣ ሃይማኖትን፣ ምግባርን ፈለገ አላገኘም፡፡

እስራኤልን ሕዝበ እግዚአብሔር መባ ልን እንጂ፣ ነቢይነት፣ ካህንነት፣ መሥ ዋዕት አይገኝብሽ ብሎ ረገማት፡፡ በመርገሙ ምክንያት ትንቢት ክህነት መሥዋዕት ከቤተ እስራኤል ጠፉ፡፡

በለስ ኦሪት ናት፦ ኦሪትን በዚህ ዓለም ሰፍና ቢያገኛት ኦሪትና ነቢያትን ልሽር አልመጣሁም ልፈጽም እንጂ በማለት ፈጸማት፤ ሕገ ኦሪትን ከመፈጸም በቀር በእርሷ ድኅነት አላደረገባትምና ፍሬ ባንቺ አይሁን አላት፤ ድኅነት በአንቺ አይደረግብሽ ብሏታልና እንደመድረቅ ፈጥና አለፈች፡፡ በአዲስ ኪዳን የድኅነት ዘመንም ተተካች፡፡

በለስ ኃጢአት ናት የበለስ ቅጠል ሰፊ እንደሆነች ሁሉ ኃጢአት በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፍና አገኛት፡፡ በለስ ሲበሉት ይጣፍጣል ቆይቶ ግን ይመራል፤ ኃጢአትም ሲሠሩት ደስ ደስ ያሰኛል ኋላ ግን ያሳዝናል፡፡

በአንቺ ፍሬ አይገኝ የሚለውም፤ በኃጢአት ፍዳ ተይዞ የሚቀር አይኑር ለማለት ነው፡፡ በለሷም ስትረገም ፈጥና መድረቋ፣ በአዳም ምክንያት ያገኘችን ዕዳ በደል በእርሱ እንደጠፋችልን ለመግለጽ ነው፡፡

ከዚህ ቀጥሎ ወደ ቤተ መቅደስ ሔደ፤ ቤተ መቅደስ ቤተ ጸሎት፣ ቤተ መሥዋዕት መሆኑ ቀርቶ ቤተ ምሥያጥ /የንግድ ቤት/ ሆኖ ቢያገኘው፤ "ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች... እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት"ማቴ ፳፩፥፲፫  ብሎ የሚሸጡበትን ሁሉ ገለበጠባቸዉ፣ ገርፎም አስወጣቸዉ፣ ይህም የሚያሳየው፦ ማደሪያው ቤቱ የነበርን እኛ የአዳም ልጆች ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአታ ችንን ሁሉ እንዳራቀልን የሚገልጽ ነው፡፡ ከዚህም የተነሣ አንጽሖተ ቤተ መቅደስ የተፈጸመበት ሰኞም ይባላል፡፡

ማክሰኞ፦

        ይቆየን    
  
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ያብጽሐነ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም
  ፦
ያለ ደዌ ያለ መከራ ያለ ድካም እግዚአብሔር በደስታና በሰላም ለብርሃነ ትንሳኤው ያድርሰን።  
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
    @yemezmur_gexem
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈




✞ በዝምታ ✞

በዝምታ መልስ አለ ከጌታ (፫)

        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ለእግዚአብሔር ነግሮ ለሰው ዝም የሚል
ተሸክሞ ኖሮ እርጥቡን መስቀል
ስለ እራሱ ትቶ እውነት የሚያወራ
ይሻገራል ገደል ይወጣል ተራራ [፪]

        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ይወቁልኝ ብሎ ስሙኝ ስሙኝ ያለ
ንፋስ ተደገፈ ጉምን ተከተለ
ሰዉ በራሱ ጥላ እንደማይጠለል
ከሰማይ ካልሆነ ምስክር የታል [፪]

        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ዳንኤል ዝም አለ ፍርድን ሲቀበል
አልተከራከረም ለአንበሶች ሲጣል
ለእግዚአብሔር ሲናገር ተረፈ ከሞት
ስንፍና ስሕተት አልተገኘበት [፪]

        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
የእግዚአብሔር ልጅ ያለው ምስክር አለው
መንፈሱ ነዉና የሚናገረው
ሸንጎ ቢያቆሟችሁ ልባችሁ ይበርታ
ስለ እናንተ ሆኖ ይናገራል ጌታ [፪]

              መዝሙር|
ዘማሪ ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE


https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ ወደ ልቤ ✞

ወደ ልቤ እንድመለስ
ይርዳኝ የአንተ ቅዱስ መንፈስ
አማኑኤል [፪] ልመናዬን ተቀበል


      አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
እንድሮጥ ወደ አንተ በንስሐ መንገድ
ሳበኝ በመንፈስህ በፍቅርህ ገመድ
ወደ ሞት እንዳይዘምት እንዳይፈጥን እግሬ
ቀድመህ ድረስልኝ በአንተ ነዉ መኖሬ

