Amhara Police Commission


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Политика


Peace keeper

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Политика
Статистика
Фильтр публикаций


በማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ 6 የጽንፈኛዉ ቡድን አባላት በዛሬው እለት የሰላም አማራጭን መርጠዉ ተቀላቅለዋል።

በዛሬው እለት የሰላም አማራጩን ተቀብለው የተቀላቀሉ አካላትም ለሰላም ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በወረዳው ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ከሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ከሀይማኖት አባቶች፣ ከሀገር ሽማግሌዎችና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብሩክ መኮነን በወረዳው በዛሬው እለት 6 የታጠቁ ሀይሎች የሰላም አማራጩን ተቀብለው እንደገቡ ገልፀው የሚፈጠሩ ችግሮችን በሰለጠነ አኳኻን በውይይት መፍታት ተገቢ መሆኑን አንስተዋል።

መረጃው የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ኮሙኒኬሽን ነው።


በፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ዳሞት መሰናዶ ቁጥር 1 ት/ቤት ላይ በተፈፀመ የቦምብ ጥቃት በ31 ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የፍኖተ ሰላም ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ገለፀ።

በቦምብ ጥቃቱ 6 ተማሪዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ሙሉዓም ገሰሰ ገልፀዋል።

የቦምብ ጥቃቱ ዛሬ ማለትም መጋቢት 26/2016 ዓ/ም ከጥዋቱ 2፡30 ሰዓት መፈፀሙን የተናገሩት ምክትል ኮማንደሩ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው 6 ተማሪዎች ለከፍተኛ ህክምና ሪፈር ተፅፎላቸው የህክምና ክትትል እያገኙ ሲሆን 15 ተማሪዎች ደግሞ በፍኖተ ሰላም ጠቅላላ ሆስፒታል ህክምና እያገኙ ናቸው ብለዋል።

10 ተማሪዎች ላይ ደግም ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
አደጋውን ተከትሎ አንድ ተጠርጣሪ ተማሪ መያዙን የገለፁት ምክትል ኮማንደሩ በድርጊቱ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ስር ለማዋል ጽ/ቤቱ እየሰራ መሆኑን ምክትል ኮማንደር ሙሉዓለም ተናግረዋል።




በሕገ-ወጥ መንገድ የጦር መሣሪያ በማዘዋወር ለፀረ ሰላም ኃይሎች ሊያቀብሉ የሞከሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ወሎ እና ደሴ ከተማ ኮማንድ ፖስት አስታውቋል፡፡

47 ሺህ ጥይትን ጨምሮ አራት ክላሽና አንድ ስናይፐር በሕገወጥ መንገድ ሲገበያዩ እና ሲያዘዋውሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የመከላከያ ሠራዊት አስታውቋል።

በሀገር መከላከያ ሠራዊት ኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ የ103ኛ ክፍለ ጦር 5ኛ ኮማንዶ ሪጅመንት ዋና አዛዥና የኮማንድ ፖስቱ አባል ሻምበል ታሪኩ ሻሜቦ እንደገለጹት፤ በሕገ ወጥ መንገድ የጦር መሣሪያ በማዘዋወር ላይ የተሳተፉ 42 ተጠርጣሪዎችን ከኅብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት መያዝ ተችሏል ብለዋል።

ለጽንፈኛ ኀይሎች ሊተላለፍ የነበረ 47 ሺህ ጥይት፣ አራት ክላሽና አንድ ስናይፐር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የገለጹት ሻምበል ታሪኩ፤ ከዚህ ባሻገር ለመሣሪያ ግዢ ሊውል የነበረ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብም በሠራዊቱ በቁጥጥር ስር ውሏል ብለዋል።

ተጠርጣሪዎች መሣሪያ በማዘዋወርና በመገበያየት ለፀረ ሰላም ኃይሉ በማቀበል ቀጣናውን የግጭት አካባቢ ሊያርጉ እንደነበሩ የገለጹት ሻምበል ታሪኩ፤ "ከኅብረተሰቡ ጋር በተደረገ ትብብር ሴራቸውን ማክሸፍ ተችሏል" ብለዋል፡፡

