ኑ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


#ወደ_ኤፌሶን_ሰዎች_ምዕ 4፥5

#አንድ ጌታ #አንድ ሃይማኖት #አንዲት ጥምቀት
ከዅሉ በላይ የሚኾን በዅሉም የሚሠራ በዅሉም የሚኖር #አንድ አምላክ የዅሉም አባት አለ።
ነገር ግን እንደክርስቶስ ስጦታ መጠን ለያንዳንዳችን ጸጋ ተሰጠን።
#ማንኛውም_አስተያየት_ሀሳብ 👉 @kasechtadese

@yetwahdotemrtmaskemch

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций






✝️እንኳን ደስ አላችሁ በዩቲዩብ የምናውቀው #ማኅቶት_ቲዩብ አሁን ደግሞ በቴሌግራም መጥታል ለመቀላቀል ከስር Join የሚለውን ንኩት።

https://t.me/+2ua4-eAbNTI1MTRk
https://t.me/+2ua4-eAbNTI1MTRk


🙋‍♂አንድጥያቄ

✞በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው ሰውን መግደል የጀመረው በማን ነበር ⁉️✟

         


"አቤቱ፥ ምሕረትህን እንዴት አበዛህ!
የሰው ልጆች በክንፎችህ ጥላ ይታመናሉ።ከቤትህ ጠል ይጠጣሉ፥ ከተድላም ፈሳሽ ታጠጣቸዋለህ።የሕይወት ምንጭ ከአንተ ዘንድ ነውና፤
በብርሃንህ ብርሃንን እናያለን።''

(መዝሙረ ቅዱስ ዳዊት ፴፮፥፯-፱)


"ለዐቢይ ጾሙ የሚኾኑ በ MP3 የአዘጋጀሁትን የንስሓ የመዝሙራት ስብስብ አጣነው" እያላችሁ በተደጋጋሚ ለጠየቃችሁ እኅት ወንድሞች ኹሉ!
(መዝሙሩን በድጋሚ "share" አድርጌላችኋለሁ። መዝሙራቱ ፍጹም የንስሓ ሲኾኑ ከምድራዊው ዓለም አውጥተው በመንፈስ ቀራኒዮ ወስደው የመድኀኔ ዓለም ክርስቶስን መከራ መስቀል የሚያሳዩን የሚያሳስቡን ስለኾኑ በተለይም በዚኽ ዐቢይ ወቅት በሚገባ ተጠቀሙባቸው።)


"እመቤቴ ኪዳነ ምሕረት ሆይ! በአካል ሦስት ሲሆን በመለኮታዊ ባሕርይ በአንድነቱ ጸንቶ የሚኖር የብርሃን መገኛ እርሱ እግዚአብሔር ለቃል ኪዳንሽ የተሰጠውን ልዩ ክብር አይ ዘንድ የቸርነቱ ፀዳለ ብርሃን ዐይነ ልቡናየን ያብራልኝ፤ የቃል ኪዳኗ እመቤት ሆይ! ከእግዚአብሔር በታች በሰማይም በምድርም አንቺ የሁሉ እመቤት ነሽ እኮን።"

"እመቤቴ ኪዳነ ምሕረት ሆይ በብርሃናዊው ኮከብ ለተመሰለው ስም አጠራርሽ ሰላምታ ይገባል፤ በጨለማለሚኖሩ ሕዝቦች ብርሃኑን አብርቶላቸዋልና፡፡ የቃል ኪዳኗ እመቤት ሆይ! የአምላክ ቃል ኪዳኑ መዛግብት በዕለተ ዐርብ የተገኘውን የደኅንነታችንን ተስፋ ያስገኘሽ እውነተኛ መዝገብ ነሽ እኮን፡፡ አባታችን ቀዳማዊ አዳም በጭንቅና በኀዘን ከገነት ወጥቶ በተሰደደ ጊዜ ከልቡናው ኀዘን ተረጋግቶብሻል፡፡" (መልክዐ ኪዳነ ምሕረት)

የብርሃን እናት ድንግል ወላዲተ አምላክ ከቃል ኪዳኗ ታሳትፈን! ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን እና የዐሥራት ሀገሯን ቅድስት ኢትዮጵያን ትጠብቅልን! ኦርቶዶክሳውያን ሁላችሁ እንኳን አደረሳችሁ! አደረሰን!!!




