ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


❤ በየቀኑ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በስንክሳር የሚታሰቡ የቅዱሳን ታሪክ፣ የኢትዮጵያኑ ቅዱሳን በየበዐላቸው ቀን አስደናቂ፣ አስገራሚ ገድላቸው፣ ቃል ኪዳናቸው፣ የቅዱሳን ሰላምታ፣ የየቀኑ የቅዳሴ መልዕክታ፣ የሐዋርያት ሥራ፣ የወንጌል ጥቅስ እና ምስባክ ይቀርብበታል።
❤ የፌስቡክ አድራሻዬ ሊንክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций








"ከአባቶችህ ጋር ትኖር ዘንድ ወደ ገዳምህ ተመለስ" የሚል ቃል መጣ፡፡ በተመለሰም ጊዜ አቡነ አክርስጥሮስ በሰላም ዐረፈ፡፡

✝ ✝ ✝
❤ #ሰማዕቷ_ቅድስት_ጤቅላ፡- ጤቅላ ማለት "ልጅ፣ ለግላጋ" ማለት ነው፡፡ ቅድስት ጤቅላና ከእርሷ ጋር የነበሩ አራት ደናግል ጥር 30 ቀን ፎላ በሚባል ኃጥእ ቄስ እጅ ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ፡፡ ይህም ፎላ የተባለ ቄስ በአመጽ የሰበሰበው ብዙ ገንዘብ እንዳለው በከሃዲው መኰንን ዘንድ ነገሩበት፡፡ ስለዚህም መኮንኑ ገንዘቡን ሁሉ እንዲወርሱ አዘዘ፡፡ ፎላም ወደ መኰንኑ ዘንድ በመሄድ ገንዘቡን ይመልስለት ዘንድ ቢለምነው እምቢ አለው፡፡ ከሃዲው መኰንንም ስለ እነቅድስት ጤቅላ የምግባር የሃይማኖታቸውን ዜናቸውን በሰማ ጊዜ ወደ እርሱ እንዲያመጧቸው አዘዘና አስመጣቸው፡፡ ጌታችንን አስክዶ እምነታቸው አውጥቶ ለጣዖት እንዲገዙ ግድ አላቸው፡፡ እነርሱ ግን በእምነታቸው በጸኑ ጊዜ መኰንኑ ፎላንን ጠርቶ "እነዚህ ደናግል ለፀሐይ ይሰግዱ ዘንድ እነርሱን ብትሸግልልኝ ገንዘብህን መልሼ እሰጥሃለሁ" አለው፡፡ ፎላንም እነ ቅድስት ጤቅላን ይሸነግላቸው ጀመረ፡፡ ደናግሉም "አንተ የሰይጣን ልጅ የክብር ባለቤት ክርስቶስን እንክው ዘንድ እንዴት ትፈትነናለህ? አንተ ቀድሞ መምህራችን የነበርክ ስትሆን" ብለው ዘለፉት፡፡ መኰንኑም ይህን ቃላቸውን ከአንደበታቸው በሰማ ጊዜ በጅራፍ ጽኑ ግርፋትን አስገረፋቸው፡፡ እነዚህ ቅዱሳት ደናግል ግን ስለ ጌታችን ይመሰክሩ ነበር እንጂ ምንም አልፈሩም ነበር፡፡ መኰንኑም ፎላንን "የበከተ ብትበላ ደምንም ብትጠጣ ገንዘብህን እመልስልሃለሁ" ባለው ጊዜ እንዳለው አደረገ፡፡ ዳግመኛም "እነዚህን ደናግል ብትገድላቸው ገንዘብህን እመልስልሃለሁ" አለው፡፡ ፎላም ይህን በሰማ ጊዜ እንደ አስቆሮቱ ይሁዳ ልቡ በገንዘብ ፍቅር ተነድፏልና ልቡናውን አጽንቶ ቅዱሳት ደናግሉን ሊገድላቸው ሄደ፡፡ እነርሱም እንዲህ አሉት፡- "ከሃዲ ሆይ የመድኃኒታችንን የክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን በእጅህ ታቀበን አልነበረምን? ስለ ገንዘብ ፍቅር ብለህ እኛን የክርስቶስን በጎች ልታርድ መጣህን?" እያሉ በገሠጹት ጊዜ ሰልፍ እንደተማረ አርበኛ ሰው ሆኖ በሰይፍ ራስ ራሶቻቸውን ቆረጣቸው፡፡ መኰንኑም የፎላንን ብላሽነትና ድንቁርናውን አይቶ ወዲያው በሰይፍ ገደለው፡፡ ፎላም ገንዘቡን፣ ሃይማኖቱንና ነፍሱን አጣ፡፡ የእነዚህም ቅዱሳት ደናግል ስማቸው መሪ የሆነቻቸው ጤቅላ፣ ማርያ፣ ማርታ፣ አመታ፣ አበያ ሲሆን ጥር 30 ቀን ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጽመው የክብር አክሊልን ተቀዳጅተዋል፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን በአባ ጎርጎርዮስና አቡነ አክርስጥሮስ በቅድስት ጤቅላ በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸው ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር30 ስንክሳር።


✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወይወስዱ ለንጉሥ ደናግል ድኅሬሃ። ወቢጻሂ ይወስዱ ለከ። ወይወስድዎን በትፍሥሕት ወበኃሤት"። መዝ 44፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 5፥1-7፣ 1ኛ ጴጥ 5፥2-5 እና የሐዋ ሥራ 9፥37-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 23፥26-32። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታች የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የማኅበረ ጻድቃን (ዴጔ) በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።