ሠራዊቱ በደቡብ ወሎ እና አካባቢው በጽንፈኞች ላይ እየወሰደ ያለውን ርምጃ አጠናክሮ መቀጠሉን የገለጹት ሻምበል ታሪኩ ሻሜቦ ኅብረተሰቡ አንድነቱንና ሰላሙን ጠብቆ ከሠራዊቱ ጎን መሰለፉን ተናግረዋል።
በቀጣይም በጽንፈኞች ላይ የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ያስታወቁት።

ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ሲገዙና ሲደልሉ የተያዙት ተጠርጣሪዎችም በመከላከያ ሠራዊት በቁጥጥር ሥር ከዋልንበት ጊዜ ጀምሮ ምንም የደረሰብን ችግር የለም በሠራነውም ሥራ ተፀፅተናል ብለዋል።
ዘጋቢ፦ አማኮ




በቡሬ ዙሪያ ወረዳ በቁጭ ንዑስ ቀበሌ ስር የሚገኙ ሁለት አካባቢዎች ራሳቸውን ከጽንፈኛው ጥቃት መከላከላቸውን የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ ።

የቡሬ ወረዳ አስተዳደር አቶ ሃይማኖት አሰፋ እንዳስታወቁት፣ በቁጭ ስር የሚገኙት ሶንቶም እና ቦቆጣቦ አካባቢዎች ከመከላከያ ሰራዊቱና የክልሉ የፀጥታ ኃይሎች ጋር ተሰልፈው ዘመቻ ጀምረዋል፡፡

ከዚህ በፊት በቡሬ ዙሪያ ባሉት ሶንቶም እና ቦቆጣቦ ማኅበረሰብ ላይ ጽንፈኛው ቡድን ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ከመፈፀም ባለፈ በርካታ ንብረት ዘርፏል፤ ሴት ወንድ ሳይል የጨፍጭፋ ተግባሩን ሕዝብ ላይ አሳይቷል ብለዋል፡፡

በቁጭ እና አካባቢው የሚገኙት እነዚህ አካባቢዎች ተደራጅተው የአማራ ሕዝብ ገዳዮች እና ዘራፊዎችን የማጽዳት ሥራ በሰፊው በመሥራት ቀጣናውን ከጽንፈኛ ነጻ ማውጣት ችለዋል ያሉት አቶ ሃይማኖት፣ አሁን ላይ በወረዳው ስር የሚገኙ ቀበሌዎች በፖሊስ እና በሚሊሻ የፀጥታ ሥራ እየሠሩ ኅብረተሰቡም ያለ ስጋት የእለት ኑሮው እንዲገፋ ማድረግ መቻላቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በነዚህ ሁለቱ ቀበሌዎች ጽንፈኛው በአሳቻ ሰዓት የፈፀመው ጭፍጨፋ እና የንብረት ዘረፋ ያስቆጣው ኅብረተሰብ ዳግመኛ በወረዳው እንደይደገም በአካባቢው ከሚገኙ የፀጥታ ኃይሎች እና መሥተዳደሮች ጋር በመቀናጀት የአካባቢውን ሰላም ዘላቂነት ለማረጋገጥ የተቀናጀ ዘመቻ መጀመራቸውንም ተናግረዋል ፡፡
ጽንፈኛው በተሳሳተ የማደናገሪያ ትርክቶች "የአማራ ሕዝብ ጥያቄ መላሽ እኔ ነኝ" ብሎ የተገዘተ ቢኾንም በተቃራኒው በመግደል፣ እገታ እና ዝርፊያ በመፈፀም በስቃይ አለንጋ ሕዝቡን ገርፎታል፡፡ በተለይም በሶንቶም እና ቦቆጣሞ ቀበሌዎች የፈፀመው ጭፍጨፋ እና ዝርፊያ ብሶት የወለደው ኅብረተሰብ እንዲፈጠር አድረጎታል ነው ያሉት፡፡

ኅብረተሰቡ ይህንን በታሪክ ገጥሞት የማያውቀውን ጥቃት ከመከላከያ እና ከአማራ የጸጥታ ኃይል ጋር በመጣመር እየተከላከለ ይገኛል። በእስካሁኑም መልካም ውጤት ማስገኘት ችሏል ብለዋል።

