Фильтр публикаций


ካርቱም ውስጥ ገበያ ላይ በተፈጸመ ጥቃት 56 ሰዎች ሲገደሉ፣ ከ150 በላይ ቆሰሉ።

በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም በሚገኘው አትክልት ገበያ ላይ በተፈጸመ የአየር ላይ ጥቃት 158 ሰዎች ቆስለዋል፡፡

ጥቃቱ የተፈጸመው ከሱዳን ጦር ጋር እየተፋለመ በሚገኘው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ አማካኝነት መሆኑን የሱዳን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ "ጥቃቱን አልፈጸምኩም" ሲል አስተባብሏል፡፡

በሁለቱ ኃይሎች ግጭት በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ሱዳናውያን ሲሞቱ፤ ከ12 ሚሊዮን የሚልቁት ደግሞ ለሀገር ውስጥ እና ለሀገር ውጭ ስደት ተዳርገዋል፡፡  
#dailypost

@ThiqahEth


በአንድ አመት ውስጥ 970,000 ህገ ወጥ የመድሃኒት ምርቶች መያዛቸው ተመላከተ፡፡

ባሳለፍነው የፈረንጆቹ አመት 2024፣ በኦን ላይን በታገዘ ማጭበርበር ህገ ወጥ የመድሃኒት ንግድ ሲያከናውኑ የነበሩ 2,868 ነጋዴዎች መያዛቸውን ተቀማጭነቱን ሲንጋፖር ያደረገው የጤና ሳይንስ ባለስልጣን (HSA) አስታውቋል፡፡

ግብይቶቹ ሚከናወኑት በኢ-ኮሜርስ እና በማህበራዊ ሚዲያ በመሆኑ ለቁጥጥር አስቸጋሪ ሆኖ መቆየቱን ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡

ወጣቶች ለህገ ወጥ የመድሃኒት ምርቶቹን በመጠቀም ተጋላጭ መሆናቸውም ተመላክቷል፡፡ #thestraightstimes

@ThiqahEth


በሶሪያ ቢያንስ 15 ንጹሐን በቦምብ ጥቃት ተገደሉ፡፡

በሰሜናዊ ሶሪያ በምትገኘው የማንቢጅ ከተማ መኪና ላይ በተፈጸመ የቦምብ ጥቃት የ15 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተዘግቧል፡፡

የጥቃቱ ሰለባዎች በግብርና ስራ ተሰማርተው የሚኖሩ ሲሆኑ፤ ከስራ ሲመለሱ ጥቃቱ እንደተፈጸመባቸው የዓይን እማኞች ተናግረዋል።

ከሟቾቹ መካከል 14ቱ ሴቶች ሲሆኑ፣ አንዱ ደግሞ ወንድ ነው ተብሏል፡፡

ምንም እንኳን በከተማዋ በቱርክ የሚደገፉ የሶሪያ ታጣቂዎች እና በአሜሪካ የሚደገፉ የኩርድ ታጣቂዎች ግጭት ውስጥ ቢገኙም ለደረሰው ጥቃት ኃላፊነት የወሰደ አካል ግን የለም፡፡ 
#sananewsxgency   #apnews

@ThiqahEth


''ሳዑድ አረቢያ ሶሪያን የመርዳት ከፍተኛ የሆነ ፍላጎት አላት''  - አህመድ አልሻራ

የሶሪያ ጊዚያዊ የሽግግር ፕሬዝዳንት ሆነው የተመረጡት አሕመድ አልሻራ የመጀመሪያ የውጭ ሀገር ጉዟቸውን በሳዑዲ አረቢያ አድርገዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ በሪያድ ከልዑል አልጋ ወራሽ መሃመድ ቢን ሳልማን ጋር ባደረጉት ውይይት፤ በጦርነት የተጎዳቸውን ሶሪያን መልሶ በመገንባት ዙሪያ ሰፋ ያለ ጊዜ ወስደው ተነጋግረዋል ተብሏል፡፡