@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

https://www.facebook.com/profile.php?id=61552828743736&mibextid=ZbWKwL


✝ ✝ ✝
❤ #ታላቋ_ሰማዕት_ቅድስት_ኦርኒ፡- ይኽችም ቅድስት ስሙ መርቅያኖስ የሚባል ለጣዖት የሚሰግድ የሮሙ ንጉሥ ልጅ ናት፡፡ እናቷ ግን ክርስቲያናዊት ናት፡፡ ንጉሡ አባቷም እልፍኝ አሠርቶላት በወርቅና በብር አስጊጦ ከ12 ደናግል ጠባቂዎች ጋር ወደዚያ አስገባት፡፡ ከዚያም ልጁ ኦርኒና ደናግሉ ይሰግዱላቸው ዘንድ 17 ጣዖታትን አመጣላቸው፡፡ ቅድስት ኦርኒም ሰባት ዓመት በዚያ ስትቆይ ወደ እግዚአብሔር ከመጸለይ አላቋረጠችም ነበር፡፡

❤ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ዐይኖቿን አቅንታ ስትጸልይ በአፏ የዘይት ቅጠል የያዘች ርግብን አየች፡፡ ርብቧም ቅጠሉን ከማዕዷ ላይ ጥላው ወጣች፡፡ ዳግመኛም ወደ ቅድስት ኦርኒ ወደ ምዕራብ ስትመለከት በአፉ ከይሲ የያዘ ቁራ መጥቶ በመዕዷ ላይ ጥሎት ሄደ፡፡ መምህሯም በመጣ ጊዜ ያየችውን ራእይ ነገረችው፡፡ እርሱም ሲተረጉምላት "ርግብ የጥበብ ነገር ነው፣ የዘይቱም ቅርንጫፍ በጥምቀት የሚገኝ ክብር ነው፣ ቁራውም ንጉሥ ነው፣ ከይሲውም መከራ ነው፣ አንቺም በርቺ ጠንክሪ በክርስቶስ ስም መከራ ትቀበይ ዘንድ አለሽና የሕይወትንም አክሊል ትቀበያለሽ" አላት፡፡

❤ ቅድስት ኦርኒ ዕድሜዋ ከፍ ሲል ወላጆቿ ከታላላቅ ወገን ለሆነ ለከበረ ሰው ሊድሯት አሰቡ እርሷ ግን "ሰባት ቀን ታገሱኝ" አለችና ወደ ፈቀደው መንገድ እንዲመራት እግዚአብሔርን በጸሎት ጠየቀች፡፡ በዚህም ጊዜ የታዘዘ መልአክ መጥቶ "ኦርኒ ሆይ በርቺ፣ ኃይልንም ልበሺ፣ ሐዋርያው ጢሞቴዎስ ወዳንቺ መጥቶ የወንጌልን ትእዛዝ ያስተምርሻል፣ ያጠምቅሻል" አላት፡፡ ወዲያውም ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስ መጥቶ የቤቷን ግድግዳ ሰንጥቆ ገብቶ ሁሉንም ነገር አስተማራት፡፡ ከቆመበትም መሬት ውኃ አፍልቆ በውኃው ላይ ጸልዮ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃትና ከእርሷ ዘንድ ሄደ፡፡

❤ ከዚህም በኋላ ቅድስት ኦርኒ ተነሥታ የአባቷን ጣዖቶች ሰባበረቻቸው፡፡ አባቷም መጥቶ ይህን ባየ ጊዜ በንዴት ወዲያው ሊድራት ሞከረ፡፡ እርሷ ግን "እኔስ ለሰማያዊው ሙሽራ ለክርስቶስ ተጠርቻለሁ፣ በስሙም ተጠምቄያለሁ" አለችው፡፡ ንጉሡ አበቷም የቅድስት ኦርኒ ንግግር በሰማ ጊዜ ታላቅ ቁጣን ተሞልቶ ከእልፍኟ እየጎተተ አወረዳት፡፡ ክርስቲያናዊት እናቷም ይህንን ስታይ እያለቀሰች በራሷ ላይ አመድ ነሰነሰች፡፡ አባቷም ታስረው ይቀለቡ የነበሩ 4 ኃያላን ፈረሶችን አምጥቶ የቅድስት ኦርኒን ፀጉር ከጅራታቸው ጋር አሥሮ እንዲጎትቷትና ሰውነቷ ተቆራርጦ እንዲያልቅ ፈረሶቹን አስሮጣቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አንዱ ፈረስ ሲሮጥ ሰንሰለቱን በጥሶ ሲያመልጥ የንጉሡን ቀኝ እጅ ቆረጠውና አባቷ ወዲያው ሞተ፡፡ የከበረች ቅድስት ኦርኒ ግን ተነሥታ ጸሎት በማድረግ ንጉሥ አባቷን ከሞት አስነሣችው፡፡ የተቆረጠ እጁንም እንደቀድሞው አድርጋ መለሰችለት፡፡ ሕዝቡም ይህንን ድንቅ ተአምር አይተው ከንጉሡ አባቷ ጋር በጌታችን አምነው ተጠመቁ፡፡ በዚህም የቅድስት ኦርኒ ተአምር ምክንያት የተጠመቁት ሰዎች ቁጥር ከሰላሳ ሺህ በላይ ነው፡፡

