Фильтр публикаций


በምሥራቅ ጎጃም በድሮን ጥቃት ሕፃናትን ጨምሮ 16 ሰዎች መገደላቸውን የዓይን እማኞች እና ቤተሰቦች ተናገሩ

በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ሐሙስ የካቲት 13/2017 ዓ.ም. ተያይዘው በተሠሩ አራት ቤቶች ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 16 ሰዎች ሲገደሉ 10 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ቤተሰቦች እና የዓይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።

ጥቃቱ በዞኑ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ እነገሽ ቀበሌ (ሐሙስ ገበያ) በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሐሙስ ረፋድ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በሦስት ሱቆች እና ሻይ ቤት ላይ መድረሱን ቢቢሲ ያናገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

"[ድሮን] ስትዞረን ነበር" ያሉ አንድ የዓይን እማኝ ጥቃቱ ከደረሰበት ስፍራ በግምት 100 ሜትር ርቀት ላይ እንደነበሩ ጠቅሰው፤ የጥቃቱ ሰለባዎች መንገድ ላይ ሲጫወቱ የነበሩ ህፃናት፣ ገበያተኞች እና ሻይ እየጠጡ የነበሩ ሰዎች ናቸው ብለዋል።

ከፍተኛ ፍንዳታ መፈጠሩን የሚናገሩት እማኙ፤ ወዲያው "አካባቢውን አቧራው፤ የቤቱ ፍርስራሽ በጭስ" እንዳፈነው እና ድንጋጤ እና ግርግር እንደተፈጠረ ገልፀዋል።
ሌላ የዓይን እማኝም በፍንዳታው አካባቢው በአቧራ ጭስ መሸፈኑን ጠቅሰው፤ በስፍራው ለመተያትም አስቸጋሪ እንደነበር ተናግረዋል።

በደቂቃዎች ውስጥ ጥቃቱ ወደ ተፈፀመባቸው ቤቶች ደርሰው የቆሰሉ ሰዎችን እንዳወጡ እና አስከሬን እንዳነሱ የተናገሩት ሌላ የዓይን እማኝ "የሚጫወቱ ህፃናት እና ቆርቆሮ ሊገዙ የመጡ ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል" ብለዋል።

Via BBC News Amharic/meseret media

@sheger_press
@sheger_press


Репост из: Sheger Press️️
ጥቆማ‼️

በሀገራችን ታማኝ የዜና ምንጮችን የሚያገኙበት የቴሌግራም ቻናል ነው!

ሊንክ👇
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የ2017 ዐቢይ ጾምን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የጾመ ኢየሱስ ሱባኤ ዋና ዓላማ ዲያቢሎስን ድል መንሳት መኾኑን የገለጹት ብጹዕነታቸው ኢየሱስ ክርስቶስ አርባ የቀን እና አርባ ለሊት ሲጾም በዲያቢሎስ መፈተኑን አንስተዋል። በእርግጥም በአጽዋማት ወቅት ፈተናዎች ይበዛሉ ያሉት ፓትርያሪኩ ከጌታችን ጾም የምንወስደው ትምህርት የዲያቢሎስን ፈተና በመንፈስ ልዕልና ማለፍ እንደሚቻል ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምዕመናንም አስተምህሮውን መነሻ በማድረግ ታላቁን የዐቢይ ጾም በፈጣሪ የተከለከሉ ግብረ ኃጥያትን ባለመፈጸም በመልካም የመንፈስ ልዕልና መጾም እንደሚገባ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገልጸዋል።

ወርሃ ጾሙን ሰብዓዊ ክብር እንዳይነካ በመጸለይ፣ ከነገሮች ሁሉ ለሰላም እና እኩልነት ቅድሚያ በመስጠት፣ የተቸገሩትን በመርዳት በአጠቃላይ በመልካም ሥራ ማሳለፍ እንደሚገባም ብፁዕነታቸው መልእክት አስተላልፈዋል።(አሚኮ

@sheger_press
@sheger_press


"ኒቃብ ከመማር፣ ከፍተኛ ውጤት ከማምጣትና ከመሸለም አያግድም"

