"እምትናደድበት ነገር ቸግሮሀል መሰል ወዳጄ እሚካፈል ቢሆን ባከፈልኩህ ኧረ እንደውም ሁሉንም በሰጠሁህ
እንዴት
ምን እንዴት አለው አሁን እምትናደድበት አጥተህ ነው በዚህ እምትናደደው
"እስቲ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ
"ባልና ሚሽት ካንድ ወንዝ ይቀዳሉ" ብሎ ለመጀመሪያ ግዜ የተናገረው ወይ የጣፈው ግን ማን እንደሆን ታውቃለህ ? ""
ቲለኝ•••
አባቷ የጀመሩይን እሱ ሊጨርሰይ ነው እንዴ አልሁና በሆዴ!!
አብደሀል እንዴ አንተ ሰው እሄ ተስንት ዘመን ዥምሮ ቲወርድ ቲዋረድ የመጣ አባብልም እይደል እንዴ
እንደዛ ሲሉ እሰማለሁ እይ ማን እንዳለው በምን አውቃለሁ ዳምጤ !?" ብለው ።
"እሄን ሰው ባገኘው አንድ ጥያቄ እጠይቀው ነበር አንድ ብቻ !ሳልደግም ሳልሰልስ አንድ ብቻ ጠይቄው ምን እንደሚለኝ በሰማሁ "
ምን ብለህ ነው እምጠይቀው ጃል?አልሁት ለካ እኔ ብቻ አይደለሁም ቀልቤን ያጣሁት እያልሁ።
"ከነኝህ ከንድ ወንዝ ከሚቀዱ ወይ ከሚጨለፉ ባልና ሚሽቶች ስም ዝርዝር መሀል የኔና የሚሽቴን ስም ልታሳየኝ ትችላለህ ወይ ብዬነዋ?
እንደው ባገኘው ይህን ጠይቄ ጉዱን ነበር እማፈላው! መልሱ የናንተ ሽም የለም እንደሚሆን መች አጣሁት!•••
ቀኑን ተወው ሳምንቱን ፣ሳምንቱን ተወው ወርና አመቱን የኔና የባልተቤቴን ሽም ለማግኘት ቢኳትን አያገኘውም ስልህ••
ታይኔ ነው ብሎ መነጥር ቢደረግም፣ ተመነጥሩ ነው ብሎ አጉሊ መነጥር ቢገረግድ ያልሆነውን ተዌት ያመጣናል!"
ተው እይ ጃል ታንድ ወንዝ ባትቀዱ ምን አቆራኛችሁ እህል ውሃ ባንተና በሷ መሀል ባይጣፍ ስሜት ጋልቧችሁ ብትጋቡ እንኳ ተሶስት ወር በላይ አብራችሁ ባልዘለቃችሁ ? ብለው ቱግ ብሎ ተመቀመጫው ተነሳና•••
"እኔና ሚስቴ ነን ታንድ ወንዝ የተቀዳነው?
ስማ ትሰማኛለህ እኔና ሚሽቴ አይደለም
ታንድ ወንዝ ልንቀዳ ተሁለት የተለያዩ ወንዞይ እንኳ አልተቀዳንም
ምን ይላል እሄ •••" አለይ።ቱግ ሲል በረድ ብዬ
እንዴት ? ብለው "እንዴት ማለት ጥሩ ነው" አለና•••
ስለኔ እና ስለሚስቴ እውነቱን ማወቅ እምትፈልግ ተሆነ ልንገርህ አድምጠይ
እኔ እና አሷ ማለት እኔ ወንዝ ትሆን እሷ ተራራ ነይ ተራራ ታውቃለህ አደል
ወንዝ ተራራ ላይ ይወጣል??
በፍፁም አይወጣም! ቁልቁል ተሆነ ይሄዳል ብለው
"ልክ ብለሀል ብሄደም ሽቅብ ታይሆን ቁልቁል ተምዘግዝጎ ባናቱ መፈጥፈጥ ይሆናል እጣ ፋንታው
ዛድያ እሷ ተራራም አይደለይ እኔ ከሷ ጋር የምኖረው ሁሌ እየተፈጠፈጥሁ ስልህ ምን ነካህ ፊቴን ተመልከተው እይ
እውነቱን ተናገር እሄ ድሮ የምታውቀው የዳምጠው ፊት ነው ? በጭራሽ !•••
እሄውልህ የኔ ሚሽት ማለት አዘውትራ የምትለብሰው ልብሱን እኔ ያልወደድሁት እንደሆነ ብቻ ነው። አዘውትራ የምትሰራው ወጥም እኔ ባልበላው ደስ ይለኛል ያልኋትን ነው!"
