አጋፔ ዘ ኦርቶዶክስ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


✝️በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን✝️
በዚህ ቻናል ውስጥ ኦርቶዶክሳዊ እና መንፈሳዊ ትምህርቶች ፣ ጸሎት ፣ ምክር ፣ ተከታታይ ትምህርት ፣ ወንጌል ወዘተ የምንማማርበት መንፈሳዊ ቻናል ነው ።
Share💯share💯share💯
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Agape_ze_orthodox
ለኃሳብ አስተያየት በዚህ ያግኙን
👉 📨 @wededen

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций




⨳ #ክርስትና #ይህ #አይደለም፡

• የሚያምሩ የመዝሙር ግጥሞችን ማወቅ
• በራስ ፍላጎት የሚያማምሩ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን መሸምደድ
• አለምንና ንብረቶቿን ማሳደድ፣ መከተል
• ደስ ስልህ ብቻ ኢየሱስን መከተል
• በሰንበት ወይም በእረፍት ቀን ቅዱስ መሆን፣ ከእሁድ በኋላ ወዳደፈው መንገድ መመለስ። ይሄ ፈጽሞ ክርስቲና አይደለም።

⨳ #ክርስትና
• ራስን መካድ እና ለሥጋዊ መሻት መሞት
• ሰሚ ብቻ ሳይሆን የቃሉ አድራጊዎች መሆን
• ሕይወት ምንም ያህል ከባድ ቢሆን ሁል ጊዜ በሁሉም ቦታ ለእግዚአብሔር ክብር መኖር፣ እርሱን ማምለክ
• ከሰዎች ይልቅ ኢየሱስን ማስደሰት [ዋጋ ቢያስከፍልም]
• እግዚአብሔር ደስ ማይሰኝባቸውን ግንኙነቶች ማቆም
• ከአለም ደስታ መለየት
• ሰው ሰራሹን ሳይሆን የእግዚአብሔርን ቃል መከተል፣ ሕግጋቱን ማሰላሰል
• በወዳጆች ፊት በኢየሱስ አለማፈር
• ወንጌልን በድፍረት በኑሮም በንግግርም መናገር።

@Agape_ze_orthodox


ያለውን ደገሰበት 🙆🏻‍♂️

በምድር ላይ በጣም ሀብት አለው ብላቹ የምታስቡት ሰው ማን ነው?። ያ ያሰባችሁት ሰው ያሉትን ንብረቶች በሙሉ ሽጦ፤ አለኝ የሚለውን ገንዘቡን በሙሉ አውጥቶ የሚያስደንቅ ድግስ ቢደግስ፤ እና ኑና ድግሴን በነፃ ታደሙ ብሎ ቢጠራችሁ "እንደው ምን አይነት ድግስ ቢደግስ ነው ያለውን ብር በሙሉ ያወጣበት?" ብሎ ድግሱን  ለማየት የማይጓጓ አለ 😃?

እግዚአብሔርም ብቸኛ እና አለኝ የሚለውን አንድያ ልጁን ሰውቶ ነው ሰማያዊውን ጥሪ እንድንካፈል የጠራን። ጥሪው ተራ ጥሪ አይደለም ብቸኛ ልጅ ነው የታረደበት። ከሞት ድግስ ወደ ሕይወት ድግስ ነው የተጠራነው። ጠላት ብር እያስከፈለን ነው ወደ ሞት ድግስ የጠራን (ከፍለን እየጠጣን፣ ከፍለን እየዘሞትን፣ ከፍለን እየቃምን፣ ከፍለን እያስጠነቆልን፣ ከፍለን እየቆመርን)። የሚገርመው ደግሞ እግዚአብሔር ያለውን ሀብት ማውጣቱ ሳያንስ፤ እኛን በነጻ ኑ ታደሙ ብሎ መጋበዙ ነው የሚገርመው። ብቻኛ ልጅ የተሰዋበት ጥሪ ምን ያህል የከበረ እንደሆነ አይተናል። እውነተኛውን ጥሪ ተቀብሎ የታደመ ሁሉ የእድለኝነት ስሜት የማይሰማው የለም። እግዚአብሔር ልጁን የሰዋበትን ጥሪ እንደ ቀልድ አያየውም እጅግ የከበረ ነው።

“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ #እግዚአብሔር_አንድያ_ልጁንእስኪሰጥ_ድረስ_ዓለሙን_እንዲሁ_ወዶአልና።”
  — ዮሐንስ 3፥16

@Agape_ze_orthodox


መሄጃ ጠፍቶ አይደለም። ብዙ የሚኬድበት አለ። የምንሄድባቸው ቦታዎች ግን ደካማን አያከብሩም፣ ኃጢአተኛን አይወዱም፣ ለኃጢአተኛ አይሞቱም፣ ስለኛ ተጠያቂ አይሆኑም፣ ነብስን "እፎይ" የሚያስብል የዕረፍት ቃል የላቸውም፣ ከጨለማ የሚያወጣ የብርሃን ቃል የላቸውም። ከኢየሱስ ወዴት?
“ስምዖን ጴጥሮስ፦ ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? #አንተ_የዘላለም_ሕይወት_ቃል_አለህ፤” ዮሐንስ 6፥68

@Agape_ze_orthodox


"የበጉ በግነት"