''ሳዑድ አረቢያ ሶሪያን የመርዳት ከፍተኛ የሆነ ፍላጎት አላት'' ሲሉም ተናግረዋል።

ባሳለፍነው ታህሳስ ወር ላይ የበሽር አላሳድን መንግስት በኃይል ገርስሰው ስልጣን የተቆጣጠሩት አልሻራም፤ የሽግግር ፕሬዝዳንት ተደርገው ሲመረጡ የመጀመሪያው የደስታ መግለጫ የተላከላቸው ከሳውድው ንጉስ ሳልማን ነበር፡፡
#brecorder

@ThiqahEth


የአውሮፓ መሪዎች በሩሲያና አሜሪካ ጉዳይ ለመነጋገር እንግሊዝ ውስጥ ተሰባስበዋል፡፡

27ቱ የአባል ሀገራቱ መሪዎች በዛሬው እለት የሩሲያን ኢኮኖሚ ለመገዳደር በሚያስችላቸው ሁኔታዎች ላይ እየመከሩ ይገኛሉ፡፡

ከዚህ ባለፈም ስብሰባው አውሮፓ ከአሜሪካ ሊቃጣ ስለሚችለው የንግድ ጦርነት ቅድመ ጥንቃቄ ለማድረግ ያስችላል ነው የተባለው፡፡

ፕሬዝዳንት ትራምፕ በካናዳ፤ ሜክሲኮና ቻይና ላይ የወሰዱትን የቀረጥ መጣል እርምጃ በአውሮፓ ሀገራት ምርቶች ላይም ሊደግሙት እንደሚችሉ ዝተዋል፡፡ #voa

@ThiqahEth


"ካናዳ አሜሪካ ንግድ ላይ ለወሰደችው እርምጃ 155 ቢሊየን ዶላር በሚያወጡ የአሜሪካ ምርቶች ላይ የ25% ቀረጥ መጀመሯን አሳውቃለሁ"  - ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ

ካናዳ በፕሬዝዳንት ትራምፕ ውሳኔ ላይ የአፀፋ እርምጃ ወስዳለች።

ወደ አሜሪካ በሚገቡ ምርቶች ላይ የ25% ቀረጥ የተጣለባት ካናዳ፣ በአሜሪካ ምርቶች ላይም ተመሳሳይ ታሪፍ ጥላለች።

የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ፣ "ዛሬ ካናዳ አሜሪካ ንግድ ላይ ለወሰደችው እርምጃ 155 ቢሊየን ዶላር በሚያወጡ የአሜሪካ ምርቶች ላይ የ25% ቀረጥ መጀመሯን አሳውቃለሁ" ብለዋል።

ከአሜሪካ በሚገቡ የቢራ እና የወይን ምርቶች ላይ ቀረጥ መጣላቸውን አስታውቀዋል።

የነጩ ቤተ መንግሥት እርምጃ እንዳሳዘናቸው ገልጸው፣ ውሳኔው የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች እንደሚጎዳ ግልጽ ነው ብለዋል። #bbc #shine

@ThiqahEth


#BahirdarUniversity

“ስፔሻሊስት ዶክተሩ በተተኮሰባቸው ጥይት ተገድለዋል” - የዓይን እማኞች

የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጥበበ ግዮን ግቢ ስፔሻላንስድ ሆስፒታል የቀዶ ህክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር ዶክተር አንዷለም ዳኘ “በተተኮሰባቸው ጥይት” መገደላቸው ተገለጸ።

ግድያው የተፈጸመው ትላንት ምሽት 12 ሰዓት ከ40 ደቂቃ ገደማ በመሆኑን የገለጹ የዓይን እማኞች፣ “ስፔሻሊስት ዶክተሩ በተተኮሰባቸው ጥይት ተገድለዋል” ብለዋል።