"" የሚቀብራቸው አጡ! "" (መዝ. ፸፰:፫)

"የሰማዕታት መታሰቢያ"

(የካቲት 12 - 2017)

https://t.me/zikirekdusn


✝እንኳን አደረሳችሁ !

"ስንክሳር - የካቲት ፲፮/16"

☞በዓለ ኪዳና ለድንግል

(የካቲት 15 - 2017)

https://t.me/zikirekdusn




የተጠሙትንም ቃሉን ከፍ አድርጎ ወደ እኔ ኑ ብሎ በምህረት ጠራቸው ።
ክንዶቿ መርጧቸዋልና ታቀፉት።ከንፈሯቿ ሳሙት ጀርባዋ አዘለችው ።ጡቶቿ አጥብተው አሳደጉት ።ጽዮን ማለት መጠጊያ ማለት ነው።ጽዮንም የእግዚአብሔር ቤት ናት ።የእግዚአብሔር ቤትም ማርያም ናት ።የጽዮን በሮች የእመቤታችን ክቡራን ሕዋሳቶቿ ናቸው።የጽዮን በሮች ከሌሎች ቤቶች በር ይልቅ በእግዚአብሔር የተወደዱ እንደ ሆነ ከሰው ልጆች ህዋሳትም ሁሉ የድንግል ማርያም ሕዋሳት ይበልጣል።

አሐቲ ድንግል ገፅ 526-527

እናቴ እመቤቴ ወላዲተ አምላክ ቅዱሰ ቅዱሳን ንጽህተ ንጹሐን
ድንግል ማርያም እናቴ ሆይ ምልጃሽ በረከት ረድኤትሽ አይለየን ከልጅሽ ከወዳጅሽ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ አስታርቂን አሜን፫ አ ሐ ቲ ድ ን ግ ል አንዲት ድንግል ✝


#እሴብሀ ጸጋኪ ኦ እግዝእትየ ማርያም አንቀጸ ብርሐን ወሙዳየ ቅዱስ ቁርባን - የብርሐን በር የቅዱስ ቁርባን ሙዳይ የሆንሽ እመቤቴ ማርያም ሆይ የተሰጠሽ ጸጋ ሰማያዊ አመሰግናለሁ

ትመስሊ መሶበ
ወትወልዲ ኮኮበ
ወትወልዲ ርኁበ
ሐረገ ወይን ሐረገወይን ሐረገወይን አንቲ ማርያም -

መሶብን ትመስያለሽ ፤
ኮኮብን ትወልጃለሽ ፤
የተራቡትን ታጠግቢ አለሽ ፤
እመቤቲቱ ማርያም ሆይ የወይን ሐረግ ነሽ

#ሐዳስ ሐመር ዘመና ጎሞር ሲሳየ ኩሉ ፍጡር ስአሊ ለነ ማርያም ኀበ ወልዲኪ ኄር ከመ ያርፍቀነ ምስሌሁ በሐዳስ ቀመር - አዲስ መከርብ ፤የዓለሙ ሁሉ ምግብ የመና ጎሞር ማርያም ሆይ ከመሐሪው ልጅሽ ለምኝልን በእርሱ ጋር በአዲስ ድንኳን ያኖረን ዘንድ 🙏
እሐቲ ድንግል መፅሐፍ ገፅ 328