ያልረጋ ያልሰከነ ማንነት ለብሼ
እመላለሳለዉ በኃጢአት ረክሼ
እንደ ሕፃናቱ ልበል ሆሳዕና
ማራናታ ስልህ ጌታ ሆይ ቶሎና


      አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ቀኑ ሳይጨላልም ሳይረፍድብኝ ጊዜዉ
ጉብዝናዬ እንዳይነጉድ አረሜን ሳልነቅለዉ
ፍሬን ሳላፈራ እንዳልጣል ሲኦል
በቃል መዶሻ ቅርጼን አስተካክል

      አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ቃልህን ምሰማበት ጆሮዬ ሳይከዳኝ
ፍቅርህን የማይበት አይኔም ሳይደክምብኝ
አስበኝ ስላልከኝ አንተ የኔ ወዳጅ
ሳይዝልብኝ እግሬ ላቅና ወደ ደጅ
 
      አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
አመስጋኝ ከንፈርን ርቱዕ አንደበትን
አድለኝ አምላኬ የምትከብርበትን
ስጠኝና ልስጥህ አትርፌ ልመለስ
ልባረክ በብዙ ጸጋህ በኔ ይፍሰስ

      አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
የሕይወቴ መዓዛ ጠረኔ እንዲቀየር
አንተን[፪] እንድል ለቃልህ እንዳድር
ሳኦል ማንነቴን በጳዉሎስ ተክተ
የወንጌል ገበሬ አድርገኝ ስለአንተ

               መዝሙር|
       ዘማሪ የአብቃል ደሳለኝ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE


https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ እግዚአብሔር ይመጣል ✞

እግዚአብሔር በገሀድ ይመጣል
ከመላእክቱ ጋር ይገለጣል
በደብረ ዘይት ሲነግሥ በክብሩ
ያኔ ይመዘናል የሰው ምግባሩ (፪)


       አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
በግርማ ሲመጣ ከመላእክት ጋራ
በፊቱ እሳት ሲነድ ውብ መልኩ ሲያበራ
ለደስታ ይጠራሉ ጻድቃን በሥራቸው
ከበደሉት ጋር ነው የኃጥኣን ሥፍራቸው
ያን ጊዜ ራራልኝ ጌታዬ
ያን ጊዜ እዘንልኝ ጌታዬ
ከንቱ እንዳይሆብኝ ዋይታዬ


       አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
በቀርነ መለከት ተቀስቅሰው ሙታን
ይሰማሉ ፍርድን ቃለ ኃያል ጌታን
የሰው ልጅ ምግባሩ በአምላክ ሲመዘን
በምጽአት ይሆናል ዝማሬና ኀዘን
ያን ጊዜ ራራልኝ ጌታዬ
ያን ጊዜ እዘንልኝ ጌታዬ
ከንቱ እንዳይሆብኝ ዋይታዬ


       አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
በዚያን ጊዜ እናት ልጇን አታድንም
አባት መሸሸጊያ በፍጹም አይሆንም
በጎ መልካም ሥራ ነው የሚታደገው
ሰው ቃሉን ያስተውል ወንጌሉን ልብ ያርገው
ያን ጊዜ ራራልኝ ጌታዬ
ያን ጊዜ እዘንልኝ ጌታዬ
ከንቱ እንዳይሆብኝ ዋይታዬ

                   
       አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ፀሐይ ይጨልማል ኳክብት ይወድቃሉ
ኃይላተ ሰማያት ያኔ ይናወጻሉ
በእሳት ላንቃ ላይ በእግሩ ይራመዳል
በክብር ዙፋኑ ተቀምጦ ይፈርዳል
ያን ጊዜ ራራልኝ ጌታዬ
ያን ጊዜ እዘንልኝ ጌታዬ
ከንቱ እንዳይሆብኝ ዋይታዬ


               መዝሙር|
  ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE


https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ ኪዳነ ምሕረት እናቴ ✞

ኪዳነ ምህረት እናቴ ምስጢረኛ ጓዳዬ
የጎደለኝን ታውቂያለሽ
ከአፌ ሳይወጣ ሳልነግርሽ(፪)


አልፏል መናኛው ኑሮ
ምልጃሽ ውኃውን ቀይሮ
መልካሙ ወይን ደረሰ
እንባዬ ባንቺ ታበሰ(፪)

    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ልዘምር ልቁም ከፊትሽ
ልምጣ ልንበርከክ ለክብርሽ
ብርቅ ከሀገር ከቤቴ
ከቶ አልረሳሽም እናቴ(፪)

    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
አልልም መቼ ነው ቀኑ
የኔ መጎብኛ ዘመኑ
እንደሚፈፀም አውቃለው
ሁሉን በጊዜው አያለው(፪)

    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
የልቤን ችግር ላዋይሽ
ከስዕልሽ ፊት ቆሜ
እንባዬ ቀድሞ ዝም አልኩኝ
ሳልነግርሽ ስለምታውቂ(፪)

