ምሥጢረ ሥላሴ
ከአምስቱ አዕማደ ምሥጢር አንደኛው ይህ ምሥጢረ ሥላሴ ሲሆን ይህም የአግዚአብሔር የአምላካችን አንድነትና ሦስትነት የሚገለጽበት ነው።
* አንድነቱ፡- በመለኮት በባሕርይ በህልውና በፈቃድ በአገዛዝ ይህን ዓለም በመፍጠርና በማሳለፍ አንድ ነው።
*ሦስትነት፡- በስም በግብር በአካል በኩነት
#በስም፡-አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይባላሉ ፡፡ ማቴ 28:19
#በግብር፡- አብ ወላዲ ወልድ ተወላዲ መንፈስ ቅዱስ ሠራፂ ነው። ዮሐ. ፩፡፳፭ (1፥25)
#በአካል፡- ለአብ ፍጹም አካል፣ ፍጹም ገጽ፣ ፍጹም መልክ አለው። ለወልድም እንዲሁ ለመንፈስ ቅዱስም አንዲሁ
#በኩነት፡-አብ ልብ ነው። ወልድ ቃል ነው፣ መንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ ነው።
ስለዚህ እግዚአብሔር በስም በአካል በግብር በኩነት ሦስት ነው ብንልም በመስኮት በህልውና በባሕርይ በአገዛዝና በመሳሰሉት አንድ ስለሆነ አንድ አምላክ ተብሎ ይታመናል ይጠራል እንጂ ሦስት አማልክት አይባልም። ከዚህም የተነሣ ሥካሴ ሦስት ሲሆኑ አንድ አንድ ሲሆኑ ሦስት በመሆናቸው ይህ ምሥጢር ተባለ ለሚያምን ብቻ የሚገለጽ ምስጢር።
#ለምሳሌ:-
- አዳም አንድ ነው ሦስት ሊሆን አይችልም።
- ኣብርሃም ይስሐቅ ያዕቆብ ደግሞ ሦስት ናቸው አንድ ሊሆኑ አይችሉም። ስለዚሀም ቅድስት ሥካሴ ሰንል “ቅድስት” ልዩ -ሥላሴ" ሦስትነት ሲሆን ልዩ የሆነች ሦስትነት ብለን እናምናለን።
* በመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃዎች
#አንድነት ፡ በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ፈጠረ የሚለው ቃል አንድነቱን ያሳያል ዘፍ. ፩፡፩(1:1)
#ሦስትነት፡- “የጌታችን የኢየሱስ (ወልድ) ከርስቶሰ ጸጋ የአግዚአብሔርም (አብ) ፍቅር የመንፈስ ቅዱሰም ኅብረት ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን።” 2ቆሮ 13:14 ይህ ቃል ሐዋርያት ሕዝቡን የሚባርኩበት ቃል ነው ይህም ሰመ ሥካሴ ነው።
#አንድነትና ሦስትነት፡- እግዚአብሔርም አለ "ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር።” ዘፍ1፥26 “እግዚአብሔር አለ” ሲል አንድነቱን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር የሚሉት ቃላት ሦስትነቱን በግልጽ ያመለክታሉ።
#ሌሎች ምሳሌዎችን እንመልክት
1. ፀሐይ ፡-
ሀ/ ከበብ (ቅርፅ) አላት
ለ/ ብርሃን አላት
ሐ/ ሙቀት አላት
አንድ የሆነችው ፀሐይ ክበብ ብርሃን ሙቀት ስላላት ሦሰት ፀሐዮች አትባልም እንድ ፀሐይ እንጂ። በክበቡ አብ ይመስላል በብርሃኑ ወልድ ይመሰላል በሙቀቱ ደግሞ መንፈሰ ቅዱስ ይመሰላል። ኣብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ቢባሉም እርሱ ግን አንድ ፈጣሪ አምላከ ነው።
“ኣብ ፀሐይ ወልድ ፀሐይ ወመንፈስ ቅዱስ ፀሐይ ፩ዱ ውእቱ ፀሐየ ጽድቅ ዘላዕለ ኩሉ
“አብ ፀሐይ ነው። ወልድ ፀሐይ ነው። መንፈስ ቅዱስም ፀሐይ ነው፡ ከሁሉ በላይ የሚሆን አንድ የእውነት ፀሐይ ነው“ ቅዳሴ ማርያም
2. ነፍሰ፡- ሦስትነት አላት
ሀ/ ለባዊነት
ለ/ ነባቢነት
ሐ/ ሕያዊነት
ይህ ማለት ነፍስ ለባዊት ናት (ልብ) ነባቢት ናት (ቃል) ሕያዊት ናት (እስትንፋስ) አሁን አንደምታዩት ልብ የምታደርግ የምትናገር ሕያው የሆነች ብለን ብንመለከትም ሦስት ነፍሳት ሳይሆን አንድ ነፍስ ብቻ ነች። በለባዊነት አብ ይመስላል። በነባቢት ወልድ ይመስላል በሕያዊነት ደግሞ መንፈስ ቅዱስ ይመስላል።አብ ልብ ነው፡ ወልድ ቃል ነው፡ መንፈስ ቅዱስ አስትንፋስ ነው። ልክ ነፍስ ሦስትነት ሲኖራት አንድ ነፍስ አንደምንል ሥላሴም ሦስት ሲሆን አንድ ነውና አንድ እምላክ ብለን እናምናለን።
#በቀጣይ ምስጢረ ሥጋዌን አጠር አጠር አድርገን እናያለን
ለሌሎች በማጋራት{share} ክርስትያናዊ ግደታዎን ይወጡ!