ተው እንጂ ዳምጤ መስሎህ እንዳይሆን?
"መስሎህ እንዳይሆን ይለኛል እንዴ እሄ ሰው ምን ነካው ዛሬ?
እሄውልህ የኔ ሚስት አጥብቃ የምትይዛት ጋደኛ ምናልባት ይቺ ልዥ ምኗም አይጥመይ፣ ደስ አትለኝም ፣ ያልሁ እንደሆነ ነው!"
ኧረ ተው እታጋነው ዳምጤ! •••
"እስቲ ዝም ብልህ ስማይ ! •••
እኔ ነኝ ያለሁበትን ንዳድ የማውቀው ወይ ጉድ ገና ሲሶውን እንኳ መች ነገርኩህና የውልህ •••
ገብስማ ዶሮ አልወድም የሚል ቃል ታፌ ተወጣ ገብስማ ዶሮ ገዝታ ለመምጣት ተትናገርሁበት ቀን ቀጥሎ ያለውን አመትባል እንደሷ በጉጉት የሚጠብቅ ሰው በመላ ምድሪቱ እግርህ እስቲነቃ ብትፈልግ አታገኝም ስልህ ቲለኝ •••
ካካካካ ኦሮ አሁንስ በግድ ልታስቀይ ነው መሰል አንተ ሰው ብለው
ይልቅ ስማኝማ ለሳቁ ኋላ ትደርስበታለህ ብሎ •••
"ስማኝ ወዳጄ አንዳርጌ•••
ጥቁር በግ አልወድም ታልኋት መግዣ ገንዘብ ብታጣ ብታጣ ስታረግዝ ጠብቃ ጥቁር በግ አማረይ ትለኛለይ።
ያኔ የገባሁበት ገብቼ ተለቅቼም ቢሆን እልወድም ያልኋትን ጥቁር በግ እኔው ገዥቼ እየጎተትሁ ይዧላት እመጣለሁ።
ገና ጥቁሩን በግ ይዤ ስገባ እንዳየይ ደስታዋን እንዴት ብዬ ልግለጥልህ ጃል?
እንደው ተግር ጥፍራ እስተራስ ጠጉሯ ሁለመናዋ ጥርስ እስቲመስለይ ድረስ ስታገጥብይ ትውላለይ።
ዛድያ የገብስማ ዶሮውንም የጥቁር በጉንም ስጋ እንዲች ታልቀምስ ብቻዋን ቅርጥፍ አርጋነው የበላችው። ብትለምነኝም አልቀምሳት ። እየተጠየፍሁ ብብላውስ መች ሆዴ ውስጥ ይረጋልኝ እና•••
ምስር ወጥ ደስ አይለኝም ካልሁ ሳምንቱን ሙሉ ተምስር ወጥ ውጪ አትስራም ስልህ።
እየው አሁን ባለፈ ለት በዶሮው እና በበጉ ግዜ ጠብቃ የማልወደውን እየገዛይ ትታነደኝ ቆይታ የለ ሆን ብዬ ጥቁር በሬ በጣም ነው እምጠላው አልኋት ።
ተዌት ታምጣው ?እንዴት እርጋ ጥቁር በሬ አርዳ ታብግነይ ?
መንደሩን አስተባብራ እቁብ ሰብስባ ቅርጫ ልታሳርድም አሰበይ፣
ዛድያ በሬውን እሷ ሄዳ አትገዛው ነገር ። አልያም ገዥዎቹን
ጥቁር በሬ ታልሆነ ሌላ እንዳትገዙ ብትል ስንት ሰው ባዋጣው ብር ምን ብላ ብቻዋን ታዛለይ ?
ብትል እንኳ ገዥዎቹ ጥቁር በሬ ያለይው ምን አስባ ነው ?
