👩◈ ሚስቴና አባቷ ◈👴🏻
ክፍል - ሦስት [፫]
✍ (በጥላሁን ተስፋዬ)
.
.
.
ለሶስተኛ ግዜ አንኳኳሁ ሰምታኝ ነው መሰለኝ አይኗን ገልጣ እኔ ክፍል ውስጥ ሆኜ እሷን እያየሁ ወዳለሁበት መስኮት ተመለከተች ።የምታየኝ መስሎኝ ፈገግ አልሁ •••
አወይ መጃጃል! እንዲህ ጅል ላረጉይ አባቷ የስራቸውን ይስጣቸው አቦ እያልሁ እንደመንቀሳቀስ ስትል ተነስታ መስኮቷን በመክፈት አባቷ ታይሰሙ ልታስገባይ መስሎይ ትንፋሼን አጥፍቼ ትጠባበቅ ቀና አልይና መብራቱን ደረገመችው።
መብራቱን አጥፍታ ልከፍትልይ ይሆን ብዬ ብጠብቅም ድምጧን አጥፍታ ተሸፋፍና ተኛይ ።
"ያባቷ ልጅ!!"
አልሁና ታጣፊዋ አልጋዬ ላይ ሆድ ውስጥ እንዳለ ፅንስ ተጣጥፌ ተኛሁ።
በንጋታው ሆን ብዬ አባቷ ታይነሱ ቀደም ብዬ ተዋቡ ቁርስ በምታዘጋጅበት ሰአት ተነሳሁ።
ተዚህ በፊት እኔና ተወቡ የቱን ያህል ብንጣላ ተሁለት ቀን በላይ መኮራረፍ እንደማይሆንልን ጠንቅቄ ትለማውቅ በድፍረት ላናግራት ወሰንሁ።
ተትልቁ ቤት እኔ ታለሁበት በታች ወዳለው ማድ ቤት ሽር ጉድ እያለይ ቁርስ እያሰናዳይ ነው።
ለሽንት እንደሚወጣ ሰው ተክፍሌ ወጥቼ ሽንት ቤቱ ወዳለበት አቅጣጫ አንድ ሁለት እርምጃ ተራመድሁና ማድቤት መሆኗን አየት አድርጌ ታበቃ መለስ ብዬ ወደ ማድቤቱ ሄድሁ።
እማድቤቱ በር ላይ ቆም እንዳልሁ ቀና ብላ አየችይና ፊቷ ላይ ምንም ለውጥ ታታሳይ ምንም ታትለይ ስራዋን ቀጠለይ።
"ተዋቡዬ የኔ ድንብሽቡሽ እስቲ ንገርኝ እንደው እውነት አስችሎሽ ከልብሽ ጨክነሽ ነው እራት ቀን ሙሉ ጥርቅም አርገሽ የዘጋሽይ? አልኋት።
መልስ ሳትሰጠይ ዝምብላ ትንጎዳጎዳለይ።
"እኔ አሁን አንድ ነገር ብቻ ነው እምፈልገው እውነት ተልብሽ ተቀይመሽኝ ጠልተሽኝ ተሆነ ግልጡን ንገሪኝ ?! " ብላት አሁንም መልስ የለም ።
ብድግ ብላ ልትወጣ ትትል እግሬን ከፈት አርጌ መውጫ አሳጣኋትና •••
"ታልነገርሽኝ አታልፊም!" አልኋት።
"አንተ ወግድ ልለፍበት ኦሮ !" ብላ ያንን የበቆሎ እሸት የመሰለ ጥርሷን ብልጭ አድርጋ ፈገግ ትትልልይ ውስጤ እየፈገገ እግሬን ሰብስቤ አሳልፍኋትና ሽንቴን ልሸና ወረድሁ።
በቃ አበቃ እኔና ተዋቡ ታረቅን ። ድሮስ አባቷ ናቸው እይ የነገር እድሜ የሚያረዝሙት የኔ ተዋቡ በተጣላን እና በተናደደች ሰአት ንዴት እና እልኋ የምታረገውን ቢያሳጣትም፣ ንዴቷ ቲበርድላት ሁሉን ነገር ወድያው የምትረሳ ልቧ ውስጥ ለፍቅር እይ ለቂም የሚሆን ቦታ የሌላት፣ ገራገር ነይ።
ምን ያህል እንደማፈቅራትም ጠንቅቃ ታውቃለይ።
