አትሮኖስ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።

Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


profile ይፈልጋሉ
    እንግዴውስ join ይበሉ




🎥የትርጉም ፊልሞች፣ተከታታይ የእንግሊዝ እና 🎬🎬የአሜሪካ  ፊልሞች ፣  VIP CHANNEL በነፃ 📺
 
      ይህንን ቻናል ለመቀላቀል ለምትፈልጉ
👇👇👇👇👇👇

https://t.me/addlist/UbA-kbT9Nk0yOWI0


ቢያጥረኝ (ያኔ እሷ ትምህርቷን ጨርሳ ነበር) ገጠር ለገጠር ተንከራታ ያጠራቀመቻትን ብር አውጥታ ተማሪ ብላ የሰጠችኝ እህቴ ናት። በደመወዝ ከእሷ እሻል ነበር፤ ግን ለሜካፕ፣ ለልብስ፣ ቶማስ ለሚባል ሥራ ፈት ጓደኛዬ የማወጣው ወጭ አራግፎኝ ነበር። ተይው ይቅርብኝ ስላት እጄን ይዛ ወስዳ ያስመዘገበችኝ ማኅደረ ናት፡፡ ይኼን ሳስብ ዕንባዬ ይመጣል፤ ግን የማላውቀው በሸታ አለብኝ፣ ውድቀቷ ያስደስተኛል፡፡ እሷ ካልወደቀች እኔ የምነሳ አይመስለኝም። ከእኔ መዳን ይልቅ የእርሷ መታመም ነበር ነፍሴን የሚያስደስታት። ውበቷ ሥር ተደብቄ ነበር፡፡ በውበቷ አምሬ ታይቼበታለሁ፤ ፀሐይነቷ ነበር ጨረቃ አስመስሎ ያሳዬኝ። እንደሆነ ውድ ጌጥ ማኅደረን አጊጨባታለሁ፤ ደምቄባታለሁ።

ያንን ውበት የውፍረት ናዳ ቆንጆ ሴት ውበት ጥላ ሥር ሲቀብረው ቀስ በቀስ መራቅ ጀመርኩ፡፡ በእያንዳንዷ “ባለ ድርሻ አካላት'' ነን ብለው የሚጠለሉት ወንዶች ብቻ አይደሉም፤ ዓላማው ይለያይ እንጂ እኛም ሴቶች አለንበት፡፡ ክፉ ነኝ የምለው በዚህ ብቻ አይደለም ከማኅደረ ጋር ከመራቄ በፊት ናፈቅሽኝ በሚል ሰበብ ሄጄ፣ አብርሃም ጋር ስላዬኋት አዚዛ የምትባለው ሴት ውበት አንድ በአንድ ነገርኳት፤ ያውም ካዬኋት ከስንት ጊዜ በኋላ “ምን ዓይነቱ ልክስክስ ነው!?'' እያልኩ “አዚዛ ነው ስሟ አልኳት” የሰውነት ቅርጽዋ ተይው... ይመስለኛል ውጭ አገር ቆይታ የመጣች ስልጡን ሴት ናት...'' እያልኩ... ማኅደረን በእያንዳንዱ ቃል ሰውነቷን በመርፌ የምጠቀጥቃት እስኪመስለኝ ስቃይዋን ፊቷ ላይ አዬው ነበር፡፡ እነዚያ መርፌዎች ለዓመታት እንደ ጋሻ ፊቷ ቆሜ፣ እኔ ሰውነት ላይ ሲሰኩ የኖሩ ነበሩ... ጓደኛዬ ናት፤ ባካፍላት ምን ችግር አለው? ብዬ በውስጤ እስቅና መልሼ “ምን አደረገችኝ ግን?'' እላለሁ፡፡ ይኼም ሁሉ ሆኖ የምትኖርበት የተንጣለለ ግቢና “ቪላ' ያበሳጨኛል፡፡ እናቴ ስለ ማኅደረ በተነሳ ቁጥር ባይነሳም ራሷ ድንገት አንስታ "ደሀና ሰው ላይ ወደቀች" ትላለች። እዚያ ግቢ ውስጥ የቆመች ባሏ የገዛላት መኪና፤ ምንም ሳትሠራ ዘና ብላ መኖሯ ጭምር ደሜን ያፈለዋል፡፡ እጇን አጣጥፋ ተቀምጣ እንኳን ለአሸናፊነት መፈጠሯ የሚገባኝ፣ የባሏ ቤተሰቦች እንደ ልዕልት ሲያቀማጥሏት ስመለከት ነው፡፡ ተፈጥሮ ፍርደ ገምድል ይሆንብኛል፡፡ ጓደኝነቴ ከምን ዓይነት መንፈስ እንደተሠራ እንጃ! ምናልባትም እያንዳንዱ ጓደኝነት ውስጥ ትንሽ ትንሽ ጠላትነት ሳይኖር አይቀርም። ለእሷ አዝኜ ሳይሆን በራሴ ውድድር ዐሥር ጊዜ እየወደቁ መላላጥ ሰልችቶኝ መራቁ ይሻለኛል አልኩ፡፡

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ገና እንደኛ ክፍል ስገባ ማኅደረ ጋር አንድ ወንበር ላይ ነበር የተቀመጥነው፡፡ ያኔ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቅነው፡፡ ያቺ የቆላት እናቷ እንደ አሻንጉሊት አሰማምራ ነበር የምትልካት፤ ደብተሯ ሳይቀር ጠረኑ የሽቶ ነበር። እኔ ለእንጀራ ሻጭ እናቴ ገና በጧቱ ቅጠል ሳቀብል ምድጃ ለምድጃ ቆይቼ የጸጉሬ ላይ ሸቀጥ እንኳን ሳይራገፍ pስ ጭስ እየሸተትኩ ነበር ተንጨባርሬ ክፍል የገባሁት፡፡ የመጀመሪያ ቀን አርፍጄ ስደርስ ክፍሉን የሞሉት ማቲዎች በአዲስ ዓመት ልብስ ዘንጠው የልብ ልብ ስለተሰማቼው፣ _ እንደ እኔ ዓይነት ጨብራራ _ አመዳም _ ሕፃን _ አጠገባቼው እንድቀመጥ አልፈለጉም። ታዲያ ያቺ እንደ አሻንጉሊት የምታምር ጥቁር ልጅ “ነይ እዚህ” ብላ ጠጋ አለችልኝና ልክ እንደ ትልቅ ሰው “ማነው ስምሽ? እኔ ማኅደረ ነው ስሜ'' አለችኝ፡፡ ቅልብልብ ያለች ነበረች። ዓመቱን ሙሉ ከእርሳስ እስከ ቸኮሌት እያካፈለች ጓደኝነታችንን በትንሽ ደግ ልቧ ሠራችው፡፡ ቸኮሌት ለመጀመሪያ ጊዜ ያቀመሰችኝ ማኅደረ ናት። እነዚያ ከረሚላዎች እና ቸኮሌቶች የቅንጦት ጣፋጭ ብቻ አልነበሩም-ለእኔ፤ በአሥር ጥፍሩ ይሟጭረኝ ከነበረ አስቀያሚ ርሃብ የሚገላግሉኝ መደበኛ ምግቦች ነበሩ፡፡ ችጋራም፣አስቀያሚ እና ሰነፍ ነበርኩ፡፡ በዚያ ላይ አብዝታ ትዘፍንልኝ ነበር፡፡ለእኔ ብቻም ሳይሆን ተማሪ ፊት ወጥታ ትዘፍን ነበር። የማታውቀው ዘፈን አልነበረም፤ አፍ የፈታችው በዘፈን ይመስላል። በዚያ ዓመት ምኑም ባልገባኝ በማላውቀው ትምህርት ወድቀሻል አሉኝ፤ ማኅደረ ግን አለፈች፡፡ በማለፏ ከመደሰት ይልቅ በእኔ መውደቅ አለቀሰች። እናቴ ካርዴን ጎረቤት ወስዳ አስነበበችና አገር እስኪቃጠል _ ስድብና ርግማን _ እያወረደች እስኪበቃት ቀጠቀጠችኝ። ከምንም በላይ ያበሳጫት ደግሞ ካርዴ ላይ “የወላጅ ክትትል ያስፈልጋታል" የሚል አስተያዬት መጻፉን ጎረቤቶቻችን ከነገሯት በኋላ ነበር፣ (እናቴ ማንበብም ሆነ መጻፍ አትችልም፤ እስከዛሬም ነገሮችን የምትተረጉምበት መንገድ የተለዬ ነው) “እናቷ አትከታተለትም አስባልሽኝ እና ማነው የሚከታተልሽ?” ሌላ ዱላ፡፡ በመኻል ድብደባውን አቁማ “ማኅደረ አለፈች?''

