YeneTube


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


ጥሩ ዜና ለሸማቾች

የቻይናው የአሊባባ ግሩፕ እህት ኩባንያ አሊ ኤክስፕረስ ከመጪው Feb 24 ጀምሮ አሊ ክፍያዎችን በብር መቀበል ሊጀመር መሆኑን አስታውቋል።

እንግዴ ነጋዴ እንደፈለግሽ 300% መጨመር የለም 😁


የነዳጅ ማደያዎች ፈቃድ የመስጠት ሥራ ሙሉ በሙሉ መታገዱ ተገለጸ!

በኢትዮጵያ ያሉ የነዳጅ ማደያዎች የትኞቹ የሚጠበቅባቸውን ደረጃ አሟልተዋል? የትኞቹስ አስፈላጊውን አገልግሎት እየሰጡ ነው? የሚለውን እና ተያያዥ ጉዳይዎች እስኪጣሩ ድረስ ፈቃድ የመስጠት ሥራው ለጊዜው መታገዱን የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ለአሐዱ ገልጿል፡፡

የባለስልጣኑ የሕዝብ ግንኙነት እና የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ ወይዘሮ በቀለች ኩማ በዚህ ጉዳይ ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ጥናት እየተደረገ መሆኑን አንስተው፤ በአዲስ አበባ በልማት የፈረሱ መኖራቸውን አስታውሰዋል፡፡

በአዲስ አበባ በልማት የፈረሱትን ጨምሮ የትኞቹ ማደያዎች አስፈላጊ ቦታ ላይ ናቸው? የትኞቹ ደረጃ አሟልተዋል የሚሉ እና ተያያዥ ጉዳይዎችን በተመለከተ ከከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ጋር በመሆን ለመለየት ጥናት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ጥናቱ ሲጠናቅ እና ውጤቱ ሲታወቅ ፍቃድ የመስጠት ሥራው ሊጀምር እንደሚችልም ጠቁመዋል፡፡

ጥናቱ ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲገባ ማደያ የሌለባቸው ቦታዎች ላይ ማደያዎች እንዲኖሩ ለማድረግ ያግዛልም ነው የተባለው፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘ የነዳጅ ግብይት ክልሎች ያቀረቡት ጥያቄ ሁሉም የፋይናስ ተቋማት ወደ ነዳጅ ግብይት እንዲገቡ ማስገደዱ አንስተዋል፡፡

የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የግብይት ስርዓትን በኤሌክትሮኒክስ ካደረገ በኋላ ያሉት ሦስቱ የፋይናስ ተቋማት ብቻ ማለትም፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ እና ቴሌ ብር መሆናቸው በተገልጋዮች ላይ ቅሬታ ፈጥሮ እንደነበር ነው የተነሳው፡፡

"ክልሎች የሚገበያዩባቸው የፋይናንስ ተቋማት እና ባለስልጣኑ ግብይት እንዲፈፅሙ የፈቀደላቸው ተቋማት መጣጣም ባለመቻላቸው፤ ሁሉም የፋይናስ ተቋማት ወደ ዘርፉ እንዲገቡ ማድረግ አስፈላጊ ሆኗልም" ሲሉም ወይዘሮ በቀለች አክለዋል፡፡

"በሁሉም ክልሎች ያሉ እና የፋይናንስ ግብይቱ የሚጠይቀውን መስፈርት አሟልተው የግብይት ሪፖርት ማቅረብ የሚችሉ ባንኮች ሁሉ መግባት እና በዘርፉ ላይ መስራት ይችላሉ" ሲሉም ገልጸዋል፡፡

"የፋይናስ ተቋማቱ መብዛት እና የግብይት ሁኔታው መስፋት ለቁጥጥር አዳጋች አይሆንም ወይ?" ሲል አሐዱ የጠየቀ ሲሆን፤ ተቋማቱ የፈቃድ ግዴታዎችን አሟልተው የሚገቡ ስለሚሆን ለቁጥጥር እና ለክትትል የሚከብድ ሁኔታን አይፈጥርም የሚል ምላሽ አግኝቷል፡፡የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ቢደረግም ነገር ግን በተደጋጋሚ ሕገ-ወጥ የነዳጅ ነጋዴዎች ምርቱን ሲያዘዋዉሩ መያዙን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እና ተባባሪ አካላት ሲገልጹ ይደመጣል፡፡

Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa


Репост из: HuluPay Community
በTelegram ላይ የተረጋገጠ ምልክት (Verified Checkmark) ለማግኘት የእርስዎን አካውንት አሁን Premium ያድርጉት

Telegram Premium በመግዛት የተረጋገጠ ምልክት ያግኙ!
በHulupay በTelebirr አማካኝነት በቀላሉ ይክፈሉ።
አስደናቂ ፊቸሮችን ያግኙ!