አዲስ ቤት ተሰርቶ በመስታወት አሸብርቆ ዘመድ ጎሮቤት ወዳጅ ሁሉ ለቤቱ ምርቃት ይጠራል። ታዲያ የቤቱ ባለቤት ለዚሁ ድግስ ማጣፈጫ የሚሆን አንድ ትልቅ በግ ይገዛል። የገዛውን በግ በአዲሱ ቤት አጠገብ አስሮ ወደ ገበያ ይሄዳል። ጥበብ የጎደለው የጸቡ ሱስ ትዝ አለውና እንደተለመደው ሊጋጭ እየተዟዟረ ሌላ ተቃራኒ በግ ይፈልጋል ትንሽ ቆይቶ በአዲሱ ቤት መስታወት ውስጥ እራሱን ያያል የሌሎቹን እንጂ የራሱን መልክ የማያውቀው በግ ሌላ በግ ስለ መሰለው ተንደርድሮ እገጫለሁ ብሎ ከመስታወቱ ጋር ተጋጨ። ባለቤቱ ሲመጣ እራስን ባለማወቅ ጣጣ ከራሱ ተጋጭቶ ተንጋሎ ሳይሆን ተንከባሎ አገኘው። ከራሱ ጋር ተጣልቶ አራሱን አጠፋ። የበጉ በግነት ይሄ ነው መልኩን ባለማወቁ ከእራሱ ጋር መጣላቱ።

በግ በጣም ብዙ ነገር ያውቃል ለምሳሌ እረኛውን፤ ጋጣውን(ማደሪያውን)፤ ከእርሱ ጋር የሚሰማሩትን በጎች የሚገርመው ግን ይሄን ሁሉ የሚያውቀው በግ የራሱን መልክ ግን አያውቀውም። ለምን? መልኩን ስላላየው ነዋ ለምን አላየውም? መስታወት አላየማ የሰው ልጅም እንዲሁ ነው። በጣም ብዙ ነገር ያውቃል ስለ ፕላኔት ስለ የብስ ስለ ምድር ስለ ፍልስፍና... ብቻ ምናለፋችሁ ስለነገሮች ብዙ ያውቃል የሚያሳዝነው ግን ሰው እስከ ዛሬ እራሱን አላገኘም(አላወቀም) በዚህ ምክንያት የማንነት ቀውስ ተጠቂ ሆኗል። ለምን? ሌሎቹን እንጂ አራሱን አይቶ ስለማያውቅ ለምሳሌ እኔ አንገቴን፤ ቅንድቤን፤ ጀርባዬን አይቼ አላውቅም ግን አውቃቸዋለሁ እድሜ ለመስታወት ያላየሁትን መልኬን አሳወቀኝ። በዙ ጊዜ ህጻናት ልጆች መስታወት ሲያዩ የሚያለቅሱት በመስታወት የሚያዩት የሌላ ሰው መልክ እንጂ የራሳው ስለማይመስላቸው ነው። የራሳቸው መልክ መሆኑን ሲያውቁ ግን መፍራት ትተው መደሰት ይጀምራሉ። መልክህን አለማወቅ ልክ እንደበጉ ከመልክህ ጋር እንድትጣላ ያደርግሃል ።

በጣም ብዙ ሰው ከራሱ ጋር የሚጣለው እውነተኛውን መልኩን (ምንነቱን) ስላላወቀ ነው። ለባለሀብቶች በማንነት ቀውስ አንገታቸው ላይ ገመድ አስገበተዋል ብዙ አዋቂዎች በብቸኝነትና በጭንቀት መዕበል ተንጠዋል። የቀውሶች ሁሉ ምንጭ ሰው እራሱን በትክክል አለማወቁ ነው መጸሐፍ " ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው ይመስላል፤"
(የያዕቆብ መልእክት 1:23) ይላል አለም ትክክለኛውን መልኳን በቃሉ መነጽር እስካላየች በማንነት ቀውስ ከራሷ ጋር እደተላተመች ተኖራለች። በጉ ከራሱ ጋር የተጋጨው እራሱን በትክክል ስላላወቀ ነው። ያላወቀው ደግሞ እራሱን በመስታወት ስላላየ ነው። ሰውም እንዲሁ ነው በቃሉ መስታወትነት አራሱን እስካላየ ድረስ ከራሱ ጋር እየተላተመ ይኖራል።

"በራስህ ጸብ ገዳይም ሟችም አንተ ነህና በቃሉ መነጽርነት መልክህን ለይተህ ከራስህ ተስማማ(ከበጉ በግነት እራስህን አጽዳ)"!!!!

@Agape_ze_orthodox


ይህ_ማነው❓

=>ሁሉ ሳለው ከድሆች ቤት ያደረ?
=>ክቡር ሲሆን የተናቁትን ያከበረ?
=>ባለ ፀጋ እርሱ ከምስኪኖች ደጃፍ የቆመ?
=>ንጉስ እርሱ ያገልጋዮቹን እግር ያጠበ?

👉ይህ ማነው❓

=>እየጣሉት የሚያነሳ
=>እየቀሙት የሚለግስ
=>እያቆሰሉት የሚጠግን
=>እየራበው የሚያጎርስ
=>እየታረዘ የሚያለብስ
=>እየተጠማ የሚያጠጣ

👉ይህ ማነው❓

=>ሙሽራ ሲሆን ያላዘዘ
=>ባለመድሀኒት ሲሆን የታመመ
=>ከሁሉ ከፍ ያለ ሲሆን ያነሰ
=>ኃያል ሲሆን የደከመ

👉ይህ ማነው❓

=>ቀና ስል ሰማይን ሞልቶ ያየሁት
=>ዝቅ ስልም ከድንግል ጎን ያየሁት

👉ይህ ማነው❓

=>በሰማይ የማይወሰን ከድንግል ማህፀን ያረፈ
=>በእጁ አለማትን የጨበጠ
=>በፍጡር ጀርባ የታዘለ
=>በብላቴና ክንድ የታቀፈ

👉አረ ይህ ማነው❓

=>ከዙፋኑ ሳይለቅ ከአገልጋዮች ጋር አብሮ ያለ
=>ከላይ ሙሉ የሆነው ከታችም ያልጎደለው
=>አይኔን ባቀና ከላይ የማየው
=>ባጎነብስም የማላጣው

