+#አዋልድ_መጻሕፍት_ለሃይማኖት_ማስረጃ_ኾነው_አይጠቀሱምን?+++
[] የሚጠቀሱ አሉ፤ የማይጠቀሱም አሉ!
አንዳንዴ ገድላትም ሃይማኖታዊ ጉዳይ ለማስረዳት ይጠቀሱ ይኾናል።
ለምሳሌ በሃይማኖተ አበው " ቅዱስ ባስልዮስ ... ስለ ቦሊጣ ሰማዕት በተናገረው ድርሳኑ ስለኛ እግዚአብሔር በሰው መካከል ተገለጠ፤ ብሉይ ሥጋን ለማደስ ቃል ሥጋ ኾነ፤ ባሕርያችንንም ገንዘብ አደረገ፤ የኃጢአት ምርኮኞችን ነጻ የሚያወጣቸው፥ ከበደለኞች ጋር ተቈጠረ፤ በጨለማ ውስጥ ለነበሩ ሰዎች እውነተኛ ፀሐይ ወጣላቸው፤ የማይታመመው በመስቀል ላይ ታመመ፤ ሕይወት እርሱ ሞተ፤ ብርሃን በሲኦል ተገለጠ፤ የተቀበሩትን የሚያነሣ እርሱ ከሙታን ጋር ተቈጠረ ብሎ ተናገረ" ይላል። (ሃይ ዘባስልዮስ ምዕ 96፥42)።
- "የቤተ ክርስቲያን ዐምድ ቅድስ ባስልዮስም ስለ ኢየሉጣ ሰማዕት በተናገረው ድርሳኑ አምላክ ስለኛ ሰው ኾነ፤ በሰው መካከል ተመላለሰ፤ ከተገፉት ጋር የሚገፋ ኾነ፤ የተጎዱትን ያድን ዘንድ ረዳት ለሌላቸውም ረዳት ይኾናቸው ዘንድ ይህን ኹሉ ሠራ፤ ቀድሞ ሥጋ ያልነበረው ዛሬ ሥጋን ተዋሐደ፤ ተሰቀለ፤ ሕይወት እሱ በሥጋ ሞተ፤ ብርሃን እሱ ወደ ሲኦል ገባ፤ ይህም ኹሉ የኾነው አዳምና ልጆቹም ስለ ተጎዱ ነው አለ" እንዲል። (ሃይ ዘዮሐንስ (የአንጾኪያ፣ የሶርያ፣ የባቢሎን ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሐንስ) ምዕ 114፥20)።
- አድማሱ ጀንበሬ በአጽንዖት የሚሉን አለ፦ "ሃይማኖተ አበው፣ አፈወርቅ፣ ቄርሎስ፣ ፍትሐ ነገሥት፣ 14ቱ ቅዳሴያት፣ ፊልክስዩስ፣ ማር ይስሐቅ፣ አረጋዊ መንፈሳዊም ሠለስቱ ምዕት በፍትሐ ነገሥት ከቈጠሯቸው ጋር አንድ ኾነው ይቆጠራሉ። ቅዱሳት መጻሕፍት ይባላሉ።" ይላሉ። (አድማሱ ጀንበሬ፣ ኰኵሐ ሃይማኖት፣ 2012 ዓ.ም፣ ገጽ 176)። ለአበው የትርጓሜያት መጻሕፍትና ሥርዓተ አምልኮትን የሚፈጸምባቸው የሥርዓት መጻሕፍትን እንዲሁም ኅብስትና ወይን ቀርቦ ወደ አማናዊው ቅዱስ ሥጋና ደም (ቅዱስ ቍርባን) የሚለወጥበት ጸሎት የሚከወንበትን የቅዳሴያት መጻሕፍት እንዴት በጥንቃቄ እንደ ጠቀሷቸው ልብ እንበል። እነዚህን አዋልድ መጻሕፍት እንደ መሠረታዊ መጻሕፍት አድርገው መጥቀሳቸውን ልብ ማለት ይገባል። ከዚህ በተጨማሪ በጒሜ ትምህርት የሚሰጥበትን የምንኲስናን ሕይወት ማዕከል አድርጎ የተዘጋጀውን መጽሐፍም ትልቅ ቦታ እንዳለው ይጠቁሙናል። አድማሱ ጀንበሬ ፕሮቴስታንታዊውን መናፍቅ "... እንግዲህ የእግዚአብሔርን አምላክነት ከሚናገሩት መጻሕፍት ውስጥ ይህ ሰው የጻፈው