አዲስ ሪፖርተር - NEWS


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !
=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !
🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addis_reporter_bot
#ADDIS ABABA, ETHIOPIA

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


የአሜሪካው የተራድዖ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) ዕርዳታ መቋረጥ፣ በመላው ኢትዮጵያ ከባድ ንዝረት ፈጥሯል ሲል ዘ ጋርዲያን ዘግቧል

በዕርዳታ ዕገዳው ሳቢያ፣ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ኢትዮጵያ ውስጥ ለተጠለሉ 800 ሺሕ ለሚጠጉ ስደተኞች ይሰጥ የነበረውን ዕርዳታ በ40 በመቶ መቀነሱን ዘገባው ጠቅሷል።

በተያዘው የአውሮፓውያኑ ዓመት የምግብ ዕርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር ወደ 5 ሚሊዮን የተቀነሰበት አንዱ ምክንያት፣ የዕርዳታ ድርጅቶቹ እጅጉን ዕርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ብቻ ዕርዳታ እንዲያቀርቡ የሚያስገድድ ኹኔታ በመፍጠሩ መኾኑንም ጋዜጣው ጠቅሷል።

አሁን ባለው ተጨባጭ ኹኔታ፣ የዓለም ምግብ ፕሮግራም የምግብ አቅርቦቶቹን ከጨረሰ፣ ተጨማሪ የዕርዳታ ምግብ መግዛት እንደማይችልና ማሽላና የምግብ ዘይትን ጨምሮ 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎችን ላንድ ወር መመገብ የሚችል 34 ሺሕ 800 ሜትሪክ ቶን እህል፣ ወደ አገር ውስጥ ለሚያስገቡ ኮንትራክተሮች የሚከፈል ገንዘብ ባለመኖሩ ጅቡቲ ወደብ ላይ መቆሙንም የዜና ምንጩ ጠቅሷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


♨️ እንኳን ደስ አላችሁ ለመላው ስራ ፈላጊ ኢትዮጲያዊያን!
  -----------------------------------
✅ Make Money Online In Ethiopia 2025 🇪🇹 ✅

           በቀን 3000 ብር የሚከፍል ዌብሳይት

15,000- በላይ ክፍት ቦታዎች በ0 አመት  እና በልምድ

🔺የትምህርት አይነት: በተለያዩ ዲፓርትመንቶች
🔺የስራ ልምድ: በ 0 ዓመትና በልምድ
🔺 የቅጥር ሁኔታ: በቋሚ ቅጥር
🔺 ብዛት: 15,000+ በላይ
🔺ደሞዝ:  በቀን 3000 ብር
 
🛑 ፈጥነው ታች ባለው ሊንክ  ስራውን ይጀምሩ

⁉️ ማሳሰቢያ:- VPN ወይም Psiphon ይክፈቱና

      👇👇👇👇Apply Now👇👇👇👇👇
                        👇👇👇👇
https://reportervacancy.com/make-money-online/

--------Follow Our Website--------
                     👇👇👇👇👇👇
         https://reportervacancy.com


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ህንዳዊቷ ከብደት አንሺ ከአቅሟ በላይ የሆነ ክብደት ስታነሳ ህይወቷ አለፈ

የ 17 አመቷ ያሽቲኪ አቻሪያ 270 ኪሎ ግራም የሚመዝነውን ክብደት ስታነሳ እጅ መያዣው ትከሻዋ ላይ አንጠልጥላ ከፍ ለማድረግ ስትሞክር ክብደቱ አንገቷ ላይ አርፎ ወዲያውኑ ህይወቷ ማለፉን ሰሞኑን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ቪዲዮ: ማህበራዊ አውታረ መረቦች.

