Фильтр публикаций


ቢሊየነሩ ኤለን መስክ የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ እንዲዘጋ ሀሳብ አቀረቡ።

በአዲሱ የመንግሥት ተቋመትን አፈጻጸም የሚገመግመውና በርካታ ውሳኔዎችን እያስተላለፈ የሚገኘው Department of Government Efficiency እያሥተዳደሩ የሚገኙት ኤሎን መስክ የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ እንዲዘጋ በኤክስ ገጻቸው ሀሳብ አቅርበዋል።

"ማንም ሰው አያዳምጣቸውም ይዘጉ" ይላል ያሰፈሩት ጽሑፍ።

የአሜሪካ ድምፅ የሬዲዮና እና የቴሌቪዥን ሥርጭት መሠረቱን በአገረ አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ያደረገና በ47 ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች ሥርጭቱን የሚያከናውን ተቋም ነው።



Via @mussesolomon


ዴንማርካውያን የአሜሪካዋን ካሊፎርኒያ ለመግዛት ዘመቻ ጀመሩ

ከ200 ሺህ በላይ ሰዎች እስካሁን ፊርማቸውን ያኖሩበት ዘመቻ ውጤታማ እንዲሆን እያንዳንዱ ዴንማርካዊ 18 ሺህ ዶላር እንዲያዋጣ ተጠይቋል።



Via @mussesolomon


ትራምፕ “ግብፅና ዮርዳኖስ የጋዛ ተፈናቃዮችን የማይቀበሉ ከሆነ የሚያገኝቱን እርዳታ አቆማለሁ” ሲሉ ዛቱ

ፕሬዝዳንት ትራምፕ “ፍልስጤማውያን ከጋዛ በቋሚነት ይወገዳሉ” ሲሉ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ትራምፕ ጋዛን ለመቆጣጠር የያዙትን እቅድ ግብጽና ዮርዳኖስን ጨምሮ በርካታ ሀገራት እየተቃወሙት ነው።




Via @mussesolomon


የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የሞተር ሳይክል እንቅስቃሴ ተከልክሏል - የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ

በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የሞተር ሳይክል እንቅስቃሴ መከልከሉን የአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።

በዚህም ከዛሬ የካቲት 04 2017 ዓ.ም ከዚህ ሰዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 09 2017 ዓ.ም ድረስ በመዲናዋ በየትኛውም አካባቢ ሞተር ሳይክል ማሽከርከር የማይቻል መሆኑን ቢሮው በማህበራዊ ትስስር ገፁ ገልጿል።



Via @mussesolomon


ፕሬዝደንት ትራምፕ "ዩክሬን አንድ ቀን የሩሲያ ልትሆን ትችላለች" ሲሉ ተናገሩ

ትራምፕ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲቆም የሚፈልጉ ሲሆን ዩክሬን ስምምነት ላይ ከመድረሷ በፊት ከአሜሪካ የደህነት ዋስትና ትፈልጋለች።



Via @mussesolomon


ዋይኒ ሩኒ በተንታኝነት !

ዋይኒ ሮኒ on prime ስፖርት በሚባል  ጣቢያ ላይ የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ተንታኝ ሆኖ ስራውን ይፋ ዛሬ ማንችስተር ሲቲ ከሪያል ማድሪድ የሚያደርጉት የጥሎ ማለፍ ጫወታ ላይ ይጀመራል !



Via @mussesolomon


Google officially removes Pride Month from its calendar app.


ግዙፉ የአለማችን ኩባንያ ጎግል የ Pride month ን ከ ካላንደር መተግበሪያቸው ላይ በይፋ አጥፍተውታል::


Via @mussesolomon


Baby Shark የሚለው የህፃናት ዘፈን Despacito ን በመብለጥ ዩቲዩብ ላይ ብዙ ግዜ የታየ ቪድዮ ሆንዋል።

ይህ መዝሙር ከ 15.6 ቢልዮን በላይ ቪው አለው



Via @mussesolomon


🛑 25% ብቻ በመክፈል ለውጥ ፈጣሪ ኮርሶችን እንደ Graphics design, video Editing, Digital Marketing, Upwork የምትወስዱበት የተራዘመው የዘውድ ቴክ 4ተኛ ዙር ምዝገባ ሊጠናቀቅ ነው።