▣ ከአርባምንጭ ዩንቨርሲቲ በሜዲስን ዲፓርትመንት የወርቅ ሜዳለያ ተሸላሚዋ ዛኪራ ተባረክ

ተማሪ ዛኪራ ተባረክ ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሜዲስን ትምህርት ክፍል 3.87 አምጥታ በከፍተኛ ውጤት በዛሬው እለት ተመርቃለች።

ዛኪራ ተባረክ በዛሬው ዕለት በተካሄደው የአርባምንጭ ዩንቨርስቲ የምርቃ መርኃግብር ላይ በሶስት ዘርፍ ተሸላሚ ሆና ነው የተመረቀችው። ከሁሉም የህክምና ተማሪዎች አንደኛ በመውጣት፣ ከሁሉም ሴቶች አንደኛ በመውጣት፣ ከሁሉም ተማሪዎች አንደኛ ወጥታ የወርቅ ሜዳለያ ተሸላሚ መሆኗን እንዲሁም በጀመአ እንቅስቃሴ ላይ በስፋት እንደምትሳተፍ የሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ለሀሩን ሚድያ ያደረሱን መረጃ ያመላክታል።

ሀሩን ሚድያ

@sheger_press
@sheger_press


ኤርትራ‼️

የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒትር ኣይተ የማነ ገ/መስቀል እና የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊው ኮለኔል ተስፋልልደት፣የኤርትራ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች እንዲሁም የደህንነት ሃላፊዎች ከ ጥር 11/2017 ዓ.ም እስከ ጥር 13/2017 ዓ.ም ድረስ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ከጋሽ ባርካ፣ ከሰሜናዊ እና ደቡባዊ ቀይ ባህር፣ ዓንሰባ እና ደቡባዊ ዞኖች የተውጣጡ የፀጥታ አስተዳደር እና የህግደፍ (ሻዕቢያ) ጽ/ቤት አባላት በአስመራ ከተማ በሚገኘው የማስታወቂ ሚኒስቴር አዳራሽ አስቸኳይ  ሰብሰባ አካሂደው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈዋል።
በስብሰባው ፍጻሜ በተሰብሳቢዎች ከተወሰኑና ሳይሸራረፉ እንዲፈጸሙ መግባባት ላይ ከተደረሰባቸው መካከል፦

➊ ኢትዮጵያ ልትወረን ነው የሚል ሰፊ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እንዲከፈትና ለዚህም ተባባሪ የሆኑ በዋናነት የአረብ ሃገራት ሚዲያዎች እንዲመረጡ፣

➋ ሁሉም ዞኖች ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማእከል የሚገቡ ምልምል ሰልጣኞችን በፍጥነት እንዲያዘጋጁ፣

➌ ታጣቂዎች ላይ ልዩ ትኩረት በማድረግ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ወኪሎቻችን የማዛባት ስምሪት ወስደው እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ በ NSO በኩል ልዩ ክትትል እንዲደረግና ተቋሙ የተግባራት ዝርዝር በአስቸኳይ እንዲያቀርብ፣

➍ በውጭ ሃገራት የሚኖሩና መንግስትን የሚቃወሙ ዜጎች ዝርዝር መረጃ በየሃገራት ባሉ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች በኩል ተጠንቶ እንዲቀርብ፤ በቀረበው መረጃ መሰረት NSO NSO በሃገር ቤት ያሉ የተቃዋሚ ቤተሰቦቻቸውን በመያዝ ከገንዝብ ቅጣት እሰከ እሰራት የሚደርሱ እርምጃዎችን እንዲወስድ ጥብቅ ትዕዛዝ እንዲተላለፍ፣

➎ የኤርትራ ሰራዊትን ሞራል የሚያነሳሱ የተለያዩ ስራዎች እንዲሰሩ እንዲሁም ኢትዮጵያን የሚያወግዙ ህዝባዊ ሰልፎች በከተሞች እንዲከናዎኑና ሃላፊነቱን የማስታወቂያ ሚንስቴር ከሃገር ውስጥ ደህንነት ጋር በመቀናጀት እንዲወስድ፣