አለችኝ፤ መልሴን ሳትጠብቅ “እሷማ ታልፋለች'' ብላ እንደገና ድብደባዋን ቀጠለች። ከመውደቄ በላይ በማኅደረ ማለፍ ቅናትና ጥላቻ እንደ መንፈስ እዚያው ላይ ገባብኝ፤ ከዚያ ሁሉ ሥጋዬን ያዛለ ድብደባ ይልቅ እናቴ የማኅደረን ስም ከጠራች በኋላ የሰነዘረቻቼው ዱላዎች ነፍሴ ላይ ነበር ያረፉት። ቢሆንም በአንድ ክፍል እንደተበላለጥን ጓደኝነታችን ቀጠለ። ማኅደረ አራተኛ ክፍል፣ እኔ ሦስተኛ ክፍል ሆነን ማኅደረ እናቴ ጠፋች እያለች በየቀኑ ማልቀስ ሆነ ሥራዋ፡፡ መዝፈኗን አቆመች...ያቺ ምላሳም ልጅ የማትናገር የማትጋገር ዝምተኛ ሆነች፡፡ እኔ ጋር ብቻ ነበር የምታወራው፤ በዚያው ዓመት በጭራሸ ያላሰብኩት ነገር ተፈጠረ። በጉብዝናዋ የምትታወቀው ማኅደረ ወደቀች። ካርዷ ላይ የታተመውን አልተዘዋወረችም የሚል ማኅተም ሳይ ውስጤ በደስታ ዘለለ፡፡ ጓደኝነታችን እንደገና አንድ ክፍል አንድ ወንበር በመጋራት ቀጠለ። ያቺን ድል የሕፃንነት ተራ ጉዳይ አድርጌ አላያትም፡፡ በሳታወስኳት ቁጥር ነፍሴ ይደሰታል፡፡ አልተዘዋወረችም! የሚል ቃል በወርቃማ ፊደል የተጻፈ የድል ቃል ነው የሚመስለኝ፡፡ በትምህርት መጎበዝ የጀመርኩት በማኅደረ ርዳታ ከአራተኛ ክፍል በኋላ ነበር። ያ ውለታዋ ግን ከቅናት አልፈወሰኝም፤ እንዲያውም በረዳችኝ ቁጥር ውስጤ ይበሳጭ ነበር። ሰነፍ ሆና ወደቀች የተባለችው ልጅ፣ በዓመቱ ከክፍል አንደኛ ወጥታ ወደ አምስተኛ ክፍል ተዘዋወረች፤ ሃያ ምናምነኛ ወጥቼ ተከተልኳት፤ ደስታዬ ደፈረሰ፡፡

ድል ሁለት!

ከጋሽ ዓለምነህ አርግዠ ካስወረድኩ በኋላ፣ ከሃይማኖት ሰባኪውም፣ ከሬዲዮና ምናምን _ ሰባኪውም በላይ የበለጠ መርከስና ትንሽነት ይሰማኝ የነበረው፣ ከማኅደረ ጎን ስቆም ነበር፡፡ ሲጀማምረኝ ሕክምናም መሄድ ፈርቼ ስለዘገዬሁ ኢንፌክሸን _ፈጥሮብኝ የሆነ ሽታ ያለው ፈሳሸ ከማሕፀኔ እየወጣ ያሳቅቀኝ ነበር። አንድ ቀን ታዲያ ልናጠና ተቀጣጥረን እቤታቼው ስሄድ፤ ማኅደረ በተለመደው የጓደኝነት ስሜት ፊቷን አጨፍግጋ “የሆነ ነገር ይሼተኛል፤ አንቺ ደንባራ ምናምን

ረግጠሻል እንዴ?' አለችኝ ወደ ጫማዬ እያዬች። ጊዜ ሄደ፤ ከዓመታት በኋላ አብርሃም ጋር _ጉድ ጉድ ስትል አረገዘች፤ እየጎተትኩ ወስጄ ባለፍኩበት መንገድ ታልፍ ዘንድ ጋበዝኳት፤ አስወረደች፡፡ እንደ ሰው ስቃይዋ ቢያሳዝነኝም ጥልቅ በሆነ የአእምሮዬ ክፍል ግን እኩልነት ሰፈነ።

ድል ሦስት!

ማኅደረ ካገባች በኋላ በሚያስደነግጥ ፍጥነት ሰውነቷ መቀዬር ጀመረ። መወፈር ጀመረች “መወፈር” የሚለውን ቃል የምጠቀመው ሆነ ብዬ ነው። ክብደት ጨመረች ምናምን አልልም፤ እኔን ቀጨጭሽ እንጅ ክብደት ቀነሽ ማን ብሎኛል? ከከንፈሬ ባያልፍም በውስጤ ወፈረች- ተድበለበለች ስል ነው ደስ የሚለኝ፡፡ የጀመራት እርጉዝ ሆና ነበር፡፡ ከወለደች በኋላ ይቀንሳል ሲባል ጭራሽ ብሶ ከራስ ጸጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ ተድበለበለች፡፡ ያ ቅርጽ፣ ያ ውበት ድራሹ ጠፋ። በዚያ ፍጥነት ከምድረ ገጽ የጠፋ ውበት አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡ እንዳንዴ አእምሮዬ የሚያስባት ማኅደረ እና ሳገኛት የማያት ማኅደረ ስለሚለያዩብኝ መልመድ አቅቶኝ እቸገር ነበር፡፡ ባዬኋት ቁጥር በአየር የተወጠረ የፕላስቲክ አሻንጉሊት ነበር የምትመስለኝ፡፡እነዚያ አምባገነን ጡቶቿ ባንዴ ወረዱ፤ ደግሞ አተላለቃቼው! እሷ ለተሸከመቻቼው እኔ ይከብዱኛል። ከምንም በላይ የሚገርመኝ ውፍረቷ ፈገግታዋን ማበላሸቱ ነበር፡፡ ያንን በእናቴ የሚደነቅ የሚጠቀስ ፈገግታዋን። እናቴ ምን ጊዜም በእኔ አሳሳቅ እንደተበሳጨች ነው። “ሴት ልጅ እንጥሏ እስኪታይ አትስቅም። _ ማኅደረን አታያትም? ውይ የማኅደሬ ፈገግታ! የእቴጌ ፈገግታ የመሰለ'' ትላለች። ደግሞ የእቴጌ ፈገግታ ምን ይሆን? እያልኩ የምበሳጭበት፡፡ ከድሮ ጀምሮ ስትስቅ ከንፈሯን እንደከደነች ወደ ግራ ጠመም የምታደርገው ነገር ነበራት፣ በተለይ ነገር አልጥም ሲላት። የሚያምር ማሸሟጠጥ የሚመስል ፈገግታ፤ አሁን ግን እንደዚያ ስታደርግ የቀኝ ጉንጯ ከመወፈሩ የተነሳ ወደ ታች ወረድ

ስለሚል ፊቷ ላይ የሆነ መዛባት ያለባት ሴት ያስመስላት ነበር፤ ፈገግታዋ ሞተ። ለሞተ ፈገግተዋ በውስጤ ፈገግ አልኩ። ያ ፈገግታዬ የ “እቴጌ ፈገግታ' ሰይመስል አይቀርም። ፈገግታዋን መግደል የጀመርኩት ከውፍረቱም በፊት ነበር። የሰርጓ ቀን እናቴ አስተናጋጅ ነበረች። ሙሽራው ከመድረሱ በፊት ማኅደረ “ቬሎዋን' ለብላ ሚዜዎቹ የቀረውን ነገር እያዘገጃጄን ውር ውር ስንል እናቴ ድንገት ወደ ማኅደረ ክፍል ብቅ አለችና “የኔ እናት እቴጌ መሰልሽ'ኮ ቱ! ቱ! ቱ! ከዓይን ያውጣሽ” አለቻት። ማኅደረ ተፍነከነከች። ቃሉ ያበሳጨኛል “እቴጌ”። ሚዚዎቹ ዞር ሲሉ ጠብቄ “ማሂዬ የኔ ውድ በቃ አገባሽ፤ ሁልጊዜ እንደዚህ ደስተኛ ሁኝ፡፡ ያለፈውን እርሺው፤ ደግሞ ከትላንት ወዲያ ከፀጉር ቤት ጠፍተሸ ያደረግሽውን ትደግሚያትና እኔ ራሴ አለቅሽም ከምር!'' ብዬ በስሱ እጇን ቆንጠጥ አደረኳት። “ያላወቅን እንዳይመስልሽ” ብዬ ሳቅ ጨመርኩበት፤ ፈገግታዋ ድራሹ ጠፋ! “ያላወቅን እንዳይመስልሽ” ያልኩት ሆነ ብዬ ነበር። ልክስክስነትሽን ሁሉም አውቋል ተሳቀቂ ነበር መልእክቱ፤ እንዳሰብኩትም ተሳቅቃ ፊቷን ጥላው ዋለች በሰርጓ ቀን። እልልልልልል እያልኩ በጭፈራው መኻል አያታለሁ! ማን ለምን ዕልል እንደሚል ማ'ናባቱ ያውቃል?! ማኅደረ ለእኔ መጥፎ ነበረች? በጭራሸ! ሁለተኛ ድግሪ ለመማር ገንዘብ


💥💞#አልተዘዋወረችም💥💞
✍ አሌክስ አብርሃም

ክፍል  ሃያ


ማነሽ ባለ ሳምንት?