✅100% የስራ እድል
✅ጥራት ያለው ስልጠና በ professional አስተማሪዎች
✅አንዴ ከፍለው 4 ስልጠናዎችን የሚወስዱበት
✅ certificate ያለው

️ያሉት ቦታዎች ውስን ስለሆኑ አሁኑኑ ከታች ባለው የዘውድ ቴክ ቻናል ሊንክ ተቀላቅለው orientation ይመልከቱ በመቀጠልም እዛ ላይ ባሉት ስልክ ቁጥሮች መልዕክት መላክ ወይንም መደወል ይችላሉ።

📩ቻናል ሊንክ👇

https://t.me/zewdtech/43


የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የደህንነት መረጃ እንዳያገኙ ታገዱ

አሜሪካንን በፕሬዝዳንትነት ያገለገሉ መሪዎች በየዕለቱ ያሉ የአሜሪካ ደህንነት መረጃዎች እንዲያውቁት የሚፈቅድ ህግ አላት፡፡

ከአራት ዓመት በፊት በስልጣን ላይ የነበሩት ዶናልድ ትራምፕ በምርጫ ተሸንፈው ስልጣን ለጆ ባይደን ካስረከቡ በኋላ ይህ አሰራር ከዶናልድ ትራምፕ ላይ ተሸሮ ነበር፡፡

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በወቅቱ ዶናልድ ትራምፕ የሚታመኑ ሰዉ ባለመሆናቸው የአሜሪካ ዕለታዊ ደህንነት መረጃ ሊደርሳቸው አይገባም ሲሉ አግደዋቸው ነበር፡፡



Via @mussesolomon


በአሜሪካዋ አላስካ 10 መንገደኞችን የጫነች አውሮፕላን መጥፋቷ ተገለጸ


የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች አውሮፕላኗን እየፈለጉ ነው ተብሏል


በአሜሪካ ባሁለት ሳምንት ውስጥ ሁለት የአውሮፕላን አደጋዎች ተከስተዋል



Via @mussesolomon


በ26 ጎማዎች የሚንቀሳቀሰው የዓለማችን ረጅሙ መኪና

ባንድ ጊዜ 75 ሰዎችን የሚያጓጉዘው ይህ መኪና በዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ ላይ ሰፍሯል

መኪናው ከትራንስፖርት ባለፈ የመዋኛ፣ አነስተኛ የጎልፍ ሜዳ እና አነስተኛ ሂልኮፕተር ማረፊያ ቦታ አለው ተብሏል



Via @mussesolomon


በግሪክ ካንሰር ቀዳሚው የሞት መንስኤ መሆኑ ተነገረ

ካንሰር በግሪክ ውስጥ ዋነኛው የሞት መንስኤ ሲሆን በአብዛኛው በከፍተኛ የሲጋራ ማጨስ መጠን፣ በአየር ብክለት እና በደካማ የህዝብ ጤና ስርዓት ምክንያት እንደሆነ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

የሳንባ ካንሰር በጣም የተለመደ ከካንሰር ጋር በተገናኘ ለሞት የሚዳርግ መንስኤ ነው ሲል ዕለታዊ ቶ ቪማ ዘግቧል። በሴቶች ላይ በብዛት የሚታወቁት የጡት እና የሳንባ ካንሰር ሲሆኑ የፕሮስቴት እና የሳንባ ካንሰር በወንዶች ላይ በብዛት እንደሚገኙ ዘገባው አክሎ ገልጿል።

እንደ ጣሊያን እና ስፔን ካሉ የሜዲትራኒያን ሀገራት ግሪክ ከፍተኛ የሆነ የዜጎች ውፍረት ያለባት ሀገር ስትሆን እስከ 70 በመቶው ዝቅተኛ ገቢ ያለው ህዝብ ይጎዳል ይላል ዘገባው። ዕለታዊው የብሔራዊ የካንሰር ስትራቴጂ አስፈላጊነትን አበክሮ ገልጿል።  “ካንሰርን ለመከላከል ቅድሚያ በመስጠት፣ አዳዲስ ሕክምናዎችን በማድረግ ኢንቨስት በማድረግ እና እኩል የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን በማረጋገጥ፣ ግሪክ ከካንሰር ጋር የተያያዘ ሞትን በእጅጉ በመቀነስ የታካሚዎችን ውጤት ማሻሻል ትችላለች ሲል የመፍትሄ ሀሳብ አቅርባል።