👉ይህ ማነው❓

=>ቀንድ ሳለው የማይዋጋ
=>ጥፍር ሳለው የማይቧጭር
=>ጉልበት ሳለው የማይጋፋ
=>ክንድ ሳለው የማይሰብር

👉ይህ ማነው❓

=>የገፉትን የደገፈ በጨካኞች ፊት የራራው
=>የሰበሩትን የጠገነ የወጉትን ያበራ

👉ይህ ማነው❓

=>ሞትን በሞቱ ያሸነፈው
= የጠላትን ኃይል ድል የነሳው
=>የክፋትን ክንድ የሰበረው
=>የዕዳችንን ደብዳቤ የሻረው
=>ጨለማውን የገፈፈው
=>የወደሙትን የበረበረ
=>ታላቁን ዜና ያበሰረ
=>ፍቅር የፍቅር መምህር
=>ትሁት የትሁታን ክብር
=>በሁሉ ዘንድ የተወደደው
=>ግና ከሁሉ የተለየው

👉ኧረ ይህ ማነው❓

ኢየሱስ ነው 🤩

@Agape_ze_orthodox
@Agape_ze_orthodox


ተነስቷል

        "እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ።"
የማቴዎስ ወንጌል 28 : 6

      ሰው ከወደቀበት መሬት ይነሳል፤ ሰው ህመሙ አገግሞ ከአልጋ ይነሳል፤ ሰው ከተቀመጠበት ወንበር ይነሳል። መነሳትን ለእነዚህ ዓላማዎች ብቻ ይጠቀምበታል። ሰው ከእነዚህ ነገሮች ሁሉ ተነስቶ በእግሩ ቢቆም ማንም አይገረምም አይደነቅም። ኢየሱስ ብቻ ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ።

      ሰው ተገንዞ ከተቀበረበት፤ ነፍሱ ወጥታ ስጋው በድን ከሆነበት፤ አንረሳህም በልባችን ትኖራለህ ተብሎ ድንጋይ ከተገጠመበት ውስጥ ተነሳ ሲባል ተረት ፌዝ ይመስላል። ምክንያቱም ዓለም ሁሉ በአንድነት የሚያውቀው የሞትን ኃያልነት፣ የሞትን ብቸኛ ጀግንነት፣ የሞትን አስፈሪነት ነው። ዛሬ ግን የሞት ኃያልነት ታሪክ ሊሆን ኢየሱስ በዝግ መቃብር ከሞት ተነሳ።

      ዛሬ ግን የዓለምን የዕለት ተዕለት እውቀት የሚሽር፤ የዓለምን የዘመናት የልምድ መመላለስ የሚለውጥ ክስተት ተፈጥሯል። እርሱም ሞትን ድል አድርጎ የተነሳ ሰው ተገኝቷል።

       ስንቱን አልቅሳ መሸኘት ልምዷ የሆነው ዓለም የኢየሱስን መሞት ለመቀበል አልተቸገረችም። ምክንያቱም ኢየሱስ ለእርሷ ከድሀ መንደር የተገኘ አንድ ምስኪን ሰው ነው። ይህ ምስኪን ሰው በብዙ መከራ ተደብድቦ መሞቱ አይደንቃትም። ኢየሱስ ከሞት መነሳቱ ግን ደንቋታል፣ እጇን በአፏ አስጭኗታል።

       መሬት የፈጠራትን ዋጠችው ጌታዋን ነውና አልቻለችም ተፋችው፤ ፃድቅ ነውና ሲዖል ጉልበቱ ተብረክርኮ መዝጊያው ተሰበረ። ሞት ያልያዘውን ምንም ሊይዘው አልቻለም።

       አንዲት የስንዴ ቅንጣት መሬት ላይ ስትዘራ ሞታ ትበሰብሳለች ግን በዛው አትቀርም ሺህ የስንዴ ፍሬዎችን ይዛ ትነሳለች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሞቶ ቢቀበርም ድንጋይ ቢገጠምበትም በዛው አልቀረም ሞትን ድል አድርጎ እኛንም ይዞን ተነሳ። ለክብር፣ ለህይወት፣ ለሹመት ይዞን ተነሳ።

       ከጉልበታሙ ሞት ኃይሉን ነጥቆ እኛ ደካሞቹን የትንሳኤውን ኃይል አለበሰን፤ የማስፈራቱን ሞገስ ከሞት ገፍፎ ጠላታችንን የምናስፈራበት መለኮታዊ ሞገሱን አለበሰን። ይህ ሁሉ ክብር በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ ያገኘነው ነው።

       ለህይወት ተነስተን በሞት ሰፈር አንገኝም፤ ለክብር ተነስተን እግዚአብሔርን በማያከብር ስፍራ አንገኝም፤ ለፅድቅ ተነስተን ከኃጢአት ጋር አንወዳጅም፤ ላንጠፋ ተነስተን ከሚጠፉት ጋር አናብርም፤ ለዘላለም ህይወት ተነስተን ለጊዜያዊ ህይወት አንባክንም። ክብር ለትንሳኤው ጌታ ይሁን።

  >

      ከሞት የተነሳው ጌታ ከሞት አስነስቶናል!