ሰማየ ሰማያት ያመሰግኑሻል ለፈጠራቸው እናት ሁነሻልና፤ መላእክት ሊቃነ መላእክት ያመሰግኑሻል የፈጠራቸውን ወልደሽዋልና፤ ሰውና እንስሳት ስጋን የለበሰ ሁሉ ያገኑሻል ለእንስሳትና ለሰው ስጋዊ ምግብን በዝናብ አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ የሚመግባቸውን፤ ለክርስቲያኖች ስጋውና ደሙን የሚመግባቸውን ሀሊበ ድንግልናሽን እያጠባሽ አሳድገሽዋልና፤ ምድር ተራሮቿና ኮረብቶቿ በርሷም የተመሰረቱ ሁሉ ይገዙልሻል፥ ለመጠናቸው ስፋት እንዳይፈርሱ ፅናት የሰጣቸውን በክንዶችሽ ታቅፈሽዋልና። ባህርና ቀላያት ወንዞችና ፈሳሾች ልዕልናሽን ይናገራሉ ለቀላይነታቸው ጥልቀት ለባህርነታቸው ስፋት የሰጣቸውን በጠባብ ማህፀንሽ ችለሽዋልና፥ እሳትና ሙቀት መብረቆችም ክብርሽን ይመሰክራሉ እሳታውያን ከግርማው የተነሳ የሚደነግጡለትን መብረቆች ከቃሉ የተነሳ የሚንቀጠቀጡለትን በእጆችሽ ዳሰሽዋልና። ኪሩቤል ሱራፌል ይሰግዱልሻል በእነርሱ ላይ በመንበረ ክብሩ የሚኖረውን በጀርባሽ አዝለሽዋልና።
“ገነይኩ ለኪ ኦ እሙ ለፀሃየ ፅድቅ እስመ ኩሉ ፍጥረት ገነየ ለክብርኪ”። የፀሃየ ፅድቅ እናቱ ሆይ እኔም እገዛልሻለሁ ትውልድ ሁሉ ላንቺ ተገዝቷልና።
“አሐቲ ድንግል”
አሐቲ ድንግል
እመቤቴ ሆይ እንደምን ያለሽ ሰፊ እርሻ ነሽ፤ የዓለሙ ሁሉ ዘለዓለማዊ አዝመራ ከአንች ተገኝቷልና።

እንደምን ያለሽ ሰፊ ሀገር ነሽ ፤ ንጉሥ ከነሠራዊቱ ዓለሙን በእጁ እንደያዘ በአንች ከትሟልና።
እንደምን ያለሽ ሰፊ ሰማይ ነሽ፤ ብርሃናትን የፈጠረ የጽድቅ ፀሐይ በማሕፀንሽ አድሯልና።
እንደምን ያለሽ መሶብ ነሽ ፤ ለዓለሙ ሁሉ የሚበቃውን የሕይወት እንጀራ ይዘሻልና።
እንደምን ያለሽ ጥልቅ የሕይወት ጉድጓድ ነሽ ፤ ቀላያትን በእፍኙ የሚሰፍረውን የተጠማ ሁሉ ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣኝ የሚለውን የሕይወት ውኃ አፍልቀሽልናልና።
ንጽሕት የድኅነታችን ሀገር ሆይ በአንች ተጠግቶ ካለመኖር የሚከፋ ሲኦል የለም!

በአንች መኖር ምንኛ መልካም ነው! በአንች ከመኖር በላይ ገነት የለም።

ከአንች ዙፋንነት የሚጠጉ በዚያ ካለው እውነተኛ ንጉሥ ፍትሕ ያገኛሉ ፤ እርሱን ራሱን ይመገቡታል።
አንችን አለማድነቅ ሳይሆን ማድነቅም አይቻልም።