ነው፤ ይህም አዋልድ ነው፤ አልቀበልም ማለት የተሳሳተ ንግግር መኾኑን ትረዳ ዘንድ ..." ይላሉ። (እንደ ላይኛው ገጽ 168)። እንዲሁ በመሰለን ተነሥተን ይሄን አልቀበልም፣ ይህን እቀበላለሁኝ እያልን በመጻሕፍት ተጽፈው ለተቀመጡ ምንባባት የራስን አእምሮ መጣኝ ወይም መዛኝ ከማድረግ ስሑት አካሄድ እንድንወጣ ይመክሩናል። ማንኛውንም ሃይማኖታዊ ጉዳይ በራስ መረዳት ልክ አድርጎ መጓዝ ኦርቶዶክሳዊ አካሄድ ካለመኾኑም በተጨማሪ መዳረሻው በትዕቢት እሾህ ተወግቶ በክሕደት ገደል ውስጥ መግባት ነው።
አድማሱ ጀንበሬ መልክአ ማርያምን ጠቅሶ ለሚተቸው ፕሮቴስታንት ሲመልሱ "ከዚህ ከፍ ብሎ በሚገኘው መሥመር መጻሕፍት ማታለያ አዋልድ የተባሉ ልብ ወለድ መነኰሳቱ ሰበኩት ብለህ አዋልድ መጻሕፍትን ስትነቅፍ ተናግረህ ነበረ። እኛ ከጸሎት በቀር ለሃይማኖትና ለምግባር ምስክር አድርገን የማንጠቅሳቸውን መልካ መልኮችን በቂ ምስክሮች አድርገህ ከጠቀስክልኝ ከላይ የተናገርከውን አዋልድ መጻሕፍት ማታለያ መባላቸው ቀርቶ ባንተው ቃል ተሠይመው ለምስክርነት የበቁ እውነተኞች መጻሕፍት መኾናቸውን ማረጋገጥህን አስተውል። እንግዲህ አንተ የጠቀስካቸውን አዋልድ ምናልባት እኔ የጠቀስኩልህ እንደ ኾነ ቅር እንዳይልህና ሰው እንዳይታዘብህ አደራ" ይላሉ። (እንደ ላይኛው ገጽ 85-86)። ይህ ደግሞ በአንድ በኩል እንደ መልካ መልኮች ዓይነት መጻሕፍት የተዘጋጁበትን ዓላማ የሚያሳስብ ነው በሌላ በኩል አዋልድ መጻሕፍትን አልቀበልም የሚሉ መናፍቃን ያን አናምንበትም ያሉትን መጻሕፍት ጠቅሰው የመሞገት ሥልጣን እንደ ማይኖራቸው አመልካች ነው። እንግዲህ መጻሕፍትን ባልተጻፉበት ዐውድ መገምገም ፍጹም ስሑት የኾነ አካሄድ መኾኑን ልብ ከማለት ጋር አዋልድ መጻሕፍትን የማይቀበሉ መናፍቃን ለማዘናጋት የሚሄዱበትን መንገድ መለየት ያስፈልጋል።
ሌላው እዚህ ጋር ልብ ማለት የሚገባን የጸሎት መጻሕፍት ኹሉ ለሃይማኖት አስረጅ ተደርገው አይጠቀሱም ግን አይባልም። ለምሳሌ ውዳሴ ማርያም፣ 14 ቅዳሴያት፣ ... ሊጠቀሱ ይችላሉና። በኦርቶዶክስ የምናምነውን እንጸልያለን የምንጸልየውንም እናምናለን የሚለውን መሠረታዊ ሐሳብ ቸል የምንል አይደለምና። ዶግክትሪናችንን በራሱ እንደምንጸልየው ልብ ማለት ይገባልና። ጸሎተ ሃይማኖት ብለን የምንጸልየውም ለዚህ ማሳያ መኾኑ ግልጽ ነውና። መሠረታዊ ዓላማቸው ግን ርእሰ ጉዳያቸውን ማዕከል ያደረገ መኾኑን ልብ ማለት ይገባል። የተለያዩ ዓይነት አዋልድ መጻሕፍት አሉ ማለታችንም ከርእሰ ጉዳያቸው አንጻር ነው። ዋና ጉዳይ ያደረጉትን ትተን ወደ ሌላ ወስደን ቸኩል ድምዳሜ ውስጥ መግባት አይጠበቅብንም።