መነጋገር እንኳ ታያስፈልገን እኔና እሷ ተያይተን ብቻ የምንፈታውን ነገር ነው እንግዲህ ጠባችን እና መኳረፋችን ለወር እንዲራዘም የፈረዱብን እኛ አምባገነን አባቷ።
መሀላችን እንደጠብ ግድግዳ ተገሽረው ምን አርጉ እንደሚሉን እንጇ!።
ተሽንት ቤት ትመለስም ተያይተን ተሳሳቅን።
እንደጥዋት ጠሀይ ቀስ እያለ ደም በሚያሞቀው በተዋቡ ፈገግታ ደስ እያለኝ የጠባይ ማረሚያ እስር ቤት መስሏ ወደምትታየኝ ክፍሌ ገብቼ ጋደም አልሁ።
እኔና ተዋቡ ስለታረቅን ደስ ቢለኝም ተዋቡ "በቃ እኛ ታርቀናል ያንተ እዚህ መሆን አያስፈልግም!" ብላ አባቷን እንድሸኛቸው ብነግራት ደፈራ እንደማታደርገው እና እሺ እንደማትለኝ እያሰብሁ ምን ማረግ እንዳለብይ ታስብ ቆየሁ ።
እኔው እራሴው አሁኑኑ አባቷ ተንቅልፋቸው ሲነሱ ጠብቄ •••
"የተዋቡ አባት ! በቃ እኛ ታርቀናል እርሶ ተፈለጉ እዚሁ መክረም ታልያም መሄድ ይችላሉ እንደምርጫዋ!እኔን ግን ተንግዲህ ቡሀላ ተምሽቴ ጎን ተመተኛት ሊከለክሉይ አይችሉም ነው የምላችው !"
እያልሁ ትፎክር ቆየሁና እንደተነሱ አሁን እንዲህ ብላቸው •••
"ተደፈርሁ!! ክብሬ ተነካ ! "ብለው እንቧከረዩ ማለታቸው ታያንስ እኔ ያልሁት አንድ ወር እስቲሟላ ተዋቡ ልጄ እኔው ጋር ትቆያለይ ብለው ይዘዋት ተመሄድ የማይመለሱ መሆኑን ታስበው ፈርቼ ተውሁት።
ተዛ ይልቅ ተምሽቴ ጋር እንዴት አድርገን እንድሄዱ ማድረግ እንዳለብን ብንማከርባት እንደሚሻል ወሰንሁ።
ሁለት ቀን ተዋቡን አግኝቼ ላወራት ባደፍጥም አባቷ ለምን ቆየሽ እንዳይሏት ነው መሰል ምግብ እክፍሌ አምጥታልይ "እንዴት ነህ አንዱዬ?"
ብላ ፈገግታዋን ብልጭ እያረገይ አፍታም ታትቆይ ውልቅ ስለምትል ላወራት ቸገረይ።
አባቷን ያላከበረይ ባላን አታከብርምና ሚሽቴ ላባቷ ያላት ክብር ደስ ቢለኝም በትዳሯ በህይወታ መሀል ገብተው እኔ ያልሁት ታልሆነ እኔ የወሰንሁት ታልተተገበረ ቲሉ ተቀብላ ፍላጎታቸውን ለሟሟላት እየተሽቆጠቆጠይ ላማውራት እንኳን ግዜ ስታሳጣይ ስትቀር ዴሜ ፈላ።
በይህ ምክንያት አሁንም አባቷ ተመጡ በሰባተኛው ቀን ወደ ጠጅ ቤት ሄድሁ።
ሞቅ ብሎይ ተጠጅ ቤት እንደወጣሁ እቤት እስትደርስ የውስጤን ብሶት በንጉርጉሮ እየተነፈስሁ ሄድሁ።
ደርሼ ክፍሌ ተገባሁ ቡሀላም ዝፈን ዝፈን አለይ ። ዘፍናለኋ! በገዛ ክፍሌ አታንጎራጉር የሚለኝ ታለ አያለሁ እንግዲህ አልሁና
ተቀብል ብዬ ድምጤን ከፍ አድርጌ መዝፈን ጀመርሁ •••
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
እንኳንስ ላአንድ ወር ቢተኙ ላመት
ሰው አለ ተብሎ ይፈታል ወይ ሚስት!