- 4GB እስከሆኑ ፋይሎችን ይጫኑ
- በፍጥነት ያውርዱ
- የእርስዎን online status ከሌሎች ይደብቁ
- እስከ 4 accounts ድረስ ይጠቀሙ
- ልዩ ስቲከሮች እና ኢሞጂዎች 🎭
- የድምፅ መልእክቶችን ጽሁፍ ያድርጉ
- ልዩ badges ያግኙ
- ማስታወቂያዎችን ያስወግዱ


አሁኑኑ ይቀላቀሉ እና የእርስዎን Telegram ተሞክሮ ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግሩ! 🚀

📲 ሁሉፔይን ለመጠቀም ሁሉፔይ ሚኒ አፕን
https://t.me/HuluPayOfficialBot/start?startapp እዚህ ሊንክ ጋር ያገኛሉ 🔗።



5 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ ተለያዩ ክልሎች መጓጓዙ ተገለፀ፡፡

5 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ ክልሎች መጓጓዙን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡የግብርና ሚኒስትር ዴኤታዋ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደተናገሩት በተያዘው ዓመት 24 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት እቅድ ተይዞ ነበር።

በዚህም እስካሁን 7 ሚሊየን ኩንታል የሚሆነው የአፈር ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ መድረሱን እና 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታሉ ደግሞ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች መጓጓዙን ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም በአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ስርጭት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመፍታት ከሀረሪ ክልል እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ውጭ ሁሉም ክልሎች በአፈር ማዳበሪያ ግዥ ላይ እንዲካተቱ እና አልሚ ባለሃብቶች ደግሞ በሚያለሙበት ክልል ማዳበሪያ እንዲያገኙ ተደርጓል ነው ያሉት።

በተጨማሪም በአፈር ማዳበሪያ ስርጭት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመፍታት በዚህ ዓመት የዲጂታል አሰራር ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ስለመሆኑም ሚኒስትር ዴኤታዋ መግለፃቸን ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa


በደቡብ ወሎ ዞን የ 7 ዓመት ህፃን አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

በደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ የሰባት ዓመት ህፃን ልጅ አስገድዶ የደፈረው ተከሳሽ በእስራት መቀጣቱን የቃሉ ወረዳ ፖሊስ አስታወቀ።

ተከሳሹ ከድር ይመር በእስራት ሊቀጣ የቻለው ታህሳስ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ቃሉ ወረዳ 029 ቀበሌ ልዩ ቦታው ገረገራ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ የ7 ዓመት ታዳጊ ህፃን ልጅ አስገድዶ በመድፈሩ የተነሳ ነው። የወረዳው ፖሊስ ከማህበረሰቡ በደረሰው ጥቆማ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር በማዋል የምርመራ መዝገቡን በሰውና በቴክኒክ ማስጃ አጠናክሮ መዝገቡን ለሚመከተው የፍትህ አካል ልኳል።

የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍረድ ቤትም ጉዳዩን ሲመረምር ከቆዬ በኋላ ተከሳሹ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ የካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ17 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ እና ለ 4 ዓመት ያህል ከማንኛውም ህዝባዊ መብቶች እንዲታገድ ተወስኖበታል ሲል  የቃሉ ወረዳ ፖሊስ ኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ክፍል አስታውቋል።

@Yenetube @Fikerassefa


በአዲስ አበባ ከተማ በእንቁላል ዋጋ ላይ በተደረገው ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በቂ ጥናት አለመደረጉን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ

በአዲስ አበባ ከተማ ከሌላው ጊዜ በተለየ በእንቁላል ላይ በተደረገው የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ዙሪያ በቂ ጥናት አለመደረጉን  ሚኒስቴሩ ይፋ አድርጓል።

በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ የተለያዩ የግብይት ቦታዎች የእንቁላል ዋጋ ምን እንደሚመስል ብስራት ባደረገው የገበያ ቅኝት አንድ የሀበሻ እንቁላል ከ20 ብር በላይ እንዲሁም የፈረንጅ እንቁላል ደግሞ በ18 ብር እንደሚሸጥ ለማወቅ ችሏል።

በምርቱ ዙሪያ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ የታየው በምን ምክንያት ነው ሲል ብስራት ላቀረበው ጥያቄ በሚኒስቴሩ የእንስሳትና አሳ ሀብት ልማት  መሪ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ፅጌረዳ ፍቃዱ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን እንደገለፁት ይህ የሆነበትን ምክንያት ለማወቅ  ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

አያይዘውም ሁኔታውን ያባባሰው የአቅርቦት ችግር ይሁን፣የነዳጅ ዋጋ መጨመር እንዲሁም በገበያ ሰንሰለቱ ውስጥ የተፈጠሩ ሌሎች መንስኤዎች ካሉ ክትትል ማድረግና ለዋጋ ጭማሪው መነሻ መንስኤውን መለየት ይገባል ብለዋል።በሌላ በኩል እንቁላልን አስመልክቶ ጥሩ የሚባል ምርት መኖሩን የገለፁት መሪ ስራ አስፈፃሚዋ ባለፋት ስድስት ወራት ብቻ ከእቅድ በላይ መመረቱን ተናግረዋል።

በዚህ ጊዜ ውስጥም 4 ቢሊየን እንቁላልን እንደ ሀገር ለማምረት ታቅዶ እንደነበር ተናግረው ከእቅድ በላይ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንቁላል መመረቱን አስረድተዋል።ከሰሞኑን በተለየ መልኩ በእንቁላል ላይ እየታየ የሚገኘውን የዋጋ ንረት ለማስቆም ምርቱን በስፋት ከማቅረብ ባለፈ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉት አካላት ላይ ክትትል ማድረግ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

@Yenetube @Fikerassefa


አቅመ ደካማወችን በነፃ ሀኪም ጥበቡ

እውነታውን ቻናሉን በመቀላቀል የብዙሀኖችን ድምፅ እንስማ

ታምራዊ ፈውስ እና ሰወች ከነበራቸው ህምም በሽታ ሲፈወሱ ሲመሰክሩ እንባቸው ሲታበስ  የምናይበትን ቻናል በመቀላቀል አይተን ተረድተን ለሌሎች ሸር እናድርግ  ኢትዮጵያውይነት ደግነት
    👇
https://vm.tiktok.com/ZMkQ1pTSL/
    ለበለጠ መረጃ
      ሀኪም ጥበቡ
0912718883
0917040506 በቴሌግራም በውስጥ መስመር የሚፈልጉትን ያስቀምጡ
👉አድራሻችን አዲስ አበባ አየር ጤና ካራቆሬ ወደመድኀኒአለም 200ሜትር ገባ ይበሉ
ቁጥር 2ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በአሮየው 
አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት ያገኙናል ይምጡ
ይፈወስ
https://vm.tiktok.com/ZMkQJh8WX/


‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251923931130
    


Australia work visa
አውስትራሊያ የሥራ ቪዛ
መሥፈርቶች
የታደሰ ፖስፖርት
እድሜ ከ 18_35
የትምህርት ደረጃ: Highschool እና ከዛ በላይ

የስራወቹ አይነት
የኮንስትራክሽን ሥራዎች
የግብርና ሥራዎች

ደሞዝ በሰአት ከ25-35 ዶላር
አኮሜዴሽን ያለው
የጤና ኢንሹራንስ ያለው
ከ 2 አመት በኋላ የመኖሪይ ፍቃድ ማግኘት የምትችሉበት እና ቤተሰባችሁን የምትወስዱብት እድልም ይፈጥራል