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ለመረጃ ያህል‼️
ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር የማስከፈያ ምጣኔዎች‼️
በፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 መሰረት ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር የማስከፈያ ምጣኔዎች እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የሚከተሉትን ይላል፡-

👉 ከግብር ነፃ ከሆነው በስተቀር ቀጣሪው ለተቀጣሪው በሚከፍለው ማንኛውም የገንዘብ መጠን ላይ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር ይከፈልበታል፡፡
👉 ቀጣሪ ማለት ተቀጣሪን የቀጠረ ወይም ለተቀጣሪው ደመወዝ የሚከፍል ሰው ነው፡፡
👉ተቀጣሪ ማለት ደግሞ ራሱን ችሎ የሚሰራን የስራ ተቋራጭ ሳይጨምር በሌላ ሰው /በቀጣሪው/ መሪነትና ቁጥጥር ስር ሆኖ አገልግሎት ለመስጠት በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት የተቀጠረ ግለሰብ ሲሆን የድርጅት ዳይሬክተር፣ ወይም በድርጅቱ አመራር ውስጥ ኃላፊነት የተሰጠውን ሌላ ሰው እንዲሁም ተሿሚንና የህዝብ ተመራጭን ጨምሮ የመንግስት ስራ ኃላፊን ያጠቃልላል፡፡

• ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ የሚከተሉትን ይጨምራል፡-

👉 ከሰራተኛው ቅጥር ጋር በተያያዘ ሰራተኛው የተቀበለው የደመወዝ ምንዳ፣ አበል፣ ጉርሻ፣ ኮሚሽን፣ የመልካም ስራ አፈፃፀም ማበረታቻ ስጦታ ወይም ሌላ የአገልግሎት ክፍያ፣
👉 ሰራተኛው ከቅጥር ውሉ ጋር በተያያዘ በዓይነት የሚቀበለው ማንኛውም ጥቅማጥቅም ዋጋ፣
👉 ተቀጣሪው ከስራ ሲቀነስ ወይም ከስራ ሲለቅ ወይም ስራን እንዲለቅ ለማግባባት የሚከፈል ገንዘብን ጨምሮ የስራ ውል በመቋረጡ ምክንያት በፈቃደኝነት፣ በስምምነት ወይም በዳኝነት ውሳኔ መሠረት የተቀበለ ሰው ማንኛውም የገንዘብ መጠን፣

• ቀጣሪው ለተቀጣሪው ከተከፈለው የገንዘብ መጠን ላይ ግብሩን ሳይቀንስ ከራሱ ግብሩን የከፈለ እንደሆነ የተከፈለው ግብር በተቀጣሪው ደመወዝ ላይ ተደምሮ ግብሩ ይሰላል፡፡

ለምሳሌ፡- የ4ሺ 500 ብር ተቀጣሪ ግብር ተቀንሶበት የተጣራ ደመወዙ ይህ ነው፡፡
ይህ ደመወዝ ተራ ቁጥር 4 ላይ የሚያርፍ ሲሆን ስሌቱ፡-
ተቀናሽ ግብር = የወር ደመወዝ x የማስከፈያ መጣኔ - ተቀናሽ ብር
ተቀናሽ ግብር = 4,500 x 20% - 302.50
ተቀናሽ ግብር = 597.50
የተጣራ ደመወዝ   = አጠቃላይ ደመወዝ - ተቀናሽ ግብር
የተጣራ ደመወዝ   =  4,500 – 597.50
የተጣራ ደመወዝ   =  3ሺ 902 ብር ከ50 ሳንቲም (ይህ የጡረታ ተቀናሽን አያካትትም)።
ገቢዎች ሚኒስቴር

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter




ምርጫው የእርሶ ነው !