➎ ወደውጭ በሚጓዙና ወደሃገር ቤት በሚገቡ ዜጎች ላይ ልዩ ትኩረት እንዲደረግ የሚሉ ይገኙባቸዋል።

ከሰሞኑ ደግሞ ያገቡና የልጆች እናት የሆኑ ሴቶችን ጨምሮ እድሜአቸው ከ60 አመት በታች የሆኑ  ዜጎቹ እንዲዘመገቡና  ወደ ማሰልጠኛ ካምፕ እንዲገቡ ትዕዛዝ ማስተላለፉ ተረጋግጧል።

@sheger_press
@sheger_press


የዩ ኤስ ኤ አይ ዲ ዕርዳታ መቋረጥ በመላው ኢትዮጵያ ከባድ ንዝረት ፈጥሯል - ዘ ጋርዲያን

የአሜሪካው የተራድዖ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) ዕርዳታ መቋረጥ፣ በመላው ኢትዮጵያ ከባድ ንዝረት ፈጥሯል ሲል ዘ ጋርዲያን ዘግቧል።

በዕርዳታ ዕገዳው ሳቢያ፣ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ኢትዮጵያ ውስጥ ለተጠለሉ 800 ሺሕ ለሚጠጉ ስደተኞች ይሰጥ የነበረውን ዕርዳታ በ40 በመቶ መቀነሱን ዘገባው ጠቅሷል።

በተያዘው የአውሮፓውያኑ ዓመት የምግብ ዕርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር ወደ 5 ሚሊዮን የተቀነሰበት አንዱ ምክንያት፣ የዕርዳታ ድርጅቶቹ እጅጉን ዕርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ብቻ ዕርዳታ እንዲያቀርቡ የሚያስገድድ ሁኔታ በመፍጠሩ መኾኑንም ተገልጿል።

አሁን ባለው ተጨባጭ ኹኔታ፣ የዓለም ምግብ ፕሮግራም የምግብ አቅርቦቶቹን ከጨረሰ፣ ተጨማሪ የዕርዳታ ምግብ መግዛት እንደማይችልና ማሽላና የምግብ ዘይትን ጨምሮ 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎችን ላንድ ወር መመገብ የሚችል 34 ሺሕ 800 ሜትሪክ ቶን እህል፣ ወደ አገር ውስጥ ለሚያስገቡ ኮንትራክተሮች የሚከፈል ገንዘብ ባለመኖሩ ጅቡቲ ወደብ ላይ መቆሙንም የዜና ምንጩ ጠቅሷል።

@sheger_press
@sheger_press


#የወላድ ማኀፀን እንዲፈታ በእግዚአብሔር የተሾመ

ቊጥሩ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሲኾን፤ “ሩፋ” ማለት ሐኪም፤ ኤል ማለት እግዚአብሔር ማለት ሲኾን ሩፋኤል ማለት “እግዚአብሔር ሐኪሜ ነው” ማለት ነው፡፡ በመጽሐፈ ሄኖክ 6÷3ም “በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” ተብሏል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ነገደ መናብርት የሚባሉትን ራማ በሚባለው ሰማይ የሚኖሩትን ነገደ መላእክት የሚመራቸው ናቸው፡፡ ቅዱስ ኤጲፋንዮስም በመጽሐፈ አክሲማሮስ “በራማ ሰማይ የሚገኘውን ሁለተኛውን ዐሥሩን ነገድ መናብርት ሲላቸው አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፤ እነዚኽም ረቂቅ የኾነ የመብረቅ ጋሻ የእሳት ጦር ይዘው ከነፋስ ይልቅ የፈጠኑ ሲኾኑ በራማ በኹለተኛው ክፍል ላይ አስፍሯቸዋል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ከሚመራው ከዚኽ ነገድ 24ቱ ካህናተ ሰማይ ወጥተዋል፡፡” ይለናል፡፡