❤ ንጉሥ ዳኬዎስም ይህን ተአምርና የቅድስት ኦርኒ ዜና ስለሰማ ወደዚያች አገር ገባ፡፡ የከበረች ቅድስት ኦርኒንም ይዞ በራሷ ፀጉር ሰቀላትና አሠቃያት፡፡ ዳግመኛም መርዛማ እባቦችና ጊንጦች ወደተሞሉበት ጉድጓድ ውስጥ ጨመራት፣ ነገር ግን መርዛማ እባቦቹና ጊንጦቹ በእግዚአብሔር ኃይል ሁሉም ወዲያው ሞቱ፡፡ ዳግመኛም ንጉሥ ዳኬዎስ በመጋዝ ይሰነጥቋት ዘንድ አዘዘ፤ እንዳዘዘውም ሊያደርጉባት ሲሉ መጋዙ ተሰበረ፡፡ ንጉሡም ወዲያው በሞት ተቀሰፈ፡፡ የዳኬዎስ ልጅም ይህን ሰምቶ በታላቅ ሆኖ መጣና አገሪቱን ከበባት፡፡ ቅድስት ኦርኒንም ይዞ የተሳሉ ወስፌዎችን በእጆቿና በእግሮቿ እንዲሰገሰጉ አደረገ፡፡ በጀርባዋም ላይ አሸዋ የተመላ ዳውላ አድርገው ከአራት ፈረሶች ላይ አስረው ሥጋዋ ተበጣጥሶ እስኪጠፋ ድረስ ፈረሶቹን አስሮጧቸው፡፡ በዚህም አልቻሏትም፤ የታዘዘ መልአክ መጥቶ እርሷ ከፈወሳት በኋላ የዳኬዎስን ልጅ በጦር ወግቶ ገደለው፡፡

❤ የከበረች ቅድስት ኦርኒም ሃይማኖትን እያስተማረች፣ ድውያንን እየፈወሰች፣ ሙታንን እያስነሣች በታላቅ አገልግሎት ተቀመጠች፡፡ ከዚህም በኋላ 4ኛ ንጉሠሥ መጣና የእርሷን ዜና ሰምቶ ወደ እርሱ አስመጣት፡፡ ለጣዖትም እንድትሰግድ ባስገደዳት ጊዜ ጣዖቱቹንና እርሱን ረገመቻው፡፡ ንጉሡም በዚህ ተናዶ ከእሳት ውስጥ ጨመራት፡፡ እርሷም ከእሳቱ ውስጥ ሆና ስትጸልይ የታዘዘ መልአክ መጥቶ እሳቱን አቀዝቅዞ በሰላም አወጣት፡፡ ከእሳቱም ከወጣች በኋላ የንጉሡን ጣዖታት ዳግመኛ ዘለፈች፡፡ ንጉሡም በእርሷ ላይ የተፈጸመውን ታላቅ ተአምር አይቶ ቤታችን አመነ፡፡ አምስተኛውም የፋርስ ንጉሥ በመጣ ጊዜ ቅድስት ኦርኒን ይዞ በእጁ በያዘው ጦር ወጋትና ሞተች፡፡ የታዘዘ መልአክም መጥቶ ከሞት አስነሣትና ዳግመኛ በጌታችን ስም ማስተማር ጀመረች፡፡ ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ተነጥቃ ወጣች፡፡ ማኅበርተኞቿ የሆኑ 13 ሺህ ሰዎች በዚሁ ዕለት በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ኦርኒ በጸሎቷ ይማረን በከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

✝ ✝ ✝
❤ #የመለኮትን_ነገር_የሚናገር_አቡነ_ጎርጎርዮስ፡- በሌላም በኩል "ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ" እየተባለም ይጠራል፡፡ ሀገሩ ቂሳርያ ነው፡፡ በመጀመሪያ የሕግ ባለሙያ የነበረ ሲሆን በኋላ ግን የቍስጥንጥንያ ሊቀጳጳስ ሆኖ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በሐዋርያነት አገልግሏል፡፡ በደራሲነቱ ምድራውያን መላእክት ከተሰኙት ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ነው፡፡ የአምላክን ሰው መሆንና ምሥጢረ ሥላሴን እጅግ አስፍቶና አራቆ ያስተማረ ከመሆኑም በላይ ‹‹ዳግማዊ ዮሐንስ ነባቤ መነኮት›› ተብሎ እስኪጠራ ድረስ በነገረ መለኮት የተራቀቀ ታላቅ ሊቅ መምህር ነው፡፡ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙን የማይጠቅስ መጽሐፍና መምህር የለም፡፡ ሃይማኖተ አበው አጥብቆ የሚጠራው የቤተ ክርስቲያናችን መመኪያ ነው፡፡ የአርመንን ኦርቶዶክስ ያቀና ሲሆን መንበሩን የኖኅ መርከብ ባረፈችበት አራራት ተራራ ላይ ነው የሠራው፡፡

✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_አክርስጥሮስ፡- ይኽም ቅዱስ አባት በዮርዳኖስ በረሃ የሚኖር ታላቅ ተጋዳይ ነው፡፡ ከመነኮሳቱም አንዱ በፊቱ እየሰገደ ሥራውን ይገልጥለት ዘንድ በእግዚአብሔር ስም አማለው፡፡ ሽማግሌው አክርስጥሮስም እንዲህ ብሎ መለሰለት፡- "ልጄ ሆይ! ጎልማሳ ሆኜ ሳለ በመነኰስኩ ጊዜ በዚያ እጸልይ ዘንድ በሌሊት ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ መቅደስ እሄድ ነበር፡፡ 12 ደረጃዎችም አሏት፣ በእንዳንዱ ደረጃ መቶ መቶ ስግደቶቸን እሰግዳለሁ፡፡ ደወልንም በሚደውሉ ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመግባት ከወንደሞች ጋር የማኅበሩን የጸሎት ሥርዓት እፈጽማለሁ፣ እንዲህም በማድረግ 10 ዓመት ኖርኩ፡፡ ከሌሊቶቹም በአንዲቱ የተለመደ ጸሎቴን ከፈጸምኩ በኋላ ልቡናዬ በተመስጦ ተማረከ፡፡ ነጫጭ ልብሶችን የለበሱ ሁለት ሰዎች መቅረዞችን ሲያበሩ እኩሌቶቹ ሲበሩ እኩሌቶቹ ሲጠፉ አየሁ፡፡ እኔም "ይህ ሥራ ምንድነው?" አልኳቸው፡፡ እነዚያም አባቶች "ባልጀራውን የሚወድ መቅረዙ ይበራለታል" አሉኝ፡፡ እኔም ደግሙ "መቅረዜ የትኛው ነው?" አልኳቸው፡፡ እነርሱም "ሂድ ከወንድሞችህ ጋር ተፋቀር፣ እኛ እናበራልሃለን" አሉኝ፡፡ በነቃሁም ጊዜ ማንንም አላገኘሁም" ብሎ ለጠየቀው መነኮስ ነገረው፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ አክርስጥሮስ ብቻውን ወደ ደብረ ሲና ሄዶ በዚያ እየተጋደለ 50 ዓመት ኖረ፡፡ ወደ እርሱም


❤ ጌታችን "እግድያስ እኔ የጠጣሁበት ዋንጫ ትቅረብና ትመስክርብኝ" አለው። በዚህ ተስማምተው ሙሴው ሄዶ አንድ ሽራፊ ዋንጫ አምጥቶ "በዚህ ነበር የሚሰጠውና የሚጠጣው" ብሎ አቀረበ። ዋንጫዋም ከተቀመጠችበት አንድ ክንድ ከስንዝር ተነስታ "ዓለማትን የፈጠረ አምላክ ምስክሬ ነው እኔ የያዝኩትን የወይን ጠጅ ዕቃ ሙሴም በእጆቹ አልያዘኝም በከንፈሩ አልካኝም በሌሎች ሰዎች እጅ ግን ተይዤ ያየን ነበር" አለች። ያን ጊዜ ሰውም እንስሳትም እፀዋትም ሁሉ ፆራ (ተሸክማ) የምትሔድ ሙሴን ልትጾር (ልትሸከመው) አልቻለችም። እንደ ዳታ አቤሮን ምድር ተከፍታ ከነልጁ ጋር ዋጠቻቸው። ማኅበረ ጻድቃንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ተረድተው እንደገና ከእግሩ ወድቀው ይቅርታ እንዲያደርግላቸው ለመኑት ቀኑም ጥር29 ነበር። ጌታችን ኢየሱስ ክስቶስ ይቅርታ ካደረገላቸው በኋላ "ስማችሁን የጠራ በስማችሁ ተዝካር ያወጣ በስማችሁ ድሆችን የረዳ፣ ያለበሰ፣ ያጎረሰ፣ የሰጠ፣ የመፀወተ፣ ቤተ ክርስትያኖች ሆነ የሠራ ያሠራ፣ እስከ14 ትውልድ ድረስ ምሬላችኋለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጣቸው። ይህችን ቦታችሁ መጥቶ የሳመ ኢየሩሳሌም እንደሳመ አድርጌላችኋለሁ" አላቸው።

❤ በኦሪት ኄኖክና፣ ዕዝራና ኤልያስ በሐዲስ ኪዳን እነ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድና በየጊዜው የሚሰወሩ ቅዱሳን ግልጽ ነውና እንዚሁም ጌታችን እነዚህ የማኅበረ ደጔ ጻድቃንም ከሞት ተሰወሩ ብሎ በበነገታው ጥር30 ቀን ሠውሮአቸዋል። በዚህም መሠረት ይህ ታላቅ በዓል ሆኖ ዛሬም በየዓመቱ ጥር30 ሲከበር ይኖራል። በገዳሙ ውስጥ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው የተፈጸመውን ነገር በውል የሚያስረዱ በዐይን የሚታዩ በእጅ የሚዳሰሱ በጌታችን ተአምራት የተደረገባቸው ቅርሶች በክብር ተጠብቀው ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ፡-

1.ክንድ ከስንዝር ወደላይ ተነሥታ በሰው አንደበት በመመስከር ጌታችን በእርሷ እንዳልጠጣባት የመሰከረችው ዋንጫ (ጽዋ)

2.ጌታችን የተቀመጠባትና ያስተማረባት ድንጋይ ከነምልክቷ።

3.ምስዋሮም የሚባል ጻድድቃኑ የተሰወሩበትን ሥፍራ።

4.ጌታችን ከድንጋይዋ ላይ ሁኖ ወርቅ ዘንጉን ወርውሮ ያፈለቀውና "ማየ ዮርዳኖስ" ይሁን ብሎ የሰየመው ጠበል።

4.ቅዱሳኑ ሲወቅጡበት የነበረው የድንጋይ ሙቀጫ።

5.በማህበራቸው ጊዜ ሲደግሱባቸው የነበሩ የድንጋይ ገበታዎች።

7.ቅዱሳኑ ከሀገራቸው ከሮም ያመጡት ባለመስታወት ቋሚ ዕፀ መስቀል።

8.ርዕሰ ዮሐንስ የሚባል ነገሥታት ከነዘውዳቸው ጳጳሳት ከነአክሊላቸውና ከነመስቀላቸው በዚያን ጊዜ የተሳሉበት ሥዕል።

9.ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ በማኅበረ ጻድቃን ዴጔ ሆኖ ያስተማረበትና የጠመቀበትን በሥዕል የሚያሳይ።