"ባንክ ሲቆጥቡ 7% ወለድ ያገኛሉ
የአያት አክሲዮን ባለቤት ሲሆኑ ግን በግማሽ ያተርፋሉ"

በ2016 ዓ.ም ብቻ

❇️የ100,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 45,020 ብር አትርፈዋል

❇️የ1,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 450,200 ብር አትርፈዋል

❇️የ2,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 900,400 ብር አትርፈዋል

❇️የ5,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 2,251,000 ብር አትርፈዋል

❇️የ10,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 4,502,000 ብር አትርፈዋል

❇️ከተመዘገቡ ከ1 ወር ጊዜ ጀምሮ የትርፍ ተካፋይ ስለሚሆኑ  ከ112,500 ብር ጀምሮ ፈጥነው በመመዝገብ የ8 ግዙፍ ድርጅቶች ባለቤት በመሆን በቶሎ የትርፍ ተካፋይ ይሁኑ

❇️ ትርፋማ የሆነውን የአያት አክሲዮንን ለእርስዎ ፣ ለታዳጊ ልጅዎ  ፣ ለቤተሰብዎ እና ለወዳጅ ዘመድዎ በስጦታ ያበርክቱ

❇️ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች ባላችሁበት ወይንም በወዳጆቻችሁ በኩል የአያት አክሲዮን ባለቤት መሆን ትችላላቹህ

☎️ ለበለጠ መረጃ
0912024560 በቀጥታ 
በቴሌግራም 
ወይንም  በዋትሳፕ ይደውሉ 


በቻይና ውስጥ በሌሊት ወፎች ውስጥ አደገኛ የሆነ አዲስ የኮሮናቫይረስ ዝርያ ተገኘ

ሳይንቲስቶች ቫይረሱ ተላላፊ እና የመተንፈሻ አካላትን ሊያዳክም እንደሚችል አስጠንቅቀዋል

Via : fidel

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


የተሽከርካሪ አስመጪዎች በአዲስ የጥራት ደረጃ ሰርተፍኬት ላይ ቅሬታቸውን አቀረቡ

👉 መንግስት በበኩሉ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል

የኢትዮ ተሸከርካሪዎች አስመጪ ባለቤቶች ማህበር አባላት መንግስት ባስቀመጠው አዲስ የጥራት ደረጃ ሰርተፍኬት ምክንያት ስራቸውን በአግባቡ ማከናወን መቸገራቸውንና ይህም በሀገሪቱ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እያሳደረ መሆኑን ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በጻፉት ደብዳቤ ገልጸዋል።

ማህበሩ አባላቱ በአንድ ተሽከርካሪ እስከ 200 ዶላር ወጪ እያወጡ መሆኑንና ይህም ከፍተኛ የዲሜሬጅ ወጪን እንደሚያስከትል እንዲሁም ይህ ሁሉ ገንዘብ ለጎረቤት ሀገር መከፈሉ አግባብነት እንደሌለው ትላንት የካቲት 13፤2017 ዓ.ም. በደብዳቤው አስታውቋል።

በተጨማሪም መንግስት አዲሱን የጥራት ደረጃ ሰርተፍኬት ተግባራዊ በማድረጉ ቀረጥና ታክስ ለመሰብሰብ አስቸጋሪ ሁኔታ መፈጠሩንና ይህም ሀገሪቱን እየጎዳ መሆኑን ማህበሩ ገልጿል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ፈንታሌ‼️

በኢትዮጵያ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መናወጥ methane ጋዝ ይዞ መጥቷል‼️
የኢሮፒያን ሳተላያት መረጃ ይዞ በወጣው መሰረት ከሰሞኑን በፈንታሌ ሲከሰት የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ባልተለመደ መልኩ ሚቴን የተሰኘውን የተፈጥሮ ጋዝ ከምድር ሆድ እቃ ውስጥ ይዞ ወጥቷል ብሏል።

በሚቴን የተፈጥሮ ጋዝ ዙሪያ የሚሰራው የካናዳው ድርጅት GHGsat እንደገለፀው በፈንታሌ ተራራ በአሁን ሰዓት በ ቀን 1,400 ቶን የሚቴን ጋዝ እየወጣ ይገኛል ።

ይህንንም በንፅፅር ሲያስረዳ 1,400 ቶን ጋዝ በቀን ማለት 20ሚሊየን ኪሎ ግራም የከሰል ድንጋይ ቢቃጠል የሚገኘው ሃይል እንደ ማለት ነው ብሏል ግዝፈቱን ለማስረዳት ።