ስለገዳዮቹ ማንነት ገና የታወቀ ነገር የለም ተብሏል።
  
ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ በበኩሉ፣ የዶክተር አንዷለምን ሞት በማረጋገጥ የሀዘን መግለጫ አውጥቷል።

የኢትዮጵያ ህክምና ማኀቀር በበከሉ፣ በግድያው የተሰማውን ሀዘን አስታውቆ፣ ለወዳጅ ቤተሰብ መጽናናትን ተመኝቷል።

@ThiqahEth


#Update

"በአምስት ቀናት  ውስጥ ብቻ 700 ሰዎች ተድለዋል፤ 2,800 ሰዎች ቆስለዋል" - ተ.መ.ድ

የመንግስታቱ ድርጅት በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እንደ አዲስ በተለይ ጎማ ከተማ ያገረሸውን ጦርነ፣ "አሳሳቢ ሁኔታ ላይ ደርሷል" ሲል ገልጾታል።

"በአምስት ቀናት ውስጥ ብቻ 700 ሰዎች ሞተዋል፤ 2,800 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል" ብሏል።

የታጣቂ ቡድኑ ኤም 23 ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠራት የጎማ ከተማ ሰብዓዊ ቀውስ መጎባቱንም ገልጿል።

በሩዋንዳ እንደሚደገፍ የሚነገርለት ቡድኑ ሰፋፊ ስትራቴጂካዊ ስፍራዎችን መቆጣጠር ጀምሯል።

የምሥራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጦርነት በአውሮፓውያኑ 1990ዎቹ ቢጀመርም ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ተባብሷል።

የቱትሲ ብሔርን ያቀፈው የኤም23 አማጺያን ለአናሳዎች መብት እንደሚታገሉ ይናገራሉ።

የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግሥት በበኩሉ በሩዋንዳ የሚደገፉት "አማጺያኑ" በማዕድን ሃብታም የሆነውን የምስራቃዊውን ሰፊ ሥፍራ ለመቆጣጠር ይፈልጋሉ ሲል ይወቅሳል።

#Anadoluagency #Bbc

@ThiqahEth


"በዚህ ሰዓት በህይወት የተረፈውን ተጓዥ ማረጋገጥ አንችልም"  - የኤይር አምቡላንስ ካምፓኒ

በፊላደልፊያ አንድ ህፃንና አምስት ሰዎችን ጭና ስትጓዝ የነበረች አነስተኛ የግል አውሮፕላን  ተከስክሳለች።

አውሮፕላኗ አደጋ የገጠማት ጉዞ በጀመረች በ30 ደቂቃ ውስጥ፣ ከፊላዴልፊያ አየር መንገድ ሦስት ማይል ርቀት ላይ ነው።  

አደጋው በደረሰበት አካባቢ የመኖሪያ ቤቶች ላይ እሳት መነሳቱን የአምቡላንስ ካምፓኒው አስታውቋል።   

በሰዎች ላይ የሞት አደጋ ይሁን ከባድ የደረሰው ጉዳት ይህ ዘገባ እስከተዘጋጀበት ጊዜ አልተገለጸም።

ካምፓኒው በበኩሉ፣ "በዚህ ሰዓት በሕይወት የተረፈውን ተጓዥ ማረጋገጥ አንችልም" ብሏል።

ከሁለት ቀን በፊት በአሜሪካ ከካንሳስ ወደ ቨርጂኒያ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን ተከስክሶ ሁሉም 64 ተጓዦች ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።
#newsmax  #gulfnews

@ThiqahEth


#እንድታውቁት

"ከየካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ልዩ መለያ ኮድ (Unique Qr code የሌለው ደረሰኝ መውሰድ የማይቻል መሆኑ ይታወቃል" - ገቢዎች ሚኒስቴር

የታክስ ደረሰኝ አጠቃቀም እና አስተዳደር መመሪያን ለማሻሻል በወጣ መመሪያ ቁጥር 118/2017 መሠረት ከቀጣይ ወር ጀምሮ ልዩ መለያ ኮድ የሌለው ደረሰኝ መጠቀም የማይቻል መሆኑን ገቢዎች ሚኒስቴር አስታውሷል።

