የኢትዮጵያ ሠራዊት ስምሪት የአል ሻባብ እንቅስቃሴ እንዲጨምር አድርጓል’ - ሶማሊያ
ባለፉት ጊዜያት በሶማሊያ ውስጥ ለሰላም ማስከበር የተደረገው የኢትዮጵያ ሠራዊት ስምሪት የአል ሻባብ እንቅስቃሴ እንዲጨምር አድርጓል ሲል የሶማሊያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ወቀሰ።
የኢትዮጵያ ወታደሮች ከግዛቷ እንዲወጡ ስትጠይቅ የቆየችው ሶማሊያ ከጥቂት ወራት በኋላ የሚያበቃውን የሰላም አስከባሪ ተልዕኮን ተከትሎ በምትኩ በሚሰማራው ኃይል ውስጥ የየትኛው አገር ወታደሮች እንደሚሳተፉ የምትመርጠው ራሷ መሆኗን ገልጻለች።
የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ በአገሪቱ ወታደሮቻቸውን ካሰማሩ አምስት አገራት በተለየ የኢትዮጵያ ሠራዊት ላይ በማተኮር ተልዕኮው የአል ሻባብ እንቅስቃሴ ከፍ እንዲል ከማድረግ ባሻገር ያስገኘው ለውጥ ውስን ነው ብሏል።
በዚህም የተለያዩ ምክንያቶችን ያስቀመጠው የሶማሊያ መንግሥት በቀጣይ በተተኪነት በአገሩ የሚሠማሩትን ሰላም አስከባሪዎች ውስጥ የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲካተቱ እንደማይፈለግ ባወጣው መግለጫ ላይ ፍንጭ ሰጥቷል።
የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቀጣይ በሶማሊያ ከሚሰማራው የአፍሪካ ኅብረት አረጋጊ ተልዕኮ አንጻር የሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የኢትዮጵያ ሚና በሚል ረቡዕ አመሻሽ ባወጣው መግለጫ በሁለቱ አገራት መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ጠቅሷል።
በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ስር በሶማሊያ የተሰማሩት የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲወጡ ባለፉት ወራት የሶማሊያ ባለሥልጣናት በተደጋጋሚ ሲጠይቁ መቆየታቸው ይታወሳል።
በመጪው ጥር የሚጠናቀቀውን የሰላም አስከባሪውን ውክልና ተከትሎ በሚተካው አዲስ ተልዕኮ ውስጥ አገራት የሚኖራቸውን ተሳትፎ በተመለከተ የሶማሊያ መንግሥት የበላይ በመሆን በአገሪቱ ሉዓላዊነት ላይ በማተኮር የተልዕኮውን ሚና እንደሚመራ አሳውቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ በቅርቡ የተናጠል እርምጃ መውሰዷን በመጥቀስ ለአብነትም ነጻ አገርነቷን ካወጀችው ሶማሊላንድ ጋር የደረሰችው ስምምነት የሶማሊያን ሉዓላዊነት የሚቃረን ነው በማለት ዋነኛው ትኩረቱ ኢትዮጵያ ላይ መሆኑን አመልክቷል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ መግለጫ ኢትዮጵያ “ከሰሜናዊ ግዛት ጋር የደረሰችው ሕገወጥ ስምምነት፣ ሉዓላዊነታችንን የሚጥስ እና ለሰላም ማስከበሩ ተግባር አስፈላጊ የሆነውን መተማመን የሚሸረሽር ነው” ብሏል።
👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
ባለፉት ጊዜያት በሶማሊያ ውስጥ ለሰላም ማስከበር የተደረገው የኢትዮጵያ ሠራዊት ስምሪት የአል ሻባብ እንቅስቃሴ እንዲጨምር አድርጓል ሲል የሶማሊያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ወቀሰ።
የኢትዮጵያ ወታደሮች ከግዛቷ እንዲወጡ ስትጠይቅ የቆየችው ሶማሊያ ከጥቂት ወራት በኋላ የሚያበቃውን የሰላም አስከባሪ ተልዕኮን ተከትሎ በምትኩ በሚሰማራው ኃይል ውስጥ የየትኛው አገር ወታደሮች እንደሚሳተፉ የምትመርጠው ራሷ መሆኗን ገልጻለች።
የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ በአገሪቱ ወታደሮቻቸውን ካሰማሩ አምስት አገራት በተለየ የኢትዮጵያ ሠራዊት ላይ በማተኮር ተልዕኮው የአል ሻባብ እንቅስቃሴ ከፍ እንዲል ከማድረግ ባሻገር ያስገኘው ለውጥ ውስን ነው ብሏል።
በዚህም የተለያዩ ምክንያቶችን ያስቀመጠው የሶማሊያ መንግሥት በቀጣይ በተተኪነት በአገሩ የሚሠማሩትን ሰላም አስከባሪዎች ውስጥ የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲካተቱ እንደማይፈለግ ባወጣው መግለጫ ላይ ፍንጭ ሰጥቷል።
የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቀጣይ በሶማሊያ ከሚሰማራው የአፍሪካ ኅብረት አረጋጊ ተልዕኮ አንጻር የሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የኢትዮጵያ ሚና በሚል ረቡዕ አመሻሽ ባወጣው መግለጫ በሁለቱ አገራት መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ጠቅሷል።
በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ስር በሶማሊያ የተሰማሩት የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲወጡ ባለፉት ወራት የሶማሊያ ባለሥልጣናት በተደጋጋሚ ሲጠይቁ መቆየታቸው ይታወሳል።
በመጪው ጥር የሚጠናቀቀውን የሰላም አስከባሪውን ውክልና ተከትሎ በሚተካው አዲስ ተልዕኮ ውስጥ አገራት የሚኖራቸውን ተሳትፎ በተመለከተ የሶማሊያ መንግሥት የበላይ በመሆን በአገሪቱ ሉዓላዊነት ላይ በማተኮር የተልዕኮውን ሚና እንደሚመራ አሳውቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ በቅርቡ የተናጠል እርምጃ መውሰዷን በመጥቀስ ለአብነትም ነጻ አገርነቷን ካወጀችው ሶማሊላንድ ጋር የደረሰችው ስምምነት የሶማሊያን ሉዓላዊነት የሚቃረን ነው በማለት ዋነኛው ትኩረቱ ኢትዮጵያ ላይ መሆኑን አመልክቷል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ መግለጫ ኢትዮጵያ “ከሰሜናዊ ግዛት ጋር የደረሰችው ሕገወጥ ስምምነት፣ ሉዓላዊነታችንን የሚጥስ እና ለሰላም ማስከበሩ ተግባር አስፈላጊ የሆነውን መተማመን የሚሸረሽር ነው” ብሏል።
👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s