በሌላ በኩል በአሁን ሰዓት በቀን እየወጣ ያለው 1400 ቶን የሚቴን ጋዝ 8000 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጨት የሚችል ሲሆን ይህም... ከህዳሴው ግድብ ሀይል ማመንጫ በ3ሺ ሜጋ ዋት ይልቃል ።

ይህ ብቻ ሳይሆን እንደማየነኛውም የተፈጥሮ ጋዝ ይህ አሁን ፈንታሌ በራሱ ግዜ በገዛ ፍቃዱ እነሆ በረከት ብሎ ብቅ ያለው ሚቴን በአግባቡ ጥቅም ላይ ከዋለ በአሁን ሰዓት እጅግ ተፈላጊ ወደ ሆነው LNG (Liquefied Natural gas ) ተቀይሮ ወደ 2 ሚሊየን ሊትር በቀን ማምረት ይቻላል"ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ ለግብርና ምርጥ  ወሳኝ የሆነው የተፈጥሮ ማዳበሪያ  ቢለወጥ ኢትዮጵያ በአለማችን ከፍተኛው ፖታሽ ሃብት ባለቤት እንደመሆኗ    የኢትዮጵያን የማዳበሪያ ፍላጎት አሟልቶ በኤክስፖርት የሀብት ምንጭ የሚሆን  ሀብት ነው  ተብሏል። 

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ለቀድሞ የኦነግ አመራሮች ሹመት ተሰጠ!

የኦሮሚያ ክልል የመንግስትን የሰላም ጥሪ ለተቀበሉ የቀድሞ የኦነግ አመራሮች ሹመት ሰጥቷል፡፡
በዚህ መሰረትም፡-
1. አቶ ያደሳ ነጋሳ--------- በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ
2. አቶ ኦሮሚያ ረቡማ --------- የኦሮሚያ ክልል ዓቃቤ ሕግ ምክትል ሃላፊ
3. አቶ ቶሌራ ረጋሳ --------- የኦሮሚያ ክልል ጸጥታና አስተዳደር ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሆነው መሾማቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


በአዲስ አበባ ከተማ አምስት ሊትር ዘይት ከ1400 እስከ 1600 ብር እየተሸጠ ይገኛል

በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የመሰረታዊ ሸቀጦች ዋጋ በከፍተኛ መጠን እየጨመረ እንደሚገኝ ብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ባደረገው የገበያ ቅኝት ለማወቅ ችሏል።

በተደገው የገበያ ቅኝት ከዚህ ቀደም 1200 እስከ 1300 ብር ይሸጥ የነበረው አምስት ሊትር የምግብ ዘይት አሁን ላይ ከ200 መቶ እስከ 300 ብር ጭማሪ አሳይቷል።

እንዲሁም መሰረታዊ የምግብ ፍጆታ የሚባሉት ምስር ከ200 ወደ 270 ፣ እንቁላል ከ11 ብር ወደ 18 ብር ጭማሪ የታየበት ሲሆን ሌሎች ምርቶች ላይ በአንድ ሳምንት ውስጥ የተጋነነ የዋጋ ጭማሬ መኖሩን በቅኝታችን አረጋግጠናል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