ያኔ ነው ስለ አብርሃም አጥብቄ ማሰብ የጀመርኩት።እንግዲህ በዚያ ሰሞን በፍቅረኛው ማኅደረ ተክዷል (መካድ ከተባለ) ከአሜሪካ በመጠ ሰው ተፈንግሏል፤ በዚያ ላይ የእኔም ፍቅረኛ፣ የሱም ጓደኛ የሆነ የጋራችን ሰው ደግሞ ሞቶብናል፣ የሚያቀራርብ የጋራ ጉዳይ አለን ብዬ፣አጉል ዓይነት ተስፋ በልቤ አደረ፡፡ እንደዚያ እንዳልጠላሁት፤ ከመሬት ተነስቼ ደወልኩና ወሬ ጀመርኩት፡፡ ለቶማስ ስላደረገው ነገር ሁሉ አመሰገንኩት፤ በጣም ቁም ነገረኛ መሆኑንም አጋንኜ አዳነቅሁ፤ በአካል አግኝቼው ለማመስገን ቡና እንድንጠጣ ጠዬቅሁት “እንዲያውም ላገኝሸ ሳስብ ነበር የደወልሽው” አለ። ምናልባት ስለ ማኅደረ አንዳንድ ወሬ ለመስማት ፈልጎ ይሆናል ብዬ አሰብኩ። እሱ ግን "ቶማስ የጻፈው የሆነ ነገር እጅሽ ላይ ይኖር ይሆን? ግጥም ወይም ልብወለድ? ለማስታወሻ ይሆን ዘንድ ከሌሎች ሥራዎች ጋር ላሳትምለት አስቤ ነበር" አለኝ። ስለ ባዶዎቹ ማስታወሻ ደብተሮች

ምንም ሳልል “ቦርሳውን ሰጥተውኛል፤ አቀብልሃለሁ- አንተው ታዬዋለህ'' አልኩትና ለመገናኜት ቀጠሮ ያዝን፡፡ ያቺን የማኅደረ ከንፈር...ቁራጭ ወረቀት ለብቻ አውጥቼ አስቀመጥኩና ቦርሳውን ልወስድለት አዘጋጄሁ።የዚያን ጥልማሞታም ቶማስ ጉዳይ ወደዚያ ጨርሶ፣ የዚያኑ ቀን እየጎተተ እቤቱ ቢወስደኝ እና ልተኛሽ ቢለኝ እምቢ አልልም ነበር። ደግሞ ተጎትቶ ለመተኛት! እንዲያውም እውነተኛው ማጽናናት በሆነልኝ ነበር(ባላዝንም)። የቀጠሯችን ቀን ጸጉሬን ተሰርቼ፣ አዲስ ቀሚስ ገዝቼ እና የመጨረሻ ራሴን አሳምሬ (እኔን ማሳመር _ቢከብድም) ቀጠሯችን ቦታ ቀድሜ ደርሼ ስጠብቀው ምን ተፈጠረ? ከርዝመቷ -ቅላቷ፣ ከቅላቷ- የሰውነቷ ቅርጽ፣ ልብ ከሚያስደነግጥ ሴት ጋር ሰበር ሰካ እያለ መጣ። ማነሽ ባለ ሳምንት? አልኩ። ከዚህ በፊት የሆነ ቦታ ባያትም የት እንዳዬኋት ጠፋብኝ። የልጅቱ የተጋነነ ቁንጅና የሆነ የሚረብሽ ነገር ነበረው፡፡ ከገባች ጀምሮ ሬስቶራንቱ ውስጥ የነበሩ ወንዶች ሰበብ እየፈለጉ ሊያይዋት ሲጣጣሩ እታዘባለሁ፡፡ አንዱ የሆነ ነገር የወደቀበት መስሎ ዞር ይልና ከኋላዋ አዬት፤ ሌላው 'ባዝ ሩም' ደርሶ ሲመለስ ፊቷን በቁሙ ሸምድዶጽ ያልፋል፤ 'በዝ ሩም' የሚመላለሰው ወንድ ምነው በረከተ እላለሁ? (የተቀመጥነው ወደ በዝ ሩም መሄጃው ጋር ነበር) ከሕፃንነቴ ጀምሮ አልታይም እንጂ፤ እንደ ስውር ካሜራ አካባቢዬ ላይ የምትፈጠር ነገር ከዓይኖቼ አታመልጥም፡፡ ያኔም ምን እየሆነ እንዳለ ገብቶኛል፡፡ ወንዶች ከምንድን ነው የተሠሩት?! ድምፃቼው የጎላ የወንድ ሳቆች ከኋላችን ... ትኩረት ለመሳብ መሆኑ ነው። አለባበሷ አስገራሚ ነበር፡፡ከግራ ወደ ቀኝ ተላላፊ ጋውን የመሰለ አጭር፣ ጥቁር ቀሚስ፣ ወገቡ ላይ በባለ አበባ የፈረንጅ መቀነት ሸብ የተደረገ፤ ቀበቶውን ጫፉን ይዛ ብትስበው፣ ቀሚሷ ግራናቀኝ ተከፍቶ ራቁቷን የምትቀር ነበር የምትመስለው፡፡ ማን ነው ወንድ ያንን ሸብ የተደረገ ቀበቶ ሳብ አድርጎ ለመፍታት የማይመኝ!? እፍ አውጥቶ የሚጣራ ቀሚስ! ተቀምጣ እግሯን ስታነባብር ቀሚሷ እስከታፋዋ በከፊል ከፈት አለ፤ በጥቁር ቀሚስ እንደዚያ ዓይነት ዓይን ላይ የሚያበራ ጭን። በዚያ ቁመት ላይ፣ ከቁም ሣጥን የላይኛው ክፍል ዕቃ ሳወርድ የምቆምበትን ዱካ

የሚያክል ተረከዝ ረጅም ጫማ ተጫምታለች፡፡ ሰው ቁመት በቃኝ አይልም ይሆን? የካቶቿ ጥፍሮች ጥፍር ቀለም አልተቀቡም።ግን ንጹህ ሆነው የሚያንጸባርቁ ነበሩ? እንደ ብዙዎቹ አብርሃም ጋር እንደማያቼው ሴቶች ክንዱን ይዛ አትተሻሽም፡፡ አብረው ሲራመዱም፣ ሲቀመጡም ራሷን የቻለች ዘናጭ። አረማመዷ ትሁት የሆነ እምባገነን ነበር፤ ምናልባት ሌሎች ግርማሞገስ ያለው የሚሉት ሳይሆን አይቀርም፤ ቀና ብላ ብቻዋን መኝታ ቤቷ ያለች ማንም የማያያት ዓይነት፣ ጡቶቿ እረጋ ብለው ግራና ቀኝ ይንቀሳቀሳሉ፣ ቁመቷ ጋር _ ስለሚመጣጠኑ አይጋነኑ እንጂ ጡቶቿ ትልልቆች ነበሩ። እንደ ብዙ ቀይ ሴቶች በቅላት የተድበሰበሰ ቁንጅና ሳይሆን ልቅም ያለ ውብ ፊት ያላት ሴት ነበረች። አፍንጫዋ አንድ አገር ዓይኗ ሌላ አገር ቢገኝ ለየብቻው ቆንጆ እየተባለ የሚደነቅ። ይሀች ቆንጆ እንደ ብራ መብረቅ ፊቴ ስትወድቅ፣ ኩሌ ከቅንድቤ ላይ ልትረግፍ ምንም አልቀራትም። ለቅሶ እንድረስ ብሎ ነውና ያመጣት፣ ብዙ ባትስቅም ስንተዋወቅ ፈገግ ባለችበት ቅጽበት የጥርሶቿን ውበት ዓይቻለሁ። የሆነ ሴት አውል ወንድ ከሄዳቼው ሴቶች ሁሉ ቆንጆ ቆንጆ ነገራቼውን ወስዶ እቤቱ የሠራት ነበር የምትመስለው፡፡ እኔ ጋር ቢተኛ ኖሮ ከእኔ ምኔን ወስዶ ይሰጣት ነበር? እላለሁ። “አዚዛ” አለችኝ፣ ከፍ ባለ ትህትና፡፡ “ሃይማኖት” አልኩና፣ ሳልወድ በግዴ ባሏ የሞተባት ምስኪን መስዬ ለቅሶ እንዲደርሱኝ ተመቻቼሁ። አቤት የልባችንና አፋችን መራራቅ፣ አውርተን ሳቀረቅር ረዣዣምና ውብ ጣቶቿ እጄ ላይ አረፉ፡፡ ደንግጨ እጄን ላሸሽ ነበር- ማጽናናቷ ነው፣ጠንካራና የሚቀዘቅዝ መዳፍ፡፡ ውስጤ የነበረው ብቼኛ ፍላጎት፣ ቶሎ ተለያይተን ቤቴ ሄጄ ማልቀስ ነበር፡፡ እንኳን የያዙት፣ ገና የተመኙት ተስፋ ሲሞት አያስለቅስም!? እሱ ግን ምን ዓይነት ሴት አውል ነው!? ልክስክስ!! ማን ነበር ስሟን ያለችኝ ... አዚዛ! ልክ እንደ ማስቲካ ልጥጥ ብሎ ነፍስ ጋር የሚጣበቅ ስም አዚዛ!!!

ወደ ቤቴ ስመለስ ሳላስበው እንደ አዚዛ ተራመጅ ተራመጅ የሚለኝ መንፈስ ነበር: ቀና ብዬ ማንንም ሳልደገፍ፣ ማንንም ሳልፈራ፣ አጉል ጨዋ ጨዋ ሳልጫዎት፣ ቀና ማለት አማረኝ - ቀና ማለት፡፡ ማን ነው ቀና ማለትን ለቆንጆ ብቻ የሰጠው?, እንዲህ እያሰብኩ ቀና ከማለቴ ዓይኖቸ በዕንባ ተሞልተው መንገዴ ብዥ አለብኝ፤ መልሼ አቀረቀርኩ። ዕምባዬ እንደ ድንገተኛ ምጥ መንገድ ላይ ይታገለኛል? ርምጃዬን አፈጥናለሁ! በዬት በኩል ቀና ይባላል?!

የሴቶች እኩልነት ሲባል...