               መዝሙር |
ሊቀ መዘምራን ዲያቆን ቴድሮስ ዮሴፍ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE


https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ በዕፀ መስቀሉ ✞

በዕፀ  መስቀሉ የተከፈለልኝ
የኢየሱስ ፍቅር  ምንኛ ማረከኝ
ከፍቅርም በላይ ሆነና መሠጠኝ
ከመስቀል ሥር ሁኜ ፊቱን እያየሁኝ


ዓለምን በፍቅሩ ያሸነፈ ጌታ
የጸብን ማዕበል በፍቅሩ የገታ
ሕይወቴን ጸጥ አድርጎ ይምራት በምልሐቱ
እኔ ምን አለፍኝ አልደክምም በከንቱ

            አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►

ደሙ ከወዙ ጋር ተዋሕዶ ሲወርድ
በእኔ በደል ጌታዬ ቀረብልኝ ለፍርድ
ኃጢአቴን በጫንቃዉ ተሸክሞልኛል
በደሌን ደምሥሶ ንፁሕ አድርጎኛል

            አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►

የቀራንዮ ግፍ በአንተ ላይ የሆነዉ
ሰይጣንን ጠርቆ ከመንገድ አወጣዉ
እሾሕ አሜኬላዉ ተደምስሶልናል
የንጹሕ በግ ደም አዳምን ታድጓል

            አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►

ይኽንን ሥጋዬን ብሉ ይላችሁዋል
ይኽንን ደሜንም ጠጡ ይላችሁዋል
ከመስቀል ሥር ሆነን ደሙን እንቀበል
ሥጋዉን እንብላ ሠዉ ሆይ ችላ አንበል

              መዝሙር|
  ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ የታለ ፍቅራችን ✞

የታለ የታለ ፍቅራችን
የታለ የታለ ፍቅራችን
እዳላገለገልን እደየ ፀጋችን
መጋዉን በተነ መለያየታችን


        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
የአንዳችን ከአንዳችን ቢለያይም ፀጋው
የመረጠን ጌታ የጠራን አንድ ነው
እርሱ ቢያወርሰን እያለችን እርስት
ሕብረታችን ጠፋ በኛ መለያየት [፪]

        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
አሕዛብ ደንግጠው በትላንት ቅኔያችን
ወደቤቱ ገብቶ የራቀ ሕዝባችን
እዳይሰናከል መንጋው በመንደኛ
ምሳሌ እንሁነው እዉነተኛ እረኛ[፪]

        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
የማንኖረዉ ስለምንናገር
የሕጉ ፍጻሜ ስለሌለን ፍቅር
መንጋዉ ሳይለወጥ ዘመናት አለፉ
ብርቱ የነበሩ ስቶቹ ሰነፉ [፪]

        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
የአንድ እናት የአንድ አባት ልጆች ከተባልን
ከአንድ ማዕድ በልተን ለምን ተለያይን
እንግዳዉን ትምህርት ወደኛ ያመጣ
የበግ ለምዱን ያውልቅ ከመካከል ይዉጣ[፪]

               መዝሙር|
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ እንደምትወደኝ አውቃለሁ ✞

እንደምትወደኝ አውቃለሁ [፪]
ሁሌም ስትጠራኝ እሠማለሁ
የቅጠል ልብስን ብለብስም
ሞቴን አትፈልግም

ኧኧኧ ሞቴን አትፈልግም

አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ከቤተልሔም ጎልጎታ
እስከ ቀራንዮ ኮረብታ
እየተከተልክ ፈለከኝ
ከኃጢአት ቁስሌ ፈወስከኝ

ኧኧኧ ሞቴን አትፈልግም
አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
እረሳው ጌታ ሕግህን
ቀጥፌ በላው በለስን
ከገነት ቤቴ ተሰደድኩኝ
ከፍቅር እጅህ ተለየሁኝ

እንደምትወደኝ አውቃለሁ
አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ተብለህልኝ ወንጀለኛ
ቆመህልኛል ከሐሰት ዳኛ
አንተ ስትሞት ተሰቅለህ
ክብርን ጠገብኩኝ ከእጅህ

እንደምትወደኝ አውቃለሁ
አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
አሁን የለብኝ ወቀሳ
ከፍለህልኛል ለእኔ ካሳ
መልሰኸኛል ወደ ቤቴ
አክብረኸኛል ደጉ አባቴ

እንደምትወደኝ አውቃለሁ

መዝሙር|
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ የኢዮብ መልሱ ✞

እንደምነህ ቢሉት ዘመዶች ከድተውት
ሚስቱ ትታው ሄዳ ልጆች ሞተውበት
ዓይኖቹ በምሬት እንባ አላፈሰሱ
እግዚአብሔር ይመስገን [፪] ነበር የኢዮብ መልሱ