በቦሩ ሜዳ ላይ ሦስት ልደት የሚል ከመጻሕፍት ምንጭ አምጣ ሲባል "በደብረ ብርሃን በሚገኝ ተአምረ ማርያም ላይ አለ" ማለቱ ትችትን ያመጣበት ተአምረ ማርያምን አንቀበልም ለማለት ወይም አያስፈልግም ለማለት ሳይኾን ሃይማኖታዊ ዶክትሪንን ለማስተማር ታቅዶ የተጻፈ አይደለም ለማለት ነው። የተአምር ማርያም ዋና ዓላማው እግዚአብሔር በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አድሮ ያደረገውን መክራት ማሳየት እንጂ ትምህርተ ቤተ ክርስቲያንን ማስተማር አይደለምና። ብዙ ጊዜ Missing the point Fallacy (ነጥቡን የመሳት ስሕተት) ይሠራል። አዋልድ መጻሕፍት ሲጠኑ ከተጻፉበት መሠረታዊ ሐሳብ አንጻር ይገመገማሉ እንጂ ወደ ሌላ ዘወር ተደርገው ሊገመገሙ አይገባም። ተአምር የሚታየው ከታምር አንጻር ነው፤ ገድልም ከገድል አንጻር፤ ሌላውም ከዚያ አንጻር እንጂ ገድልን ሃይማኖተ አበው፥ ሃይማኖተ አበውንም ገድል አድርጎ ማሰብ መሠረታዊውን ነጥብ መሳት ነው። የቦሩ ሜዳው ጒባኤ አዋልድ መጻሕፍት ብዙም ጥቅም እንደሌላቸው አስረጅ ሳይኾን እንዲያውም እጅጉን ጠቃሚ መኾኑን ጠቋሚ ነው። ኹለት ልደት የሚለው በዋነኛነት ትክክል መኾኑ የተረዳው በሃይማኖተ አበው ባሉ ምንባባት ነውና። ሃይማኖተ አበው ደግሞ ቍጥሩ ከአዋልድ መኾኑ ግልጽ ነው። ከዚያ ውጭ ያልተባለን ማለት አግባብ አይደለም። ይህም ማለት ተአምረ ማርያምን ሃይማኖተ አበው አድርጎ ከማሰብ ነጥብን ከመሳት ስሕተት መጠበቅ ይገባል።
ታምራትን በተመለከተ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ የቅድስት ማክሪንን ሕይወት ሲጽፍ የሰጠው ጠቃሚ አስተያየት አለ። ይኸውም፦ "በጣም ትንሽ እምነት ያላቸውና በእግዚአብሔር ስጦታ የማያምኑ ሰዎች ወደ መጎዳት እንዳይመጡ፥ በዚህ ምክንያት ታላቅ ታምራትን መጻፍ ትቼያለሁኝ፤ ስለዚህ እንደማስበው ከኾነ አስቀድሜ ያልኹት የማክሪንን ታሪክ መጽሐፍ ለመፈጸም በቂ ነው።" ይላል። (The Life of SAINT MACRINA BY Gregorry, BisHop of Nyssa /Translated, with introduction and notes, by Kevin Corrigan p.54)። ይህ እንግዲህ አስተውሎት ያለበት ጥንቃቄ ነው። ይህን ሊቁ ማለት በፈለገበት መንፈስ ብቻ ኾነን የምንረዳው እንጂ ታላላቅ ታምራት በዐሥራው መጻሕፍት ውስጥ ተጽፈው ስለምናገኝ
[] የሚጠቀሱ አሉ፤ የማይጠቀሱም አሉ!