በየቴሌቪዥን እና ሬዲዮው የሴቶች እኩልነት ሲሉ እኔ የሚታዬኝ ብቸኛ ነገር፣ በእኔና በማኅደረ መካከል የነበረው የእኩልነት ትግል ነበር። ይኼ ውድድር መኖሩን ማኅደረን ጨምሮ ማንም አያውቅም፤ አሸነፍኩም ተሸነፍኩም የውስጤ ድልና የውስጤ ውድቀት ነበር። ተወዳዳሪ እኔ፣ ተመልካች እኔ፣ ዳኛም እኔ የሆንኩበት የዕድሜ ልክ ውድድር ውስጥ ነበር የምኖረው። ዕድሜ ልኬን የተወዳደርኩት ማኅደረ ጋር እኩል ለመሆን፣ ከቻልኩም ለመብለጥ ነበር፤ የተዳላላት ልጅ ናት፡፡ ተፈጥሮ አዳልቶላታል፤ ማኅበሰቡ አዳልቶላታል፤ ወንዶች አዳልተውላታል፣ አጠገቧ ቆሜ ተረስቻለሁ፡፡ የመጡት ሁሉ ከፊቷ የተዘረጋሁ እኔን እንደ ምርቃት 'ሪቫን' በቸልተኝነት መቀስ ቆርጠው እሷን ሲያከብሩና ሲያሞግሱ ነው የኖሩት፡፡ ማኅደረ ውድድር መኖሩን እንኳን ሳታውቅ ስታሼንፈኝ ነው የኖረችው። የራሴ እናት ሳትቀር “እንደ ማኅደረ ጎብዥ፣ እንደ ማኅደረ ቁጥብ ሁኚ፣ እንደ ማኅደረ ንጹህ ሁኚ!" ስትለኝ ነው የኖርኩት፡፡ ታዲያ በእኔ ጉብዝና ሳይሆን በሁኔታዎች ማኅደረን ያሸነፍኩባቼዉ አጋጣሚዎች ነበሩ። ድሎቼን ደጋግሜ በመቁጠር የማገኜውን እርካታ ከሌላ ከምንም ነገር አላገኜውም።

ድል አንድ!


እባክሽ አትሂጂ…..
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-19


///
አካባቢው ደረስኩ… የውጩ በራፍ ወለል ብሎ ተከፍቶ ታየኛል… ብዛት ያላቸው ሰዎች በመቻኮል እየገቡ ይወጣሉ …መሪ የያዘው እጄ ያልበኝ ጀመረ…‹‹ምንድነበር ጥዋት ያለችኝ ?ድኗል ብላኝ አልነበረ እንዴ…?መድሀኒቱ መጀመሪያ አድኖ ከዛ እንደሚገድል አላውቅም ነበር፡፡እንደምንም ተጠጋሁና መኪናዬን ወደውስጥ ማስገባት ስላልቻልኩ የግቢውን አጥር በማስጠጋት አቁሜ  ተንደርድሬ ወደውስጥ ገባሁ፡፡ ግቢው በሰው ትርምስ በግርገርርና በጩኸት ተሞልቷል፡፡ፊት ለፊቴ የተጋረጠብኝን ሰው ሁሉ ያለይሉኝታ እየገፈታተርኩ ወደውስጥ ተጠጋሁ…አዎ  ልእልትን አየኋት፡፡በሰዎች ተከባ  እንደእብድ ትጮሀለች..ፀጉሯን ትነጫለች…ደረቷን ትደቃለች…አረ ታጓራለች ማለቱ ይቀላል፡፡፡ፀጉሯ ጭብርር ብሎ ተተረማምሶል..አይኖቾ በለቅሶ ብዛት  ደፈራርሶል …በአጠቃላይ አቅሏን ስታለች ማለት ይቻላል፡፡እንደምንም በሚንቀጠቀጡ እግሮቼ እየተሳብኩ ስሮ ደርስኩና ፊቷ የተጋረጡ ሰዎችን ወዲህና ወዲያ ገለል አድርጌ‹‹ልዕልት ምን ተፈጠረ…?መስፍኔ ምን ሆነ?››
‹‹ዶ/ር  መስፍኔ እኮ ጥሎኝ ሄደ፡፡››
እንዲህ እንደሚሆን ከበፊት የማውቅና ራሴ ያደረኩት ቢሆንም አሁን ቁርጡ ሲመጣ ግን ሰውነቴ በፍራቻ ራደ….የምላት ጠፋኝና ‹‹ስንት ሰዓት ላይ አረፈ?››ስል ጠየቅኳት፡፡
ዙሪያዋ ያሉት ሰዎች ሁሉ ገለማመጡኝ…እኔ ግራ ተጋባሁ…እሷ እኔ ምላትን የሰማች አይመስለኝም፡፡
እንደድንገት እይታዬን ወዲህ ወዲያ ሳሽከረክር ወንድሟ አቤል በእጁ አንድ ብጣሽ ወረቀት እያውለበለበ  ከወደሳሎን እየወጣ ወደእኛ ሲመጣ ተመለከትኩት…. ተንደርድሬ ሄድኩና ፊቱ ተጋረጥኩ፡፡ሲያየኝ….
‹‹ዶ/ር ጉዳችንን ሰማህ አይደል?››አለኝ፡፡
‹‹አዎ  ሰማሁ… በጣም ያሳዝናል…እንግዲህ ተፅናንቶ እሷን ማፅናናት እንጂ ምን ማድረግ ይቻላል፡፡››
‹‹እሷን እንዴት ማፅናናት እንደምንችል ግራ ገባን እንጂ እኛማ ተገላገልነው….ከድሮም ነቀርሳ ነገር ነበር….››
በንግግሩ ሽምቅቅ አልኩ….እስቲ እኔ መርዝ ግቼ የገደልኩት እያለሁ እሱ ሰደበው ብዬ መሸማቀቄ…..ድሮም የሰው ልጆች ስንባል ተራራ የሚያህል የአይናችንን ጉድፍ ተሸክመን ስለሌላው ቅንጣት ቆሻሻ የማብሰልሰል ክፉ አመል አለብን፡፡
‹‹ግን ጥዋት ደውላልኝ… ድኗል ብላኝ ነበር እኮ››
‹‹እኮ ስለዳነማ ነው እንዲህ የእህቴን ልብ የሰባበረው..ተመልከተው እስቲ እንኳን ሰው ሰይጣን አንዲህ አይነት ስራ ይሰራል?››ብሎ በእጁ የያዘውን ወረቀት አቀበለኝ፡፡በፍጹም ግራ በመጋት ወረቀቱን ወደአይኖቼ አስጠግቼ ማንበብ ጀመርኩ፡፡
ልእልት የእኔ ቆንጆ እንደምወድሽ ታውቂለሽ…በአንቺ ላይ እንዲህ ማድረግ አልፈልግም ነበር..ግን ደግሞ መኖር ፈልጋለሁ…እግዜያብሄር በአንቺ እና በዛ ዶ/ር ጥረት ከአልጋ ቁራኛ ምሮ ካዳነኝ ሁለተኛ የመኖር እድል ሰጥቶኛል ማለት ነው፡፡ያንን ደግሞ ማባከን አልፈልግም..፡፡እዚህ ቤት ተጨማሪ አንድ ቀን ካደርኩ ግን ይሄንን ምኞቴን ማሳካት አልችልም.፡፡ወላጆችሽና ወንድሞችሽ መልሰው ይመርዙኛል.፡፡እንደውም አሁን ወዲያው ፅጥ የሚያደርግ መድሀኒት ነው የሚሰጡኝ፡፡እስከዛሬም አመት ሙሉ እኔም እንድሰቃይ ብቻ ሳይሆን አንቺም እኔን በማስታመም ፍዳሽን እንዳታይ የፈረዱብሽ እንሱ ናቸው…ምን እንዳደረኳቸው ባላውቅም አንቺን ካገባው ከመጀመሪዋ ቀን አንሰቶ በጣም ነው አምርረው የሚጠሉኝ፡፡ለዛ ነበር መርዝ ግተው ለአልጋ ቁራኛ የዳረጉኝ፡፡እርግጥ ለዚህ ማስረጃ የለኝም…ግን ደግሞ ስሜቴ ሚነግረኝ ያንንን ነው፡፡እና ውዴ ከአሁን ወዲህ እኔም ህይወቴን አደጋ ላይ መጠል አልፈልግም አንቺንም ማሰቃየት በቃኝ፡፡፡ልጆቼን አደራ ፡፡ልትፈልጊኝ እንዳትሞክሪ…ፈፅሞ ልታገኚኝ አትቺም..ብታገኚኝም በምንም አይነት መንገድ ወደህይወትሽ ልትመልሺኝ  አትችይም፡፡እስከዛሬ ስላደረግሽልን ነገሮች ሁሉ አመሰግናለው፡፡ቸው፡፡
ይላል፡፡አንብቤ ስጨርስ አዞረኝ ፡፡እንደምን ተንገዳገድኩና በረንዳው ላይ ቁጭ አልኩ፡፡ይሄ ምን አይነት ጭካኔ ነው፡፡ምን አይነት ንክ እና ፈሪ ሰው ቢሆን ነው ይህቺን የመሰለች መላአክ ሴት እንዲህ አውላላ ሜዳ ላይ ጥሎ የሚሄደው?፡፡ደግሞ እኔ ነኝ ቀሽሙ ገና ባልተረጋገጠ መድሀኒት ልገድለው ሞክሬ እንዲህ ከማድነው ምነው ቀጥታ በተኛበት በሰል መጥረቤያ አንገቱን ቀንጥሼ ገድዬው በሆነ ….?ከተቀመጥኩበት ተነሳሁና ወደወንድሟ ሄጄ ወረቀቱን መለስኩለት… ቀጥታ ግቢውን ለቅቄ ወጣሁ..መኪናም እንደነበረኝ ዘንግቼ ቀጥታ የአስፓልቱን ጠርዝ ይዤ በትካዜ መራመድ ቀጠልኩ፡፡


ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


እባክሽ አትሂጂ…..
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-18


‹‹ዶ/ር አንተ ሠፈር ነው ያለሁት።ትንሳኤ ሆቴል አጠገብ ቆሜላሁ።››
ደነገጥኩ። ሁኔታዬን እየተከታተለች የነበረችው እርግበ ላይ አፈጠትኩ፡፡