10.ይህ ገዳሙ በዐፄ ካሌብ ዘመነ መንግሥት እንደተገደመና የገደሙትም ራሳቸው መሆኑን በአክሱም መጽሐፍ ክብረ ነገሥት ላይ ተጽፎ እንደሚገኝ በታሪኩ ተረጋግጦ ተላልፎልናል፡፡ ምንጭ፦ የማኅበረ ጻድቃን ዴጔ ጥንታዊ ገዳም ታሪክ ባጭሉ ከሚለው መጽሐፍ።



✝ ✝ ✝
❤ #የከበሩ_ቅዱሳን_ደናግል_ጲስጢስ_አላጲስና_አጋጲስ_እናቸው_ቅድስት_ሶፍያ፦ እናታቸው ከአንጾኪያ ከከበሩ ወገኖች ውስጥ ናት። እነዚህንም ሦስት ልጆች በወለደቻቸው ጊዜ በእሊህ ስሞች ጠራቻቸው ትርጓሜያቸውም ሃይማኖት ተስፋ ፍቅር ነው የራሷም ስም ትርጓሜ ጥበብ ማለት ነው። ጥቂትም በአደጉ ጊዜ ወደ ሮሜ ከተማ ወስዳ በጎ አምልኮን እግዚአብሔርን መፍራትን የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት አስተማራቻቸው በከሀዲውም የሮሜ ንጉሥ በአርያኖስ ዘንድ ወሬያቸው ተሰማ ወደ ርሱም ያመጡአቸው ዘንድ አዘዘና አመጡአቸው እናታቸውም በማስተማር ትመክራቸውና ታጸናቸው ነበር። እንዲህም ትላቸዋለች "ልጆቼ ተጠበቁ የዚህን የኃላፊውን ዓለም ክብር በማየት ልባችሁ እንዳይደክምና ከዘላለማዊ ክብር እንዳትርቁ ከሙሽራው ከክርስቶስ ጋር ሁናችሁ ወደ ሰማያዊ ሠርግ እንድትገቡ ጠንክሩ"። ዕድሜያቸውም የታላቂቱ ዐሥራ ሁለት የሁለተኛዪቱ ዐሥር የሦስተኛዪቱ ዘጠኝ ነው።

❤ እናታቸው ወደ ንጉሥ በአቀረበቻቸው ጊዜ ታላቂቱን ጲስጢስን "እኔን ስሚ ከቤተ መንግሥቴ ታላላቆች ለአንዱ አጋባሻለሁ ብዙ ስጦታም እሰጥሻለሁ ለአጵሎን ስገጂ" አላት። እርሷም እርሱንና የረከሱ አማልክቶቹን ሰደበች እርሱም ተቆጥቶ በብረት ዘንጎች እንዲደበደቧት ጡቶቿንም እንዲቆርጡ እሳትንም ከብረት ምጣድ በታች በማንደድ ባሩድ፣ ሙጫ፣ ሰሊጥን በውስጡ አድርገው እጅግ አፍልተው ወደዚያ ይጨምሩዋት ዘንድ አዘዘ። በጨመሩዋትም ጊዜ እየፀለየች በብረት ምጣዱ ውስጥ ቆመች ከቶ እሳት አልነካትም። የምጣዱም ግለት ጸጥ ብሎ እንደ ጥዋት ጊዜ ጤዛ ቀዝቅዛ ሆነ ከዚያ ያሉ ሰዎችም አድንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑት ብዙዎችም በክብር ባለቤት እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ራሶቻቸውንም ቈርጡዋቸውና በሰማዕትነት ሞቱ።

❤ ከዚህም በኋላ የቅድስት ጲስጢስን ራስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ምስክርነቷንም ፈጽማ የምስክርነት አክሊልን ተቀበለች እናቷም ሥጋዋን አንሥታ ወሰደች። ዳግመኛም ሁለተኛዋን አላጲስን አቀረቧትና ደበደቧት ጽኑዕ ግርፋትንም ገረፏት ከጋለ ብረት ምጣድ ውስጥ ጨመርዋት በዚያንም ጊዜ ቀዝቅዞ እንደ ጥዋት ጤዛ ሆነ ንጉሡም ከዚያም እንዲአወጧትና ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ምስክርነቷንም አድርሳ በመንግሥተ ሰማያት የሕይወት አክሊልን ተቀበለች እናቷም ሥጋዋን ወሰደች።

❤ ቅድስት ሶፍያም ከሥቃይ የተነሣ እንዳትደነግጥ ስለ ልጅዋ ስለ አጋጲስ ትፈራ ነበር ታጽናናትና እንድትታገሥ ታደርጋት ነበር በዚያንም ጊዜ ወስደው ከመንኰራኩር ውስጥ ጨመርዋት እግዚአብሔርም መልአኩን ልኮ ያንን መንኰራኲር ሰበረው እርሷም በደኅና ወጣች ዳግመኛም እሳትን አድደው ከውስጡ እንዲጥሏት አዘዘ እርሷም ፊቷን በመስቀል ምልክት አማትባ ወደሚነደው እሳቱ ተወርውራ ገባች በዚያንም ጊዜ እሳቱ እንደ ጥዋት ውርጭ የቀዘቀዘ ሆነ ከዚያ ያሉትም ሰዎች ብርሃን የለበሱ ሁለት ሰዎች ከነጫጭ ልብሶች ጋር ሲጋርዷዋት አይተው እጅግ አደነቁ ብዙዎችም በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ራሶቻቸውንም ቆርጠዋቸው በሰማዕትነት ሞቱ ያቺንም የዘጠኝ ዓመት ልጅ የከበረች አጋጲስን ራሷን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ። ምስክርነቷንም ፈጸመች ሁሉም የማያልፍ የማይጠፋ ሰማያዊ መንግሥትን ወረሱ።