ከአምስቱ አዕማደ ምሥጢር አንደኛው ይህ ምሥጢረ ሥላሴ ሲሆን ይህም የአግዚአብሔር የአምላካችን አንድነትና ሦስትነት የሚገለጽበት ነው።
* አንድነቱ፡- በመለኮት በባሕርይ በህልውና በፈቃድ በአገዛዝ ይህን ዓለም በመፍጠርና በማሳለፍ አንድ ነው።
*ሦስትነት፡- በስም በግብር በአካል በኩነት
#በስም፡-አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይባላሉ ፡፡ ማቴ 28:19
#በግብር፡- አብ ወላዲ ወልድ ተወላዲ መንፈስ ቅዱስ ሠራፂ ነው። ዮሐ. ፩፡፳፭ (1፥25)
#በአካል፡- ለአብ ፍጹም አካል፣ ፍጹም ገጽ፣ ፍጹም መልክ አለው። ለወልድም እንዲሁ ለመንፈስ ቅዱስም አንዲሁ
#በኩነት፡-አብ ልብ ነው። ወልድ ቃል ነው፣ መንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ ነው።
ስለዚህ እግዚአብሔር በስም በአካል በግብር በኩነት ሦስት ነው ብንልም በመስኮት በህልውና በባሕርይ በአገዛዝና በመሳሰሉት አንድ ስለሆነ አንድ አምላክ ተብሎ ይታመናል ይጠራል እንጂ ሦስት አማልክት አይባልም። ከዚህም የተነሣ ሥካሴ ሦስት ሲሆኑ አንድ አንድ ሲሆኑ ሦስት በመሆናቸው ይህ ምሥጢር ተባለ ለሚያምን ብቻ የሚገለጽ ምስጢር።
#ለምሳሌ:-
- አዳም አንድ ነው ሦስት ሊሆን አይችልም።
- ኣብርሃም ይስሐቅ ያዕቆብ ደግሞ ሦስት ናቸው አንድ ሊሆኑ አይችሉም። ስለዚሀም ቅድስት ሥካሴ ሰንል “ቅድስት” ልዩ -ሥላሴ" ሦስትነት ሲሆን ልዩ የሆነች ሦስትነት ብለን እናምናለን።
* በመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃዎች
#አንድነት ፡ በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ፈጠረ የሚለው ቃል አንድነቱን ያሳያል ዘፍ. ፩፡፩(1:1)
#ሦስትነት፡- “የጌታችን የኢየሱስ (ወልድ) ከርስቶሰ ጸጋ የአግዚአብሔርም (አብ) ፍቅር የመንፈስ ቅዱሰም ኅብረት ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን።” 2ቆሮ 13:14 ይህ ቃል ሐዋርያት ሕዝቡን የሚባርኩበት ቃል ነው ይህም ሰመ ሥካሴ ነው።
#አንድነትና ሦስትነት፡- እግዚአብሔርም አለ "ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር።” ዘፍ1፥26 “እግዚአብሔር አለ” ሲል አንድነቱን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር የሚሉት ቃላት ሦስትነቱን በግልጽ ያመለክታሉ።
#ሌሎች ምሳሌዎችን እንመልክት
1. ፀሐይ ፡-
ሀ/ ከበብ (ቅርፅ) አላት
ለ/ ብርሃን አላት
ሐ/ ሙቀት አላት
አንድ የሆነችው ፀሐይ ክበብ ብርሃን ሙቀት ስላላት ሦሰት ፀሐዮች አትባልም እንድ ፀሐይ እንጂ። በክበቡ አብ ይመስላል በብርሃኑ ወልድ ይመሰላል በሙቀቱ ደግሞ መንፈሰ ቅዱስ ይመሰላል። ኣብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ቢባሉም እርሱ ግን አንድ ፈጣሪ አምላከ ነው።
“ኣብ ፀሐይ ወልድ ፀሐይ ወመንፈስ ቅዱስ ፀሐይ ፩ዱ ውእቱ ፀሐየ ጽድቅ ዘላዕለ ኩሉ
“አብ ፀሐይ ነው። ወልድ ፀሐይ ነው። መንፈስ ቅዱስም ፀሐይ ነው፡ ከሁሉ በላይ የሚሆን አንድ የእውነት ፀሐይ ነው“ ቅዳሴ ማርያም
2. ነፍሰ፡- ሦስትነት አላት
ሀ/ ለባዊነት
ለ/ ነባቢነት
ሐ/ ሕያዊነት
ይህ ማለት ነፍስ ለባዊት ናት (ልብ) ነባቢት ናት (ቃል) ሕያዊት ናት (እስትንፋስ) አሁን አንደምታዩት ልብ የምታደርግ የምትናገር ሕያው የሆነች ብለን ብንመለከትም ሦስት ነፍሳት ሳይሆን አንድ ነፍስ ብቻ ነች። በለባዊነት አብ ይመስላል። በነባቢት ወልድ ይመስላል በሕያዊነት ደግሞ መንፈስ ቅዱስ ይመስላል።አብ ልብ ነው፡ ወልድ ቃል ነው፡ መንፈስ ቅዱስ አስትንፋስ ነው። ልክ ነፍስ ሦስትነት ሲኖራት አንድ ነፍስ አንደምንል ሥላሴም ሦስት ሲሆን አንድ ነውና አንድ እምላክ ብለን እናምናለን።
#በቀጣይ ምስጢረ ሥጋዌን አጠር አጠር አድርገን እናያለን
ለሌሎች በማጋራት{share} ክርስትያናዊ ግደታዎን ይወጡ!