በባሏ መሞት እጄ እንዳለበት ጠርጥራ  ይሆን ?ወህኒ ልታስወረውረኝ ፓሊስ አሰልፋ መጣች እንዴ? ብዙ ክፉ ሀሳቦችን  በአእምሮዬ መራወጥ ጀመሩ።
‹‹እውነትሽን ነው?እኔ ሰፈር?ለምን ችግር አለ?››ስል ጠየቅኳት፡፡
‹‹ልጠይቅህ ነዋ...ትናንት ስላልተመቸኝ እኮ ነው ያልመጣሁት..ሆስፒታል ደውዬ እንዳልገባህ ነገሩኝ….ቢብስብህ ነው ብዬ አጠያይቄ ሰፈርህ መጣሁ…፡፡

‹‹..ለማንኛውም መጣሁ ያለሽበት ጠብቂኝ›› ብዬ ስልኩን ዘጋሁትና ቶሎ ከአልጋው ወርጄ  ቢጃማዬን በማውለቅ ልብሴን በፍጥነት መለባበስ ጀመርኩ፡፡
‹‹እሷ ነች?››እርግበ ጠየቀችኝ፡፡
‹‹አዎ..ስላመመኝ ልትጠይቀኝ መጥታ ነው››ላብራራላት ሞከርኩ፡፡
‹‹ገባኝ..በቃ እኔም ልሄድ …ቸው››ብላ ቦርሳዋን አንጠለጠለችና ወደእኔ ተጠግታ በተኮሳተረ ፊት ጉንጬን ስማ ቤቱን ለቃ ወጣች፡፡ውስጤ ድፍርስርስ አለ…የልጆች እናት አፍቅሬ እየዳከርኩ ባለሁበት ሰዓት ሌላ ሴት የልጅ እናት ማድረጌ እቆቅልሽ ነው የሆነብኝ፡፡ለማንኛውም ሀሳቤን እንደምንም ገትቼ እሷን ላለማስቆም  ተንደርድሬ ከቤት ወጣሁ፡፡ከቤቴ የ3 ደቂቃ ርቀት ላይ ነው ያለችው።ነጭ በረዶ መሳይ ያሸበረቀ የሀገር ልብስ ለብሳለች።ልብሷ ብቻ ሳይሆን ፈገግታዋም ነጭ ነው።ምን እየተፈጠረ ነው የሀዘን መግለጫ ልብሳችን ከጨለማ ጥቁርነት ወደ አንፀባራቂ ነጭነት ተቀየረ እንዴ?።ስሯ ስደርስ ተንደርድራ ተጠመጠመችብኝና ጉንጮቼን እያገላበጠች ሳመቻቸው።እንደሌላ ቀን ቢሆን ከንፈሮቾ አካላቶቼ ላይ ሲያርፍ መጋሌና መቅለጤ የሚጠበቅ ነበር፤ አሁን ግን ምንም እየተሰማኝ አይደለም፤ደንዝዣለሁ።በፌርሙዝ አጥሚት ፤ብርትካን ፤ሙዝ …በሰሀን የተጠቀጠቀ ምግብ ፤ኩኪሶች ብቻ ምን አለፋችሁ አንድ ሙለ ዘንቢል ጓዝ ይዛ ነው የመጣችው፡፡እቤት እንደገባን ነው ምን እንዳስፈነደቃት የነገረችኝ፡፡ለካ መስፍኔን ይዛ ወደውጭ ለመሄድ የጀመረችው ጠቅላላ ፕሮሰስ ስላጠናቀቀች ነበር ያ ሁሉ ፈንጠዝያ፡፡አሳዘነችኝ…ነገ ወይ ተነገ ወዲያ ይሄንን ነጭ ልብስ በደማቅ ጥቁር ልብስ ቀይራ ፀጉሯን እየነጨች ስትነፈርቅ በምናቤ አየሁና አቅፌና ደረቴ ላይ ለጥፌ ከአሁኑ ማፅናናቱን ልጀመር አማራኝ፡፡ከሶስት ሰዓት በላይ ስትጫወትና ስትስቅ ቆይታ.ሄደች፡፡እኔ እዛው ከአልጋዬ ላይ አልተነሳሁም፡፡
///
በማግስቱ ማለዳ አንድ ሰዓትም ሳይሞላ ስልኬ ጮኸ፡፡የልዕልት ነው፡፡አሁን እርግጠኛ ነኝ፡፡በቃ ሞቷል..፡፡በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ለእሷ ስል ሰው ገድያለሁ፡፡በሚንቀጠቀጥ እጄ አነሳሁት፡፡ ሳነሳው ለቅሶና ጩሀት ነበር የጠበቅኩት ..ግን ጥርትና ኩልል ባለ ድምፅ‹‹ሄሎ ዶክተር እንዴት ነህ? በጎ አደርክ..በለሊት ደወልኩልህ አይደል?
‹‹አይ ሰላም ነኝ..ተሸሎኛል..አንቺ ሰላም ነሽ…?››
‹‹ሰላም ነኝ ይመስገነው፡፡››
እየጨነቀኝ አምጬ ‹‹መስፍኔስ…ደህና ነው?››ስል ጠየቅኳት፡፡
‹‹አዎ ዶክተር የሚገርም ነገር ተከስቶል….››
‹‹ምነው አመመው…?መተንፈስ እየተቸገረ ነው…?.አይኖቹ ቢጫ ሆኑ….?››የሰጠሁት መድሀኒት ሰውነቱን መርዞት ሊገድለው ሲል ሚያሳዩትን ምልክት እየዘረዘርኩ መጠየቄን ቀጠልኩ…
‹‹አረ እሱ እቴ ተአምራዊ የምስራች ልነግርህ ነው የደወልኩት..በጣም ድኖ ነው ያደረው፡፡ ለሊት 12 ሰዓት ድንገት ብድግ ብሎ  አልጋውን ለቆ ተነስቶ ቁጭ ብሏል… ግን ምንም አይናገርም …ማለት የሆነ አንደበቱን የቆለፈው ነገር አለ…..››
‹‹ምን እያልሺኝ ነው…?እንዴት ሊድን ቻለ..?እንዴት እንደዛ ይሆናል?››በብስጭት ጠየቅኳት፡፡
‹‹ዶ/ር እኔም እኮ እንደተአምር ነው የሆነብኝ..ብታይ ከደስታ የተነሳ ክንፍ አብቅዬ እየበረርኩልህ ነው..እንደው የማላስቸግርህ ከሆነ መጥተህ  ለምን መናገር እንዳልቻለ ብታየው..የሆነ ነገር ጉሮሮው ላይ ተሰንቅሮ ሊሆን ይችላል…፡፡››
‹‹እሺ ጥሩ እመጣለሁ…እንኳን ደስ አለሽ…ያው ስለዳነ ውጭ መሄዱም አያስፈልግም ማለት ነው፡፡››
አይ እሱን እንኳን አንቀርም…ሁሉ ነገር ያለቀለት ስለሆነ ይዤው ሄዳለው…ፍፅም ጤነኛ መሆኑን መረጋገጥ እፈልጋለሁ..በዛውም ለአመት አልጋ ላይ ስለከረመ እንደመዝናኛ ይሆነናል..እንደጫጉላ ሽርሽር በለው….ከሁሉ ነገር ራቅ ብለን የራሳችን የሆነ ጌዜ እናሳልፍለን፡፡››
ቅዝዝና ድክም ባለ ድምፅ ‹‹አይ ጥሩ አስበሻል..በቀ መጥቼ አየዋለው››
‹‹እሺ እጠብቅሀለው፡፡››ስልኩ ተዘጋ፡፡የማደርገው ጠፋኝ….ህልም ውስጥ ያለውም መሰለኝ፡፡
በትካዜና በሀዘን  ስተሻሽ ውዬ አስር ሰዓት አካባቤ በተሰላቸ ወኔ እና በተዳከመ ፍላጎት  ወደ ልእልት ቤት  ሄድኩ፡፡ግን ሳላስበው ምን አይነት የተወሳሰበ የህይወት ውጥንቅጥ ውስጥ ነው የገባሁት…?ምኞቴና የዘመናት ጥረቴ ያልተወሳሰበና ያልተጨመላለቀ ሲምፕል ኑሮ መኖር ነበር፡፡ፈላስፎቹ ቀላል ህይወት ኑር እያሉ ይመክራሉ፡፡በእኔ ልምድ ግን …ቀላል ህይወት ኑር መኖር ማለት….ቀላሉን መንገድ መምረጥ አይደለም፡፡ቀላል ህይወት  መኖር   ጥቂቶች ብቻ ሊያሳኩት የሚችሉት እጅግ አሰቸጋሪ ልምምድ እና ውሳኔ የሚጠይቅ አስተሳሰብን በማረቅና ስሜትን በመግራት ላይ የተመሰረተ  የህይወት ዘይቤ ነው፡፡እና አሁን ሳስበው ቀላል ህይወት ለመኖር ብቃቱም እውቀቱም ሆና ቀርጠኝነቱ እንደሌለኝ ነው፡፡
አካባቢው ደረስኩ… የውጩ በራፍ ወለል ብሎ ተከፍቶ ታየኛል…