እኛ ልንበላ እይ ለሷ ሰይጣን ልንገብር አላዋጣን ብለው ነገር እንደሚያጠሙባት ጠንቅቃ ታውቀዋለይ ።
ሁሉንም እኔን ሊያናድዱ የሚችሉ ነገሮችን አድርጋ ስታበቃ እሄን ማድረግ ተሳናት ስልህ።
እኔም በዚህ ተረታለይ ብዬ ደረቴን ነፋቼ ትንጎማለል ተቀናት ቡሀላ ዘመድ ጥየቃ ወደኸተማው አብረን ወጣን።
ድንገት እጥርግያው መንገድ መሀል •••
"ዳምጥዬ! "
አለይኝ ትከሻዬን ነካ አድርጋ ።
ሁሌም እንዲህ ብላ ትትጠራይ ለምን እንደሆን እንጃ ልቤ ትርክክ ትላለይ ብቻ ምን ልትለይ ነው ብዬ
"ወዬ!" አልኋት ••••
እስቲ በደንብ እየው ስሞትልህ ዳምጥዬ ያኛው በሬ ደስ አይልም በዲማው ጊዬርጊስ አለችይ።
ዘወር ብዬ ወደአመላከተችይ አቅጣጫ ትመለከት እመንገዱ ዳር ላይ ታለ አንድ ስጋ ቤት ነጭ እተቀባ ግርግዳ ላይ የተሳለ ትልቅ ጥቁር በሬ ነው !
እንደው አንዳርጌ ሙት ነው እምልህ ብልጭጭ አለብይ!"
•••••••ይቀጥላል
ክፍል - ሰባት ... ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like❤️ ማድረግ አይርሱ።
የመወያያ ግሩፑን ይቀላቀሉን!
t.me/ethio_lifes_group
t.me/ethio_lifes_group
t.me/ethio_lifes_group
╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗
@fkrn_be_kalat
@fkrn_be_kalat
@fkrn_be_kalat
╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝
Ғᴏʀ ᴀɴʏ ᴄᴏᴍᴍᴇɴᴛ
@fkrn_be_kalat_bot
❥❥________⚘_______❥❥
እንዴት
ምን እንዴት አለው አሁን እምትናደድበት አጥተህ ነው በዚህ እምትናደደው
"እስቲ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ
"ባልና ሚሽት ካንድ ወንዝ ይቀዳሉ" ብሎ ለመጀመሪያ ግዜ የተናገረው ወይ የጣፈው ግን ማን እንደሆን ታውቃለህ ? ""
ቲለኝ•••
አባቷ የጀመሩይን እሱ ሊጨርሰይ ነው እንዴ አልሁና በሆዴ!!
አብደሀል እንዴ አንተ ሰው እሄ ተስንት ዘመን ዥምሮ ቲወርድ ቲዋረድ የመጣ አባብልም እይደል እንዴ
እንደዛ ሲሉ እሰማለሁ እይ ማን እንዳለው በምን አውቃለሁ ዳምጤ !?" ብለው ።
"እሄን ሰው ባገኘው አንድ ጥያቄ እጠይቀው ነበር አንድ ብቻ !ሳልደግም ሳልሰልስ አንድ ብቻ ጠይቄው ምን እንደሚለኝ በሰማሁ "
ምን ብለህ ነው እምጠይቀው ጃል?አልሁት ለካ እኔ ብቻ አይደለሁም ቀልቤን ያጣሁት እያልሁ።
"ከነኝህ ከንድ ወንዝ ከሚቀዱ ወይ ከሚጨለፉ ባልና ሚሽቶች ስም ዝርዝር መሀል የኔና የሚሽቴን ስም ልታሳየኝ ትችላለህ ወይ ብዬነዋ?
እንደው ባገኘው ይህን ጠይቄ ጉዱን ነበር እማፈላው! መልሱ የናንተ ሽም የለም እንደሚሆን መች አጣሁት!•••
ቀኑን ተወው ሳምንቱን ፣ሳምንቱን ተወው ወርና አመቱን የኔና የባልተቤቴን ሽም ለማግኘት ቢኳትን አያገኘውም ስልህ••
ታይኔ ነው ብሎ መነጥር ቢደረግም፣ ተመነጥሩ ነው ብሎ አጉሊ መነጥር ቢገረግድ ያልሆነውን ተዌት ያመጣናል!"