ፕሮሰስ ግዜ ከ 2-3 ወር ይፈጃል
የመሳካት እድሉ ከ 95%
   በተጨማሪ

እርሶ ወደ የትኛው ሀገር መሄድ አስበዋል፡፡
ካናዳ፡ አሜሪካ፡ አውስትራሊያ ፡አውሮፓ ወይስ ወደ በሌሎች አለም ሀገራት
ለሁሉም ከሳቢና መልስ አለ
የስራ ቪዛ
የቢዝነስ ቪዛ
የቤተሰብ ቪዛ
የትምህርት ቪዛ
የጉብኝት ቪዛ
የህክምና ቪዛ
የተለያዩ ሁነቶች ላይ ለመታደም የሚያገለግል ቪዛ የማማከር አገልግሎት
እንዲሁም የአየር ቲኬት
ሆቴል ቡኪንግ
የኢንባሲ ቀጠሮዎችን ማመቻቸት
ለተጓዦች ለጉዞ የሚረዱ ስልጠናዎችን እንሰጣለን፡፡
ለሚፈልጉት አገልግሎትና የጉዞ ጉዳዮች ሳቢናን ምርጫዎ ያድርጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳዮ መፍትሄ ያገኛል፡፡

   👇👇  ለበለጠ መረጃ 👇👇

Contact Us:

@Sabinavisa2

☎️👇

🤳ስልክ  ቁጥራችን 0927555551/2/3/4/7/8

Website

https://sabina.et/

👉 ወደ ቢሮአችን ይምጡ !
👉 ሃያ ሁለት ታውን ስኩዬር ህንፃ 6ኛ ቢሮ ቁጥር 602

እንዲሁም በ ሀዋሳ ቱሩፋት ወርቁ ቡቼ ታወር ፊት ለፊት አዲስ የ ገበያ ማዕከል ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201

ከታላቅ አክብሮት ጋር   !!!

https://t.me/sabinaadvisor


የሕዳሴ ግድብ አምስተኛው ተርባይ ኃይል ማመንጨት ጀመረ!

የቅድመ ኃይል ማመንጨት ሙከራ ስራ በተሳካ ሁኔታ ተከናውኖባቸው ወደ ዋና ስራቸው እንዲገቡ ዝግጁ ከሆኑ ተርባይኖች መካከል ተርባይን ቁጥር 6 የሙከራ ስራው ተጠናቆ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀምሯል።አሁን ባለው ተጨባጭ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም እስከ 401.26 MW ኃይል እያመነጨ ይገኛል።

በተጨማሪ ተርባይን ቁጥር 5 ደግሞ የኮሚሽኒንግ ስራው የመጨረሻ ምዕራፍ ሙከራ ላይ ይገኛል ሲል ኢፕድ ነው የዘገበው፡፡የግድቡ ስድስተኛው ተርባይን የሆነው ተርባይን ቁጥር 5 በቅርቡ ማለፍ ያለበትን የሙከራ ሂደቶቹን አጠናቆ ወደ ማመንጨት ስራ እንደሚገባም የማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤቱ መረጃ ያመለክታል ሲል አክሏል።

@YeneTube @FikerAssefa


አፍሪካ የዕዳ ቀውስን ለመከላከል የ20 ቢሊዮን ዶላር ፈንድ አቋቋመች!

የአፍሪካ መሪዎች በአህጉሪቱ ሊከሰቱ የሚችሉ የዕዳ ቀውሶችን አስቀድሞ ለመከላከል ያለመ የ20 ቢሊዮን ዶላር አህጉራዊ የፋይናንስ ማረጋጊያ ፈንድ ማቋቋምን አጽድቀዋል ሲል የአፍሪካ ልማት ባንክ አስታውቋል።ይህ እርምጃ አፍሪካ የራሷ የፋይናንስ ድጋፍ እንዲኖራት ከማስቻሉም በላይ አገራቱ ለከፍተኛ የዕዳ ጫናዎች እንዳይጋለጡ እንደሚረዳ ተጠቁሟል።

ይህ ፈንድ፣ የአፍሪካ የፋይናንስ ማረጋጊያ ዘዴ በመባል የሚታወቀው፣ በአለም አቀፋዊ የካፒታል ገበያዎች ላይ ለመበደር የሚያስችለውን የራሱን የብድር ደረጃ ያገኛል።ይህ ማለት ፈንዱ ለተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ ለመስጠት የሚያስችል በቂ ገንዘብ ማግኘት ይችላል ያስችለዋል ተብሏል።