በዚህም ለግብር ከፋዮች የህትመት ፈቃድ አገልግሎቱን ለመስጠት ቅዳሜ ሙሉ ቀን እንደሚሰራ በደብዳቤ ጠቁሟል።


#ኢትዮጵያ #ገቢዎችሚኒስቴር

@ThiqahEth


"በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና ቻይና ላይ የተጣለው ቀረጥ ከቅዳሜ ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል"  - ካሮሊን ሌቪት

"አስገዳጅ ሊሆን ይችላል ግን ምክንያታዊ መሆን አለበት"  - ጀስቲን ትሩዶ


በካናዳ እና ሜክሲኮ ላይ የ25% እንዲሁም በቻይና ላይ ደግሞ የ10% የቀረጥ ጭማሪ መደረጉን የነጩ ቤተመንግስት ቃል አቀባይ ሌቪት ገልጸዋል።

"በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና ቻይና ላይ የተጣለው ቀረጥ ተግባራዊ ይሆናል" ነው ያሉት።

በተለይ ሁለቱ ጎረቤት ሀገራት አሜሪካን ለስደተኞች ተጋላጭ አድርገዋል በሚል ነው ከፍተኛ ቀረጥ እንዲከፍሉ የተወሰነው።

የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ታዲያ፣ "አስገዳጅ ሊሆን ይችላል ግን ምክንያታዊ መሆን አለበት" ሲሉ በውሳኔው የተሰማቸውን ቅሬታ ገልጸዋል።   #thenewarab  #aninews

@ThiqhEth


#America

ትራምፕ ከነገ (ቅዳሜ) ጀምሮ ከሜክሲኮና ካናዳ በሚገቡ ምርቶች የ25 በመቶ ቀረጥ እንደሚጥሉ ተነግሯል።

ከቻይና በሚገቡ ምርቶች ደግሞ 10 በመቶ ቀረጥ ከነገ ጀምሮ መጣላቸውን "ዋይት ሐውስ" ገልጿል።


@ThiqahEth


#Ethiopia #OromiaRegion

“ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የተወሰዱት 50 ገቢያተኞቹ እስካሁን አልተመለሱም” - ነዋሪ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሚስተዋለው የጸጥታ ችግር ሰዎች ለቅሶና ገበያ ሲሄዱ ጭምር እየታገቱ እንደሚገኙ ነዋሪዎች ተግረዋል። 

“ታጣቂዎች በየቦታው ሰው ይወስዳሉ” ያሉ አስተያየት ሰጪ በተለይም ሰው ገቢያም ሆነ ለቅሶ እንኳ ለመሄድ ስጋት እንደሚገባው አስረድተዋል፡፡ 

ከሳምንት በፊት ከደብረሊባኖስ አካባቢ ወደ ያያ ጉሌሌ ለገቢያ ሲጓዙ የነበሩ አንድ ተሽከርካሪ ሙሉ 50 ሰዎች ሳዲኒ ብዮ በሚባል የያያ ጉሉለ ወረዳ ታፍነው ከደተወሰዱ እንዳልተመለሱ ሌላኛው ነዋሪ ገልጸዋል።

“ገቢያ ስሄዱ የነበሩ አንድ ሙሉ መኪና አብዛኞቻቸው ነጋዴዎችና ገቢያተኞች የሚገኙባቸው ያለፈው ማክሰኞ ሳምንት ወደ ጉሌሌ ለገቢያ እየመጡ ሳለ ነው ሳዲኒ በሚባል ቀበሌ በታጣቂዎች ታፍነው የተወሰዱት፡፡ 