ተው እይ ጃል ታንድ ወንዝ ባትቀዱ ምን አቆራኛችሁ እህል ውሃ ባንተና በሷ መሀል ባይጣፍ ስሜት ጋልቧችሁ ብትጋቡ እንኳ ተሶስት ወር በላይ አብራችሁ ባልዘለቃችሁ ? ብለው ቱግ ብሎ ተመቀመጫው ተነሳና•••
"እኔና ሚስቴ ነን ታንድ ወንዝ የተቀዳነው?
ስማ ትሰማኛለህ እኔና ሚሽቴ አይደለም
ታንድ ወንዝ ልንቀዳ ተሁለት የተለያዩ ወንዞይ እንኳ አልተቀዳንም
ምን ይላል እሄ •••" አለይ።ቱግ ሲል በረድ ብዬ
እንዴት ? ብለው "እንዴት ማለት ጥሩ ነው" አለና•••
ስለኔ እና ስለሚስቴ እውነቱን ማወቅ እምትፈልግ ተሆነ ልንገርህ አድምጠይ
እኔ እና አሷ ማለት እኔ ወንዝ ትሆን እሷ ተራራ ነይ ተራራ ታውቃለህ አደል
ወንዝ ተራራ ላይ ይወጣል??
በፍፁም አይወጣም! ቁልቁል ተሆነ ይሄዳል ብለው
"ልክ ብለሀል ብሄደም ሽቅብ ታይሆን ቁልቁል ተምዘግዝጎ ባናቱ መፈጥፈጥ ይሆናል እጣ ፋንታው
ዛድያ እሷ ተራራም አይደለይ እኔ ከሷ ጋር የምኖረው ሁሌ እየተፈጠፈጥሁ ስልህ ምን ነካህ ፊቴን ተመልከተው እይ
እውነቱን ተናገር እሄ ድሮ የምታውቀው የዳምጠው ፊት ነው ? በጭራሽ !•••
እሄውልህ የኔ ሚሽት ማለት አዘውትራ የምትለብሰው ልብሱን እኔ ያልወደድሁት እንደሆነ ብቻ ነው። አዘውትራ የምትሰራው ወጥም እኔ ባልበላው ደስ ይለኛል ያልኋትን ነው!"
ተው እንጂ ዳምጤ መስሎህ እንዳይሆን?
"መስሎህ እንዳይሆን ይለኛል እንዴ እሄ ሰው ምን ነካው ዛሬ?
እሄውልህ የኔ ሚስት አጥብቃ የምትይዛት ጋደኛ ምናልባት ይቺ ልዥ ምኗም አይጥመይ፣ ደስ አትለኝም ፣ ያልሁ እንደሆነ ነው!"
ኧረ ተው እታጋነው ዳምጤ! •••
"እስቲ ዝም ብልህ ስማይ ! •••
እኔ ነኝ ያለሁበትን ንዳድ የማውቀው ወይ ጉድ ገና ሲሶውን እንኳ መች ነገርኩህና የውልህ •••
ገብስማ ዶሮ አልወድም የሚል ቃል ታፌ ተወጣ ገብስማ ዶሮ ገዝታ ለመምጣት ተትናገርሁበት ቀን ቀጥሎ ያለውን አመትባል እንደሷ በጉጉት የሚጠብቅ ሰው በመላ ምድሪቱ እግርህ እስቲነቃ ብትፈልግ አታገኝም ስልህ ቲለኝ •••
ካካካካ ኦሮ አሁንስ በግድ ልታስቀይ ነው መሰል አንተ ሰው ብለው
ይልቅ ስማኝማ ለሳቁ ኋላ ትደርስበታለህ ብሎ •••
"ስማኝ ወዳጄ አንዳርጌ•••
ጥቁር በግ አልወድም ታልኋት መግዣ ገንዘብ ብታጣ ብታጣ ስታረግዝ ጠብቃ ጥቁር በግ አማረይ ትለኛለይ።
ያኔ የገባሁበት ገብቼ ተለቅቼም ቢሆን እልወድም ያልኋትን ጥቁር በግ እኔው ገዥቼ እየጎተትሁ ይዧላት እመጣለሁ።
ገና ጥቁሩን በግ ይዤ ስገባ እንዳየይ ደስታዋን እንዴት ብዬ ልግለጥልህ ጃል?