@Agape_ze_orthodox
@Agape_ze_orthodox


መጸለይህን አታቋርጥ
  “ሳታቋርጡ ጸልዩ” — (1ኛ ተሰሎንቄ 5፥17-18)


       ውስጥህ መጥፎ ሃሳብ ሲመላለስ፣ ክፉ ነገር ውስጥህ ሲጠነሰስ ጸልይ። ክፉም መጥፎም ሃሳብ ከውስጥህ የሚወገደው በጸሎት ነው። አጋንንት የማይወደው ተግባራችን ጸሎት ነው። ከእግዚአብሔር ጋር ስናወራ፣ ስሙን ከፍ ከፍ ስናደርገው ይንቀጠቀጣል። ከሰይጣን ወጥመድ የምናመልጠው በጸሎት ነው። ሰይጣን ጊዜ እንደሌለህ፣ እንደደከመህና እረፍት እንደሚያስፈልግህ እያሳሰበ እንዳትጸልይ ሊያደርግህ ይፈልጋል። አንተ ግን ምንም ውጊያው ፈታኝ ቢሆንብህ በሙሉ ሃሳብህ በፍፁም ልብህ በጸሎት በርታ።

     "ዲያብሎስን ተቃወሙት ከእናንተ ይሸሻል" ተብሏልና በጸሎትና ቃሉን በመታዘዝ ስንቃወመው ከእኛ ይሸሻል። በፍፁም መንገድ አትስጪው። ተዋጊበት እንጂ ትጥቅሽን አትፍቺ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነው። ጸሎት እግዚአብሔርን የናፈቀ ልብ ሲቃ ነውና ለእግዚአብሔር ያለሽ ፍቅር ይለካበታል ስለዚህ ጸልዪ።

     ስንጸልይ በፍቅር ይሁን። ፍቅር የተለየው የቃላት ብቻ የሆነ ጸሎት ፍሬ ቢስ ስለሆነ ፍቅርን የማያውቁ ሰዎች ይጸልያሉ። ነገር ግን መጽናናት አይሰማቸውም። ስለዚህ ጸሎታችን በፍቅር የተቀመመና የጣፈጠ ሊሆን ይገባዋል።
@Agape_ze_orthodox


በክርስቶስ መሆን መንጻት ፣ መቀደስ እና አዲስ ሰው መሆን ነው። አዲስ ፍጥረት መሆን ብቻም ሳይሆን አዲስ አኗኗርንም መጀመር ነው ። ኢየሱስ ሁሉን አዲስ ያደረገ የዘላለም ሊቀ ካህን ነው ። እኛም በእርሱ በኩል ወደማይለመድና ወደማይጠገብ ኑሮ ተሻግረናል ። ገና ደግሞ ልዩ ክብር በሰማይ ይጠብቀናል ። ይህ ሁሉ የሆነው ከኢየሱስ ማዳን የተነሳ ነው ። ይህ ክብር የማይገባው ሃብታም ፣ ባለ ስልጣን ፣ ደሃ ፣ የኔቢጤ የለም ። ኢየሱስ የሰራው ማዳን ሁሉም በአንድነት የሚቋደሱት ማዕድ ነው ።


እግዚአብሔር ቤተክርስቲያናችንን ያስብ። ቢገድሏችሁ ቢያሳድዷችሁ ክፉውን በክፉ አትመልሱ ፈራጅ እግዚአብሔር አለ። ከጥይት ጸሎት ሐይል አለው። ከስልጣን ይልቅ የእግዚአብሔር ሆኖ መዋረድ ክብር ነው። በሸንጎ ፊት ቢወስዷችሁ ስለምትናገሩት ነገር አትጨነቁ መንፈስ ቅዱስ የምትናገሩትን ይሰጣችኃል። እናንተ ጋር ያለው ጌታ ሐሰትን እና ደባን አይፈልግምና እውነትን ብቻ ያዙ። ጥይት የያዘ ሳይሆን እውነትን የያዘ አሸናፊ ነው።
ጸሎት
እግዚአብሔር ሆይ የሰላም አለቃ ሁሉን ሰላም አድርግ። ተሰብስቦ የሚያመልክህ እንጂ ተከፋፍሎ የሚያመልክህ ሕዝብ አይነሳ። ጠላት ያሰበው አይሁን። አንተ ተናገረን። ሁሉም በድሏል ንጹህ አንተ ብቻ ነህና የሚበጀንን አንተ እይልን። በልጅህ በኢሱስ ክርስቶስ ስም አሜን !!

@Agape_ze_orthodox
@Agape_ze_orthodox


Репост из: ሕያው ቃል
ኢየሱስ ክርስቶስ በአሮግው ፍጥረት መጨረሻ እና የአዲሱ ፍጥረት መገኛ ምንጭ ነው

Christ Jesus is the last Adam and the second (New) Man.

መፅሐፍ ቅዱስ በ 1ቆሮንቶስ መልዕክት 15፡45 እና 47
ለኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት ስሞችን ይጠቀማል .

1, ኃለኛው አዳም the last Adam
2, ሁለተኛው ( አዲሱ) ሰው the second or New Man

✍️ ሁለቱን መጠሪያዎች በመጠቀም ትልቅ ቁም ነገር መማር እንችላለን።

▸ ኢየሱስ ኃለኛው አዳም( the last Adam) የሚለው መጠሪያው የምድር ቆይታውን፣በመስቀሉ እና በሞቱ የመጀመሪያው አዳም መጨረሻ እና በአዳም የገባው ሃጢአት እና የሀጢአት ውጤቶች ፋፃሜ ያገኙበት ማለት ሲሆን
ሁለተኛው (አዲሱ) ሰው (the New Man) የሚለው መጠሪያው በትንሳኤ የአዲሱ ፍጥረት መገኛ ምንጭ በመሆን አዲሱ ፍጥረት ወደ ህልውና እንዲመጣ አድርጓል።

▸እንዲሁም በ 2 ቆሮንቶስ 5፡17 (2 Corinthians)
ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።

▸በማስተዋል ስናጠናው ማንም በኢየሱስ ሳይሆ ቃሉ የሚለው ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው ይላል ክርስቶስነቱን ደግሞ አብ በሙላት ያረጋገጠው በትንሳኤው ነው። ሐሥ 2፡36..