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ከማኅደረ ይልቅ እኔ ጋር ነበር የበለጠ ይቀራረብ የነበረው፤ እንዲያውም ስደት ቀደመን እንጂ የቀለጠ ፍቅር ውስጥ እንገባ ነበር ብዬ ፋይሉን የዘጋሁት ሰው ነ እንደዚያ ያሰብኩት ከመሬት ተነስቼ አልነበረም። ጊዜው ስለራቀ በብዥታ ቢታጠርም ዮናስ ከኮሌጅ ከመጥፋቱ አንድ ቀን በፊት የተፈጠረውን ነገር እልረሳዉም። ላይብረሪ አምሸቼ እየወጣሁ ነበር፤ የዚያን ቀን ማኅደረ የለችም ብቻዬን ነበርኩ። በዚያው የሆነ ነገር ኮፒ ላድርግ ብዬ እዚያ አካባቢ ወደነበረች ፎቶ ኮፒ ቤት ስሄድ ዮናስ ጋር ተገናኜን፤ ሁልጊዜ እዚያች ቤት አይጠፋም ነበር። ኮፒ _የማደርገውን _ አድርጌ _ ስወጣ እጁን ኪስና ኪሱ እንዳስገባ ቆሞ ነበር “አትሸኜኝም?'' አልኩት፤ አብሮኝ ወጣና ትንሽ ሄደን መንገዱ ዳር ቆምን። የባጥ የቆጡን አውርተን እንደልማዳችን ጉንጭ ለጉንጭ ተነካክተን ልንሰነባበት ስንጠጋጋ ድንገት ከንፈሬን በስሱ ሳመኝ(ከንፈራችን ተነካካ?) ሲስመኝ ትንፋሹ ጠላ ጠላ ይሸት ነበር። እስካሁን ጠላ ሲሸተኝ መሳሳም አብሮ ትዝ ይለኛል፡፡ ሰዎች ጠላ ሊጠጡ፣ ከንፈራቼውን ሲያሞጠሙጡ ጠላውን የሚስሙት ነው የሚመስለኝ። የአሳሳሙ ፍጥነት እንደሳመኝ እንኳን እስክጠራጠር ግራ አጋብቶኝ ነበር፡፡ አልተቆጣሁም፤ አጋጣሚ ይሁን ፈልጎ ስላልገባኝ ከደገመው ብዬ ዝም ብዬ ቆምኩ፤ ምንም እንዳልተፈጠረ “ቻው በቃ” ብሎኝ ወደ ፎቶኮፒው ቤት ተመለሰ። ግራ ተጋብቼ ከቆምኩበት ሳልንቀሳቀስ ዝም ብዬ ከኋላው አዬሁት። አንዴ እንኳን ሳይዞር እየተጣደፈ ወደ ፎቶ ኮፒ ቤቱ ገባ። በቀጣዮቹ ቀናት የሆነ ነገር በመካከላችን እንደሚፈጠር፤ ተስፋ አድርጌ ነበር። የተፈጠረው ነገር ግን ፈጽሞ ያልጠበኩት ነገር ሆነ፤ ጠፋ ተባለ፡፡ በቃ ወደዚያ ግቢ → ዝር ሳይል ዐሥራ አምስት ቀን አለፈው። በኋላ ወደ ሱዳን ተሰደደ የሚል ወሬ ▣ ተናፈሰ። ስሞኝ ጠፋ! ዐሥራ ምናምን ዓመት የምትታወስ የማይክሮ ሰከንድ -- መሳም። ታዲያ እጠራጠራለሁ እንደለመደው ጉንጨን ሊስመኝ የላከው ከንፈሩ ሳላስበው ዞሬ ከንፈሬን ነክቶበት ይሆን? ወይስ ጠላው የእኔን ከንፈር የማኅደረ አድርጎ አሳይቶት? እንደዚያ መሆን አለበት፤ ሰዎች ጠላ ሲጠጡ ገፈቱን ትፍ ትፍ

እንደሚሉት ዮናስ ያኔ እንደ ጠላ ለቅምሻ ፉት ብሎኝ ከዐሥራ አምስት ዓመት በኋላ ማኅደረን ውጦ እኔን እንደ ገፈት ትፍ ያለኝ መሰለኝ። ስሙን አልጠራ ነገር ችግር ነው፤ ዝም እንዳልል አፌን ይበላኛል፤ አንዳንዴ ታዲያ እንደቀልድ ከመሬት ተነስቼ አበበ ጠላ ጠጣ! ብዬ እጮኻለሁ፤ ሥራ ቦታዬ እንደዚያ ስል የሰሙኝ ባልደረቦቼ ለምዶባቼው እንደ ተረት ይደግሙታል፡፡ የሆነ ሆኖ ሦስት ወንዶች ሳሙኝ፣ ሦስቱም ማኅደረን ይወዷት ነበር፡፡ ሁለቱ አገር ጥለው ጠፉ፥ አንዱ ሞተ። ቀጣዩን እግዜር ይሁነው፤ ቀጣይ ካለ። የመልኩ ሲገርመኝ አሁንማ ዕድሜውም ሄደ! ከንቱ ዓለም!!

ዝም!

ባወጣ ባወርድ ባልገባኝ ምክንያት ማኅደረ ዮናስን ላገባ ነው አለችኝ፡፡ ያውም ሞትኩለት፣ ከነፍኩለት የምትለው ፍቅረኛዋ አብርሃም ጋር አብረው ሆነው ሳይለያዩ፤ ጥያቄዬን ላዥጎደጉድ ስዘጋጅ አፌን በእጇ አፈነችኝና ስለነገሩ ምንም ነገር እንዳልናገር በቁጣ አስጠነቀቀችኝ (ማግባቱን የራሷ ጉዳይ፣ ቁጣውን ምን አመጣው?) ሰው የት ላይ እንደሚቀየር አይታወቅም፤ ቅይርይር ብላ ነበር። ዝም አልኩ።ነገሩ ተጣድፎ ድል ባለ ሰርግ ተጋቡ። ምናገባኝ ብዬ እንደጠየቀችኝ ሚዜ ሆንኩ፤ በአንዴ እልል ብዬ አጋባሁ- እልል ብዬ አለያዬሁ፡፡ ሁልጊዜ ያንን ጋብቻ ሳስብ ግን ቀድሞ ወደ አእምሮዬ የሚመጣው አንድ አስገራሚ ነገር ነበር፣ ከጋብቻው ሁለት ቀን በፊት ማኅደረ፣ እኔና ሌሎችም ሚዜዎች ሆነን ቄራ አካባቢ የሚገኝ ጸጉር ቤት ጸጉራችንን እየተሠራን ነበር። በመኻል ማኅደረ ጠፋችብን፣ ድንገት ነው ተነስታ የጠፋችው። በጣም ነበር ግራ የተጋባነው፡፡ ስንት ሰዓት ሙሉ ቆይታ መጣችና “እስክትጨርሱ ቤተክርስቲያን ስዕለት ላስገባ ሄጄ እኮ ነው. . .'' አለችን! “እና አስገባሽ?!'' አልኳት ሽሙጡ ገብቷት ፊቷን አዙራ ዕቃዋን መሰባሰብ ጀመረች። እንዲህ ያለም ስዕለት የለ! ቤተክርስቲያን የሄደ ሰው በነፍስም በሥጋም

ተረጋግቶ እንጂ እንደዚያ ተወዛግቦና ላብ ላብ እየሸተተ አይመጣም፡፡ በዚያ ላይ ገና ቅድም የተሠራ ጸጉሯ ከማሠሪያው አፈትልኮ ወጥቶ ዓይኔን እንኳን በሙሉ ዓይኗ ለማዬት አፍራ ስትደናበር ነበር። አብርሃም ጋ ሄዳ የምታደርገውን አድርጋ እንደመጣች በደንብ ገብቶኛል፡፡ እንዴት አወቅሁ? ዮናስ ደውሎ ስልኳን አታነሳም ፈልጊያት ነበር አለኝ። አሁን ማናገር አትችልም ቆይተህ ደውል ብዬ ያንን ድርጊቷን ተበበርኩ። የማኅደረ ሕይወት እንደ ቀጥታ መስመር ሁለት መዳረሻ ነጥቦች ብቻ ነበሩት አንዷ እኔ፣ ሌላኛው አብርሃም፡፡ የእውነት ግን ደስ አላለኝም፡፡ ቅናትም ወግ አጥባቂነትም አልነበረም፤ በቃ የሆነ ቅፍፍ ነበር ያለኝ፤ እንደ ሰው መሳሳት ሳይሆን፣ እንደ እንስሳ ኅሊና ቢስ መሆን ነበር፡፡ ብቀናባትም እኔ ውስጥ የሌለ ጨዋነቷን እወደው ነበር፤ ፈራረሰብኝ። ያኔ ልክ እንደ ስልሳ ዓመት አሮጊት “ምን ዓይነት ዘመን ላይ ደረስን?" ብዬ ዝም አልኩ። ዝም!!

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


💥💞#አልተዘዋወረችም💥💞
✍ አሌክስ አብርሃም

ክፍል  አስራ ዘጠኝ


ከአሟሟቱ የቀብሩ...!


ፍቅረኛዬ ቶማስ ሞተ፡፡ እንዲህ በቅርብ የማውቀው ሰው ሲሞት የመጀመሪያዬ ስለነበር፣ ስለሞት አብዝቼ አሰብኩ። ስለ ቶማስም _ ሳምንቱን ሙሉ ማሰብ አላቆምኩም፡፡ ምናልባት በቁሙ ያላስተዋልኩት አንዳች በጎ ነገር ይኖረው እንደሆነ ብዬ፣ ከሞተ በኋላ ብዙ አሰብኩ፡፡ ስለ ሞተ ብዬ አንገቱ ረዢም ነው አልልም። ፍቅረኛዬ ስለነበርም ብዙዎች የሚያውቁን እንደሚያስቡት፣ የማይሆን የማይሆን ዓይነት ማለቃቀስ ውስጥ አልገባም። እውነታው ለሰው ባላወራም ቶማስ ቀናተኛ፣ ምቀኛ፣ የሰው ስኬት የማያስደስተው፣ ነገረ ሥራው ሁሉ አስፈሪ ነገር ነበር፡፡ የመጽሐፍት ምረቃ ላይ ታላላቅ ሰዎች(እሱ ባለስም ደላሎች የሚላቸው) ስለ ጸሐፊው በጎ በጎውን ሲናገሩ፣ ዓይኑ በንዴት ቀልቶ ፂሙን (አስቀያሚ ፂሙን) እየለቃቀመ ይነቅላል። ፂሙን በመንቀል ነበር የሚያስተካክለው። እሱ ለነቀለው እኔ ያመኝ ነበር፡፡ እንዳንዴ በሚነቅለው ቦታ ትንንሽ የደም ነቁጦች ብቅ ይሉ ነበር፡፡

“አያምህም?'” ስለው፣ “ያማል!ግን ስቃዩ ደስ ይለኛል” ይላል፣ ፍልስፍና መሆኑ ነው፡፡ ነብይ ነኝ ለማለት ሳይሆን፣ ፈጠነም ዘገዬ እንደሚሞት ቀልቤ ነግሮኝ ነበር፤ ግን አሟሟቱ እንዲህ ይሆናል ብዬ አላሰብኩም፡፡ አንድ ቀን ወይ የሆነ ሰው አጥፍቶ ይጠፋል፤ አልያም ራሱን ያጠፋል፤ ብዬ ነበር የምጠብቀው፡፡ ምናልባትም እኔን ይገለኛል የሚል ሐሳብ ነበረኝ፤ ግን አልፈራም ነበር፡፡ ሐሳቡን ፊት አልስጠው እንጂ በውስጤ በጣም ጥልቅ በሆነ የአእምሮዬ ክፍል፣ ትንሸ ለሰሚው ግራ የሆነ አነጋጋሪ አሟሟት መሞት እፈልግ ነበር፡፡ አለ አይደል “የሚያፈቅራት ልጅ በቅናት ተነሳስቶ ገደላት” መባል፡፡ ቶማስ የሞተው ምንም በሌለበት በተባራሪ ጥይት ተመትቶ ነው አሉ። መጠጥ ቤት ውስጥ፡፡ ከአምሳ በላይ ሰው በታጨቀበት መጠጥ ቤት በተነሳ ተራ የሁለት ሰዎች ጸብ አንዲት ጥይት ተተኮሰች፣ ቶማስን ገደለችው፡፡ ስሰማ ደንግጨ አለቀስኩ፣ ደንግጨ ነው። የሚያውቁት ሰው ሲሞት ያስደነግጣል፣ እንኳን አንሶላ ተጋፈዉ። በዚህ ሁሉ ውስጥ ታዲያ የሰውን ዘር ጠልቶ የሚኖር ቶማስ፣ ሞቶ እንኳን ባሕሪው ያስፈራኝ ነበር፡፡ በዚያ ልክ ሰዎችን መጥላት፣ ያውም እንደሚለው በግሉ ምንም ያልበደሉትን፣ ከዚያ በፊት ዓይቷቼው እንኳን የማያውቃቼውን 中午:: ስለ ቶማስ ሳስብ እፈራለሁ፡፡ ሰዎች በልብስ እና መኪናቼው፣ በስልጣን እና ውበታቼው ሸፋፍነውት፣ ውስጣቼው ግን እንደ ቶማስ በጥላቻ ያበደ ቢሆንስ? እያልኩ እፈራ ነበር፡፡ ሴቶች ቆንጆ በመሆናቼው ይጠላቼዋል፤ ወንዶች በሴት በመፈቀራቼው ይጠላቼዋል፤ ሕፃናትን ሳይቀር ሳቃቼው ፍንደቃቼው ያበሳጨዋል፡፡ ሁሉንም ሕፃናት ዲቃላ ነበር የሚላቸው፡፡ በዚህ ሁሉ ጥላቻው መኻል አብርሃምን ይወደው ነበር “ጅል ነው'' ይለዋል።

“ጽሑፍስ ላይ?” እለዋለሁ፡፡ የማጥላላበት ሙያዊ ስድብ ከእሱ ለመዋስ በጉጉት “የእኔ 'ታይፕ' አይደለም፤ ግን አሪፍ ይጽፋል።ይቀረዋል! ግን ጠብ፣ ትቾት አይፈራም ብዙም መታዬት ምናምን አይወድም። ሴት ይወዳል፣ ሴቶች ደግሞ “ይሻፍዱለታል'' ምክንያቱም ሴት ይወዳል። ሁላችንም ሴት እንወዳለን፤ ሴቶች መልሰው የሚወዱትን ግን ጥቂቶችን ብቻ ነው፡፡ 'ባዮሎጂው' አይገባኝም'' እንዲህ ሲል ፊቱ ላይ የቅናት ቅሬታ ያንዣብብ ነበር፡፡ታዲያ ቅር ይለኛል... ምንም ሳይሆን ሴትነቴን፣ ገንዘቤን፣ ጊዜዬን ሰጥቼዋለሁ፤ ለምን የሌላ ወንድ በሴቶች መወደድ ያስቀናዋል!? እኔ ሴት አይደለሁም? የቀብሩ ቀን ምን ገረመኝ? መጀመሪያ የገረመኝ አካሄዴ ነበር። ምንም ይሁን ምን ቶማስ ፍቅረኛዬ ነበር። በውስጤ ልጥላው እንጂ ለአንድም ሰው ስለ እሱ ክፉ ተናግሬ አላውቅም፤ ሥራ ሳይኖረው፣ ከሰው የሚያኗኑር ባሕሪ ሳይኖረው፣ አብሬው ኖሪያለሁ። ይኼ ደግሞ እንዴት ብታፈቅረው ነው? ሲያስብለኝ የኖረ ነገር ነበር። እና ድንገተኛ ሞቱን ስትሰማ አንድ ነገር ትሆናለች ብሎ ከጎኔ የሚሆን ሰው እንዴት ይጠፋል? ይኼም ቢቀር፣ ወግ አለ ባህል አለ፤ አነሰም በዛም ከምቀርባቼውና ግንኙነታችንን ከሚያውቁ ጓደኞቼ አንድ እንኳን ሰው አብሬሽ ልሂድ አለማለቱ ገረመኝ። የሁሉም ይቅር የማኅደረ ነገር ነው የደነቀኝ፤ ደውዬ የቀብሩን ቀን ነግሪያት አይመቼኝም ብላ ቀብሩ ላይ አልተገኜችም። ሁለተኛው የገረመኝ ነገር የቀብሩ ቦታ ነበር፡፡ እዚያ አብርሃም የሚኖርበት ሰፈር መንገድ ዳር የታክሲ ፌርማታው እዚህ ሆኖ፣ ቀብሩ እንደ መድረክ ከፍ ያለ ቦታ መንገዱን ተሻግሮ፣ በግራ በኩል እዚያ። ወደ ቀብሩ ለመሄድ፣ ከፍያለዉ መሬት ወደ አስፖልቱ እንዳይንሸራተት በተገነባው የድጋፍ ግንብ መኻል ያለውን የድንጋይ ደረጃ በመጠቀም ነው። ብዙ ጸሐፊ ጓደኞች ስለነበሩት፣ የቀብር ኮሚቴ የተባሉት እነሱ ናቸው። ዘመድ የለው! ምን የለው። በሕይወት ዘመኔ አንድም ሰው ያላለቀሰበት ቀብር ያንን አዬሁ። ብዙዎቹ እኔ እንዳለቅስ ጠብቀው ነበር ይመስለኛል ዕንባዬ ከዬት ይምጠ?! ነገረኛ ነውና መንገድ ዳር እንቅበረው ብለው እንደሆን እንጃ፤ ብቻ እዚያ ቀበሩት፡፡

ከቀብር መልስ ቶማስ ዘመድ የለውም ነበርና ሁልጊዜ በሄደበት የሚይዛትን ማንገቻዋ የነተበ የቆዳ ቦርሳ አምጥተው ሰጡኝ (ውርስ መሆኑ ነው) ማታ ቁጭ ብዬ ስበረብር ምን አገኜሁ? ብዙ ቀይና ሰማያዊ እስክርቢቶዎች፤ ሁለት ምንም ሳይጻፍባቼው ያረጁ ማስታወሻ ደብተሮች (አልፎ አልፎ ርዕስ ነገር ተጽፎ ተሰርዟል) በዚህ ሁሉ ጊዜ የጻፈው አንድ ነገር የለም፤ የባከነ! ፍተሻዬን ስቀጥል፣ ከአንደኛው ማስታወሻ ደብተር ውስጥ ተጣጥፋ የተቀመጠች ቁራጭ ወረቀት አገኜሁ፤ ዘረጋግቼ በላይዋ ላይ የተጻፉትን ሁለት ቃላት አነበብኩ “የማኅደረ ከንፈር..” ይላል! የማኅደረ ከንፈር ምን?... ሰው ሞኝ ነው ቶማስ ምንም ሳይጽፍ ሞተ ይላል፣ ከዚህ ወዲያ ምን ይጻፍ?! ልክስክስ! ከመቃብሩ አውጥቼ በጥርሴ ብዘለዝለው ደስታዬ ነበር። አንዳንድ ሴቶች አሉ እንደ ዳሌ፣ እንደ ጡት፣ ዝምታና ትህትናቸውን ወንድ ለማማለል የሚጠቀሙበት። የእርሷ ጥፋት ይሁን አይሁን ግድ አልሰጠኝም ብቻ ማኅደረን ከነፍሴ ጠላኋት፡፡ ቶማስ በተቀበረ በሳምንቱ፣ አብርሃም አንድ ግጥም መድረክ ላይ አንብቦ፣ “ለጓደኛዬ ቶማስ መታሰቢያ ይሁን” አለ፡፡ እውነቱን ለመናገር በግጥሙ ምን እንዳለም አልሰማሁም፤ መታሰቢያ ነው ሲል ነበር የገባኝ። አንዳንዶች ታዲያ እያጨበጨቡ ወደኔ ዞር ዞር አሉ ... ግድ አልቅሺ ነው!? ወጉ አይቅር ብዬ እንዳዘነ ሰው አቀረቀርኩ፡፡ሳቀረቅር ጫማዬን በትኩረት ተመለከትኩ፤ ለምንድን ነው ሁልጊዜ ፍላት ጫማ የማደርገው? ብዬ ያሰብኩት እና ለመጀመሪያ ጊዜ ተረከዘ ረዥም ጫማ መግዛት እንዳለብኝ የወሰንኩት በዚያች ምሸት ነበር፡፡ አበበ ጠላ ጠጣ! ዮናስ እና ማኅደር ተጋቡ እያልኩ ለራሴ ደጋግሜ የምናገረው ስለሚገርመኝ ነው። ባል ተብዬው እዚያ ንግድ ሥራ ኮሌጅ እያለን ትምህርቱን አቋርጦ ሱዳን እንደሄደ ነበር የሰማሁት፡፡ በዬት በዬት ዞሮ አሜሪካ እንደገባ እንጃለት፡፡ ማህደረ ጋር እንዴት እንደተገናኙ እዴት እስከ ጋብቻ እንደደረሱም አላውቅም፡፡ አንድ ቀን እንኳን ስሙን አንስተነው አናውቅም፤ ለእኔ ተአምር ነበር፡፡ይኼ ዮናስ የሚባል ልጅ