አንዳንዴ ገድላትም ሃይማኖታዊ ጉዳይ ለማስረዳት ይጠቀሱ ይኾናል።
ለምሳሌ በሃይማኖተ አበው " ቅዱስ ባስልዮስ ... ስለ ቦሊጣ ሰማዕት በተናገረው ድርሳኑ ስለኛ እግዚአብሔር በሰው መካከል ተገለጠ፤ ብሉይ ሥጋን ለማደስ ቃል ሥጋ ኾነ፤ ባሕርያችንንም ገንዘብ አደረገ፤ የኃጢአት ምርኮኞችን ነጻ የሚያወጣቸው፥ ከበደለኞች ጋር ተቈጠረ፤ በጨለማ ውስጥ ለነበሩ ሰዎች እውነተኛ ፀሐይ ወጣላቸው፤ የማይታመመው በመስቀል ላይ ታመመ፤ ሕይወት እርሱ ሞተ፤ ብርሃን በሲኦል ተገለጠ፤ የተቀበሩትን የሚያነሣ እርሱ ከሙታን ጋር ተቈጠረ ብሎ ተናገረ" ይላል። (ሃይ ዘባስልዮስ ምዕ 96፥42)።
- "የቤተ ክርስቲያን ዐምድ ቅድስ ባስልዮስም ስለ ኢየሉጣ ሰማዕት በተናገረው ድርሳኑ አምላክ ስለኛ ሰው ኾነ፤ በሰው መካከል ተመላለሰ፤ ከተገፉት ጋር የሚገፋ ኾነ፤ የተጎዱትን ያድን ዘንድ ረዳት ለሌላቸውም ረዳት ይኾናቸው ዘንድ ይህን ኹሉ ሠራ፤ ቀድሞ ሥጋ ያልነበረው ዛሬ ሥጋን ተዋሐደ፤ ተሰቀለ፤ ሕይወት እሱ በሥጋ ሞተ፤ ብርሃን እሱ ወደ ሲኦል ገባ፤ ይህም ኹሉ የኾነው አዳምና ልጆቹም ስለ ተጎዱ ነው አለ" እንዲል። (ሃይ ዘዮሐንስ (የአንጾኪያ፣ የሶርያ፣ የባቢሎን ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሐንስ) ምዕ 114፥20)።
- አድማሱ ጀንበሬ በአጽንዖት የሚሉን አለ፦ "ሃይማኖተ አበው፣ አፈወርቅ፣ ቄርሎስ፣ ፍትሐ ነገሥት፣ 14ቱ ቅዳሴያት፣ ፊልክስዩስ፣ ማር ይስሐቅ፣ አረጋዊ መንፈሳዊም ሠለስቱ ምዕት በፍትሐ ነገሥት ከቈጠሯቸው ጋር አንድ ኾነው ይቆጠራሉ። ቅዱሳት መጻሕፍት ይባላሉ።" ይላሉ። (አድማሱ ጀንበሬ፣ ኰኵሐ ሃይማኖት፣ 2012 ዓ.ም፣ ገጽ 176)። ለአበው የትርጓሜያት መጻሕፍትና ሥርዓተ አምልኮትን የሚፈጸምባቸው የሥርዓት መጻሕፍትን እንዲሁም ኅብስትና ወይን ቀርቦ ወደ አማናዊው ቅዱስ ሥጋና ደም (ቅዱስ ቍርባን) የሚለወጥበት ጸሎት የሚከወንበትን የቅዳሴያት መጻሕፍት እንዴት በጥንቃቄ እንደ ጠቀሷቸው ልብ እንበል። እነዚህን አዋልድ መጻሕፍት እንደ መሠረታዊ መጻሕፍት አድርገው መጥቀሳቸውን ልብ ማለት ይገባል። ከዚህ በተጨማሪ በጒሜ ትምህርት የሚሰጥበትን የምንኲስናን ሕይወት ማዕከል አድርጎ የተዘጋጀውን መጽሐፍም ትልቅ ቦታ እንዳለው ይጠቁሙናል። አድማሱ ጀንበሬ ፕሮቴስታንታዊውን መናፍቅ "... እንግዲህ የእግዚአብሔርን አምላክነት ከሚናገሩት መጻሕፍት ውስጥ ይህ ሰው የጻፈው ነው፤ ይህም አዋልድ ነው፤ አልቀበልም ማለት የተሳሳተ ንግግር መኾኑን ትረዳ ዘንድ ..." ይላሉ። (እንደ ላይኛው ገጽ 168)። እንዲሁ በመሰለን ተነሥተን ይሄን አልቀበልም፣ ይህን እቀበላለሁኝ እያልን በመጻሕፍት ተጽፈው ለተቀመጡ ምንባባት የራስን አእምሮ መጣኝ ወይም መዛኝ ከማድረግ ስሑት አካሄድ እንድንወጣ ይመክሩናል። ማንኛውንም ሃይማኖታዊ ጉዳይ በራስ መረዳት ልክ አድርጎ መጓዝ ኦርቶዶክሳዊ አካሄድ ካለመኾኑም በተጨማሪ መዳረሻው በትዕቢት እሾህ ተወግቶ በክሕደት ገደል ውስጥ መግባት ነው።
አድማሱ ጀንበሬ መልክአ ማርያምን ጠቅሶ ለሚተቸው ፕሮቴስታንት ሲመልሱ "ከዚህ ከፍ ብሎ በሚገኘው መሥመር መጻሕፍት ማታለያ አዋልድ የተባሉ ልብ ወለድ መነኰሳቱ ሰበኩት ብለህ አዋልድ መጻሕፍትን ስትነቅፍ ተናግረህ ነበረ። እኛ ከጸሎት በቀር ለሃይማኖትና ለምግባር ምስክር አድርገን የማንጠቅሳቸውን መልካ መልኮችን በቂ ምስክሮች አድርገህ ከጠቀስክልኝ ከላይ የተናገርከውን አዋልድ መጻሕፍት ማታለያ መባላቸው ቀርቶ ባንተው ቃል ተሠይመው ለምስክርነት የበቁ እውነተኞች መጻሕፍት መኾናቸውን ማረጋገጥህን አስተውል። እንግዲህ አንተ የጠቀስካቸውን አዋልድ ምናልባት እኔ የጠቀስኩልህ እንደ ኾነ ቅር እንዳይልህና ሰው እንዳይታዘብህ አደራ" ይላሉ። (እንደ ላይኛው ገጽ 85-86)። ይህ ደግሞ በአንድ በኩል እንደ መልካ መልኮች ዓይነት መጻሕፍት የተዘጋጁበትን ዓላማ የሚያሳስብ ነው በሌላ በኩል አዋልድ መጻሕፍትን አልቀበልም የሚሉ መናፍቃን ያን አናምንበትም ያሉትን መጻሕፍት ጠቅሰው የመሞገት ሥልጣን እንደ ማይኖራቸው አመልካች ነው። እንግዲህ መጻሕፍትን ባልተጻፉበት ዐውድ መገምገም ፍጹም ስሑት የኾነ አካሄድ መኾኑን ልብ ከማለት ጋር አዋልድ መጻሕፍትን የማይቀበሉ መናፍቃን ለማዘናጋት የሚሄዱበትን መንገድ መለየት ያስፈልጋል።
ሌላው እዚህ ጋር ልብ ማለት የሚገባን የጸሎት መጻሕፍት ኹሉ ለሃይማኖት አስረጅ ተደርገው አይጠቀሱም ግን አይባልም። ለምሳሌ ውዳሴ ማርያም፣ 14 ቅዳሴያት፣ ... ሊጠቀሱ ይችላሉና። በኦርቶዶክስ የምናምነውን እንጸልያለን የምንጸልየውንም እናምናለን የሚለውን መሠረታዊ ሐሳብ ቸል የምንል አይደለምና። ዶግክትሪናችንን በራሱ እንደምንጸልየው ልብ ማለት ይገባልና። ጸሎተ ሃይማኖት ብለን የምንጸልየውም ለዚህ ማሳያ መኾኑ ግልጽ ነውና። መሠረታዊ ዓላማቸው ግን ርእሰ ጉዳያቸውን ማዕከል ያደረገ መኾኑን ልብ ማለት ይገባል። የተለያዩ ዓይነት አዋልድ መጻሕፍት አሉ ማለታችንም ከርእሰ ጉዳያቸው አንጻር ነው። ዋና ጉዳይ ያደረጉትን ትተን ወደ ሌላ ወስደን ቸኩል ድምዳሜ ውስጥ መግባት አይጠበቅብንም።