▸የኢየሱስ  መስቀል የአሮጌው ፍጥረት መጨረሻ ሲሆን የክርስቶስ ትንሳኤ የአዲሱ ፍጥረት መጀመሪያ ነው። 2ቆሮ 5፡17.

▸ የኢየሱስ መስቀል ከአሮጌው አዳም እና ከሙሴ ህግ ጋር ላንገናኝ በሞት የተለያየንበት ሲሆን የክርስቶስ ትንሳኤ ከክርስቶስ ጋር ህይወት አግኝተን የአካል ክፍሎቹ የሆንበት ነው።ሮሜ 6, ሮሜ 7፡1-4, አፌ 2፡4-, ኤፌ 5፡30 KJV.

▸ የኢየሱስ መስቀል ሃጥያት የተቀጣበት ሲሆን የክርስቶስ ትንሳኤ ፅድቃችን የተረጋገጠበት እና በእግዚአብሔር ፊት ሃጢአት አልባ የሆንበት ነው።2ቆሮ 5፡21

▸የኢየሱስ መስቀል እርግማን የተወገደበት ሲሆን የክርስቶስ ትንሳኤ በመንፈስ እና በስጋ የተባረክንበት ነው። ገላ 3፡13 , ኤፌ 1፡4

የኢየሱስ መስቀል በሽታ የተወገደበት ሲሆን የክርስቶስ ትንሳኤ የክርስቶስ ጤና ለኛ የተቆጠረበት ነው።ኢሳ53 , 1ጴጥ 2፡24-25.

▸ የኢየሱስ መስቀል ከአዳም ግዛት ጊዜያዊ ከሆነ ከምድር ተስፋ ነፃ የወጣሁበት ሲሆን የክርስቶስ ትንሳኤ ግን ለሕያው ተስፋና ለማይጠፋ፥ እድፈትም ለሌለበት፥ ለማያልፍም ርስት ብቁ የሆንኩበት ነው። 1 ጴጥሮስ 1፡3-5፤

▸ የኢየሱስ መስቀል አለቅነት እና ስልጣናት የተሻሩበት ሲሆን። ቆላስይስ 2፡15 የክርስቶስ ትንሳኤ በጠላት ሀይል ሁሉ ላይ ባለስልጣን ለመሆን ስልጣን የተቀበልንበት ነው። ማቴ 28፡18-20,ሉቃ 10፡19

▸ የኢየሱስ መስቀል አባት ከልጁ ከኢየሱስ ፊቱን ያዞረበት የተወው ሲሆን። መዝ 22፡1 የክርስቶስ ትንሳኤ አባት እኛን የተቀበለበት እና አለቅህም ከቶም አልተውህም ያለበት ነው። ዕብ 13፡5

▸ የኢየሱስ መስቀል ኢየሱስ አምላኬ አምላኬ ብሎ የጮኅበት ሲሆን።/ መዝ 22፡1/የክርስቶስ ትንሳኤ አባ አባት ብለን የምንጮህበት የልጅነት መንፈስ የተቀበልንበት ነው። ሮሜ 8፡14-17
ገላ 4፡5-7

▸ የኢየሱስ መስቀል የዘር፣ የነገድ እና የቋንቋ ልዩነት የጠፋበት ሲሆን
የክርስቶስ ትንሳኤ አማኝ ሁሉ አዲስ ፍጥረት እና ሰማያዊ ዜጋ የሆንበት ነው። ራዕ 5፡10-, ፊሊ 3፡20

1 ጴጥሮስ 2፡9-19 (1 Peter)
እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤ እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል።

ፀጋ እና ሰላም ለሁላችን ይብዛ።

ለሌሎች አካፍሉ
Telegram: https://t.me/Hiyaw_qal
Facebook :https://m.facebook.com/103351765227313


ለእግዚአብሔር ስንገዛ


በእግዚአብሄር ፍቅር ልብህ ከተሸነፈ ጠላት ላንተ ይሸነፋል። ለእግዚአብሔር ስትገዛ የማይገዙ ነገሮች የሚመስሉህ ይገዙልሀል። ባህርን በበትር መትቼ እከፍላለው ብለህ ዳር ላይ ቆመህ ስታንቦጫርቅ ብትውል የሚከፈል ነገር አይኖርም፤ እንኳን ባህርን የሳፋ ውሀ በበትር አትከፍልም። አንተ ግን ለእግዚአብሄር ከተገዛህ የእግዚአብሄር የሆኑት ፍጥረት እንኳ እንደሙሴ ይከፈልልሃል። ባህር ይሰነጠቃል ፀሀይ ነክቶት በማያውቅ ደረቅ ምድር እየረገጥህ ትጓዛለህ። " ሙሴም በባሕሩ ላይ እጁን ዘረጋ፤ እግዚአብሔርም ሌሊቱን ሁሉ ጽኑ የምሥራቅ ነፋስ አምጥቶ ባሕሩን አስወገደው፥ ባሕሩንም አደረቀው፥ ውኃውም ተከፈለ።
(ኦሪት ዘጸአት 14 : 21)