ይህ ቦታ ከአንድ ወር በፊት አምስት የዞን ባለስልጣናትን ጨምሮ የመንግስት ሰራተኞች የተገደሉበትም ነው፡፡ ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የተወሰዱት ወደ 50 የሚሆኑት ገቢያተኞቹ እስካሁን አልተመለሱም፡፡ ሾፈርም አብሮ እንደተወሰደ ነው” ብለዋል፡፡
#DW-Amharic

@ThiqahEth


#Ethiopia #AfarRegion

“የሟቾች ቁጥር 8 ነው። ቁስለኞች ከ10 በላይ ናቸው። ቁስለኞች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል” - ነዋሪዎች

“ጥቃቱ የድሮን ጥቃት ነው፡፡ የሟቾች ቁጥር እስካሁን ባለኝ መረጃ ስምንት ነው" - ኤሊዳዓር ወረዳ

በአፋር ክልል ኤሊዳዓር ወረዳ ሲያሩ ቀበሌ ተፈጸመ ባሉት የድሮን ጥቃት አርሶ አደሮች፣ ሴቶች፣ ህፃናት ላይ ሞትና ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን የአካባቢው ነዋሪዎችና ወረዳው አረጋግጠዋል።

በነዋሪዎቹ ገለጻ መሠረት ጥቃቱ የደረሰው፣ "ከወደ ጅቡቲ በመጣ ድሮን" ነው።

በዚሁ ጥቃት እስካሁን ባለው መረጃ 8 ሰዎች ሲሞቱ፣ ሴቶችና ህፃናትን ጭምር ከ10 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

የወረዳው አካል በበኩሉ፣ ስምንት ሰዎች እንደተገደሉ፣ ቁስኞችም እንዳሉ ገልጿል። More፡ https://t.me/tikvahethiopia/94169

@ThiqhEth


#Ethiopia

“ላለፉት ስድስት ዓመታት፤ ብታምኑም ባታምኑም አንድ ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ torture አይደረግም። በዚህ እኛ እንኮራለን” - ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ያሉ ግጭቶች ጠንሳሾች፤ “ትላንትና ፖለቲካ ሲያንቦራጭቁ የነበሩ ሰዎች ናቸው” አሉ።

በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶች “ጠንሳሽ” እና “ጨማቂዎች”፤ “ትላንትና ፖለቲካ ሲያንቦራጭቁ የነበሩ ሰዎች ናቸው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) ወነጀሉ።

አቢይ በሚመሩት ብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ዛሬ ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ “ሰው torture አይደረግም” ሲሉ ተደምጠዋል። 

ገዢው ፓርቲ እስከ መጪው እሁድ ጥር 25፤ 2017 ዓ/ም የሚቆየውን ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤ እያካሄደ ያለው፤ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የመሰብሰቢያ አዳራሽ ነው።

የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት የሆኑት አቢይ፤ ፓርቲው ቃል ከገባቸው ጉዳዮች መካከል “በኢትዮጵያ ቶርቸር ይቁም” የሚለው አንዱ እንደነበር አስታውሰዋል።

ብልጽግና ፓርቲ “ባለፉት ጥቂት ዓመታት” በተጓዘበት “የመጀመሪያ ምዕራፍ” ካሳካቸው ጉዳዮች አንዱ፤ ይኸው እንደሆነም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለጉባኤው ታዳሚያን ተናግረዋል።

“ላለፉት ስድስት ዓመታት፤ ብታምኑም ባታምኑም አንድ ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ torture አይደረግም። በዚህ እኛ እንኮራለን” ብለዋል አቢይ።

በዚህ ንግግራቸው “ፖለቲካን በቅጡ አልተለማመዱም” ያሏቸውን “አባቶች” ወርፈዋቸዋል። “አባቶቻችን ሀገርኛ ሀሳብ አላፈለቁም። በተዋሱት ሃሳብ ሲጨቃጨቁ፣ ሲጋደሉ የኖሩ ስለሆነ፤ አሁንም ያንን ማስቀጠል ይፈልጋሉ” ብለዋል። #EthiopianInsider

@ThiqahEth

Показано 15 последних публикаций.