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ(2)
እንኳንስ ሆድ ሆዴን ይብላው አንጀቴን
ባሌ አይደለም ወይ ያቆመው ቤቴን
ብላ እንድዘፍንልይ ብነግራት ሚሽቴን
ድምጧን አጥፍታለይ ፈርታ አባቷን!!
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
ጎመኑ ይቅርብኝ አውጪልኝ ከወጡ
ትናንት አጋብተውን ሊለያዩን መጡ
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
በተለ የመጨረሻዋን ይችን •••
ጎመኑ ይቅርብኝ አውጪልኝ ከወጡ
ትናንት አጋብተውን ሊለያዩን መጡ!
የምትለውን ቅኔ ሆን ብዬ እየደጋገምሁ እንቅልፍ እስቲጥለኝ ታዜማት ቆየሁና ተኛሁ።
በንጋታው ምሳ ሰአት አለፍ ታለ ቡሀላ ምሳ ይዛልይ የመጣይው ተዋቡ አልጋዬ ጠርዝ ቁጭ አለይና ።
አገጫን በግርምት በጇ መዳፍ ደግፋ እንደመሳቅ ቲቃጣት ።
ምንው ለምን ትታገይዋለሽ ሳቂና ይውጣልሽ አልኋት ማታ ሳንጎራጉር ሰምታይ እንደሆነ ገብቶኛል።
"ኪኪኪኩኩ እንድዬ ሙት እንዲህ ውብ ድምጥ እንዳለህ ትናንት ነው የሰማሁት "
ተይ እንጂ ድምጥ እንኳን የለኝም ምናልባት ሆድ የባሰው ሰው ተሆዱ ስለሚያንጎራጉር ድምጡ ሆድ ይበላ ይሆን እንደሆን እይ የለለውን ድምጥ ተዌት ያመጣዋል?
እሺ ድምጡስ ይሁን ግጥሙንስ ተዌት አመጣህው በል።
"ኬት አመጣዋለሁ እራሴው ነኛ የገጠምሁት ሰው ፍቅር ቲይዘውና ሆድ ቲብሰው ገጣሚ እንደሚሆን አታዉቂም።
አይ አንዱዬ የትናንት ማታው እማ የተለየ ነው። ተኝተህ ዝም እስትትል ድረስ እንዲሁ በተጋደምሁበት እየሰማሁህ ስስቅ እኮ ነው ያመሸሁት።አብዋም ተኝቶ አልሰማህም እይ ተመሳቅ ባልተመለሰ!"
" መች ስቀው ያውቁና? ይልቅ አንቺ ግን ሳቅሽ አደል? ሳቂ ምናለብሽ እኔ እንባ እንባ እያለኝ ታንጎራጉር መሳቅሽ ይገርማል!
ለኔ እንደቋጥኝ የከበደኝ ያባትሽ ውሳኔ ተስማምቶሻል ማለት ነው ተዋቡ ? 'ስላት።
"ምን ላድርግ የኔ አለም እስቲ ንገረኝ ምን ላድርግ?እኔም ሂድ አልለው ነገር ተቸገርሁ እኮ!ምን ላድርግ አለሜ እስቲ ንገረይ? አቡዋ እንደሁ አንድ ወር ይቀጣ ብሌ ተወሰነ ወሰነ ነው ፍንክች አይል እኛ ታርቀናል ሰላም ወርዷል ሂድ ብለው ያዋረድሁት ይመስለውና ይናደድብኛል ብዬ እይ ወድጄ መሰለህ ?
ተተናደደ ደሞ ታውቃለህ ያ መከረኛ ደም ብዛቱ ይጨምርና ሌላ ጦስ ይመጣብናል ብዬ ፈራሁ!"
