ወደ አላህ እንሺሽ‼
============
✍ አቡ ሁረይራህ እንዲህ ብለዋል፦ "ከጎጆዋ ውስጥ ያለች አሞራ በበዳይ በደል ምክንያት ትሞታለች።" ሙጃሂድ የተባሉ ዐሊምም እንዲህ ብለዋል፦ "እንስሳት ድርቅ በበረታ ጊዜ፤ የሰውን ልጅ ይረግማሉ። 'ይህ ሁሉ የሆነው በአደም ልጅ ጥፋት ነው!' ይላሉ።" ዒክሪማህም እንዲህ ብለዋል፦ "የምድር እንስሳትና ነፍሳት፤ እባብና ጊንጥ እንኳ ሳይቀሩ \በአደም ልጅ ጥፋት ምክንያት ዝናብ ተከለከልን!' ይላሉ።"
||
አውስትራሊያ የብዙ ፈሳድ መነኻሪያ ናት።
ለሙስሊሞችም አትመችም።
የህዝቧ ወንጀል መዘዙ ለዱር አራዊቷም ተርፏል።
በአውስትራሊያ ሰደድ እሳት እየተሰቃዩ ያሉ እንስሳት በጣም ያሳዝናሉ።
ሸሽተው ሸሽተው ሲደርስባቸው ያሳርራቸዋል።
እናት ልጇን ታቅፋ ለራሷ እየተቃጠለች፤ ከደቂቃዎች በኋላ እርሷንም ይጨምራታል።
ብቻ ያሳዝናሉ።
♠
ወንድሜ ሆይ! አደራ ስውር ወንጀልን ተጠንቀቅ። በውጭ ስትታይ መልካም መስለህ፤ በውስጥ ግን እኩይ አትሁን። ሁልጊዜም አላህ በእውቀቱ ከአንተ ጋር መሆኑን አስብ፤ ያይሀል፣ ይሰማሀል። አቡ ደርዳዕ እንዲህ ብለዋል፦ "አላህን እንደምታዩት አድርጋችሁ ተገዙት። ራሳችሁን ከሙታን ቁጠሩ። ከሚያበላሻችሁ ብዙ ሐብት ይልቅ የሚበቃችሁ ጥቂት በላጭ ነው። በጎ ሥራ እንደማይጠፋ፣ ወንጀል እንደማይረሳ እወቅ።" [አሕመድ ዘግበውታል።]
ሱለይማን አት-ተሚሚ እንዲህ ይላሉ፦ "አንድ ሰው በሚስጥር ወንጀል ሲፈጽም፤ ውርደቱ ከርሱ ላይ የተገለጸ ሁኖ ያነጋል።"
ዘኑን የተባሉ ዐሊምም "አላህን በሚስጥር የከዳ፤ ሚስጥሩን አላህ ይፋ ያወጣበታል!" ብለዋል። በአጠቃላይ ሐቢቢ "በድብቅ ወንጀል ስትሠራ፤ ገልጦ የሚያይህ አምላክ እንዳለ አትዘንጋ።" በቃ! የትም አታመልጠውምና ፍራው። "ወንጀል" የእውቀትን ችሎታ ይጋርዳል፣ ግንዛቤን ይዘጋል፣ ሲሳይን ያቅባል፣ ደስታን ያሳጣል፣ ከሰዎች ጋር ያቃቅራል፣ ነገሮችን ይቆላልፋል፣ መነገዶች እንዲዘጋጉና እንዲውሰበሰቡ ያደርጋል፣ ቀልብን ጽልመት ያወርሳል፣ ከበጎ ሥራ ያቅባል፣ እድሜን ያሳጥራል፣ አካልንም ልብንም ያደክማል፣ ሌላ ወንጀልንም ይወልዳል፣ ያዋርዳል፣ አዕምሮንና ቀልብን ይበክላል፣ ለእርግማን ይዳርጋል፣ በመጪው አለም ያስቀጣል፣ ይሉኝታን ያሳጣል፣ አላህን የማላቅ ስሜትን ያሟኣሽሻል፣ ከአላህ ጋር ያጣላል፣ ጸጋን ያስወግዳል፣ ብቀላን ያሰንፋል፣ የሰይጣንና ከንቱ ስሜት ምርኮኛ ያደርጋል። ስለዚህ ወንድሜ! አደራህን ከወንጀል ራቅ። ዛሬ በአለም ላይ በሙስሊሞች ላይ እየደረሰ ባለው ስቃይና መከራ የኔና ያንተ ወንጀል የፈጠረው ውጤት ሊሆን እንደሚችል አስብ። ምክንያቱም የወንጀል ቅጣት ለወንጀል ሠሪው ብቻ ላይሆን ይችላል።