አባ ጊዮርጊስም በሰዓታቱ “ጽርሐ አርያም አዳራሹ፤ የትጉሃን መኖሪያ ቦታው የሚኾን እግዚአብሔር ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ ተብሎ በአንድነት በሦስትነት ይመሰገናል፤ ካህናተ ሰማይ በዙሪያው ይቆማሉ፤ በዙፋኑ ፊት እየሰገዱ አክሊሎቻቸውን ያወርዳሉ፤ እሳትነቱ በሚበርቅ፣ በሚል ጊዜ እንዳይመታቸው ይንቀጠቀጣሉ” ይላል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ባስልዮስም “በፊቱ የሚቆሙ የመላእክት ሰራዊትም ኹሉ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ የመላእክት አለቆችም ለማይታይ ለባለዚህ ስም ዘንበል ብለው ይሰግዳሉ፤ ዙፋኑን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ ዕጣንን የተመሉ የወርቅ ማዕጠንት በእጆቻቸው ያለ ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ይኸውም የቅዱሳን ጸሎት ነው እስከ ዘላለሙ ሕያው በኾነው ፊት የሚቀበለው መሥዋዕት አድርገው ወደ ላይ ያሳርጋሉ” በማለት አስተምሯል፡፡

ቅዱስ ሩፋኤል ጦቢትን የተራዳ መልአክም ነው፡፡ ጦቢት ዐሥሩ ነገድ በ720 ዓ.ዓ ሲማረኩ ዐብሮ የተማረከ ጻድቅ ሰው ነው፡፡ በመጽሐፈ ጦቢት 2÷14 እንደተጻፈው ሰውን በመርዳት በደግነቱ የታወቀው ጦቢት ከመንገድ ወድቆ የተገኘ በድን ቀብሮ፤ በዚያው ሌሊት ከቅጥሩ አጠገብ ፊቱን ተገልጦ ተኝቶ ሳለ አዕዋፍ ትኩስ ፋንድያ ዐይኑ ላይ ጥለውበት እንደ ብልዝ ያለ ወጥቶበት ዐይኑ ጠፋ፤ ሚስቱም ባለማስተዋል “በጐነትኽ ምጽዋትኽ ያዳነኽ ወዴት ነው?” በማለት ስትናገረው ዐዝኖ ሞትን ተመኘ፡፡ ቅዱስ ሩፋኤልም አይኑን ሲፈውሰው፣ በላይዋ ላይ ያደረ ጋኔን ባሎቿን ይገድልባት ቤተሰቦቿ ያንቋሽሿት የነበረችውን የራጉኤል ልጅ ሳራን ያደረባትን ርኩስ መንፈስ አስወጥቶ የጦቢት ልጅ ጦብያ እንዲያገባት አድርጓል፡፡

በዚኽም “ፈታሔ ማሕፀን” ተብሏል፡፡ በኋላም ወደ ጦቢት በመኼድ ረዥም ዘመን የታወረ ዐይኑን አብርቶለት ከሰብዐቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሩፋኤል እኔ ነኝ ብሏቸው ተሰውሯል፡፡ ጦቢ 12÷15፡፡ ፈታሔ ማኀፀን ወሰፋድል። መወለድ መንፈሳዊ። ወሐኪም ሰማያዊ ይባላል። የወላድ ማኀፀን እንዲፈታ በእግዚአብሔር ስለተሾመ አዋላጅ ብትኖርም ባትኖርም ቅዱስ ሩፋኤል በዚያ አይታጣም፡፡ በተለይ በባላገር ያሉ ሴቶች በምጥ ጊዜ ሁሉ መልክአ ሩፋኤል ያነግታሉ፣ ይጸልያሉ፣ የተጸለየበትንም ጸበል ይጠጣሉ፡፡ በፍጥነትም ይወልዳሉ። በይሩ በ13 ቀን መታሰቢያ በዓሉ የሚከበር ሲሆን ጳጉሜ 3 ደግሞ ዓመታዊ በዓሉ ነው፡፡ የመላዕክት ተራዳኢነት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ትልቅ ስፍራ አለው፡፡ በረከትና ረድኤታቸው አይለየን፤ ምልጃቸው ይጠብቀን፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




አዋጭ ሁለት ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ ብር ለሜቄዶንያ ለገሰ

አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር ለሜቄዶንያ 2,500,000 (ሁለት ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ )ብር ለግሷል።

አንድ ሚሊየን ብር በቁጠባና ብድር አንድ ሚሊየን በፋውንዴሽኑ አምስት መቶ ሺህ ብር ከሰራተኞቹና ከአባላት በአጠቃላይ ሁለት ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ ለመቅዶኒያ አስገብቷል።

