❤ የኬልቄዶንን ጉባኤ በሰበሰበ በከሀዲው መርቅያኖስም ዘመን ወደ አገሮችም ሁሉ መልእክተኞችን ላከ ከእርሳቸውም ጋር አንዱን ክርስቶስን ወደ ሁለት ባሕርይ የምትከፍል የረከሰች የሃይማኖቱ ደብዳቤ አለች። ከንጉሥ መልእክተኞች ሦስቱ ወደ ደብረ ዝጋግ በደረሱ ጊዜ ያንን ደብዳቤ ለአባ ለንጊኖስ ሰጡት በዚህ "ጽሑፍ እንድታምኑ በውስጡም እንድትፈርሙ ንጉሥ መርቅያኖስ አዝዞአል" አሉት። አባ ለንጊኖስም "ከቅዱሳን አባቶቼ ጋር ሳልማከር እኔ ምንም ምን መሥራት አልችልም እንድንማከርም እናንተም ከእኔ ጋር ኑ" አላቸውና የቅዱሳን በድኖች ወደ አሉበት ዋሻ ውስጥ አስገባቸውና "የከበራችሁ አባቶቼ ሆይ እናንተ ዐርፈን ተኝተናል አትበሉ እነሆ አንዱን ክርስቶስን ሁለት ባሕርይ የሚያደርግ በውስጡ የተጻፈበትን ይህን ደብዳቤ አምጥተዋልና በቃሉ አምን ዘንድ በውስጡም እፈርም ዘንድ ታዙኛላችሁን ወይም አታዙኝም የምሠራውንም ካልነገራችሁኝ ሕያው እግዚአብሔር ዐፅማቻችሁን ከዚህ ቦታ አወጣለሁ" አላቸው።
❤ ያን ጊዜ ሰዎች ሁሉም እየሰሙ ከአስከሬናቸው "የአባቶቻችንን የሐዋርያትንና የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንቱን የቀናች ሃይማኖትን አትተው ይህንንም የረከሰ ደብዳቤ አትከተል ከአስከሬናችን ቦታ አርቀው እንጂ" የሚል ቃል ወጣ የንጉሥ መልክተኞችም ይህን ነገር ሰምተው እጅግ አደነቁ በላያቸውም ታላቅ ፍርሀት አደረባቸው ወደ ንጉሡም አልተመለሱም ራሳቸውን ተላጭተው መነኰሱ እንጂ እስከ ዐረፉም ድረስ ብዙ ዘመን እየተጋደሉ ኖሩ። የከበረ አባ ለንጊዮስ ያማረ ተጋድሎውን ጨርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ የካቲት 2 ቀን በሰላም ዐረፈ የሕይወት አክሊልንም ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ለጊዮኖስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የካቲት 2 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ለስሒት መኑ ይሌብዋ። እምኅቡዓትየ አንጽሐኒ። ወእምነኪር መሐኮ ለገብርከ"። መዝ 18፥12። የሚበበው ወንጌል ማቴ 5፥32-33።
@sigewe https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886 https://www.facebook.com/profile.php?id=61552828743736&mibextid=ZbWKwL