ጥበብ ከእግዚአብሄር ትገኛለች። የዓለም ሳይንቲስቶች ብዙ ዓይነት ምርምር እያደረጉ ኑሮን ለማቅለል ቀን ከሌት ይተጋሉ እኛ ኑሮ ማለት እንጀራ በወጥ በልቶ ማደር ሆኖብን እነርሱ ኑሮ ማለት ከእለታዊ የኑሮ ልምምድ አልፈው ያልተገኘ መፈልጉ ያልታየውን ማጉላት ያልተደረሰበትን መጨበጥ ይፈልጋሉ ይህንን ጥበባቸውን ተጠቅመው ግን ፀሀይን ባለችበት አቁመው ቀኑን ማርዘም አስራ ሁለት ሰዓቱን ወደ ሀያ ሰአት መውሰድ አልቻሉም በሳይንሳዊ ምርምር ተፈጥሮን ማዛባት ፀሀይን ማቆም አይቻልም ቁሚ ቢሏትም ጆሮ የላትም። ለእግዚአብሄር ስንገዛ የፈጠራትን የምትሰማው ፀሀይ ለተገዛንለት ትገዛለችና ቁሚ ስንላት ትቆማለች። "ፀሐይም በሰማይ መካከል ዘገየ፥ አንድ ቀንም ሙሉ ያህል ለመግባት አልቸኰለም።"( ኢያሱ 10 : 13)

ለእግዚአብሔር መገዛት የህይወታችን ቅድሚያ ተግባር የእድሜ ልካችን መርህ መሆን አለበት። ለእግዚአብሄር ስትገዛ ጦረኛ በእረኛ ይወድቃል። ዛሬ ሚሳኤል የታጠቁትን ሰሜን ኮርያን፣ አሜሪካን፣ ሩሲያን በጠጠር እገዳደራለው ብሎ የሚነሳ ካለ በአለም ዘንድ መነጋገሪያ የሚሆነው እብድ ተብሎ ነው። ዳዊት የሆነውም እንደዚህ ነው። በጊዜው አለ የተባለው ዘመናዊ መሳሪያ ጦርና ጋሻ፣ ቀስትና ሰይፍ ነው። ይሄንን መሳሪያ የታጠቀውን ሀገር የሚያክል ሰው በወንዝ ጠጠሮች ለመግጠም መምጣት በተመልካች ዘንድ እብደት ነበር። ዳዊት ለእግዚአብሔር የተገዛ ሰው ነው። ወንጭፉ ስር ያለው ጠጠር የማዕዘኑ ራስ የተናቀው ድንጋይ ክርስቶስ ነበር። በዚህ ጠጠር አስጨናቂው ገንድሶ ጣለው። " ዳዊትም እጁን ወደ ኮረጆው አግብቶ አንድ ድንጋይ ወሰደ፥ ወነጨፈውም፥ ፍልስጥኤማዊውንም ግምባሩን መታ፤ ድንጋዩም በግምባሩ ተቀረቀረ፥ እርሱም በምድር ላይ በፊቱ ተደፋ።"
(1ኛሳሙ 17 : 49)

እግዚአብሄር የማይመስለውን ጨዋታ የሚመስለውን እምነት ከኛ ይሻል፤ በእርሱ ተአምር ይሰራበታል። ለእርሱ ሙሉ ለሙሉ ስንገዛ ተፈጥሮ ይገዛልናል ጠላት ይንበረከክልናል ማዕበሉ ፀጥ ይልልናል። ዛሬም ወዳጆቼ እንዲንበረከክ የምትፈልጉት ነገር ምንድነው? በላያችሁ ላይ ቆሞ የሚያፏጭባችሁ ምንድነው? አንገት ያስደፋችሁ ምንድነው? ተስፋ ያስቆረጣችሁ ምንድነው? ሙሉ ለሙሉ ለእግዚአብሄር ተገዙ፤ ራሳችሁን ምንም ሳታስቀሩ ፈርማችሁ ለእርሱ ስጡት፤ በማንኛውም ነገር ላይ እርሱን አስቀድሙት። ያን ጊዜ ለእርሱ ስትገዙ የገዛችሁን ትገዙታላችሁ፣ ባርያ ያደረጋችሁን ባርያ ታደርጉታላችሁ፣ የዛተባችሁ ላይ ድልን ትቀዳጃላችሁ፣ ሞት ሞት የሚሸታችሁ ህይወት ህይወት ይሸታችኋል።

ዛሬ ለእግዚአብሄር በመገዛት፣ ለእግዚአብሄር በመንበርከክ፣ ለእግዚአብሄር በፍቅር በመውደቅ ድል የምታደርጉበት ቀን ይሁንላችሁ። የሳቀባችሁ ጠላት ያልቅስላችሁ፤ በላያችሁ ከፍ ከፍ ያለ የጠላት ስራ ሁሉ ይዋረድላችሁ፤ ከፊታችሁ የተዘረጋ ጥቁር መጋረጃ ይቀደድላችሁ፤ አስሮ የገዛችሁ ይሙትላችሁ፤ ሰንሰለት ይበጠስላችሁ፤ ሰላማችሁ ይመለስላችሁ፤ ደስታችሁ ድርብርብ ይሁንላችሁ፤ ጠላት ይፈርጥጥላችሁ፤ በረከት ይሙላ በቤታችሁ። በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሜን።

@Agape_ze_orthodox
@Agape_ze_orthodox


ዲያቆን ሔኖክ ሃይሌ

+ የሕዝብ ቆጠራ መዝገብ +

ጌታችን በቤተልሔም ለመወለዱ ምክንያት የሆነው ለሕዝብ ቆጠራ ሲሉ ወደ ይሁዳ አውራጃ በመምጣታቸው ነበር:: ለቆጠራ መጥተው ከመቆጠራቸው በፊት ጌታችን ተወለደ:: ወደ ናዝሬት ከመመለሳቸው በፊት ግን ሁለት ሆነው ሊቆጠሩ የመጡበትን የሕዝብ ቆጠራ ሦስት ሆነው አድርገው ተቆጥረዋል::