በቀጣይም በየአመቱ አንድ ሚሊየን ብር ለመስጠት ቃል ገብተዋል።

@sheger_press
@sheger_press


473, 000,000 ብር ደረሰ‼️

ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ የገቢ ማሰባሰቢ እየተካሄደ በሚገኘው መርሀ ግብር ላይ 470,000,000 (አራት መቶ ሰባ ሚሊዮን) ብር መሰብሰብ ተችሏል።

አስራ አራተኛው ቀኑን በያዘው በዚህ የበጎ ዓላማ ድጋፍ በመላው ዓለም የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን እየተረባረቡ ይገኛሉ።

መርሀ ግብሩን በSeifu On Ebs በማህበራዊ ሚዲያ በቀጥታ ስርጭት ለተመካቾች እየደረሰ ሲሆን፣ ከተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት የመጡ መምህራን፣ የኪነ ጥበብ ሰዎች እና የሚዲያ ባለሞያዎች መድረኩን በማድመቅ ለጋሾችን በማበረታታት ላይ ናቸው።

አሁንም በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ "ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው" የምትሉ ወገኖች ድጋፋችሁን እንድትቀጥሉ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

@sheger_press
@sheger_press


በአማራ ክልል በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች ግጭት ከተፈጠረ ወዲህ፣ በክልሉ እስከታችኛው የመንግሥት መዋቅር ያሉ አመራሮች ከሥራ መልቀቅ እንደማይፈቀድላቸው ተሰምቷል ።

አመራሮቹ ከአመራርነት ተነስተው በባለሙያ የሥራ መደብ ለመቀጠል እንኳ ጥያቄያቸው ተቀባይነት እንደማያገኝ የተለያዩ አመራሮችን ተናግረዋል ።

በባሕርዳር ከተማ አንድ የክፍለ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ኃላፊ በፋኖ ታጣቂዎች ታግተው 700 ሺሕ ብር ገደማ ከፍለው ከተለቀቁ በኋላ በኃላፊነት መቀጠል እንደማይፈልጉ ቢያሳውቁም፣ ጥያቄያቸው ውድቅ እንደተደረገም ምንጮች ተተናግረዋል።

ምንጮቹ፣ ሥራ ለመልቀቅ የሚጠይቅ አመራር፣ "የጽንፈኛው ቡድን" ደጋፊ ነህ ተብሎ ሊጠረጠርና ሊታሠር ይችላል ብለዋል። የከተማዋ ኮማንድ ፖስት ከታጣቂዎች ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል የሚጠረጥራቸው አመራሮች በዳንግላ ከተማ ወደሚገኝ የተሃድሶ ማሠልጠኛ እንደሚላኩም ተገልጧል።

ከታጣቂዎች ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል ስለተጠረጠሩ ብቻ አለቆቻቸው ከሕግ ውጭ ከሥራ ያባረሯቸው ኹለት የከተማዋ አመራሮችን እንደሚያውቁም አንድ ምንጩ ለዋዜማ ተናግረዋል።)waZema)

@sheger_press
@sheger_press


የኤርትራ መንግሥት ከ60 አመት በታች ያሉ ዜጎቹ ወደካምፕ እንዲገቡ አዘዘ

የኤርትራ መንግሥት ያገቡና የልጆች እናት የሆኑ ሴቶችን ጨምሮ እድሜአቸው ከ60 አመት በታች የሆኑ ዜጎቹ እንዲዘመገቡና ወደ ካምፕ እንዲገቡ ትዕዛዝ አስተላለፈ።

ወታደራዊ ግዳጁ ከዚህ በፊት በውትድርና ላይ የነበሩ ዜጎችን የሚጨምር ሲሆን፤ ስልጠናውን የወሰዱ አካላትም በተጠባባቂነት እንዲቆዩ ይደረጋል ተብሏል።

በተጨማሪም ያገቡ እና ልጆች ያሏቸው ሴት ወታደሮች ወደ ቀድሞ ወታደራዊ ክፍላቸው እንዲመለሱ ታዝዘዋል።

በወታደራዊ ግዳጁ መመሪያ መሰረት ዕድሜያቸው ከ50 አመት በታች የሆኑ ግለሰቦች ከሀገር እንዳይወጡ የተከለከሉ ሲሆን፤ ይህም የግዳጅ ምልመላው ጥብቅ መሆኑን የሚያመላክት ነው ተብሏል።