በሕይወት ገጥሞት የበረታ ፅልመት
በአንድ ቀን ሲነጠቅ ልጆችና ንብረት
አካሉ በቁስል ተይዞ በጠና
ኢዮብ እንዴት ቻለ ለአምላኩ ምስጋና

        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►

በሰጠበት መንደር ሲቆም ለልመና
ሚስቱ ሙት ስትለው ጌታን እርገም እና
የስንፍናን ነገር አይሰማም ጆሮዬ
ይክሰኛል እርሱ ይችላል ጌታዬ

        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►

ቅን ነገር መናገር ለአፌ ከቸገረኝ
አምላኬ እንዳያዝን ምነው ዝም በአልኩኝ
ልሳኔ እንዳይጠራ ሞት እና መከራ
ለምስጋና ቆሜ ነገን ዛሬ ልሥራ

        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►

እግዚአብሔር ይመስገን ቢጎድልም ቢሞላም
ለዓይኔ ሽፋሽፍት እንቅልፍ እንኳን ባጣም
ብዙ እንደነበረው ትናንትና ደጄ
ክፉውንም ደግሞ ይቀበላል እጄ

                 መዝሙር|
    ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


የካቲት ❷❸
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን ለኢትዮጵያ ገበዝ (ጠባቂ) ለአድዋው አርበኛ፣ ለፍጡነ ረድኤት፣ ለገባሬ ተአምር ሊቀ ሰማዕታት ለቅዱስ ጊዮርጊስ በ1888ዓ.ም በአድዋ ጦርነት ንጉሠ ነገሥትን ምኒልክና ሰራዊቱ ለረዳበት፤ ኢትዮጵያ በሮማውያንን (ጣልያንን) ድል ለተቀዳጀችበት ለ129 (ለአንድ መቶ ሃያ ዘጠነኛው ) ለአድዋ በዓል በሰላም አደረሰን።

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


Репост из: ✞ ጋሜል - የመዝሙር ግጥሞች ✞
​​✞ ​​ዐቢይ ጾም ✞

በሊቀ ጉባኤ ቀለመወርቅ ውብነህ
    የካቲት ፴ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም

         ክፍል አንድ [፩]

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ
     አሐዱ አምላክ አሜን

ጾም ማለት መተው መከልከል ማለት ነው፡፡

ጾም በእግዚአብሐር የተቀደሰ ተግባር ስለኾነ ወደ ቅድስና ጎዳና የሚመራ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችንም ሥርዓት ሠርታ ጾምን ከአምላካችን ጋር ኅብረት እንዲኖረን፤ መንፈሳዊ ኃይል እንድናገኝ ታደርጋለች፡፡

በጾም ወራት ከመባልዕት መከልከል ብቻ ሳይኾን ዐይን ክፉ ከማየት፣ አንደበት ክፉ ከመናገር፣ ጆሮ ክፉ ከመስማት መቆጠብ እንደሚገባው በቅዱሳት መጻሕፍት ተጽፎአል፡፡ 

"ይጹም ዐይን ይጹም ልሳን እዝንኒ ይጹም እምሰሚዓ ኀሡም በተፋቅሮ" እንዲል ቅዱስ ያሬድ ጾመ ድጓ

በጾም ወራት ላምሮት፣ ለቅንጦት የሚበሉ ወይም ለመንፈሳዊ ኃይል ተቃራኒ የኾኑ ሥጋዊ ፍትወትን የሚያበረታቱ፣ ሥጋንና የሚያሰክሩ መጠጦችን ዳን.፲፥፪-፫

ቅቤና ወተትን ከመጠቀም መታቀብ እንደሚገባ ታዟል።መዝ.፻፰፥፳፬፣ ፩ቆሮ.፯፥፭፤ ፪ቆሮ.፮፥፮

በብሉይ ኪዳን ጾም ከፍተኛ ቦታ ነበረው፡፡ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ከእግዚአብሔር በሚገናኙበት ወራት እህልና ውኃ በአፋቸው አይገባም ነበር።ዘፀ.፴፬፥፳፰

አስቴር አስቀድማ ሦስት ቀን ጾማ ጸልያ በእስራኤል ላይ የመጣውን መቅሠፍት እንዲመለስ አድርጋለች። አስቴር ፬፥፲፭-፲፮

በዘመኑ በኃጢአት ብዛት የታዘዘው የእግዚአብሔር መዓት የሚመለሰውም ሕዝቡ በጾም ሲለምኑትና ሲማልዱት ነበር። ዮናስ ፪፥፯-፲

በሐዲስ ኪዳንም ጾም ሰው ሠራሽ ሕግ ሳይኾን ራሱ ክርስቶስ የሠራው ሕግ ነው ማቴ.፬፥፪፤ ሉቃ.፬፥፪

ቅዱሳን ሐዋርያትም በየጊዜው ከመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ የሚቀበሉት በጾም በጸሎት ላይ እንዳሉ ነበር።ሐዋ፲፫፥፪