መረጃው የጎጃም ኮማንድፖስት ነው።


የባሕርዳር ጎንደር ኮማንድ ፖስት መነሻውን አሸሬ አድርጎ ወደ ጎንደር ከተማ ሊገባ የነበረን መትረየስና ጥይት ከነ ዝናሩ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል።

ኮማንድ ፖስቱ እንዳስታወቀው መነሻውን አሸሬ አድርጎ ወደ ጎንደር ከተማ በመግባት ላይ እያለ ወለቃ ኬላ ላይ ከ3 ተጠርጣሪዎች ጋር አሽዋ በጫነ ሲኖትራክ ኮድ 3 ታርጋ 77975 E T መኪና አሽዋ ውስጥ ደብቆ ሊያሳልፍ የነበረውን አንድ ብሬን ከአንድ ዝናር ጋር እንዲሁም 214 የብሬን/የመትረየስ ጥይት በቁጥጥር ስር ማዋሉን ኮማንድ ፖስቱን ጠቅሶ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዘመቻ መምሪያ የላከው መረጃ አመልክቷል።

ገብርየ አያና አደባ ፣ሀብቴ ክብሬ መንግስቴና መልካሙ ባባይ ካሰሁን የተባሉ ተጠርጣሪዎች መሳሪያውን ሲኖትራኩ በጫነው አሸዋ ውስጥ በመቅበር ለማሳለፍ ሲሞክሩ በተደረገባቸው ጥብቅ ክትትል ወደ ጎንደር ከተማ ሳይገባ ወለቃ ኬላ ላይ ሊያዙ ችለዋል።

የባሕርዳር ጎንደር ኮማንድ ፖስት እንዳስታወቀው የተጠናከረ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ የፅንፈኛው ተላላኪዎች ሊያሳኩት የነበረው ህልም ከሽፏል፤ በቀጣይም በመረጃና ክትትል ተጠርጣሪዎች መሽገውባቸዋል የሚባሉ ስፍራዎችን የማስስ፣ የማደንና እርምጃ የመውሰድ ኦፕሬሽኖች እንደሚከናወኑም አስታውቋል።
ዘገባው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ሚዲያና ሕዝብ ግንኙነት ነው


በጭልጋ ወረዳ ከሀይማኖት አባቶች ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ

በወረዳው ከተወጣጡ የሀይማኖት አባቶች ጋር ዘላቂ ሰላምንና ልማትን ለማጠናከር ያለመ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።

በምክክር መድረኩ የወረዳውን ዘላቂ ሰላም ለማጠናከር የሚያስችሉ ሀሳብ እና አስተያየት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

ዘላቂ ሰላምንና ልማትን በማጠናከር በኩል የሀይማኖት አባቶችና ሚናቸውን እንዲወጡም ተጠይቋል።

መረጃው:- የጭልጋ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ነው


በባህርዳር -ጎንደር ኮማንድ ፖስት የኮማንዶና አየር ወለድ ክፍለጦር የሰላም አማራጭን በማይከተሉ ፅንፈኞች ላይ የሚወስደውን የኃይል እርምጃ አጠናክሮ ቀጥሏል።

ፅንፈኛው ከተሰገሰገበት መንደር የመመንጠር ዘመቻው በተጠናከረ ሁኔታ መቀጠሉንና ሌሎች የፅንፈኛውን ተላላኪዎች በሚያስተምር መንገድ ተገቢውን ቅጣት ማግኘታቸውን በባህርዳር- ጎንደር ኮማንድ ፖስት የአየር ወለድ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል አየልኝ አስናቀ ተናግረዋል።

ሰሞኑን በባህር ዳርና መሸንቲ ዙሪያ በተደረገው አሰሳ የዘራፊው ቡድን አከርካሪ መመታቱን የገለፁት ሌተናል ኮሎኔል አየልኝ አስናቀ ፅንፈኛው መሸንቲ ዙሪያ ለጥፋት ተልዕኮ ሲጠቀምባቸው የነበሩ ሞተር ሳይክሎች እንዲሁም በባህርዳር ዙሪያ በተደረገው ኦፕሬሽን ደግሞ ልዩ ልዩ የጦር መሣሪያዎች፣ ተተኳሾችና ፅንፈኛው ለጥፋት ተልዕኮ ሲገለገልባቸው የነበሩ ቁሳቁሶችን በቁጥጥር ስር አውለናል ብለዋል።