የአፍሪካ ልማት ባንክ ይህን ፈንድ የማስተዳደር ኃላፊነት እንደሚወስድ የተገለፀ ሲሆን የአፍሪካ ሀገራት ለሚገጥሟቸው የኢኮኖሚ ተግዳሮቶች ምላሽ ለመስጠት እና ዘላቂ ልማትን ለማበረታታት ይህን ፈንድ እንደሚጠቀምበት ተገልጿል።አፍሪካ ለረጅም ጊዜ የራሷ የፋይናንስ ድጋፍ ስለሌላት ለውጭ ዕዳ እና ለኢኮኖሚ ድክመቶች በጣም ተጋላጭ ነበረች።ይህ አዲስ ፈንድ አፍሪካ እነዚህን ተግዳሮቶች እንድትቋቋም እና የራሷን ኢኮኖሚ እንድታሳድግ ይረዳታል ተብሎ ይጠበቃል።

Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa


''ብልፅግና የምክክር ኮሚሽንን የመንግስት የአስተዳደር ሥርዓት ከፓርላመንታሪ ወደ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት ለማሸጋገር ላለው ፍላጎት ማሳኪያ መሳሪያ ሊያደርገው መሆኑ ይነሳል'' -የምክር ቤት አባል

ብልፅግና ፓርቲ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የመንግስት የአስተዳደር ሥርዓት ከፓርሊያመንታሪ ወደ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት ለማሸጋገር ላለው ፍላጎት ማሳኪያ መሳሪያ ሊያደርገው መሆኑ በህዝብ ዘንድ ይነሳል ሲሉ አንድ የምክር ቤት አባል ተናገሩ፡፡ይህን የተናገሩት የምክር ቤት አባል ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) ናቸው፡፡

ዶክተር ደሳለኝ ይህንን የተናገሩት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የስራ ዘመኑ የካቲት 14 አርብ ሊጠናቀቅ ለነበረው #የሀገራዊ_ምክክር_ኮሚሽን ተጨማሪ የአንድ ዓመት የስራ ዘመን ለመጨመር እና የሶስቱን ዓመት የስራ ክንውን ሪፖርት ለማዳመጥ በጠራው ስብሰባ ላይ ነው፡፡

በፓርላማው የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትሩ ተስፋዬ ቤልጅጌ (ዶ/ር) በበኩላቸው የፕሬዘዳንታዊ የአስተዳደር ስርዓት ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል ከተባለ እንደ አንድ ባለድርሻ አካል በአጀንዳነት ይዘን ልናቀርብ እንችላለን ብለዋል፡፡

የምክር ቤት አባሉ ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ምን ያህል ህዝብ የምክክር ሂደቱን ህጋዊ ነው ብሎ ያምናል? ለደረቅ ፕሮፓጋንዳ ሲባል እንደ ዓይኑ ብሌን ነው የሚጠብቀው ልንል እንችላለን ወይ? ግን ደግሞ ሰፊ ጥርጣሬ እንዳለ መካድ የለብንም ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በዋንኛነትም ብልፅግና የሆኑ የፖለቲካ አላማዎቹን ለማሳካት የሚጠበቅበት በግልፅ እንደሚነገረው ላንሳ የመንግስት የአስተዳደር ስርዓቱን ከፓርላሜንታዊ ወደ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት ለማድረግ የሚፈለገውን ሽግግር ማስኬጃ መሳሪያ ነው ተብሎ በህዝብ ዘንድ ይነሳል ብለዋል፡፡ስለዚህ በአግባቡ ለህዝብ ማስረዳት መቻል አለብን ሲሉ ዶክተር ደሳለኝ ተናግረዋል፡፡

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚንስትር የሆኑት ዶክተር ተስፋዬ በልጅጌ በበኩላቸው እንደራሴው ላነሱት ሃሳብ በሰጡት መልስ የኢትዮጵያ ህዝብ ከጫፍ እስከ ጫፍ አሁን እያነሱ ያለው ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሆይ ፍጠኑ ነው የሚለው ሲሉ አስረድተዋል፡፡