ለስብከተ ወንጌል የሚያገለግሉ ዲያቆናትና ቀሳውስትም የሚሾሙት በጾምና በጸሎት ነው።ሐዋ.፲፫፥፫፤ ፲፬፥፳፫

እንደ ቆርነሌዎስ ያሉ ምእመናን ያላሰቡትን ክብር ያዩና ያገኙ የነበረውም በጾምና በጸሎት ፈጣሪያቸውን በመማጸን ነው። ሐዋ ፲፥፴

ዐቢይ ጾም ጌታችን ከተጠመቀ በኋላ ዐርባ ቀን የጾመው፤ እኛም እንድንጾማቸው በቤተ ክርስቲያናችን ከታዘዝናቸው ሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት አንዱ ነው፡፡

ምእመናን ጌታችን ያደረገውን ምሳሌ ተከትለን ጾሙን በየዓመቱ እንጾመዋለን፡፡

ዐቢይ ጾም ስምንት ሳምንታት (፶፭ ቀኖች) አሉት፡፡ በውስጡ ስምንት ቅዳሜዎች፣ ሰባት እሑዶች ይገኛሉ፡፡ ይኸውም ዐሥራ አምስት ቀን ማለት ነው፡፡ እነዚህ ቀናት ከጥሉላት እንጂ ከእኽል ውኃ ስለማይጦሙ የጦሙ ወራት ዐርባ ቀን ብቻ ይኾናል፡፡

ጾሙ በተለያዩ ስሞች ይጠራል፤

አንደኛ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው በመኾኑ፣እንደዚሁም "ዐቢይ እግዚአብሔር ወዐቢይ ኀይሉ ዐቢይ እግዚአብሔር ወብዙኅ አኰቴቱ"መዝ.፵፯፥፩፤ መዝ.፻፵፮፥፭ የተባለ ጌታችን የጾመው ጾም ስለኾነ"ዐቢይ ጾም"ይባላል፡፡

ሁለተኛ "ሁዳዴ ጾም"ይባላል፡፡ ይህም የመንግሥት እርሻ ወይም ማንኛውም የሕዝብ ብዛት ያለበት ሥራ ሁዳድ ስለሚባል ሲኾን፣ ዐቢይ ጾምም ከአጽዋማት ዅሉ ብዙ ቀናት ስለሚጾምና ኃያሉ አምላካችን ስለጾመው ነው
አሞ ፯፥፩

ሦስተኛ "በአተ ጾም"ይባላል፡፡ የጾም መግቢያ፣ መባቻ ማለት ነው፡፡

አራተኛ "ጾመ ዐርባ"ይባላል፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ፵ ቀን ስለኾነ  ማቴ.፬፥፩

አምስተኛ "ጾመ ኢየሱስ"ይባላል፡፡ ጌታችን እርሱ ጾሞ፣ ጹሙ ብሎ ስላዘዘን፡፡

ስድስተኛ "ጾመ ሙሴ"ይባላል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በዘወረደ ጾመ   ድጓው "ከመዝ ይቤ ሙሴ እስመ ለዓለም ሙሴኒ ይቤ በውስተ ኦሪት" እያለ ስለዘመረ /የሰኞ ዕዝል/፡፡

ከዐቢይ ጾም ሳምንታት መካከል የመጀመሪያው ሳምንት"ዘወረደ (ዘመነ አዳም)ይባላል፡፡

ዘወረደ ማለት ከላይ የመጣ፣ የወረደ ማለት ነው፡፡ ይህም አምላካችን አዳምንና ልጆቹን ከሞት ለማዳን ሲል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መኾኑንና የፈጸመውን የማዳን ሥራ ያመለክታል፡፡ 

"ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም" ካለው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቃል በመነሣት ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኵሉ ዘየሐዩ በቃሉ" በማለት በጾመ ድጓው መጀመሪያ ላይ ይህን ዕለት ገልጾታል፡፡
ትርጕሙም "አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አምላክ አይሁድ ሰቀሉት፤ የሰማይ ሥልጣን ያለው የዅሉ ጌታ እንደኾነም ምንም አላወቁም" ማለት ነው፡፡

ይህም ድርሰት በቤተ ክርስቲያናችን የጾም መጀመሪያ የኾነው ዕለተ ሰንበት ዋዜማ፣ መግቢያ (መሐትው) ኾኖ ከዋዜማ በፊት ምንጊዜም በየዓመቱ ይቆማል፤ ይዘመራል፤ ይመሰገናል፡፡

በዚህ ሳምንት በተለይም እሑድና ሰኞ የሚነገሩት ውዳሴያት ከመጻሕፍተ ኦሪትና ነቢያት የተወሰዱ ናቸው፡፡ ሁለተኛም ሳምንቱ "ሙሴኒ"በመባል ይታወቃል፡፡

እግዚአብሔር አምላክ አዳምን ለማዳን ከሰማይ መውረዱንና በመስቀል መሰቀሉን ስለሚያወሳ ነው፡፡

በተጨማሪም ይህ የመጀመሪያው ሳምንት"ጾመ ሕርቃል"ይባላል፡፡ ሕርቃል (ኤራቅሊየስ) የቤዛንታይን ንጉሥ ነበር፡፡ ይህ ሳምንት በስሙ የተጠራበት ምክንያት...