የወታደራዊ ግዳጁን መመሪያ ተከትሎ የእንቅስቃሴ ገደቦች ተጥለዋል።

የክልል አስተዳደሮች ለወታደራዊ ግዳጅ የሚመለምሏቸውን ዜጎች የማሰባሰብ፣ የመመዝገብ እና የማሳወቅ ስራ መጀመራቸውንም ዘገባዎች አመላክተዋል።

ለወታደራዊ ግዳጅ ምልመላው ድንገተኛ እና ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ቅስቀሳ እየተደረገ ሲሆን፤ ይህም በኤርትራ ህዝብ ዘንድ ድንጋጤ ፈጥሯል።

የኤርትራ መንግሥት ለሌላ ዙር የትጥቅ ግጭት እየተዘጋጀ ነው የሚል ስጋትም እየጨመረ መምጣቱ ተጠቅሷል።

ቀደም ሲል ከወታደራዊ አገልግሎት በተለያየ ምክንያት የወጡትን ጨምሮ የሲቪል ዜጎችን በግዳጅ መልሶ ማሰባሰብ የመንግስትን የማያቋርጥ ወታደራዊ ፖሊሲ እና መሰረታዊ የሰብአዊ መብቶችን ችላ ባይነት እንደሚያሳይ በውጭ የሚገኙ የኤርትራ ሕዝብ ተቆርቋሪ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

@sheger_press
@sheger_press


ነባሩ ፓስፖርት ምን ይሆናል?

የኢሜግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ኢ-ፓስፖርት ዛሬ ይፋ አድርጏል::አዲሱ ኢ-ፓስፖርት የአንድን ግለሰብ ባዮሜትሪክ መረጃ ጨምሮ የጣት አሻራዎችን፣ የፊት ለይቶ ማወቂያ እና የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል።ይህን ተከትሎ ታዲያ አሁን አገልግሎት ላይ ያለው ነባሩ ፓስፖርት ምን ሊሆን ነው? የሚል ጥያቄ ያስነሳል::

የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ይፋ እንዳደረገው ነባሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስከሚያበቃ ድረስ ስራ ላይ ይውላል::ቀደም ሲል ፓስፖርት የነበራቸው የፓስፖርቱ የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ መጠቀም እንደሚችሉ ታውቋል::

አዲሱን ፓስፖርት መቀየር የሚፈልጉ ከሆነ ግን አሻራ ከሰጡ በኋላ በአስር ቀናት ውስጥ ፓስፖርቱ በእጃቸው እንደሚገባ ነው የተገለፀው፡፡በሂደት ግን ነባሩ ፓስፖርት በአዲሱ የኢ-ፓስፖርት እንደሚተካ አገልግሎቱ ይፋ አድርጏል::ከዚህ ቀደም ለ125 አመታት ኢትዮጵያ ትጠቀምበት የነበረውን የማንዋል ፓስፖርት ወደቴክኖሎጂ ለመቀየር በማሰብ ነው አዲሱ ፓስፖርት ይፋ የተደረገው::

Via EBC

@sheger_press
@sheger_press


ቀበሌዎች እና ገበሬ ማህበራት ኬላዎችን በማሰር ክፍያ እየጠየቁ ነዉ ተባለ፡፡

አሽከርካሪዎች በአጭር ኪሎሜትር ልዩነት በተደጋጋሚ ኬላዎች ላይ ክፍያ እየተጠየቁ መሆኑንም አስታዉቀዋል፡፡

ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የጣና ከባድ መኪና አሽከሪካሪዎች ማህበር ዋና ጸሃፊ አቶ ሰጡ ብርሃን፤በአማራ ክልል በ2014 ላይ ኬላዎች ተነስተዉ ነበር ያሉ ሲሆን፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ወደ ነበረዉ አሰራር በመመለሱ ቀበሌዎች እና ገበሬ ማህበራት ሳይቀሩ ኬላዎች በማድረግ ክፍያ በመጠየቅ ላይ ናቸዉ ብለዋል፡፡