Via @mussesolomon


የኦሃዮ ዩኒቨርስቲ እንዳጠናው ወንዶች የራሳቸውን ፎቶ አብዝተው የሚፖስቱ ከሆነ የአእምሮ በሽተኞች ናቸው።


Via @mussesolomon


ለ15 ቀን ለኢትዮጵያ እንዲጸለይ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አወጀች

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ባሉት ቀጣናዎች፣ ክልሎች እና አጥቢያዎች በሙሉ አገራችን ኢትዮጵያን አስመልክቶ ከየካቲት 1 ጀምሮ እስከ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በጌታ ፊት ጸሎት እንዲደረግ በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ መወሰኑን ዳጉ ጆርናል ሰምቷል::




Via @mussesolomon


በብሪታንያ ከአልኮል መጠጥ ጋር በተያያዘ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር በሀገሪቱ ታሪክ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለጸ

በ2023 በሀገሪቱ ከአልኮል መጠጥ ጋር በተያያዘ ከ10 ሺህ በላይ ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።


Via @mussesolomon


በአዲስ አበባና አካባቢዋ ድሮን ያለ ፈቃድ ማብረር አይቻልም

በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ማንኛውንም አይነት ድሮን ያለ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር እንደማይቻል የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡

አገልግሎቱ በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ የሚደረግ የድሮን እና ሌሎች በራሪ አካላት አጠቃቀምን በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል።

አገልግሎቱ በመግለጫው÷ተቋሙ በአዋጅ ቁጥር 1276/2014 በተሰጠው ስልጣን መሠረት የመሪዎችን፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶችን እና ብሔራዊ ኩነቶችን ደኅንነት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የማስጠበቅ ኃላፊነት አለበት ብሏል።

Via @mussesolomon


ዛሬ ወደ ሀገር ውስጥ መዳረሻዎች የምትጓዙ መንገደኞች በዓለም አቀፍ መንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል በኩል ወደ በረራችሁ ተሳፋሩ " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

ዛሬ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 6:30 በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሀገር ውስጥ መንገደኞች ማስተናገጃ ሕንፃ ውስጥ ወደ በረራ ይዞ መግባት ከሚከለከሉ ቁሳቁሶች መካከል ከመንገደኞች የሚሰበሰብ የሲጋራ መለኮሻ (#ላይተር) ጊዜያዊ የማስቀመጫ ስፍራ ውስጥ ጭስ በመከሰቱ ለመንገደኞች ደህንነት ሲባል ሕንፃው ለጊዜው አገልግሎት ማቋረጡን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሳውቋል።

በዛሬው ዕለት ወደ ሀገር ውስጥ መዳረሻዎች የሚጓዙ መንገደኞች በዓለም አቀፍ መንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል በኩል ወደ በረራቸው እንዲሳፈሩ አየር መንገዱ አሳስቧል።

ከነገ ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በተለመደው የሀገር ውስጥ ተርሚናል አገልግሎት መስጠት እንደሚቀጥል ገልጿል።

" ለተፈጠረው መጉላላት መንገደኞቻችንን ይቅርታ እንጠይቃለን " ብሏል።


Via @mussesolomon


በሩሲያ በተካሄደ የከንቲባነት ምርጫ የከተማዋ የቀድሞ ከንቲባ በግል ሹፌሩ ሚስት ተበለጠ

ሩሲያ የከተሞቿን ከንቲባ በምርጫ ውጤት መሰረት እንዲመራ የሚፈቅድ ህግ ትከተላለች

የከንቲባ ምርጫው ውጤት ያልታሰበ እጩ ማሸነፉ አግራሞትን ፈጥሯል



Via @mussesolomon


በማቹሴት ዩኒቨርሲቲ በተሰራ ጥናት የሀሰት ዜና ሰሚ ጋር በመድረስ 6 እጥፍ ከእውነተኛው ዜና እንደሚፈጥን አረጋግጧል::


Via @mussesolomon

Показано 20 последних публикаций.