ክፍል - ሦስት [፫]
✍ (በጥላሁን ተስፋዬ)
.
.
.
ለሶስተኛ ግዜ አንኳኳሁ ሰምታኝ ነው መሰለኝ አይኗን ገልጣ እኔ ክፍል ውስጥ ሆኜ እሷን እያየሁ ወዳለሁበት መስኮት ተመለከተች ።የምታየኝ መስሎኝ ፈገግ አልሁ •••
አወይ መጃጃል! እንዲህ ጅል ላረጉይ አባቷ የስራቸውን ይስጣቸው አቦ እያልሁ እንደመንቀሳቀስ ስትል ተነስታ መስኮቷን በመክፈት አባቷ ታይሰሙ ልታስገባይ መስሎይ ትንፋሼን አጥፍቼ ትጠባበቅ ቀና አልይና መብራቱን ደረገመችው።
መብራቱን አጥፍታ ልከፍትልይ ይሆን ብዬ ብጠብቅም ድምጧን አጥፍታ ተሸፋፍና ተኛይ ።
"ያባቷ ልጅ!!"
አልሁና ታጣፊዋ አልጋዬ ላይ ሆድ ውስጥ እንዳለ ፅንስ ተጣጥፌ ተኛሁ።
በንጋታው ሆን ብዬ አባቷ ታይነሱ ቀደም ብዬ ተዋቡ ቁርስ በምታዘጋጅበት ሰአት ተነሳሁ።
ተዚህ በፊት እኔና ተወቡ የቱን ያህል ብንጣላ ተሁለት ቀን በላይ መኮራረፍ እንደማይሆንልን ጠንቅቄ ትለማውቅ በድፍረት ላናግራት ወሰንሁ።
ተትልቁ ቤት እኔ ታለሁበት በታች ወዳለው ማድ ቤት ሽር ጉድ እያለይ ቁርስ እያሰናዳይ ነው።
ለሽንት እንደሚወጣ ሰው ተክፍሌ ወጥቼ ሽንት ቤቱ ወዳለበት አቅጣጫ አንድ ሁለት እርምጃ ተራመድሁና ማድቤት መሆኗን አየት አድርጌ ታበቃ መለስ ብዬ ወደ ማድቤቱ ሄድሁ።
እማድቤቱ በር ላይ ቆም እንዳልሁ ቀና ብላ አየችይና ፊቷ ላይ ምንም ለውጥ ታታሳይ ምንም ታትለይ ስራዋን ቀጠለይ።
"ተዋቡዬ የኔ ድንብሽቡሽ እስቲ ንገርኝ እንደው እውነት አስችሎሽ ከልብሽ ጨክነሽ ነው እራት ቀን ሙሉ ጥርቅም አርገሽ የዘጋሽይ? አልኋት።
መልስ ሳትሰጠይ ዝምብላ ትንጎዳጎዳለይ።
"እኔ አሁን አንድ ነገር ብቻ ነው እምፈልገው እውነት ተልብሽ ተቀይመሽኝ ጠልተሽኝ ተሆነ ግልጡን ንገሪኝ ?! " ብላት አሁንም መልስ የለም ።
ብድግ ብላ ልትወጣ ትትል እግሬን ከፈት አርጌ መውጫ አሳጣኋትና •••
"ታልነገርሽኝ አታልፊም!" አልኋት።
"አንተ ወግድ ልለፍበት ኦሮ !" ብላ ያንን የበቆሎ እሸት የመሰለ ጥርሷን ብልጭ አድርጋ ፈገግ ትትልልይ ውስጤ እየፈገገ እግሬን ሰብስቤ አሳልፍኋትና ሽንቴን ልሸና ወረድሁ።
በቃ አበቃ እኔና ተዋቡ ታረቅን ። ድሮስ አባቷ ናቸው እይ የነገር እድሜ የሚያረዝሙት የኔ ተዋቡ በተጣላን እና በተናደደች ሰአት ንዴት እና እልኋ የምታረገውን ቢያሳጣትም፣ ንዴቷ ቲበርድላት ሁሉን ነገር ወድያው የምትረሳ ልቧ ውስጥ ለፍቅር እይ ለቂም የሚሆን ቦታ የሌላት፣ ገራገር ነይ።
ምን ያህል እንደማፈቅራትም ጠንቅቃ ታውቃለይ።