በአጭር ኪሎሜትር ልዩነት በተደጋጋሚ ኬላዎች ላይ ክፍያ እንጠየቃለን ይህ ለትራንስፖርት አገልግሎቱ ከባድ ተጽዕኖን እየፈጠረ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ይሄ ጉዳይ አሽከርካሪዎች ላይ ከሚያሳድረዉ ጫና ባልተናነሰ በሸማች ማህበረሰቡ ላይ የራሱን ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑንም ነዉ አቶ ሰጡ የተናገሩት፡፡

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ፤ በኢትዮጵያ ኬላ ይነሳ ተብሎ በመንግሥት ደረጃ ቢወሰንም በተለያዩ ምክንያቶች ግን 2መቶ83 ሕገወጥ ኬላዎች በመላዉ አገሪቱ ይገኛሉ ማለታቸዉ ይታወሳል ።

እነዚህ ኬላዎች የምርት ነፃ ዝውውርን በመገደብ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴዉ ላይም  አሉታዊ ጫና ያላቸው መሆናቸዉ በተደጋጋሚ ተነስቷል፡፡

Via ኢትዬ ኤፍ ኤም

@sheger_press
@sheger_press


Update

የኤርትራ ኤምባሲን በተመለከተ

በአዲስ አበባ የኤርትራ ኤምባሲ በተመለከተ የኤምባሲው ጉዳይ ፈፃሚ አቶ ቢኒያም በርሄ "የተባለው ሀሰት ነው "ብለዋል።

አቶ በርሄ "ስለ ኤምባሲ የተነገረው ሀሰት ነው"ከማለት ውጭ ሌላ ምንም ያሉት ነገር የለም።

በአዲስ አበባ የኤርትራ ኤምባሲ ሠራተኞች በስራ ላይ አለመኖራቸው እና ኤምባሲው የመዘጋት እጣ ፈንታ እንደገጠመው ግን የውስጥ መረጃ ምንጮች ጠቁመዋል።

@sheger_press
@sheger_press


አዳዲስ መረጃዎችን ይፈልጋሉ?

በፕሮፌሺናል ጋዜጠኞች ተከፍቶ መረጃዎችን ተከታትሎ በሚዛናዊነት የሚያቀርብ ቻናል ልጠቁማችሁ ፡፡

ተማመኑበት ታተርፉበታላችሁ ተቀላቀሉት
👇👇👇
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0


ወሊሶ በደረሠ የትራፊክ አደጋ የስድስት ሰዎች ሕይወት አለፈ

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወሊሶ ወረዳ በደረሠ  የተሽከርካሪ አደጋ የስድስት ሰዎች ሕይወት አልፏል።

የሠሌዳ ቁጥሩ ኮድ ፣3-83143 ኢቲ የጭነት ተሽከርካሪ ሴኖትራክ ተሽከርካሪ ከጐሮ ወደወሊሶ ሲጓዝ ከወሊሶ ወደ ወልቂጤ አስራ ሰባት ሰው አሣፍሮ  ሲጓዝ ከነበረ የሕዝብ ማመላለሻ ጋር በመጋጨቱ  የሚኒባሱ ሹፌሩን ጨምሮ ወዲያው አራት ሠዎች ህይወት አልፏል።

በሆስፒታል ደግሞ ሑለት ሰው በአጠቃላይ ስድስት ሠው ሲሞት አስራ አንድ ሰው ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል። አደጋው ዛሬ ንጋት ላይ የደረሠ ሲሆ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወሊሶ ቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል በህክምና ድጋፍ ላይ እንደሚገኙ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ኢንስፔክተር ትግሉ ለገሠ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

#ዳጉ_ጆርናል

@sheger_press
@sheger_press


❖ የሚዲያ ንቅናቄ ዘመቻውም እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይም ከቤተ-ክርስቲያን የሚዲያ አካላት ጋር በመነጋገርም ዶክሜንተሪዎችን እንዲሰሩና ምዕመኑ ገዳማዊያኑ ያሉባቸውን ችግሮች በመረዳት ድጋፍ እንዲያደርጉ ለማስቻል ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል፡፡

‹ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል፣በጎነቱንም መልሶ ይክፍለዋል› እንዲል ጠቢቡ ሰለሞን፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድህነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን፣ ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957
ወይም 0938644444



Показано 19 последних публикаций.