    ክፍል ሁለት ይቀጥላል....

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ እንዲህ በአራት ነጥብ ✞

እንዲህ በአራት ነጥብ ሊዘጋ ምዕራፉ
እግዚአብሔር ሊያሸንፍ የእርሱ ሆኖ ሰልፉ
መልካም ለመናገር አፉ ባይታደል
ይኼን እስኪያይ ጠላት ምን አለ ዝም ቢል[፪]


           አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
መልካሙን ደብቆ ክፉን እያሳየ
ይለኝ ነበር ጠላት እግዚአብሔር ዘገየ
ግን ሁሉን በጊዜው ውብ አግድጎ ሲሰራ
አፍሯል ለዘላላም ደንቆት የእርሱ ሥራ[፪]

           አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
በቃ ልጅ የለህም አትወልድም ሣራ
ላይሰማህ እግዚአብሔር ጮኸ ብትጣራ
እያለ ጠላቴ መስሎት ያሸነፈ
ይስሐቅ ተወለደ ያ ቀንም አለፈ [፪]

           አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ፍፃሜዬን ሳያይ ገና ከጅምሩ
ጠላት በእሱ ግምት ብዙ መናገሩ
አስብሎታል ቴቄል ተቀይሮ ስሙ
የዘገየ መስሎ ጌታ በመቅደሙ [፪]

           አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ድንጋይ ያሸከመን ውሃ ተሸከመ
ለእኛ ቀን ወጣልን ለእርሱ ግን ጨለመ
ገዳይ ቢዘገይም ሟች በመገስገሱ
ፈረሰኛው ሞተ እስከነ ፈረሱ [፪]

           አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ቢመስለንም ሌሊቱ ፍፁም የማይነጋ
ተቆልፎ የሚቀር በሩ እንደተዘጋ
እርሱን ተስፋ አድርገው ባመንክበት ፅና
ቀን አለው እግዚአብሔር ያደርግሃል ቀና [፪]

               መዝሙር|
ሊቀ መዘምራን ዲ/ን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


​​​​VALENTINE'S DAY
ሼር በማድረግ ትውልዱን ከጥፋት እንታደግ❗

አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ ቤዛ ሆኖ በፍቅሩ የገዛን እጃችንን ለጣኦት እንድንሰጥ አይደለም ብዙ ዋጋ የተከፈለብን እስከ ሞት እንከን በሌለው ፍቅሩ የወደደን መንግስቱን እንድንወርስ እንጂ እንድንጠፋ አይደለም።

የቫላንታይ ቀን ድብቅ እውነታ ስንቶቻችን እናውቃለን? ይህን የቫላታይን ቀን (የፍቅረኛሞች ቀን) ብለን ስንቶቻችን ነን የምናከብረው ? ወይስ ሰው ስላከበረውና የስልጣኔ መገለጫ መስሎን ነው የምናከብረው ???

ከክርስቶስ ልደት በፊት በባቢሎን ፤ቤልዘቡል ፤በግሪክ ፓን ፤ ሮማ ሞሎቅ ፤ በላቲን ሳተርን ለሚባሉት ሰይጣኖች ያላገቡ ሴቶች ደም የሚፈስላቸው ቀይ ልብስ የሚለበስላቸው ጣኦቶች ናቸው ይህ ዛሬ ቫለንታይን ተብሎ የመጣው ማለት ነው።

የሚገርመው ደሞ ሴቶቹ በዚህ ቀን ለመደፈር ብለው እራቁታቸውን ጫካ መግባታቸው ነው በዚህ ቀን የተደፈረች እና ደሟን ያፈሰሰች ሴትም ሆነ ወንድ በጣኦቱ የተመረጠ እና የተባረከ ነው መባሉ ነው ይበልጥ ነገሩን ሰይጣናዊ የሚያደርገው።

ግሪክ አርኬዲያ ብለው በሚጠሩት አስቀያሚ ትርጉም ባለው ተራራቸው ላይ በዚህ ቀን ላይ ነው ያላገቡ ወንድ እና ሴቶቻቸውን ጣኦቱ ስር ወሲብ በመፈጸም ገላቸውን አርክሰው ለሰይጣን የሚገብሩት።

ይህ የሰይጣን ቀን ነው ክርስትና ይሄን ትከለክላለች ታወግዛለች። (ሁሉም ቀን የእግዚአብሔር ነው ግብሩ ነው የሰይጣን የሚያደርገው)