በህዝብ ዘንድ ኮሚሽኑ ቅቡልነት አለው ያሉት ዶክተር ተስፋዬ ነገር ግን የተወሰኑ አካላት ቅቡልነት እንዳይኖረው የሚያደርጉ አሉ ሲሉ ከሰዋል፡፡ብልፅግና ለሀገራዊ ምክክር እንደ አንድ ባለድርሻ አካል ይዞ የሚቀርባቸው የራሱ አጀንዳዎች አሉት ያሉት ዶክተር ተስፋዬ ወቅቱ እና ጊዜው ሲደርስ ይቀርባል ብለዋል፡፡

ብልፅግና ፓርቲ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት ለዚህ ሃገር ያስፈልጋል ከተባለ ይዘን ልንቀርብ እንችላለን ምን ችግር አለው? ምን የሚያስፈራ ነገርስ አለው? ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ኮሚሽኑ በህዝብ ዘንድ ያለውን ቅቡልነት በተመለከተ ምላሽ የሰጡት የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ በተለያዩ አካባቢዎች የተመለከትነው ህዝብ በኮሚሽኑ ላይ ከፍተኛ እምነት እንዳለው ነው ብለዋል፡፡

Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa


እቅዳችን ሳይሳካ ቀርቷል ጌታቸው ረዳ

በሃይማኖት አባቶች የተጀመረው ህወሓትን የማሸማገል እና የእርቅ የማድርግ ሙከራ እንዲሁም የካቲት 11'ን በጋራ የማክበር እንቅስቃሴ አልተሳካም ሲሉ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ገልፀዋል

@Yenetube @Fikerassefa


ሳልሳይ ወያነ ትግራይ ባወጣው መግለጫ ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ ያደረጉትን ንግግር እንደሚቃወም ገልጿል፡፡

የአፍሪካ ህብረት የምስራቅ አፍሪካ ልዩ መልእክተኛ የሆኑት ኦባሳንጆ ትላንት በተከናወነው የፕሪቶሪያ ስምምነትን በሚገመግም ስብሰባ ላይ የትግራይ በህገ መንግስቱ የተካተቱ ቀሪ መሬቶች በገለልተኛ አካል ቁጥጥር ስር መሆን እንደሚገባቸው ሀሳብ መስጠታቸውን ጠቅሷል፡፡

"ይህንን ማለታቸው መሬቶቹ በኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስትና አጋሮቹ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማለት ነው›› ያለው መግለጫው ይሁንና የፌዴራል መንግስቱ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተደራዳሪ አንድ አካል እንጂ ገለልተኛ እንዳልሆነ አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም እነዚህ መሬቶች በአሁኑ ወቅት በፌዴራል መንግስቱና አጋሮቹ እጅ የወደቁት የትግራይ ተወላጆችን በማፈናቀልና ዘር ማፅዳትን ጨምሮ አለም አቀፍ ወንጀሎችን በመፈፀም መሆኑን አስረድቷል፡፡ ስለዚህም የኦባሳንጆ ንግግር የፕሪቶሪያን ስምምነት መንፈስና ድንጋጌዎች የሚጥስ መሆኑን ገልፆ ንግግሩን አጥብቆ እንደሚያወግዝ አስታውቋል፡፡

@Yenetube @Fikerassefa


Репост из: HuluPay Community
በTelegram ላይ የተረጋገጠ ምልክት (Verified Checkmark) ለማግኘት የእርስዎን አካውንት አሁን Premium ያድርጉት

Telegram Premium በመግዛት የተረጋገጠ ምልክት ያግኙ!
በHulupay በTelebirr አማካኝነት በቀላሉ ይክፈሉ።


ፍርድ ቤቱ : በነጻ እንዲሰናበቱ ወስኗል

#Ethiopia | በፌዴራል ፍርድ ቤት ሀዋሳ ምድብ ችሎት ተይዞ የነበረዉ የረ/ፕ ጸጋዬ ቱኬ፣ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ኮሚሽነር አበራ አሬራና እንዲሁም የረ/ፕሮፈሰሩ የእህት ልጅ አብረሃም አማሎ ክስ ፍርድ ቤቱ በ11/06/2017 ዓ.ም በዋለዉ ችሎት በነጻ እንዲሰናበቱ ወስኗል።