እባካችሁ ያንን የቆጠራ መዝገብ ያለበትን ቦታ የምታውቁ የሮማውያን ታሪክ መርማሪዎች ካላችሁ ብትነግሩኝ ደስ ይለኛል:: ደግሞ የሕዝብ ቆጠራ መዝገብ ምን ያደርግልሃል? ካላችሁ መዝገቡ ይገኝ እንጂ እኔ ግን የምፈልገው አንድ ስም አለ:: ከብዙ የይሁዳ ተወላጆች ስም መካከል ሰሎሜ ዮሴፍ ማርያም ከሚሉ ስሞች አጠገብ አንድ ዓለም የዳነበት ስም በሕዝብ ቆጠራው መዝገብ ሥር ተጽፎአል::

#ጉልበት ሁሉ የሚሰግድለት #ስም : #ከሰማይ በታች #እንድንበት ዘንድ የተሠጠን #ስም : #ከስም በላይ የሆነ ስም : ቅዱስ ገብርኤል በክብር ይዞት የወረደና ለድንግሊቱ የነገራት ስም : አጋንንት ሲሰሙት የሚንቀጠቀጡለት #ስም : ሙታንን የሚያስነሣ ድውያንን የሚፈውስ ስም በዚያ የሕዝብ ቆጠራ መዝገብ ላይ እንደዋዛ እንዲህ ተብሎ ተጽፎአል::

#ኢየሱስ ✍🏽

አንተ የሕዝብ ቆጠራ ሠራተኛ ሆይ ይህንን ስም እዚያ መዝገብ ላይ ስትጽፈው ብዕርህ አልተሰበረም ወይ? ቀለሙስ አልሸሸም ወይ? እጆችህስ አልተንቀጠቀጡም ወይ?

ኢየሱስ በዚያ መዝገብ ላይ ተጻፈ:: በዚያ መዝገብ ከጌታ ጋር የተጻፉት ንጽሕት ድንግልና ጻድቁ ዮሴፍ ብቻ አልነበሩም:: በዚያች ግዛት ያሉ ሰዎች ሁሉ አብረው ተጽፈዋል:: ጥሩ ሰዎች ክፉ ሰዎች ወንጀለኞች ነፍሰ ገዳዮች ሰካራሞች አመንዝሮች በዚያ መዝገብ ላይ ስማቸው ተጽፎአል::

ኢየሱስም ገና ከመወለዱ ከኃጢአተኞች ጋር ተቆጠረ:: በሕይወት ዘመኑ የኃጢአተኞች ወዳጅ የሚል ቅጽል ስም የወጣለት ጌታ በዕለተ አርብም በግራና ቀኙ ከወንበዴዎች ጋር አብሮ የተሰቀለው ጌታ አሁንም በልደቱ ጊዜ "ከዓመፀኞች ጋር ተቆጠረ" (ኢሳ 53:12)

እኛን ከቅዱሳን ጋር ሊደምረን እሱ ከኃጢአተኞች ጋር ተቆጠረ:: እኛን "ስማችሁ በሰማይ ስለተጻፈ ደስ ይበላችሁ" ለማለት እርሱ በምድር መዝገብ ላይ ተጻፈ::

ወዳጄ ኢየሱስ ስለ አንተ ሲል ከኃጢአተኞች ጋር ተቆጠረ:: አንተ ስለ እርሱ ከንጹሐን ጋር ተቆጠርለት:: በተወለደበት ጊዜ ከሰካራሞችና ዘራፊዎች ስም ዝርዝር ጋር ለአንተ ሲል አብሮ ተቆጠረ:: እስቲ አንተ ልደቱን አስበህ ከሚሰክሩት ሰዎች ስም ዝርዝር ውስጥ ውጣ:: ከዘራፊዎችም መካከል ተለይ:: ክርስቶስ ወደ አንድ ነገር የሚገባው የሚገቡትን ሊያወጣ ነው:: ወደ ሞት የገባው ሙታንን ሊያወጣ ነው:: ወደ ሲኦል የወረደው ነፍሳትን ከሲኦል ሊያወጣ ነው:: ወደ ሮማውያን የሕዝብ ቆጠራ የኃጢአተኞች መዝገብ ስሙ የገባውም የሁላችንን በደል ተሸክሞ እኛን ከዚያ መዝገብ ሊያስወጣን ነው::

"ስማችሁ ግን በሰማያት ሰለ ተጻፈ ደስ ይበላችሁ"
ሉቃ 10:20 )

@Agape_ze_orthodox
@Agape_ze_orthodox


ዛሬ በመላው ዓለም ባለች ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ላይ ከተጸለየ የተወሰደ:-