ኢየሱስ ክርስቶስ ከመውለዱ ከዘመናት በፊት አረማውያን ሮማውያኖች Feb 14 ማታ እና ለ Feb 15 ንጋት አጥቢያ የተኩላ አዱኚ ለሚሉት ሉፐርካልያ (luperkalya ) ጣኦት የሚዘጋች ክብረ በአል ነው፡፡

ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ክርስትና ተቀብሎ እውነተኛ የጽድቅ ሃይማኖት መሆኑን በማውጁ ማንኛውም የጣኦት አምልኮ እንዲቀር ቢያስጠነቅቅም የተውሰኑ የሮማውያን ሰዎች ግን በአሉን ማክበር አልተውም።

እንዴት ይህ አረማዊ ባህል ቫለንታይን የሚል ሰያሜ ተሰጠው? ቫለንታይን የሚል ስም በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ስያሜ ነው፡፡ ቫለንታይን የጥንታዊ ታዋቂው ሉፐርኩስ ጣኦት ነው።

ሉፐርኩስ በግሪካዎያን ፓን (pan) ተብሎ ሚጠራው ከወገቡ በታች በግ አናቱ ላይ ቀንድ ያለው ጣኦት ነው። በጥንታውያን አይሁድ ደግሞ ይህ ፓን ባል (baal) በሚል ስያሜ ይታወቃል።

ጥንታውያን ሮማውያን ከባቢሎናውያን የቀዱት አረማዊ የልብ (heart) ምልክት ይጠቁማሉ፡፡ በባቢሎናውያን ባል (bal) ልብ የሚል ፍች ነው ያለው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ይህ አረማዊ የልብ ምልክት ለቫለንታይን ቀን (የፍቅረኛሞች ቀን) የምንለው መግለጫነት እንጠቀምበታለን። ባል የባቢሎናውያን ጣኦት ነበር።

በዚህ የኃጢአት ቀን በትንቹ ይህ ይሆናል

1. በዚህ ቀን February 14 በብዙ የሚቆጠሩ እህቶቻችንን ክብረ ንጽህናቸውን (ድንግልናቸውን) ያጣሉ❗

2. በርካታ ወጣቶች በስካር ምክንያት በሚያሽከረክሩት መኪና ህይወታቸውን እና አካላቸውን ያጣሉ❗

3. በአለማችን ላይ በከፍተኛ ሁኔታ የአልኮል መጠጥ ሽያጭ የሚከናወንበት ቀን ነው በአጠቃላይ የዝሙት እና ስካር መንፈስ የሚነግስበት በከፍተኛ ሁኔታ ሰይጣን በደም የሚረካበት ቀን ነው።

Valentine day ማለት ሰይጣን በጥልቅ እና ረቂቅ ሃሳብ ብዙዎችን የሚያጠምድበት ቀን ነው አስተውሉ ሰይጣን ከ7ሺህ አመት በላይ የክፋት ልምድ አለው።

እንግዲህ ምርጫው የአንተ/ቺ ነው :- የእግዚአብሔር ወይም የሰይጣን ልጅ መሆን???

" ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ። "
(ትንቢተ ሆሴዕ 4 : 6)

እግዚአብሔር አምላክ ማስተዋሉን ያድለን።
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
    @yemezmur_gexem
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈


​​በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ትንቢተ ዮናስ ምዕራፍ አራት [፬]

ይህም ዮናስን ከቶ ደስ አላሰኘውም፥ እርሱም ተቈጣ።

ወደ እግዚአብሔርም ጸለየና። አቤቱ፥ እለምንሃለሁ፤ በአገሬ ሳለሁ የተናገርሁት ይህ አልነበረምን? አንተ ቸርና ይቅር ባይ፥ ታጋሽም፥ ምሕረትህም የበዛ፥ ከክፉው ነገርም የተነሣ የምትጸጸት አምላክ እንደ ሆንህ አውቄ ነበርና ስለዚህ ወደ ተርሴስ ለመኰብለል ፈጥኜ ነበር።

አሁንም፥ አቤቱ፥ ከሕይወት ሞት ይሻለኛልና እባክህ፥ ነፍሴን ከእኔ ውሰድ አለው።
እግዚአብሔርም። በውኑ ትቈጣ ዘንድ ይገባሃልን? አለ።

ዮናስም ከከተማይቱ ወጣ፥ ከከተማይቱም በስተ ምሥራቅ በኩል ተቀመጠ፤ ከተማይቱንም የሚያገኛትን እስኪያይ ድረስ በዚያ ለራሱ ዳስ ሠርቶ ከጥላው በታች ተቀመጠ።

እግዚአብሔር አምላክም ቅል አዘጋጀ፥ ከጭንቀቱም ታድነው ዘንድ በራሱ ላይ ጥላ እንድትሆን በዮናስ ላይ ከፍ ከፍ አደረጋት፤ ዮናስም ስለ ቅሊቱ እጅግ ደስ አለው።