በሦስቱ ተከሳሾች ላይ የክልሉ አቃቤ ሕግ በሙስና ፈጽመዋል በሚል ክስ አቅርቦባቸዉ ሲከራከሩ የቆዩ ሲሆን ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ሲያከራክር ከቆየ በኋላ ነጻ መሆናቸዉን አረጋግጦ ከቀረበባቸዉ የሀሰተኛ ክስ ነጻ አዉጥቷቸዋል ሲሉ ጠበቃ ገብረመድህን ተክላይ በስልክ አድርሰውኛል።

የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ እና የቀረቡባቸውን ክሶች የማይገባ ጥቅም በመቀበል የሙስና ወንጀል በመፈጸም እና በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ በማቅረብ የተከሰሱት የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጸጋዬ ቱኬ፤ በቀረቡባቸው ሁለት ክሶች ላይ እንዲከላከሉ ብይን ተሰጥቶ ነበር። በቀድሞው ከንቲባ እና አብረዋቸው በተከሰሱ ሁለት ተከሳሾች ላይ ጥቅምት 19፣ 2017 ብይኑን የሰጠው፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሀዋሳ ማዕከል ነው።

የሲዳማ ክልል ፍትህ ቢሮ፤ በአቶ ጸጋዬ እና ሁለት ተከሳሾች ላይ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ የመሰረተው፤ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር መጀመሪያ ላይ ነበር። በአንድ መዝገብ ክስ ከቀረበባቸው ተከሳሾች መካከል፤ የሲዳማ ክልል የቀድሞ የፖሊስ ኮሚሽነር አቶ አበራ አሬራ ይገኙበታል።

የክልሉ ዐቃቤ ህግ በአቶ አበራ እና በአቶ ጸጋዬ ላይ የመሰረተው የመጀመሪያ ክስ፤ በሙስና ወንጀሎች አዋጅ የተቀመጠን ድንጋጌ በመተላለፍ “የማይገባ ጥቅም በመቀበል የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል” የሚል ነው።

የመጀመሪያው ክስ፤ በሀዋሳ ከተማ ሳውዝ ስታር ኢንተርናሽናል ሆቴል ጎን የተወሰደ ቦታ ምትክ መሬት እንዲሰጥ ከቀረበ ጥያቄ ጋር የተያያዘ ነው።

የምትክ ቦታ ጥያቄ ቀርቦ የነበረው፤ ከአቶ ጸጋዬ አስቀድሞ በነበሩት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ የአመራር ጊዜ እንደነበር በክሱ ተመላክቷል። አቶ ጥራቱ የምትክ ቦታ እንዲሰጥ ውሳኔ ቢያስተላልፉም፤ የመሬት ርክክብ ከመፈጸሙ በፊት ከኃላፊነታቸው በመነሳታቸው ጉዳዩ እርሳቸውን ለተኳቸው አቶ ጸጋዬ ተላልፏል የሚል ነበር።

ዛሬ በዋለው ችሎት ሦስቱንም የፌዴራል ፍርድ ቤት ሀዋሳ ምድብ ችሎት በነጻ አሰናብቷቸዋል ፤ ሁለተኛው ክስ በክልሉ ፍርድ ቤት የሚታይ ይሆናል ሲሉ ጠበቃ ገብረመድህን ተክላይ አስረድተዋል።

@Yenetube @Fikerassefa




ጀርመን ካለ አሜሪካ ፍቃድ ወታደሮቼን ወደ ዩክሬን አልክም አለች

አሜሪካ ያልተሳተፈችበትን በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ተልዕኮ ላይ ወታደሮቿን እንዳማትልክ ጀርመን አስታዉቃለች፡፡

ያለ አሜሪካ ተሳትፎና ዕዉቅና የአዉሮፓ ወታደሮች ወደ ዩክሬን ቢላኩ ኃላፊነት እንደምትወሰድም የአገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣን መናገራቸዉን አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል፡፡

ከጀርመን በተጨማሪም ፖላንድ ጦሯን ወደ ዩክሬን እንዳምትልክ አስታዉቃለች፡፡

የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ጦራቸዉን ወደ ዩክሬን እንደሚልኩ ማሳወቃቸዉ አይዘነጋም፡፡

@Yenetube @Fikerassefa


ዜና፡ በ #ሰሜን_ጎጃም ዞን ህጻን ያዘሉ ሴት አስተማሪዎችን ጨምሮ 13 መምህራን "በፋኖ ታጣቂዎች" መታገታቸውን ቤተሰቦቻቸው ተናገሩ