የኮማንዶና አየር ወለድ ክፍለ ጦር ከሰሜን ምዕራብ ዕዝ፣ከምስራቅ ዕዝና ከሌሎች አጎራባች የጦር ክፍሎች ጋር በመሆን ፅንፈኛውንና ዘራፊውን ቡድን የመደምሰስ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት በመወጣቱ በኮማንድ ፖስቱ ቀጠና በአሁኑ ሰዓት አንፃራዊ ሰላም ተገኝቷልም ብለዋል።

የዘራፊው ቡድን ስብስብ በሠራዊታችን የደረሰበትን ጥቃት መቋቋም ተሰኖታል ያሉት የአየር ወለድ ምክትል አዛዡ በመረጃና ጥናት ላይ በመመስረት ከተሰገሰጉበት ከእያንዳንዱ አካባቢ መንጥሮ የማውጣትና አስፈላጊውን ተመጣጣኝ እርምጃ የመውሰድ ዘመቻው በሚገባ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል።

ሌተናል ኮሎኔል አየልኝ ክፍለ ጦሩ አጠናክሮ በቀጠለው ፅንፈኛውን የመደምሰስ ዘመቻ ህብረተሰቡ መረጃ በመስጠት እያደረገ ያለውን ድጋፍ አድንቀዋል።




የአጣዬ ከተማ አስተዳር እና አካባቢውን ህዝብ ሰላም ወደ ቀድሞ ሁኔታ ለመመለስ ያለመ የህዝብ ውይይት ተካሄደ፡፡

በአጣዬና አካባቢው የተፈጠረው የፀጥታ ችግር በመፍታት የአጣዬ ከተማ አስተዳር እና አካባቢውን ህዝብ ሰላም ወደ ቀድሞ ሁኔታ ለመመለስና የተዘጉ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ወደ ስራ በሚገቡበት ሁኔታ ላይ በአጣዬ ከተማ በ3ቱም ቀበሌ የህዝብ ውይይት ተደርጓል፡፡

በየቀበሌው የተደረገውን የህዝብ ውይይት የሰሜን ሸዋ ዞን አመራሮች የመሩት ሲሆን የአጣዬ 01 ቀበሌ የህዝብ መድረክ የኢፌደሪ መከላከያ ሰራዊት የ112ኛ አየር ወለድ ክ/ጦር አዛዥና የኮማንድ ፖስት አስተባባሪ ኮሎኔል አሰፋ አየለ፤ የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሽ አለማየሁ ፤ የሰሜን ሸዋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ኤልያስ አበበ በጋራ በመሆን መድረኩን የመሩት ሲሆን በውይይቱም የህግ የበላይነት መከበር እንዳለበትና ለአጣዬ ከተማ የፀጥታ ችግር ግንባር ቀደም ተዋናይ የሆኑ አጥፊዎች በህግ ተጠያቂ መሆን እንዳለባቸው ተገልጿል።

በሁለቱም ወገን ያሉ ጦርነት ደጋሾች ሊታረሙ እንደሚገባና የአማራ ህዝብና የኦሮሞ ብሄረሰብ ህዝብ እርስ በእርሱ የተሳሰረ ፣ የረጅም ዘመን የአብሮነት ትስስር ያለው ህዝብ መሆናቸውን ከመድረኩ ተገልጿል፡፡

በመሆኑም በአጣዬና አካባቢው በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ከቤት ቀያቸው የፈናቀሉ ማህበረሰቦች መመለስ እንዳለባቸው ፣ የተዘጉ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት የመንግስት የግልና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተከፍተው ህብረተሰቡን ማገልገል እንዳለባቸው አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመጨረሻም የተሰሚነት ያላቸው የሀገር ሽማግሌዎችን በመምረጥ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

Amhara North Shewa Zone Communication

Показано 11 последних публикаций.