||
በመልካም ዱዓችን አንርሳቸው።
ወደ አላህም እንሽሽ።
በኛ ላይ ለሚደርሱብን ጥቃቶች ዋናው መነሻ የራሳችን ወንጀልና ከአላህ ትዕዛዝ ማፈንገጥ ነው።
መፍትሄው ደግሞ ወደ አላህ መመለስ ብቻና ብቻ ነው።
አላህ በቁርኣን ላይ እንዲህ ይለናል፦
(وَمَا أَصَابَكُم مِّن مُّصِيبَةٍ فَبِمَا كَسَبَتْ أَيْدِيكُمْ وَيَعْفُو عَن كَثِيرٍ)
«ከመከራም ማንኛውም ያገኛችሁ ነገር፣ እጆቻችሁ በሰሩት (ኀጢያት) ምክንያት ነው፤ ከብዙውም ይቅር ይላል።»
[አሽ-ሹራ፡ 30]
*
✔️ የሚያገኘን መከራ ሁሉ መንስኤው እጃችን የከሰበችው ወንጀል ከሆነ፤
መከራው ይነሳ ዘንድ እጃችን ከወንጀል መሰብሰብ አለባት ማለት ነው። ይህን የነገረን እውነተኛው አምላካችን አላህ ነው። መቀበል እንጂ ቅንጣት ማመንታት አያስፈልግም።
||
Murad Tadesse
============
✍ አቡ ሁረይራህ እንዲህ ብለዋል፦ "ከጎጆዋ ውስጥ ያለች አሞራ በበዳይ በደል ምክንያት ትሞታለች።" ሙጃሂድ የተባሉ ዐሊምም እንዲህ ብለዋል፦ "እንስሳት ድርቅ በበረታ ጊዜ፤ የሰውን ልጅ ይረግማሉ። 'ይህ ሁሉ የሆነው በአደም ልጅ ጥፋት ነው!' ይላሉ።" ዒክሪማህም እንዲህ ብለዋል፦ "የምድር እንስሳትና ነፍሳት፤ እባብና ጊንጥ እንኳ ሳይቀሩ \በአደም ልጅ ጥፋት ምክንያት ዝናብ ተከለከልን!' ይላሉ።"
||
አውስትራሊያ የብዙ ፈሳድ መነኻሪያ ናት።
ለሙስሊሞችም አትመችም።
የህዝቧ ወንጀል መዘዙ ለዱር አራዊቷም ተርፏል።
በአውስትራሊያ ሰደድ እሳት እየተሰቃዩ ያሉ እንስሳት በጣም ያሳዝናሉ።
ሸሽተው ሸሽተው ሲደርስባቸው ያሳርራቸዋል።
እናት ልጇን ታቅፋ ለራሷ እየተቃጠለች፤ ከደቂቃዎች በኋላ እርሷንም ይጨምራታል።
ብቻ ያሳዝናሉ።
♠
ወንድሜ ሆይ! አደራ ስውር ወንጀልን ተጠንቀቅ። በውጭ ስትታይ መልካም መስለህ፤ በውስጥ ግን እኩይ አትሁን። ሁልጊዜም አላህ በእውቀቱ ከአንተ ጋር መሆኑን አስብ፤ ያይሀል፣ ይሰማሀል። አቡ ደርዳዕ እንዲህ ብለዋል፦ "አላህን እንደምታዩት አድርጋችሁ ተገዙት። ራሳችሁን ከሙታን ቁጠሩ። ከሚያበላሻችሁ ብዙ ሐብት ይልቅ የሚበቃችሁ ጥቂት በላጭ ነው። በጎ ሥራ እንደማይጠፋ፣ ወንጀል እንደማይረሳ እወቅ።" [አሕመድ ዘግበውታል።]