በ #አማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ጎንጂ ቆላላ ወረዳ ኮሬ ጣንክሪ ቀበሌ በሚገኝ ኮሬ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት በማስተማር ላይ የነበሩ 13 መምህራን "በፋኖ ታጣቂዎች" ረቡዕ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ታግተው መወሰዳቸውን የታጋች ቤተሰቦች ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸውን እንዳንጠቅስ የጠየቁ አንድ የታጋች ቤተሰብ መምህራኑ "በባጃጅ በመጡ ታጣቂዎች" መወሰዳቸውን ጠቅሰው፤ ታጣቂዎቹ "ስርዓቱን ተቃውመን እየታገልን እናንተ ለምን ታስተምራላችሁ" በሚል በነፍስ ወከፍ እያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር ቅጣት እንዲከፍሉ ካልሆነ ግን እንደማይለቀቁ አስጠንቅቀዋል ሲሉ ገልጸዋል።

ታግተው ከተወሰዱ መምህራን ውስጥ ልጃቸው እንደምትገኝ የገለጹ አንድ ወላጅ አባት በበኩላቸው ትምህርት አስተምሩ መባሉን ተከትሎ አንድ ልጇን አዝላ ወደ ጎንጂ ቆለላ ወረዳ በሚገኘው ኮሬ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የሄደች ልጃቸው መታገቷንና ይህንንም በእጅ ስልካቸው ተደውሎ እንደተነገራቸው አስረድተዋል።

@Yenetube @Fikerassefa


Australia work visa
አውስትራሊያ የሥራ ቪዛ
መሥፈርቶች
የታደሰ ፖስፖርት
እድሜ ከ 18_35
የትምህርት ደረጃ: Highschool እና ከዛ በላይ

የስራወቹ አይነት
የኮንስትራክሽን ሥራዎች
የግብርና ሥራዎች

ደሞዝ በሰአት ከ25-35 ዶላር
አኮሜዴሽን ያለው
የጤና ኢንሹራንስ ያለው
ከ 2 አመት በኋላ የመኖሪይ ፍቃድ ማግኘት የምትችሉበት እና ቤተሰባችሁን የምትወስዱብት እድልም ይፈጥራል

ፕሮሰስ ግዜ ከ 2-3 ወር ይፈጃል
የመሳካት እድሉ ከ 95%
   በተጨማሪ

እርሶ ወደ የትኛው ሀገር መሄድ አስበዋል፡፡
ካናዳ፡ አሜሪካ፡ አውስትራሊያ ፡አውሮፓ ወይስ ወደ በሌሎች አለም ሀገራት
ለሁሉም ከሳቢና መልስ አለ
የስራ ቪዛ
የቢዝነስ ቪዛ
የቤተሰብ ቪዛ
የትምህርት ቪዛ
የጉብኝት ቪዛ
የህክምና ቪዛ
የተለያዩ ሁነቶች ላይ ለመታደም የሚያገለግል ቪዛ የማማከር አገልግሎት
እንዲሁም የአየር ቲኬት
ሆቴል ቡኪንግ
የኢንባሲ ቀጠሮዎችን ማመቻቸት
ለተጓዦች ለጉዞ የሚረዱ ስልጠናዎችን እንሰጣለን፡፡
ለሚፈልጉት አገልግሎትና የጉዞ ጉዳዮች ሳቢናን ምርጫዎ ያድርጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳዮ መፍትሄ ያገኛል፡፡

   👇👇  ለበለጠ መረጃ 👇👇

Contact Us:

@Sabinavisa2

☎️👇

🤳ስልክ  ቁጥራችን 0927555551/2/3/4/7/8

Website

https://sabina.et/

👉 ወደ ቢሮአችን ይምጡ !
👉 ሃያ ሁለት ታውን ስኩዬር ህንፃ 6ኛ ቢሮ ቁጥር 602

እንዲሁም በ ሀዋሳ ቱሩፋት ወርቁ ቡቼ ታወር ፊት ለፊት አዲስ የ ገበያ ማዕከል ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201

ከታላቅ አክብሮት ጋር   !!!

https://t.me/sabinaadvisor

Показано 20 последних публикаций.