❗ባይናንስ በናይጄሪያ የ81 ቢሊዮን ዶላር ክስ ቀረበበት❗

የናይጄሪያ የፌደራል የሀገር ውስጥ ገቢ አገልግሎት የክሪፕቶከረንሲ መገበያያ በሆነው ባይናንስ ላይ የኢኮኖሚ ኪሳራ አድርሷል በማለት
በአቡጃ በሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ መስርቶበታል።
የናይጄሪያ ኢኮኖሚ ላይ ባደረሰው ኪሳራ 79.5 ቢልዮን ዶላር እንዲከፍል እንዲሁም በ2022 እና 2023 ያልተከፈለ 2 ቢሊዮን ዶላር ውዘፍ የታክስ እዳ ባለመክፈል ነው ባይናንስ ክሱ የተመሰረተበት።
ያለ ህጋዊ ፈቃድ የክሪፕቶከረንሲ ልውውጥ ሲያካሄድ እንደነበር እና በዚህም ያልተፈቀደ የፋይናንስ አገልግሎትን መስጠት እና የውጭ ምንዛሬን በማካሄድ ብሎም በበርካታ ህጎችን መጣስም የክሱ አካል ሆኗል።
ባይናንስ ከ382 ሺህ በላይ ተጠቃሚዎች ይዞ ከ21 ቢሊዮን ዶላር በላይ ግብይት በማካሄድ 35.4 ሚሊዮን ዶላር የተጣራ ትርፍ በ2023 አስመዝግቧል።
ባይናንስ በናይጄሪያ ውስጥ ከ6 ዓመት በላይ ያለ ህጋዊ ምዝገባ እና ፈቃድ ሲሰራ እንደነበርም ስፑትኒክ ዘግቧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


አዲስ የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርትን ይፋ ተደረገ

የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት አዲስ የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርትን ይፋ አደረገ ፡፡

አዲሱ ፓስፖርት ደህንነቱ የተጠበቀ እና በሀገር ዉስጥ የሚመረት ነዉ ተብሏል፡፡

ፓስፖርቱ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘዉ የለሚ ኢንደስትሪያል ፓርክ የሚመረት ሲሆን ጥራቱ አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስለመሆኑም ተነግሯል፡፡

በፓስፖርቱ ገፆች ላይ የሀገር ገፅታ የሚያስተዋዉቁ የኢትዮጵያ መለያዎች እንደተካተቱበትም ለማወቅ ተችሏል፡፡

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


♨️የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ Jobs 2025 ✅
---—----------------------------     
✅ በ0 አመት  እና በልምድ

✅  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ብቁ ሠራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፣ ስለሆነም ፍላጎት ያላችሁ ከዚህ በታች ያለዉን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ብዛት: ከ20,000 በላይ
ደሞዝ ማራኪ

                How To Apply
                     👇👇👇

🟥 ፈጥነው ታች ባለው ሊንክ ይመዝገቡ

⁉️ ማሳሰቢያ:- VPN ወይም Psiphon መጠቀም ይኖርባችሗል

👇👇👇👇👇Apply Now👇👇👇👇👇👇
                        👇👇👇👇         
https://reportervacancy.com/national-election-board-of-ethiopia-jobs-2024/

--------Follow Our Website--------
                     👇👇👇👇👇👇
         https://reportervacancy.com

--------Join Our Telegram---------
                     👇👇👇👇👇
    https://t.me/reporter_vacancy


የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር፣ የትግራይ ፀጥታ ኃይል አባላት በደቡባዊ ምሥራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ ዓለም ቀበሌ ገበሬ ማኅበር በነዋሪዎች ላይ ጥቃት አድርሰዋል በማለት ትናንት ባወጣው መግለጫ ድርጊቱን አውግዟል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ የተወሰኑ የክልሉ ፀጥታ ኃይል አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩን መዋቅሮች ለማፍረስ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ናቸው በማለት ከስሷል።

የፀጥታ ኃይሉ የአንድ ቡድን የሥልጣን መወጣጫ መሳሪያ ሊኾን እንደማይችል የገለጠው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ኹኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ክልሉ ከባድ ቀውስ ውስጥ ሊገባ ይችላል በማለት አስጠንቅቋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው፣ ትናንት የተወሰኑ የፀጥታ ኃይል አባላት የቀበሌ አስተዳደሩ ማኅተሙን እንዲያስረክብ ባስገደዱበትና፣ በዚሁ ወቅት ድርጊቱን በተቃወሙ ነዋሪዎች ላይ የኃይል ርምጃ በወሰዱበት ወቅት እንደኾነ ተገልጧል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