❤ የከበረች ሶፍያም የሦስት ልጆቿን ሥጋቸውን ወስዳ ገነዘቻቸው ወደ ከተማውም ውጭ አድርሳ በዚያ ቀበረቻቸው በሦስተኛውም ቀን ወደ መቃብራቸው ሔዳ አለቀሰች ነፍሷንም ይወስድ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነች ልመናዋንም ተቀብሎ ነፍሷን ወሰደ ምእመናን ሰዎችም መጥተው ገንዘው ከልጆቿ ጋር ቀበሩዋት። በከሀዲው ንጉሥ ላይ ግን እግዚአብሔር ጭንቅ የሆነ ደዌ ላከ ዐይኖቹም ፈረጡ ዐጥንቶቹም እስከማሚታዩ ሥጋው ሁሉ ተሠነጣጠቀ እጆቹም ተቆራረጡ ከእርሱም ደምና መግል ፈሰሰ ትልም ይወድቅ ነበር ሁለመናውም ተበላሽቶ በክፉ ሞት ሞተ። ስለ እነዚያ ደናግል ጌታ ተቀበቅሎታልና። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ደናግላን ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።


❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤

❤ #ጥር ፴ (30) ቀን።

❤ እንኳን #ለማኅበረ_ዴጔ_ለሦስት_ሺህ_ጻድቃን እንደ ቅዱሳን ኄኖክና ዕዝራ ከዚህ ዓለም ከሞት ለተሰወሩበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው፣ ለከበሩ ደናግል #ለቅድስት_ሶፍያ_ልጆች ለቅድሳት #ለጲስጢስ_ለአላጲስና_ለአጋጲስ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ ስሙ መርቅያኖስ ለሚባል ለጣዖት ለሚሰግድ ለሮሜ ንጉሥ ልጅ ለከበረች #ለቅድስት_ኦርኒ ሰማዕትነት ለተቀበለችበት ለዕረፍቷ በዓል፣ ለከበረች #ቅድስት_ጤቅላ ከእርሷ ጋር ከሚኖሩ አራት ደናግል ጋር ፎላ በሚባል ኃጥእ ቄስ እጅ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓልና ተጋዳይ ለሆነ ለመነኰስ ለከበረ #አባ_አክርስጥሮስ ለዕረፍት በዓልና ለመለኮትን ነገር ለሚናገር ለቅዱስ ጎርጎርዮስ ለመታሰቢያ በዓሉ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስክድርያ አገር አርባ ሰባተኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_ሚናስ ዕረፍትና #ከቅድስት_ኦርኒ_ማኅበር ከሆኑ #ከዐሥራ_ሦስት_ሺህ_ሰዎች በሰማዕትነት ከዐረፉ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


✝ ✝ ✝
❤ #ማኅበረ_ዴጔ፦ ማለት የደጋጎች አገር ማለት ነው። የደጋጎች አገር የተባለበት ምክንያት ብዙ ሺህ ቅዱሳን ተሰብስበው ስለሚኖሩበት ነው፡፡ ገዳሙ የሚገኘው በትግራይ ክልል በአክሱም አውራጃ ከአክሱም ከተማ ወደ ደቡብ ምዕራብ በሚወስደው መንገድ ዐሥራ ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ ነው፡፡ ከገዳሙ ተያይዞ የተላከልን ዘገባ እንደሚያስረዳው ቤተ ክርስትያኑ በ39ዓ.ም እንተተተከለ በግልፅ ያስረዳል። ይኸውም መጽሐፈ ሱባኤ በተባለው በመሪ ኤ.ኤም የተዘጋጀው መጽሐፍ ከምዕራፍ 11 በገጽ 132 ላይ አቴዥን ሕንደቼ ንግሥት ነገሥታት ዘኢትዮጵያ ሆና በነገሠች በ39ዓ.ም በአንደኛው ዓመተ መንግሥትዋ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በ40ዓ.ም ማኅበረ ጻድቃን ዴጔ ገብቶ ሲያስተምርና ሲያጠምቅ ሰምታ መኳንንትና መሳፍንትን አሰከትላ መርዌ ወረደች ይላል።

❤ በዚህም ንግሥቲቱ ቅዱስ ማቴዎስ አግኝታ "ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር አብ የባሕሪ ልጅ መሆኑ አውቃለሁ ይሁን እንጂ ዳግመኛ ከእግዚአብሔር ከድንግል ማርያም መወለዱን አላውቅም ነበር አሁን ግን በትምህርትህ መንፈስ ቅዱስ ስለ ገለጸልኝ አጥምቀኝ" አለችው። ቅዱስ ማቴዎስም ንግሥቲቱን ካጠመቀ በኋላ ቀጥሎ መኳንንቱን፣ መሳፍንቱን የጦር ሠራዊቱን ሁሉ አጥምቋቸዋል ይላል፡፡ አያይዞም ንግሥቲቱ ቅዱስ ማቴዎስን ይዛው ወደ አክሱም ተመለሰች፣ ልጆችዋንና ቤተሰቦችዋንም አስጠመቀች እንዲሁም አክሎስ የሚባል ባልዋም አምኖ ተጠመቀ። ቅዱስ ማቴዎስ ከዚህ በፊት የነባቡና የናግራንን ህዞቦች አጥምቆ ከዚህም በኋላ የጻድቃንን ዴጔ ማህበር አቋቁሞ በጌታችን ስም በየወሩ በ29ቀን እየተሰበሰቡ ጽዋ እንዲጠጡ አድርጓቸው ወደ ኢየሩሳሌም ሄዷል፡፡