የሕይወት ቃል እናት ስለምትሆኝ ስለ አንች ከማይናገር በቀር ዲዳ ከንፈር የትኛው ነው? የብርሃን ከተማ ወደ አንች እግሮቹ ከማይፈጥኑለት ሰው በቀርስ ሽባ ማን ነው? የሕይወት እንጀራ የሚገኝብሽ ማዕድ ሆይ ከአንች ከሚርቅስ በቀር ረኀብተኛው ማን ነው? የምሥራቃት ሁሉ ምሥራቅ ሆይ የሕይወት ብርሃን ከአንች ሲወጣ ያይ ዘንድ ከሚዘገይ በቀርስ የጨለማ አበጋዝ ማን ነው?
ወዮ የሰውን ዘር ሁሉ ያስመካሽን ንጽሕት የስንዴ ቅንጣት ሆይ በአንች አዝመራ እንመላለሳለን።
አይሁድ ቢነቅፉንም ሰንበታችን አንች ነሽና የሕይወት እሸትን ከድኅነት እርሻችን ከአንች እየበላን ጌታን እንተክላለን ! አንችን ለፈጠረ በአንችም ላከበረን ምስጋና ይሁን !።
አሐቲ ድንግል ገጽ 216 ፦ 217።

#በሮቿ የተወደዱ ጽዮን🌹

እግዚአብሔር መልካም ነው። ውበቱም ከሰው ልጆች ይልቅ ያምራል የእጆቹን ስራ ሁሉ መልካም አድርጎ ሰርቷቸዋን ።
ኩሉ ሠናይ ዘገብረ እግዚአብሔር በጊዜሁ -ነገርን በግዜው ውብ አድርጎ ሰራው እንዲል።ከዚያውም ውብ ዘንድ ማደሪያው ቤተ መቅደስን ከምድር በተገኙ በወርቅ በዕንቁ ለብጦ ከእርሱ በተገኘ ፀጋ ሰማያዊ አስጊጦ ሠርቷታል።እንዲህ አድርጎ ሠርቶ በልብ መታሰቡ ደስ የሚያሰኝ በልዕልናው ድንቅ ሁኖ የሚኖር እርሱ አድሮባታል።ድንቅ አድርጎ ለሰራት በፀጋ ላስጌጣትም የክብሩ ማረፊያ ሰላደረጋትም መቅደሱ ድንቅ ተብላለች። ወደ ቤተ እግዚአብሔር መሔድም የተወደደ ጎዳና ሆነ ።አደባባዮቿም ያማሩ የተወደዱ የሚናፈቁ ሆኑ ።ከያቆብ ድንኳኖች ይልቅም ጽዮን በሮቿ በእግዚአብሔር ዘንድ እጅጉን የተወደዱ ናቸው ።የያዕቆብ ውበቱም ሆነች ።የያዕቆብ አምላክ አድሯልና።ፍለጋውንም በቤተ መቅደስ አኑሯል በዚያም ይገለጣልና። ሰለዚህም ነብያት እንዲህ እያሉ ቤተ መቅደስን እየናፈቁ ዘመሩላት ተነበዩላት።የአሞጽ ልጅ ኢሳያስ ሰለ ይሁዳና ሰለ ኢየሩሳሌም ያየው ቃል በዘመኑም ፍፃሜ በእግዚአብሔር ቤት ተራራ በተራሮች ራስ ላይ ጸንቶ ይቆማል÷
ከኮረብቶችም በላይ ከፍ ከፍ ይላል አሕዛብ ሁሉ ወደ እርሱ ይሰበሰባሉ ።ሕግ ከጽዮን የእግዚአብሔር ቃለ ከኢየሩሳሌም ይወጣልና ብዙዎች አሕዛብ ሄደው ኑ ወደ እግዚአብሔር ተራራ ÷ወደ ያዕቆብ አምላክ ቤት እንውጣ እርሱም ምንገዱን ያሰረተምረናል ።በጎዳናውም እንሄዳለን ይላሁ በአህዛብ መካከል ይፈርዳል ÷በብዙ አህዛብ ላይ ይበይናል ሰይፋቸውን ማረሻ ጦራቸውንም ማጭድ ለማድረግ ይቀጠቅጣሉ÷አህዛብ በአህዛብ ላይ ሰይፍ አያነሳም ሰልፍም ከእንግዲህ ወዲህ አይማሩም ።ኢሳ ፪:፪