አዎን አቤቱ አምላካችን ስለ ስምህ አንተን ደስ ከማያሰኝ አሳብ እንለይ ዘንድ መለየቱን ስጠን። በአርያም ባለች በመቅደስህ መጋረጃ ውስጥ በስምህ ከተጻፍን ከእኛ የሞት ምክር ሁሉ ይርቅ ዘንድ መራቁን ስጠን። ያንተን ስም ሰምቶ ሞት ይደንግጥ! ቀላያትም ይሠንጠቁ። ጠላትም ይረገጥ። የጥፋት መንፈስም ይቀጥቀጥ። ከይሲም ይወገድ። አለማመንም ይራቅ። ወንጀለኛ ይቸገር። ቁጣ ጸጥ ይበል። ቅናት ጥቅም አያግኝ። ኃጢአትን የሚያዘወትር ይገሠጽ። ወርቅን የሚወዱ ይነቀሉ። ድካም ይወገድ! ሐሰተኛ ይጣል። መርዝ ያላቸው የፍጥረታት ወገን ሁሉ ይበተን። አቤቱ ለልቡናችን ዓይኖች ውሳጣዊ ብርሃንን ስጥ። እያሰቡህና ላንተ እየተገዙ አንተን ለይተው ያከብሩህና ያመሰግኑህ ዘንድ ዕድላቸው አንተ ብቻ ነህና። ሁሉ የሚገዛልህ የእግዚአብሔር ቃሉና ልጁ ሆይ የገለጽህላቸውን ጸጋ ፈጽም። አጽናም። በደኅንነት ጸጋ ያሉትንም ጠብቅ። በአንደበት ኃይል ለሚያመሰግኑ በአንደበት ቃል የተናገሩትን ሃይማኖት አቅና። ሁለጊዜ ፈቃድህን የሚሠሩትን አድን። ባል የሌላትን ጎብኝ። እናት አባት የሌለውን ተቀበል። አምነው ያረፉትንም ተቀበል። አቤቱ ለእኛም ከቅዱሳንህ ሁሉ ጋራ ዕድልን ስጠን። እነርሱ ደስ እንዳሰኙህ ደስ እናሰኝህ ዘንድ ኃይልን ስጠን።
ሰላሙ በሁላችሁ ቤት ይደር

@Agape_ze_orthodox
@Agape_ze_orthodox


እውነተኛ ደስታ 

ከምናገኛው ብዙ መልካም ነገር የተነሳ ደስታ ውስጣችን ይገኛል ይሆናል ልክ ይሁን አይሁን  የሚለው እንዳለ ሆኖ። አለማችን ብዙ የሀሰት ደስተኞች አላት። ጥርሳቸው እየሳቀ ልባቸው የሚያለቅስ፣ ሰው ፊት የከበዱ ግን ጥላቸው የሚከብዳቸው፣ ደስ እንዳላቸው የሚያስመስሉ ነገር አይምሮአቸውን ማታለል ያልቻሉ።

እውነተኛው ደስታ ያለው  በማግኘት ውስጥ ሳይሆን እግዚአብሔርን በማወቅ ውስጥ ነው። ባለማግኘት ውስጥ ሁሌ በእግዚአብሔር ደስተኛ መሆን በማግኘት ውስጥ ለአለም ደስታ ከመሰለፍ ይልቃል።

እውነተኛ ደስታ ለሽያጭ ገብያ ቢወጣ ስንቱ ደስተኛ ነኝ ባይ ደስታን ሊሸምት ገብያ ይወጣ ነበር። ስታገኝም ሆነ ስታጣ ሁሌ ደስታ በእግዚአብሔር ውስጥ ይሁን። ልታገኘው ከምትዳክረው ጥቅማጥቅም በላይ ያገኛው የእግዚአብሔር እርስት ይበልጣልና።

ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥ በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥ የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥ በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥
እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤ በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ።
ዕንባቆም 3:17-18


@Agape_ze_orthodox
@Agape_ze_orthodox


ዓለም ሁሉ ከነኃጢአቱ ፣ ከነቁስሉ ፣ ከነበደሉ ፣ ከነግፉ ቢታጠብበት የማይደፈርስ የምህረት ባህር፤ የቅድስና ሀይቅ ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ ነው።

@Agape_ze_orthodox
@Agape_ze_orthodox




ውድ ወገኖቼ በዚህ ቻናል አሳብ ጥያቄ ካላችሁ ▸ 👉 @wededen 👈 ማግኘት ይችላሉ ይላኩልን ።


ኃጢአትን ልታስወግድ ሞትን ልትሽር የዲያብሎስን ሥራ ልታፈርስ የተገለጥከው ቀዳማዊው ቃል የእግዚአብሔር ብቸኛ የባህሪይ ልጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እናመሰግንሀለን በፊትህ ስንቴ ወድቀን ይሆን አንተስ ስንቴ ምረህን ይሆን ከቋንቋ በላይ ስለሆነው ምህረትህ ስምህን ከፍ ከፍ እናደርጋለን በሀሌዮ በነቢብ በግብር ኃጢአተኞቹን በልጅህ ሞት የታረከን አባታችን እግዚአብሔር ሆይ ለዘላለም ስምህ ብሩክ ይሁን ጨለማን በብርሃን ሞትን በህይወት መቃብርን በትንሳኤ ውድቀትን በጽናት ውርደትን በክብር ኃጢአትን በጽድቅ በደልን በቅድስና ባርነትን በልጅነት የለወጥህልን ውዳችን ሆይ ተመስገን ዛሬ ላይ ቆመን ትናንትን ትናንት ያልነው ባንተ ነውና ነገም ተስፋችን አንተ ነህና እናመሰግንሃለን ከምድር እስከአርያም ከልባችን እስከ ሰማያት ጫፍ ክብር ማደርያህን ይሙላው እኛን ከመውደድህ የተነሳ ከሰማይ ወደ ምድር ከዙፋን እስከ መስቀል ድረስ የተዋረድክል ጌታችን አንተ ነህና ተመስገን። ጌታ ሆይ እባክህ ከኃጢአት እንድንርቅ ከሰይጣንም ከራሳችንም ጠብቀን ዘመናችንን ዋጅተህ የቃልህን ደጆች ከፍተህ አስተምረን ሁሉ ላንተ ክብር ይሁን በአማኑኤል ስምህ በፈሰሰው ደምህ ለዘላለሙ አሜን!!



Показано 20 последних публикаций.

3 226

подписчиков
Статистика канала