❤ በ365ዓ.ም በአስፍሕ ወልደ አብርሃም ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ዘመነ መንግሥት "ሮምያ" ከምትባል መንደር ቅዱሳን "ስለ ጽድቅ ብለው የሚሰደዱ ብፁአን ናቸው መንግሥተ ሰማያት የነርሱ ናትና" ያለውን ዳግመኛም "አባቱንና እናቱን ሚስቱንና ልጆቹን ያልተወ ሊያገለግለኝ አይችልም" ብሎ ጌታችን የተናገረውን አስበው ቅዱሳን የዚህም ዓለም ጣዕም ጥቅም ንቀው አገራቸውን ትተው መንነው ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ነበሩ፡፡ እነዚህም ቅዱሳን በአክሱም ከተማ በስተሰሜን በሐውልቱ ጀርባ ቤተ ቀጠንት በሚባል ስፍራ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህል እንደ ተቀመጡ በዚያም ምቾትና ድሎት ስለተሰማባቸው "ለዚህ ለዚህማ አገራችንን ለምን ትተን መጣን? ስለዚህ ሱባዔ ገብተን በጾም በጸሎት ተወስነን የምንሄድበትን ቦታ በረከተ ነፍስ የምናገኝበትን ስፍራ እግዚአብሔር እንዲያሳየን እናመልክት" ብለው ሱባዔ ገቡ ጾም ያዙ፡፡ ከሱባዔውም በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልጻላቸው ግማሾቹን እያንዳንዳቸው የሚኖሩበትን በዓት አመልክታቸው፣ በዚያም በጾምና በጸሎት ጸንተው እንዲኖሩ ነገረቻቸው፡፡ ሦስት ሺህ ያህሉን ደግሞ ከላይ ወደጠቀስነው ሥፍ ሄዱ፡፡ ከእነርሱ የተቀሩት ደግሞ ወደ ቆየፃ ሓባር፣ ተድባ፣ አኮርየን፣ ተንስሓ፣ ደብረ አንሳ ወደ ተባሉ ቦታዎች ሄደዋል፡፡ ተጨማሪ ሦስት ሺህ የሚሆኑት ደግሞ እዚያ ከነበሩት ጋር ተደመሩ፡፡

❤ ከዚህም በኋላ እነዚህ ቅዱሳን "ከሁሉ ፍቅር ይበልጣል" የሚለውን ጠብቀው በእምነት በፍቅር በአንድነት ጸንተው በየሣምንቱ እሁድ እሁድ ተዝካረ ሰንበትን ጠብቀው ማኅበር ሲጠጡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅራቸው አይቶ በአምሳለ ነዳይ ደሀ መስሎ በመካከላቸው ተገኘ። ከነርሱ ጋርም አንድ ማኅበርተኛ ሁኖ እንዲታወቅ ጠየቃቸው፤ እነርሱም ፈቀዱለት አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህልም ከነርሱ ጋር ሳይለይ ቆየ በዚሁ ጊዜ "ለእኔም ተራ ስጡኝ እንደ አቅሜ ዝክር ላውጣ"አላቸው። እነርሱም ግን "አይሆንም አንተ ደሀ ነህ ከኛ ጋር ሁነህ በዓሉን አክብር እንጂ ምን አለህ እና ነውን" አሉት፣ እርሱም "አይሆንም ስጡኝ እንጅ አላቸው" እርሱም ካልክማ ብለው ቀን ወስነው ሰጡት ቀኑም ጥር29 ነበር። ከማኅበርተኞቹ መካከል "ሣይዳን" የሚባል ሰው ነበር፡፡ ይህም አሳላፊ ወይም ሙሴ ማለት ነው። ይህም ሰው እንግዳና ድሀ ሰው ፈጽሞ አይወድም ነበር፣ ጌታችንም ከማኅበርተኞቹ መካከል ሲገኝ ደሀ መስሎ ስለ ነበር በጣም ይጠላው ነበር።