በነጋው ግን ወገግ ባለ ጊዜ እግዚአብሔር ትልን አዘጋጀ፥ እርስዋም ቅሊቱን እስክትደርቅ ድረስ መታቻት።

ፀሐይም በወጣች ጊዜ እግዚአብሔር ትኩስ የምሥራቅ ነፋስ አዘጋጀ ዮናስ እስኪዝል ድረስም ፀሐይ ራሱን መታው፤ ለራሱም ሞትን ፈለገና። ከሕይወት ሞት ይሻለኛል አለ።

እግዚአብሔርም ዮናስን። በውኑ ስለዚች ቅል ትቈጣ ዘንድ ይገባሃልን? አለው። እርሱም። እስከ ሞት ድረስ እቈጣ ዘንድ ይገባኛል አለ።

እግዚአብሔርም። አንተ ትበቅል ዘንድ ላልደከምህባት ላላሳደግሃትም፥ በአንድ ሌሊት ለበቀለች፥ በአንድ ሌሊትም ለደረቀችው ቅል አዝነሃል።

እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ ከመቶ ሀያ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ አላዝንምን? አለው።

    ትንቢተ ዮናስ ተፈጸመ

     ወስብሐት ለአምላክነ

   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
    @yemezmur_gexem
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈


​​በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

       ትንቢተ ዮናስ
          ምዕራፍ ሁለት [፪]


እግዚአብሔርም ዮናስን የሚውጥ ታላቅ ዓሣ አሰናዳ፤ ዮናስም ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በዓሣው ሆድ ውስጥ ነበረ።

ዮናስም በዓሣው ሆድ ውስጥ ሆኖ ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፥ እንዲህም አለ።

በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፥ እርሱም ሰማኝ፤ በሲኦልም ሆድ ውስጥ ሆኜ ጮኽሁ፥ ቃሌንም አዳመጥህ።
ወደ ጥልቁ ወደ ባሕሩ ውስጥ ጣልኸኝ፥ ፈሳሾችም በዙሪያዬ ነበሩ፤ ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ በላዬ አለፉ።

እኔም። ከዓይንህ ፊት ተጣልሁ፤ ነገር ግን ወደ ቅዱስ መቅደስህ ደግሞ እመለከታለሁ አልሁ።
ውኆችም እስከ ነፍሴ ድረስ ከበቡኝ፤ ጥልቁ ባሕር በዙሪያዬ ነበረ፤ የባሕሩ ሣር በራሴ ተጠምጥሞ ነበር።

ወደ ተራሮች መሠረት ወረድሁ፤ በምድርና በመወርወሪያዎችዋ ለዘላለም ተዘጋሁ፤ አንተ ግን፥ አቤቱ አምላኬ፥ ሕይወቴን ከጕድጓዱ አወጣህ።

ነፍሴ በዛለችብኝ ጊዜ እግዚአብሔርን አሰብሁት፤ ጸሎቴም ወደ አንተ ወደ ቅዱስ መቅደስህ ገባች።
ከንቱነትንና ሐሰትን የሚጠብቁ ምሕረታቸውን ትተዋል።


እኔ ግን በምስጋና ቃል እሠዋልሃለሁ፤ የተሳልሁትንም እከፍላለሁ። ደኅንነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

እግዚአብሔርም ዓሣውን አዘዘው፥ እርሱም ዮናስን በየብስ ላይ ተፋው።

       ምዕራፍ ሦስት [፫]

የእግዚአብሔርም ቃል ሁለተኛ ወደ ዮናስ እንዲህ ሲል መጣ።

ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ የምነግርህንም ስብከት ስበክላት አለው።
ዮናስም ተነሥቶ እንደ እግዚአብሔር ቃል ወደ ነነዌ ሄደ፤ ነነዌም የሦስት ቀን መንገድ ያህል እጅግ ታላቅ ከተማ ነበረች።

ዮናስም የአንድ ቀን መንገድ ያህል ወደ ከተማይቱ ውስጥ ሊገባ ጀመረ፤ ጮኾም። በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች አለ።

የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ፤ ለጾም አዋጅ ነገሩ፥ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ።
ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ፤ እርሱም ከዙፋኑ ተነሥቶ መጐናጸፊያውን አወለቀ ማቅም ለበሰ፥ በአመድም ላይ ተቀመጠ።

አዋጅም አስነገረ፥ በነነዌም ውስጥ የንጉሡንና የመኳንንቱን ትእዛዝ አሳወጀ፥ እንዲህም አለ። ሰዎችና እንስሶች ላሞችና በጎች አንዳችን አይቅመሱ፤ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ፤

ሰዎችና እንስሶችም በማቅ ይከደኑ፥ ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩኹ፤ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።
እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይጸጸት እንደ ሆነ፥ ከጽኑ ቍጣውም ይመለስ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?

እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደተመለሱ ሥራቸውን አየ፤ እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም።

     ምዕራፍ አራት ይቆየን....

   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
    @yemezmur_gexem
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

Показано 20 последних публикаций.