መነጋገር እንኳ ታያስፈልገን እኔና እሷ ተያይተን ብቻ የምንፈታውን ነገር ነው እንግዲህ ጠባችን እና መኳረፋችን ለወር እንዲራዘም የፈረዱብን እኛ አምባገነን አባቷ።
መሀላችን እንደጠብ ግድግዳ ተገሽረው ምን አርጉ እንደሚሉን እንጇ!።
ተሽንት ቤት ትመለስም ተያይተን ተሳሳቅን።
እንደጥዋት ጠሀይ ቀስ እያለ ደም በሚያሞቀው በተዋቡ ፈገግታ ደስ እያለኝ የጠባይ ማረሚያ እስር ቤት መስሏ ወደምትታየኝ ክፍሌ ገብቼ ጋደም አልሁ።
እኔና ተዋቡ ስለታረቅን ደስ ቢለኝም ተዋቡ "በቃ እኛ ታርቀናል ያንተ እዚህ መሆን አያስፈልግም!" ብላ አባቷን እንድሸኛቸው ብነግራት ደፈራ እንደማታደርገው እና እሺ እንደማትለኝ እያሰብሁ ምን ማረግ እንዳለብይ ታስብ ቆየሁ ።
እኔው እራሴው አሁኑኑ አባቷ ተንቅልፋቸው ሲነሱ ጠብቄ •••
"የተዋቡ አባት ! በቃ እኛ ታርቀናል እርሶ ተፈለጉ እዚሁ መክረም ታልያም መሄድ ይችላሉ እንደምርጫዋ!እኔን ግን ተንግዲህ ቡሀላ ተምሽቴ ጎን ተመተኛት ሊከለክሉይ አይችሉም ነው የምላችው !"
እያልሁ ትፎክር ቆየሁና እንደተነሱ አሁን እንዲህ ብላቸው •••
"ተደፈርሁ!! ክብሬ ተነካ ! "ብለው እንቧከረዩ ማለታቸው ታያንስ እኔ ያልሁት አንድ ወር እስቲሟላ ተዋቡ ልጄ እኔው ጋር ትቆያለይ ብለው ይዘዋት ተመሄድ የማይመለሱ መሆኑን ታስበው ፈርቼ ተውሁት።
ተዛ ይልቅ ተምሽቴ ጋር እንዴት አድርገን እንድሄዱ ማድረግ እንዳለብን ብንማከርባት እንደሚሻል ወሰንሁ።
ሁለት ቀን ተዋቡን አግኝቼ ላወራት ባደፍጥም አባቷ ለምን ቆየሽ እንዳይሏት ነው መሰል ምግብ እክፍሌ አምጥታልይ "እንዴት ነህ አንዱዬ?"
ብላ ፈገግታዋን ብልጭ እያረገይ አፍታም ታትቆይ ውልቅ ስለምትል ላወራት ቸገረይ።
አባቷን ያላከበረይ ባላን አታከብርምና ሚሽቴ ላባቷ ያላት ክብር ደስ ቢለኝም በትዳሯ በህይወታ መሀል ገብተው እኔ ያልሁት ታልሆነ እኔ የወሰንሁት ታልተተገበረ ቲሉ ተቀብላ ፍላጎታቸውን ለሟሟላት እየተሽቆጠቆጠይ ላማውራት እንኳን ግዜ ስታሳጣይ ስትቀር ዴሜ ፈላ።
በይህ ምክንያት አሁንም አባቷ ተመጡ በሰባተኛው ቀን ወደ ጠጅ ቤት ሄድሁ።
ሞቅ ብሎይ ተጠጅ ቤት እንደወጣሁ እቤት እስትደርስ የውስጤን ብሶት በንጉርጉሮ እየተነፈስሁ ሄድሁ።
ደርሼ ክፍሌ ተገባሁ ቡሀላም ዝፈን ዝፈን አለይ ። ዘፍናለኋ! በገዛ ክፍሌ አታንጎራጉር የሚለኝ ታለ አያለሁ እንግዲህ አልሁና
ተቀብል ብዬ ድምጤን ከፍ አድርጌ መዝፈን ጀመርሁ •••
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
እንኳንስ ላአንድ ወር ቢተኙ ላመት
ሰው አለ ተብሎ ይፈታል ወይ ሚስት!
