ኢትዮጵያና ሕገ ኦሪት
አሞጽ ፱፡፯ (9፡7) "የእስራኤል ልጆች ሆይ እናንተ ለአኔ እንደ
ኢትዮጵያ ልጆች አይደላችሁምን? ይላል እግዚአብሔር" ይህም ምን ይገልጽልናል ብሎ
ለሚጠይቅ ነገሩ እንዲህ ነው ዛሬ አሰራኤል ታቦቱ የላትም።
የዚህ ምሥጢር ባለቤት ግን ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ናት።
በአጠቃላይ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከፍጥረት ጀምሮ የብሉይ ኪዳንን እምነትና ሥርዓት ጠብቃ አስጠብቃ እግዚአብሔርን በማምለክ የጸናች አገር ናት፡- ቅድመ ክርስትና ይህ የብሉይ ኪዳን መሥዋዕት እየተሠዋባት የነበረች አገር እንደነበረች በሁሉም የአገሪቷ ከፍል ያለ የሃይማኖት መገለጫ የታሪከ ማስረጃ የባህልም ምስከርነት አለ።
ለምሳሌ፡- በመላው ኢትዮጵያ የብሉይ ኪዳን መሥዋዕት ይቀርብባቸው የነበሩ የንዋየ ቅድሳት ምስክሮች አሉ። ኢትዮጵያ በዚያ ዘመን ለአምላኳ መሥዋዕተ ቁርባን ታቀርብ ነበር። ነቢዩ ሶፎንያስ እንዲህ ሲል ትንቢት ተናገረ “ከኢትዮጵያ ወንዞች ማዶ የሚማልዱልኝ የተበተኑት ሴቶች ልጆቼ ቁርባኔን ያመጡልኛል” በግእዙ እንዲህ ይለዋል። “እምነ ማዕዶተ ፈለገ ኢትዮጵያ ያመጽኡ ሊተ መሥዋዕተ” የዚህም ትርጓሜ “ከኢትዮጵያ ወንዝ ጀምሮ መሥዋዕቱን ያመጡልኛል።“ ሶፎ ፫፡፲ (3:10)
እንዲህ ባለ ሁኔታ ኢትዮጵያ ለአንድ አምላከ እየሰገደች እርሱን ብቻ እያመለከች ሀገረ እግዚአብሔር ሆና አምላክ ከሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም ተወልዶ፣ ተጠምቆ፣ በመሰቀል ተስቅሎ፣ ደሙን እፍስሶ፣ ሥጋውን ቆርሶ፣ ዓለምን ሁሉ ያድናል እያለች የተቆጠረው ሱባዔ የተነገረው ትንቢት ይፈጸማል አምስት ሺህ አምስት መቶ የኃጢአት የጨለማ ዘመን ያበቃል እያለች የነቢያትን ትንቢት በመጋራት በእምነት ፀንታ ስትኖር ዘመኑ ሲፈፀም በትንቢቱ መሠረት ጌታችን አኛን ለማዳን ሰው ሆነ ተዋሕዶ ሃይማኖት በዚህ ተጀመረች ኢትዮጵያም የመጀመሪያዋ ከርስቲያን ሀገር ፤ለመሆን በቃች።
#ከላይ ኢትዮጵያና ሕገ ወንጌል (ክርስትናን) አለ
ለተፈጠረው ቅደምተከተል ይቅርታ እንጠይቃለን
አሞጽ ፱፡፯ (9፡7) "የእስራኤል ልጆች ሆይ እናንተ ለአኔ እንደ
ኢትዮጵያ ልጆች አይደላችሁምን? ይላል እግዚአብሔር" ይህም ምን ይገልጽልናል ብሎ
ለሚጠይቅ ነገሩ እንዲህ ነው ዛሬ አሰራኤል ታቦቱ የላትም።
የዚህ ምሥጢር ባለቤት ግን ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ናት።
በአጠቃላይ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከፍጥረት ጀምሮ የብሉይ ኪዳንን እምነትና ሥርዓት ጠብቃ አስጠብቃ እግዚአብሔርን በማምለክ የጸናች አገር ናት፡- ቅድመ ክርስትና ይህ የብሉይ ኪዳን መሥዋዕት እየተሠዋባት የነበረች አገር እንደነበረች በሁሉም የአገሪቷ ከፍል ያለ የሃይማኖት መገለጫ የታሪከ ማስረጃ የባህልም ምስከርነት አለ።
ለምሳሌ፡- በመላው ኢትዮጵያ የብሉይ ኪዳን መሥዋዕት ይቀርብባቸው የነበሩ የንዋየ ቅድሳት ምስክሮች አሉ። ኢትዮጵያ በዚያ ዘመን ለአምላኳ መሥዋዕተ ቁርባን ታቀርብ ነበር። ነቢዩ ሶፎንያስ እንዲህ ሲል ትንቢት ተናገረ “ከኢትዮጵያ ወንዞች ማዶ የሚማልዱልኝ የተበተኑት ሴቶች ልጆቼ ቁርባኔን ያመጡልኛል” በግእዙ እንዲህ ይለዋል። “እምነ ማዕዶተ ፈለገ ኢትዮጵያ ያመጽኡ ሊተ መሥዋዕተ” የዚህም ትርጓሜ “ከኢትዮጵያ ወንዝ ጀምሮ መሥዋዕቱን ያመጡልኛል።“ ሶፎ ፫፡፲ (3:10)
እንዲህ ባለ ሁኔታ ኢትዮጵያ ለአንድ አምላከ እየሰገደች እርሱን ብቻ እያመለከች ሀገረ እግዚአብሔር ሆና አምላክ ከሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም ተወልዶ፣ ተጠምቆ፣ በመሰቀል ተስቅሎ፣ ደሙን እፍስሶ፣ ሥጋውን ቆርሶ፣ ዓለምን ሁሉ ያድናል እያለች የተቆጠረው ሱባዔ የተነገረው ትንቢት ይፈጸማል አምስት ሺህ አምስት መቶ የኃጢአት የጨለማ ዘመን ያበቃል እያለች የነቢያትን ትንቢት በመጋራት በእምነት ፀንታ ስትኖር ዘመኑ ሲፈፀም በትንቢቱ መሠረት ጌታችን አኛን ለማዳን ሰው ሆነ ተዋሕዶ ሃይማኖት በዚህ ተጀመረች ኢትዮጵያም የመጀመሪያዋ ከርስቲያን ሀገር ፤ለመሆን በቃች።
#ከላይ ኢትዮጵያና ሕገ ወንጌል (ክርስትናን) አለ
ለተፈጠረው ቅደምተከተል ይቅርታ እንጠይቃለን