በቦሩ ሜዳ ላይ ሦስት ልደት የሚል ከመጻሕፍት ምንጭ አምጣ ሲባል "በደብረ ብርሃን በሚገኝ ተአምረ ማርያም ላይ አለ" ማለቱ ትችትን ያመጣበት ተአምረ ማርያምን አንቀበልም ለማለት ወይም አያስፈልግም ለማለት ሳይኾን ሃይማኖታዊ ዶክትሪንን ለማስተማር ታቅዶ የተጻፈ አይደለም ለማለት ነው። የተአምር ማርያም ዋና ዓላማው እግዚአብሔር በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አድሮ ያደረገውን መክራት ማሳየት እንጂ ትምህርተ ቤተ ክርስቲያንን ማስተማር አይደለምና። ብዙ ጊዜ Missing the point Fallacy (ነጥቡን የመሳት ስሕተት) ይሠራል። አዋልድ መጻሕፍት ሲጠኑ ከተጻፉበት መሠረታዊ ሐሳብ አንጻር ይገመገማሉ እንጂ ወደ ሌላ ዘወር ተደርገው ሊገመገሙ አይገባም። ተአምር የሚታየው ከታምር አንጻር ነው፤ ገድልም ከገድል አንጻር፤ ሌላውም ከዚያ አንጻር እንጂ ገድልን ሃይማኖተ አበው፥ ሃይማኖተ አበውንም ገድል አድርጎ ማሰብ መሠረታዊውን ነጥብ መሳት ነው። የቦሩ ሜዳው ጒባኤ አዋልድ መጻሕፍት ብዙም ጥቅም እንደሌላቸው አስረጅ ሳይኾን እንዲያውም እጅጉን ጠቃሚ መኾኑን ጠቋሚ ነው። ኹለት ልደት የሚለው በዋነኛነት ትክክል መኾኑ የተረዳው በሃይማኖተ አበው ባሉ ምንባባት ነውና። ሃይማኖተ አበው ደግሞ ቍጥሩ ከአዋልድ መኾኑ ግልጽ ነው። ከዚያ ውጭ ያልተባለን ማለት አግባብ አይደለም። ይህም ማለት ተአምረ ማርያምን ሃይማኖተ አበው አድርጎ ከማሰብ ነጥብን ከመሳት ስሕተት መጠበቅ ይገባል።
ታምራትን በተመለከተ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ የቅድስት ማክሪንን ሕይወት ሲጽፍ የሰጠው ጠቃሚ አስተያየት አለ። ይኸውም፦ "በጣም ትንሽ እምነት ያላቸውና በእግዚአብሔር ስጦታ የማያምኑ ሰዎች ወደ መጎዳት እንዳይመጡ፥ በዚህ ምክንያት ታላቅ ታምራትን መጻፍ ትቼያለሁኝ፤ ስለዚህ እንደማስበው ከኾነ አስቀድሜ ያልኹት የማክሪንን ታሪክ መጽሐፍ ለመፈጸም በቂ ነው።" ይላል። (The Life of SAINT MACRINA BY Gregorry, BisHop of Nyssa /Translated, with introduction and notes, by Kevin Corrigan p.54)። ይህ እንግዲህ አስተውሎት ያለበት ጥንቃቄ ነው። ይህን ሊቁ ማለት በፈለገበት መንፈስ ብቻ ኾነን የምንረዳው እንጂ ታላላቅ ታምራት በዐሥራው መጻሕፍት ውስጥ ተጽፈው ስለምናገኝ