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ(2)
እንኳንስ ሆድ ሆዴን ይብላው አንጀቴን
ባሌ አይደለም ወይ ያቆመው ቤቴን
ብላ እንድዘፍንልይ ብነግራት ሚሽቴን
ድምጧን አጥፍታለይ ፈርታ አባቷን!!
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
ጎመኑ ይቅርብኝ አውጪልኝ ከወጡ
ትናንት አጋብተውን ሊለያዩን መጡ
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
እህህ ደማሙ እህህ ደማሙ
በተለ የመጨረሻዋን ይችን •••
ጎመኑ ይቅርብኝ አውጪልኝ ከወጡ
ትናንት አጋብተውን ሊለያዩን መጡ!
የምትለውን ቅኔ ሆን ብዬ እየደጋገምሁ እንቅልፍ እስቲጥለኝ ታዜማት ቆየሁና ተኛሁ።
በንጋታው ምሳ ሰአት አለፍ ታለ ቡሀላ ምሳ ይዛልይ የመጣይው ተዋቡ አልጋዬ ጠርዝ ቁጭ አለይና ።
አገጫን በግርምት በጇ መዳፍ ደግፋ እንደመሳቅ ቲቃጣት ።
ምንው ለምን ትታገይዋለሽ ሳቂና ይውጣልሽ አልኋት ማታ ሳንጎራጉር ሰምታይ እንደሆነ ገብቶኛል።
"ኪኪኪኩኩ እንድዬ ሙት እንዲህ ውብ ድምጥ እንዳለህ ትናንት ነው የሰማሁት "
ተይ እንጂ ድምጥ እንኳን የለኝም ምናልባት ሆድ የባሰው ሰው ተሆዱ ስለሚያንጎራጉር ድምጡ ሆድ ይበላ ይሆን እንደሆን እይ የለለውን ድምጥ ተዌት ያመጣዋል?
እሺ ድምጡስ ይሁን ግጥሙንስ ተዌት አመጣህው በል።
"ኬት አመጣዋለሁ እራሴው ነኛ የገጠምሁት ሰው ፍቅር ቲይዘውና ሆድ ቲብሰው ገጣሚ እንደሚሆን አታዉቂም።
አይ አንዱዬ የትናንት ማታው እማ የተለየ ነው። ተኝተህ ዝም እስትትል ድረስ እንዲሁ በተጋደምሁበት እየሰማሁህ ስስቅ እኮ ነው ያመሸሁት።አብዋም ተኝቶ አልሰማህም እይ ተመሳቅ ባልተመለሰ!"
" መች ስቀው ያውቁና? ይልቅ አንቺ ግን ሳቅሽ አደል? ሳቂ ምናለብሽ እኔ እንባ እንባ እያለኝ ታንጎራጉር መሳቅሽ ይገርማል!
ለኔ እንደቋጥኝ የከበደኝ ያባትሽ ውሳኔ ተስማምቶሻል ማለት ነው ተዋቡ ? 'ስላት።
"ምን ላድርግ የኔ አለም እስቲ ንገረኝ ምን ላድርግ?እኔም ሂድ አልለው ነገር ተቸገርሁ እኮ!ምን ላድርግ አለሜ እስቲ ንገረይ? አቡዋ እንደሁ አንድ ወር ይቀጣ ብሌ ተወሰነ ወሰነ ነው ፍንክች አይል እኛ ታርቀናል ሰላም ወርዷል ሂድ ብለው ያዋረድሁት ይመስለውና ይናደድብኛል ብዬ እይ ወድጄ መሰለህ ?
ተተናደደ ደሞ ታውቃለህ ያ መከረኛ ደም ብዛቱ ይጨምርና ሌላ ጦስ ይመጣብናል ብዬ ፈራሁ!"