ሱለይማን አት-ተሚሚ እንዲህ ይላሉ፦ "አንድ ሰው በሚስጥር ወንጀል ሲፈጽም፤ ውርደቱ ከርሱ ላይ የተገለጸ ሁኖ ያነጋል።"
ዘኑን የተባሉ ዐሊምም "አላህን በሚስጥር የከዳ፤ ሚስጥሩን አላህ ይፋ ያወጣበታል!" ብለዋል። በአጠቃላይ ሐቢቢ "በድብቅ ወንጀል ስትሠራ፤ ገልጦ የሚያይህ አምላክ እንዳለ አትዘንጋ።" በቃ! የትም አታመልጠውምና ፍራው። "ወንጀል" የእውቀትን ችሎታ ይጋርዳል፣ ግንዛቤን ይዘጋል፣ ሲሳይን ያቅባል፣ ደስታን ያሳጣል፣ ከሰዎች ጋር ያቃቅራል፣ ነገሮችን ይቆላልፋል፣ መነገዶች እንዲዘጋጉና እንዲውሰበሰቡ ያደርጋል፣ ቀልብን ጽልመት ያወርሳል፣ ከበጎ ሥራ ያቅባል፣ እድሜን ያሳጥራል፣ አካልንም ልብንም ያደክማል፣ ሌላ ወንጀልንም ይወልዳል፣ ያዋርዳል፣ አዕምሮንና ቀልብን ይበክላል፣ ለእርግማን ይዳርጋል፣ በመጪው አለም ያስቀጣል፣ ይሉኝታን ያሳጣል፣ አላህን የማላቅ ስሜትን ያሟኣሽሻል፣ ከአላህ ጋር ያጣላል፣ ጸጋን ያስወግዳል፣ ብቀላን ያሰንፋል፣ የሰይጣንና ከንቱ ስሜት ምርኮኛ ያደርጋል። ስለዚህ ወንድሜ! አደራህን ከወንጀል ራቅ። ዛሬ በአለም ላይ በሙስሊሞች ላይ እየደረሰ ባለው ስቃይና መከራ የኔና ያንተ ወንጀል የፈጠረው ውጤት ሊሆን እንደሚችል አስብ። ምክንያቱም የወንጀል ቅጣት ለወንጀል ሠሪው ብቻ ላይሆን ይችላል።
||
በመልካም ዱዓችን አንርሳቸው።
ወደ አላህም እንሽሽ።
በኛ ላይ ለሚደርሱብን ጥቃቶች ዋናው መነሻ የራሳችን ወንጀልና ከአላህ ትዕዛዝ ማፈንገጥ ነው።
መፍትሄው ደግሞ ወደ አላህ መመለስ ብቻና ብቻ ነው።
አላህ በቁርኣን ላይ እንዲህ ይለናል፦
(وَمَا أَصَابَكُم مِّن مُّصِيبَةٍ فَبِمَا كَسَبَتْ أَيْدِيكُمْ وَيَعْفُو عَن كَثِيرٍ)
«ከመከራም ማንኛውም ያገኛችሁ ነገር፣ እጆቻችሁ በሰሩት (ኀጢያት) ምክንያት ነው፤ ከብዙውም ይቅር ይላል።»
[አሽ-ሹራ፡ 30]
*
✔️ የሚያገኘን መከራ ሁሉ መንስኤው እጃችን የከሰበችው ወንጀል ከሆነ፤
መከራው ይነሳ ዘንድ እጃችን ከወንጀል መሰብሰብ አለባት ማለት ነው። ይህን የነገረን እውነተኛው አምላካችን አላህ ነው። መቀበል እንጂ ቅንጣት ማመንታት አያስፈልግም።
||
Murad Tadesse