እንደው ተግር ጥፍራ እስተራስ ጠጉሯ ሁለመናዋ ጥርስ እስቲመስለይ ድረስ ስታገጥብይ ትውላለይ።
ዛድያ የገብስማ ዶሮውንም የጥቁር በጉንም ስጋ እንዲች ታልቀምስ ብቻዋን ቅርጥፍ አርጋነው የበላችው። ብትለምነኝም አልቀምሳት ። እየተጠየፍሁ ብብላውስ መች ሆዴ ውስጥ ይረጋልኝ እና•••
ምስር ወጥ ደስ አይለኝም ካልሁ ሳምንቱን ሙሉ ተምስር ወጥ ውጪ አትስራም ስልህ።
እየው አሁን ባለፈ ለት በዶሮው እና በበጉ ግዜ ጠብቃ የማልወደውን እየገዛይ ትታነደኝ ቆይታ የለ ሆን ብዬ ጥቁር በሬ በጣም ነው እምጠላው አልኋት ።
ተዌት ታምጣው ?እንዴት እርጋ ጥቁር በሬ አርዳ ታብግነይ ?
መንደሩን አስተባብራ እቁብ ሰብስባ ቅርጫ ልታሳርድም አሰበይ፣
ዛድያ በሬውን እሷ ሄዳ አትገዛው ነገር ። አልያም ገዥዎቹን
ጥቁር በሬ ታልሆነ ሌላ እንዳትገዙ ብትል ስንት ሰው ባዋጣው ብር ምን ብላ ብቻዋን ታዛለይ ?
ብትል እንኳ ገዥዎቹ ጥቁር በሬ ያለይው ምን አስባ ነው ?
እኛ ልንበላ እይ ለሷ ሰይጣን ልንገብር አላዋጣን ብለው ነገር እንደሚያጠሙባት ጠንቅቃ ታውቀዋለይ ።
ሁሉንም እኔን ሊያናድዱ የሚችሉ ነገሮችን አድርጋ ስታበቃ እሄን ማድረግ ተሳናት ስልህ።
እኔም በዚህ ተረታለይ ብዬ ደረቴን ነፋቼ ትንጎማለል ተቀናት ቡሀላ ዘመድ ጥየቃ ወደኸተማው አብረን ወጣን።
ድንገት እጥርግያው መንገድ መሀል •••
"ዳምጥዬ! "
አለይኝ ትከሻዬን ነካ አድርጋ ።
ሁሌም እንዲህ ብላ ትትጠራይ ለምን እንደሆን እንጃ ልቤ ትርክክ ትላለይ ብቻ ምን ልትለይ ነው ብዬ
"ወዬ!" አልኋት ••••
እስቲ በደንብ እየው ስሞትልህ ዳምጥዬ ያኛው በሬ ደስ አይልም በዲማው ጊዬርጊስ አለችይ።
ዘወር ብዬ ወደአመላከተችይ አቅጣጫ ትመለከት እመንገዱ ዳር ላይ ታለ አንድ ስጋ ቤት ነጭ እተቀባ ግርግዳ ላይ የተሳለ ትልቅ ጥቁር በሬ ነው !
እንደው አንዳርጌ ሙት ነው እምልህ ብልጭጭ አለብይ!"
•••••••ይቀጥላል
ክፍል - ሰባት ... ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like❤️ ማድረግ አይርሱ።
የመወያያ ግሩፑን ይቀላቀሉን!
t.me/ethio_lifes_group
t.me/ethio_lifes_group
t.me/ethio_lifes_group
╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗
@fkrn_be_kalat
@fkrn_be_kalat
@fkrn_be_kalat
╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝
Ғᴏʀ ᴀɴʏ ᴄᴏᴍᴍᴇɴᴛ
@fkrn_be_kalat_bot
❥❥________⚘_______❥❥