የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች ‹‹የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተመንግስት›› ህዝባዊ ንቅናቄ ተቀላቀሉ
======================================
(መስከረም 19/2014ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች ‹‹የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተመንግስት›› ህዝባዊ ንቅናቄ ፕሮግራም በዛሬዉ እለት አካሂደዋል።
“የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ-መንግስት” በሚል መሪ ሃሳብ የአሸባሪውን ሕወሓት ሀገር የማፍረስ እቅድ ለማጋለጥ እንደ ሃገር ከመስከረም 3 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ንቅናቄዉ እየተካሄደ ይገኛል።
የዚህ ንቅናቄ ዋና ዋና ዓላማዎች በአገራችን ኢትዮጵያ ላይ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እየደረሰ ያለውን ያልተገባ አሉታዊ ጫና ለመመከት፣ የኢትዮጵያውያን እውነታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ፣ የአሸባሪውን ህወሓት አገር የማፍረስ ወረራ ለማጋለጥ እና በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሰራዊት ላይ አሸባሪው ህወሓት የፈጸመውን ግፍ ማሳየት ሲሆን ይህ ፕሮግራም እንደአገር እየተካሄደ ባለዉ የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት ዘመቻ አጋርነታችንን የምንገልጽበት እና በአገራዊ ጉዳይም ያለንን ድጋፍ በፊርማ የምናረጋግጥበት መሆኑ በተሳታፊ ሰራተኞች ተገልጸዋል፡፡
በዛሬው ዕለት የተካሄደውን መርሃ ግብር ጨምሮ በዘመቻው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳይሬክተር ጀኔራሎች ፣ ዳይሬክተሮች እና ሌሎች ከ210 በላይ ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
======================================
(መስከረም 19/2014ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች ‹‹የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተመንግስት›› ህዝባዊ ንቅናቄ ፕሮግራም በዛሬዉ እለት አካሂደዋል።
“የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ-መንግስት” በሚል መሪ ሃሳብ የአሸባሪውን ሕወሓት ሀገር የማፍረስ እቅድ ለማጋለጥ እንደ ሃገር ከመስከረም 3 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ንቅናቄዉ እየተካሄደ ይገኛል።
የዚህ ንቅናቄ ዋና ዋና ዓላማዎች በአገራችን ኢትዮጵያ ላይ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እየደረሰ ያለውን ያልተገባ አሉታዊ ጫና ለመመከት፣ የኢትዮጵያውያን እውነታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ፣ የአሸባሪውን ህወሓት አገር የማፍረስ ወረራ ለማጋለጥ እና በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሰራዊት ላይ አሸባሪው ህወሓት የፈጸመውን ግፍ ማሳየት ሲሆን ይህ ፕሮግራም እንደአገር እየተካሄደ ባለዉ የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት ዘመቻ አጋርነታችንን የምንገልጽበት እና በአገራዊ ጉዳይም ያለንን ድጋፍ በፊርማ የምናረጋግጥበት መሆኑ በተሳታፊ ሰራተኞች ተገልጸዋል፡፡
በዛሬው ዕለት የተካሄደውን መርሃ ግብር ጨምሮ በዘመቻው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳይሬክተር ጀኔራሎች ፣ ዳይሬክተሮች እና ሌሎች ከ210 በላይ ሰራተኞች ተሳትፈዋል።