❤ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ከነርሱ ጋር ሲቀመጥም አንድ ቀን ስኳን አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ ሰጥቶት አያውቅም ነበር፣ ሆኖም የጌታችን ማኅበር ደረሰ፣ እንደ ማኅበሩ ሥርዓት አሳላፊው ጠርቶ "ጋኖችን እጠብልኝ አለው" አሳላፊው "ቤትህ የማይታወቅ ከየት አምጥተህ ማኅበር ልታደርግ ነው" ብሎ አናንቆ ተመለከተው ጌታም አንድ እረኛ ጠርቶ "አንተ ልጅ ከብቶችህን እኔ እጠብቅልሃለሁና ውኃ አምጣልኝ" አለው፣ ልጁም ገምቦውን ይዞ ትንሽ ወጣ እንዳለ ጌታ ዘወትር ከሚቀመጥበት ድንጋይ ላይ ሆኖ ዘንጉን ወደ ልጁ አቅጣጫ ወረወረው፣ ዘንጉንም ከልጁ ፊት ሂዶ ተተከለ ልጁንም ጠርቶ ዘንጉንም ንቀለው አለው ልጁም ዘንጉን ቢነቅለው ውኃ ፈለቀ "ከርሱ ቀድተህ አምጣልኝ" አለው። ልጁም ከዚህ ውሃ ቀድቶ አመጣለት ጌታም ልጁ ባመጣው ውኃ ጋኖቹ ቀድቶ አጠባቸው፣ በበዓሉ ቀን ማኅበርተኞቹ ምን ሊያበላን ነው ምን ሊያጠጣን ነው ሳይሉ ሁሉም ተሰበሰቡ ጌታችንም በፊታቸው ጋኖቹን ቢባርካቸው የወይን ጠጅ ሞልተው ተገኙ። ቀድቶ ቢሰጣቸውና ቢቀምሱትም በጣም ግሩም ጣፍጭ ስለነበር እጅግ አደነቁ፣ እነርሱም ጌታችን ከጻድቃን አንዱ ስለመሰላቸው ከእግሩ ላይ ወድቀው "እስካሁን ድረስ ሳንበድልህ አልቀረንምና ይቅር በለን" ብለው ለመኑት ተነሡ ብሎ ካስነሳቸው በኋላ "እናንተ አልበደላችሁም፡ በደለኝ አሳላፊያችሁ ነው አንድ ቀን ስንኳ አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ አልሰጠኝምና አፋራርዱኝ" አላቸው። ነገር ግን ሙሴው የማያፍር ደፋርና ርጉም ስለነበር ሲጠይቁት "ይህ ሰው ጌታችንን በልቶ አልበላውም ጠጥቶ አልጠጣሁም የሚል ስለሆነና ስለማይጠግብ ነው እንጂ እንዲያውም ለናንተ አንድ አንድ ዋንጫ ሲሰጣችሁ ለእርሱ ሁለት ሁለት ነበር የሚሰጠው" ብሎ የሐሰት ቃል መለሰ።




❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤

                          ✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለጸአተ_ነፍስከ_እምነ_ኀላፊት_ንብረታ። ኀበ ተደለወ ላቲ ዘኢየኀልፍ ሕይወታ። #ገብረ_ናዝራዊ ሰብሑ ወዘመሩ በበጾታ። ለንጽሕት ነፍሰ ዚኣከ ኀበ ሰማያት ሑረታ። #ሰራዊተ_ንጉሥ_ወልድ ዘሀሎ ውስቴታ"። ትርጉም፦ ከዚህ ከሚያልፍ መኖሪያዋ ወደማያልፍ ሕይወትና ወደተዘጋጀለት የክብር ቦታ #ለነፍስህ_መውጣት_ሰላምታ_ይገባል፤ አባታችን #አቡነ_ገብረ_ናዝራዊ_ሆይ! በውስጥ ያሉ #የንጉሥ_እግዚአብሔር_ወልድ_ሰራዊቶች (#መላእክት) ወደ ሰማይ በመሔዷ #ለንጽሕት_ነፍስህ በየወገኑ ፈጽመው አመሰገኑ። መልክዐ አቡነ ገብረ ናዝራዊ።
 

@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

https://www.facebook.com/profile.php?id=61552828743736&mibextid=ZbWKwL


ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ በበዐሉ ላይ ያስተማሩት ትምህርት።


አቡነ ታዴዎስ እና አቡነ ማትያስ ሰማዕትነት የተቀበሉበት ገደል የጠበል ቦታ።




❤ #በኢቲሳ_ደብረ_ጽላልሽ አካባቢ በሚገኘው #በምዕራፈ_ቅዱሳን_አቡነ_ታዴዎስ_ገዳም_ዛሬ_ጥር_ 29_ቀን_2017 ዓ.ም የአቡነ ታዴዎስ የአቡነ ማቲያስ ሰማዕትነት የተቀበሉበት የዕረፍት በዓል ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ከተለያዩ ከገዳማት የመጡ መነኰሳትና መነኰሳያት፣ የገዳማት፣ አድባራት አስተዳዳሪዎችና ከኢትዮጵያ ከአራቱም አቅጣጫ የተገኙ እጅግ በርካታ ምዕመናን ምዕመናት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከበረ። አምላከ አቡነ ታዴዎስ ወአቡነ ማትያስ ሆይ! ሳይገባን ከበዐልህ በረከት እንድንሳተፈ ስላደረከን ክብር ምስጋና ይግባህ። በአገራችን ኢትዮጽያ ያለው የእርስ በእርስ ጦርነት አስወግደህ ሰላም፣ ፍቅር፣ አድነትንና መተሳሰብን ላክልን። ለግንቦት በዓልህ በሰላምና በጤና አድርሰን።


@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

https://www.facebook.com/profile.php?id=61552828743736&mibextid=ZbWKwL




❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤

                          ✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለጸአተ_ነፍስከ እምቤተ ሰብእና ምድራዊ። ውስተ ቤተ ሰማይ ትባእ ለዓለም ዓለም ሀላዊ። #ወሬዛ_ሃይማኖት_ታዴዎስ እንዘ በምግባር አረጋዊ። እስመ ፈድፍደ ንጹሕ ሥጋከ እምንጹሐን ኵሉ ሥጋዊ። #አባ_በኪዳንከ ይትዌከል ዘማዊ። #መልክዐ_አቡነ_ታዴዎስ።


@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

https://www.facebook.com/profile.php?id=61552828743736&mibextid=ZbWKwL





Показано 17 последних публикаций.