እግዚአብሔር ከቤት በሮች ሁሉ የቤቱን የጽዮንን በሮች እንደ ሚወድ ከጸሎትም ሁሉ በጽዮን የሚቀርብን ጸሎት የይወዳል።ለከ ይደሉ ስብሐት በጽዮን ወለከ ይትፈኖ ጸሎት በኢየሩሳሌም ።እንዲል።ከሁሉ ነገር ይልቅ በእግዚአብሔር ቤት መኖርን እንዲሰጣቸው አጥብቀው ይለምኑት ነበር። ሰለዚህ ቅዱሳን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እንኳን መኖር መጣልም ቢሆን ክብር ነውና ምህረትህና ቸርነትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኝ እስከ ፍፃሜ ድረስ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ እያሉ ለምነውታል ። ብርሐንህና ፅድቅህን ልከህ እነሱ መርተው ወደ መቅደስህ ያድርሱኝ ብለው የተማፀኑበትም ጊዜ አለ።በቤትህ የሚኖሩ ኑዑዳን ክቡራን ናቸው ለዘላለሙ ያመሰግኑሀል እያሉ የተመኙበት ጊዜ አለ እኔ ግን በምህረትህ ብዛት ወደ ቤትህ እገባለሁ ብለው ያስፈቀዱበት ጊዜ አለ ።ትዕቢተኞት በእግዚአብሔር ቤት እድል ፈንታ ጽዋዐ ተርታ የላቸውምና ።የቤትህ ቅናት አቃጠለኝ ሲሉ ለቤቱ የቀኑበት ጊዜም አለ።

#እንግዲህ ምን እንላለን ?
እግዚአብሔር ነገርን ሁሉ ውብ አድርጎ ሰራው።ይልቁንም ሰውን ድንቅ አድርጎ ፈጠረው። ከሰውም ማደሪያውን ድንግል ማርያምን በንጽሐ ጠባይዕ ጠብቆ በቅድስና ሸልሞ በልዕልና አክብሮ አዘጋጃት ።ጸጋ ሰማያዊን ሀብት ሰማያዊን የተመላች አደረጋት ።ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ የጽዮን በሮች እንደ ወደደ ከያዕቆብ ልጆች ሁሉ ይልቅ የድንግል ማርያምን ህዋሳት ወደደ።ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ በጽዮን በቤቱ ክብሩን እንዳሰፈረ ከያዕቆብ ልጆች ይልቅ የድንግልን ሕዋሳት ለተዋህዶ መረጠ ።በጆሮቿ በኩል ታዛዥነቷ ሳበውና በብስራት ገባ።የዕለት ጽንስ ሁኖ ተቀረጸ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀንም ዓለሙ አድርጎት ኖረ ማህተመ ድንግልናዋን ሳይለውጥ የጽድቅ ፏፏቴ ከማህፀኗ ከታተመችው አለት ፈለቀ።


♦⛪️የኢኦተቤክ አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ⁉️ 'https://t.me/addlist/6GhqHrWjTU03M2Vk' rel='nofollow'>

👏 የቸብቸቦ መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🎻 የበገና መዝሙራት  
         📖▓⇨→vido     ⇨ግጥም
👑 የቅዱሳን መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
⛪️ የንግስ መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🤲 የምስጋና  መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🙏 የንስሐ  መዝሙራት
         📖▓⇨→vido   ⇨ግጥም
💍 የሠርግ መዝሙራት
          📖▓⇨→avido   ⇨ግጥም
🌦 ወቅታዊ መዝሙራት
          📖▓⇨→vido    ⇨ግጥም
🇪🇹 ለአገር የተዘመሩ
          📖▓⇨→vido   ⇨ግጥም
          👇👇
https://t.me/+lVXHSARuil5kZDU0

          👇🏽ከእስልምና ወደ ክርስትና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ በYOUTUBE👇🏽

         👇🏽🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏽
   https://t.me/+lVXHSARuil5kZDU0








2016"" ባሪያህን በሰላም አሰናብተው!? ""

(ሉቃ. ፪:፳፱)

(የካቲት 8 - 2016

ዝክረቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር
በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn





Показано 20 последних публикаций.