መረጃ ‼️

ሱዳን ከኬንያ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ውዝግብ ውስጥ መግቧቷን ተከትሎ፣ በኬንያ የሚገኙ አምባሳደሯን ትናንት መጥራቷን ከአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር መረዳቱን ጠቅሶ ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል።

ሱዳን አምባሳደሯን የጠራችው፣ ኬንያ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይልንና አጋሮቹ ትይዩ መንግሥት ለማቋቋም የጠሩት ስብሰባ ናይሮቢ ውስጥ እንዲካሄድ በመፍቀድ የባላንጣነት አቋም አሳይታለች በማለት እንደኾነ ዘገባው ጠቅሷል።

የኬንያ ድርጊት፣ ካኹን ቀደም በአሕጉሪቷም ይኹን በአፍሪካ ቀንድ "ታይቶ የማይታወቅ"፣ "አደገኛ" እና "አሳፋሪ" ድርጊት ነው በማለት ሚንስቴሩ ማውገዙን ዘገባው አመልክቷል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


ምርጫው የእርሶ ነው !

"ባንክ ሲቆጥቡ 7% ወለድ ያገኛሉ
የአያት አክሲዮን ባለቤት ሲሆኑ ግን በግማሽ ያተርፋሉ"

በ2016 ዓ.ም ብቻ

❇️የ100,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 45,020 ብር አትርፈዋል

❇️የ1,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 450,200 ብር አትርፈዋል

❇️የ2,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 900,400 ብር አትርፈዋል

❇️የ5,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 2,251,000 ብር አትርፈዋል

❇️የ10,000,000 ብር የአያት አክሲዮን ድርሻ ያላቸው 4,502,000 ብር አትርፈዋል

❇️ከተመዘገቡ ከ1 ወር ጊዜ ጀምሮ የትርፍ ተካፋይ ስለሚሆኑ  ከ112,500 ብር ጀምሮ ፈጥነው በመመዝገብ የ8 ግዙፍ ድርጅቶች ባለቤት በመሆን በቶሎ የትርፍ ተካፋይ ይሁኑ

❇️ ትርፋማ የሆነውን የአያት አክሲዮንን ለእርስዎ ፣ ለታዳጊ ልጅዎ  ፣ ለቤተሰብዎ እና ለወዳጅ ዘመድዎ በስጦታ ያበርክቱ

❇️ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች ባላችሁበት ወይንም በወዳጆቻችሁ በኩል የአያት አክሲዮን ባለቤት መሆን ትችላላቹህ

☎️ ለበለጠ መረጃ
0912024560 በቀጥታ 
በቴሌግራም 
ወይንም  በዋትሳፕ ይደውሉ 


የትራምፕ ህገወጥ ስደተኞችን የማፈናቀል ፖሊሲ በአሜሪካ ኢኮኖሚ ላይ ችግር መፍጠሩ ተነገረ

ዶናልድ ትራምፕ የፕሬዝዳንትነት ስልጣን በያዙ ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ ፕሬዝዳንቱ የድንበር ደህንነትን ለመቆጣጠር ባደረጉት ሙከራ ከ8,700 በላይ ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች ከአሜሪካ ተባርረዋል። የትራምፕን እርምጃ በመቃወም በመላው የአሜሪካ ከተሞች ሰፊ ተቃውሞ ቢደረግም ስደተኞችን ወንጀለኞች በማለት ይፈርጃሉ። አስደንጋጭ በሆነው እርምጃ የትራምፕ አስተዳደር በስደተኞች ጉዳይ ላይ ውሳኔ የመስጠት ኃላፊነት የነበራቸው 20 የኢሚግሬሽን ዳኞችን ኃላፊነታቸውን አልተወጡም በማለት በቅርቡ ከስራ አሰናብተዋል።

ይህው እርምጃ ቤተሰቦች እንዲለያዩ እና ህጻናት ያለ ምንም የድጋፍ ስርዓት በማስቀረት ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰነድ አልባ ስደተኞች እጣ ፈንታ በእርግጠኝነት አይታወቅም።የጥገኝነት ጉዳዮች ለመታየት እና ለመጨረስ አመታትን ሊወስድ ይችላል፣ እናም ብዙ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች የኢሚግሬሽን እና የጉምሩክ ማስፈጸሚያ ህጋዊ ሂደታቸውን እንዲቆም እና ቤተሰቦቻቸው ሊለያይ ይችላል በሚል ፍራቻ ስራ እና ትምህርት ቤት ለመቅረት እየተገደዱ ይገኛል።

የስደተኞች ጠቀሜታ እና አስተዋፅዖ በአጠቃላይ በአሜሪካ የሰው ኃይል ውስጥ የማፈናቀል ዘመቻው በኢኮኖሚው ላይ የሚኖረውን አሉታዊ ተፅእኖ የከፋ እንደሚሆን የኢኮኖሚ ተንታኞች ስጋታቸውን ያስቀምጣሉ። ዩናይትድ ስቴትስ በስደተኛ እና በተለይም ሰነድ አልባ በሆኑ ዜጎች ጉልበት ላይ የተደገፈች ነች።ስደተኞች የኢኮኖሚው ምሰሶ በመሆናቸው  ወደ ስራ መግባት ትተው መደባበቅ መጀመራቸው ችግሩ አፍጥጦ እንደሚታይ ያሳያል ብለዋል።

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter


አስተያየት ፤ ሀሳብ አልያም ጥያቄ ካላችሁ ከታች ባለው የመልዕክት ማስቀመጫ ቦት ላይ አስቀምጡልን እናመሰግናለን

መልክታችሁን አስቀምጡልን
👇👇👇
@Addis_reporter_bot


ኤርትራ በአዲስ አበባ ያለውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታወቀ

ካለፉት ሁለት አመታት ወዲህ ግንኙነታቸው እየሻከረ የመጣው የኢትዮጵያ እና ኤርትራ መንግስታት የቃላት ጦርነት መጀመራቸውን ተከትሎ ኤርትራ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታውቋል።

የዛሬ ሰባት አመት ገደማ ግንኙነታቸውን ያደሱት ሁለቱ ሀገራት በትግራይ የተካሄደው ደም አፋሳሽ ጦርነት ላይ በጋራ ቆመው ቢዋጉም የፕሪቶሪያው ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ ግንኙነቱ መሻከር መጀመሩ ይታወሳል።

"ኤምባሲው ከዚህ በኋላ የአፍሪካ ህብረት ተወካዩን ይዞ ይቀጥላል፣ በኢትዮጵያ ያለውን የኤምባሲ ስታፍ ግን እያሰናበተ ነው" ያሉን አንድ የኤምባሲው ምንጫችን ሂደቱ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ለመሠረት ሚዲያ መናገራቸውን ዳጉ ጆርናል ከዜና ምንጩ ዘገባ ተመልክቷል።

ከቀናት በፊት የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የኤርትራ መንግስት የአፍሪካ ቀንድን የማተራመስ አላማ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ነው፣ በአስቸኳይ እንዲቆም መደረግ አለበት በማለት አልጀዚራ ላይ በቀረበ ፅሁፋቸው አስነብበው ነበር።

የኤርትራው የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ለዚህ ምላሽ የሰጡ ሲሆን የፕሬዝደንቱን አስተያየት አጣጥለው የኢትዮጵያን መንግስት የቀጠናውን ሀገራት በመተንኮስ ከሰዋል።

የኤርትራ ኤምባሲ መዘጋት መጀመርን ተከትሎ በአስመራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እጣ ፈንታ እስካሁን አልታወቀም። ላለፉት ጥቂት አመታት ኤምባሲው ክፍት ቢሆንም አምባሳደር ሳይመደብበት መቆየቱም ይታወሳል።

Via_መሠረት ሚዲያ

@Addis_Reporter
@Addis_Reporter

Показано 20 последних публикаций.