‹‹እኔ እንጃ ...እሱን በምን አውቃለሁ? ላገኛት በፈለኩ ጊዜ አጥቼያት አላውቅም፤ ስንገናኝም ከልቧ በሆነ በተፍለቀለቀ ስሜት ነው አብራኝ የምታሳልፈው..በቃኝ ብዬ እሰክለያት በቃህ ብላ ገፍትራኝ አታውቅም፡፡››

ጽዮን ትንፋሽ እያጠራት‹‹ያ ማለት እኮ በጣም ታፈቅርሀለች ማለት ነው››አለችው ፡፡

‹‹ይመስለኛል፡፡››አላት፡፡ በተሰበረ ልብ ‹‹ገባኝ፡፡ ››አለችው፡፡

‹‹ምኑ ነው የገባሽ?››

‹‹ያው የእኔ እና የአንተ ጉዳይ ተስፋ የሌለው መሆኑ ነዋ፡፡ ችግር የለውም ያው ምርጥ ጓደኛዬም መሆንህ አንድ ነገር ነው..ታዲ የእውነት ልንገርህ አንተ በጣም ድንቅ ሰው ነህ፤ አንተን የቀረበች ማንኛዋም ሴት በፍቅር የመውደቅ እድሏ ከፍተኛ ነው..ስለዚህ በተቻለህ መጠን ሴት ባትቀርብ ደስ ይለኛል..ካለበለዚያ አፍቅረው ሲያጡህ ይጎዳሉ፡፡››

‹‹እኔ እኮ አሁን መልሱን የመለስኩልሽ ከእኔ እና አንቺ ጉዳይ ጋር አያይዤው ሳይሆን በቀጥታ ያለውን ነገር ነው፡፡››

‹‹እኔ ደግሞ አያይዤ ተረዳሁታ፡፡››

‹‹ፂ ትንሽ ላብራራልሽ መሰለኝ.. አሁን የነገርኩሽ ልጅ ርብቃ ትባላለች፡፡ አዲስአበባ ነው የምትኖረው፡፡ እንደነገርኩሽ ከአስር አመት በላይ
አብረን ቆይተናል፡፡በየወሩ ወደ አዲስ አበባ የምሄደው ጉዳይ ኖሮኝ ሳይሆን እሷን ለማግኘት ነው፡፡ይሁንና የእኔ እና የእሷ ጉዳይ ትንሽ ለየት ያለ ነው፡፡ እንገናኛለን፣እንዝናናለን፣ብዙ ብዙ ነገር እንጫወታለን፣በፈለግነው መንገድና መጠን(ፍቅር መጠን ባይኖረውም)ፍቅር እንሰራለን፣እንደሰታለን፣ ስለጋብቻ፣ቤት ስለመመስረት፣ልጆችን ስለመውለድ የመሳሰሉትን ጉዳዬች ግን በስህተት እንኳን ርዕሱ ተነስቶ አያውቅም፡፡››

‹‹ይገርማል!! ያንተስ ይሁን አንደኛ በብዙ ነገር የተለየ ባህሪ ነው ያለህ ፤ያም ባይሆን ወንድ ነህ የእሷ ግን::

‹‹ቆይ ቆይ.. ወንድ ነህ ስትይ?›.

‹‹የዘመኑ ወንድ 99 ፐርሰንቱ ስለጋብቻ ሲነሳበት ያጥወለውለዋል፤ አግባ ከምትለው ጦርነት ሂድ ብትለው ይቀለዋል..እያሉ ብዙ ሴቶች ሲያማርሩ ታዝቤያለሁ..የእሷ ግን ይገርማል!!ማንኛውም ሴት አንድ አመት ቢበዛ ሁለት አመት የፍቅረኛዋን ነባራዊ ሁኔታ አይታና አገናዝባ ዝምልትል ትችል ይሆናል.... ከዛ በላይ ግን  የወደፊት ህይወታችን እንዴት ነው?› ብላ መጠየቋ አይቀርም ፡፡ቢያንስ በቃል እንኳን ቢሆን ካፈቀራት ወንድ ስለወደፊቱ መተማመኛ ትፈልጋለች፡፡አንዳንዷ ሴት እንደውም አንድን ወንድ በተዋወቀች በአንድ ሳምንትም ‹እንዴት ነው አንጋባም?› ብላ ብትጠይቅ የሚያስገርም አይደለም.. ይህቺኛዋ ግን ያንተ ቢጤ ሳትሆን አትቀርም፡፡››

‹‹ይሆናል .እኔ ግን ሳስበው እሷ ጋብቻ አምርራ የምትጠላ ይመስለኛል፡፡ አንድ ቀን በጨረፍታ እንደነገረችኝ በአባት አና እናቷ መካከል የነበረው የተበላሸ የጋብቻ ታሪክ የማይድን ጠባሳ ጥሎባት ያለፈ ይመስለኛል፡፡በወላጆቾ መካከል በነበረው የዘወትር ጠብና ድብድብ እሷም ሆነች ቀሪ ወንድምና እህቶቾ አሰቃቂ የልጅነት እና የወጣትነት ህይወት እንዲያሳልፉ ሳያረጋቸው አልቀረም፤ በዛም የተነሳ በአለም ላይ የሚመሰረተው ጋብቻ ሁሉ የእናትና የአባቷን አይነት የተበላሸ ጥምረት እንደሆነ አድርጋ የምታስብ ይመስለኛል፡፡››
‹‹አንተስ... ?ማለቴ ስለጋብቻ ያለህ አመለካከት፡፡››

‹‹እኔ እንኳን እንደ እሷ ድፍን ያለ የጥላቻ አቋም የለኝም፤ባይሆን እንደዘመኑ ወንድ እንዳልሽው ኃላፊነቱ በመጠኑ ያስፈራኛል፡፡ ጋብቻ እንደ መፋቀር ቀላል አይደለም፣ኢኮኖሚ ዋስትና ያስፈልገዋል፣የልጆች መጠን መወሰን ያስፈልገዋል፣እነሱን በእንክብካቤ ለማሳደግ የሚያስችል ትዕግስት እና አቅም ያስፈልጋል፣በየጊዜው በባልና ሚስት መካከል ያለውን ፍቅር ማደስ ያስፈልጋል…አረ ጣጣው ብዙ ነው፡፡››

‹‹ቆይ የፍቅር ማደስ ስትል አልገባኝም?››

‹‹እንደእኔ ምልከታ ብዙ ትዳሮች ሚፈርሱት በዚህ ጉዳይ ነው፤ጥንዶቹ ይፋቀራሉ ይጋባሉ..አንድ ቤት መኖር አንድ አልጋ ላይ በየቀኑ መተኛት ሲጀመር መሰለቻቸት የሚባለው ነገር ይመጣል ...አዲስ ክስተት የማጣት ጉዳይ ይከሰታል፤ከዛ ቀጣዩ ሂደት ጭቅጭቅ ይሆናል፡፡ ታዲያ እንደ እዚህ አይነት ምልክቶች በጋብቻ
ውስጥ ሲታዩ ‹‹ጠልቶኝ ነው፡፡›› ...‹‹ሌላ አፍቅራ ነው›› ብሎ እጣት ከመጠቋቆም ችግሩ ተፈጥሮዊ መሆኑን በመረዳት ተጋግዞ መፍትሄ መፈለግ ነው የሚበጀው፡፡ የፍቅር ተሀድሶ ማድረግ ማለቴ ነው፡፡ለምሳሌ በሳምንት አንድ ቀንም ቢሆን አብሮ ከቤት ወጥቶ እራት መብላት ..በወር ካልተቻለ በስድስት ወር አንዴም ቢሆን ከከተማ ወጣ ብሎ ዘና ማለት…ብቻ እንደ አቅምና እንደ ሁኔታው የግል ዘዴን እየፈጠሩ ፍቅርን በየጊዜው ማደስ ያስፈልጋል.....የተዳፈነውን የፍቅር እሳት ጊዜ እየጠበቁ ከመጥፋቱ በፊት መቆስቆሱ የግድ ነው፡፡አየሽ ፍቅር ሽንቁር ገንቦ ነው ይባል የለ.. ለምን ይመስልሻል እንደዛ ሚባለው?ሽንቁር ገንቦ ከላይ ውሀውን ስትጨምሪበት ከስር በሽንቁሩ ያፈሳል፡፡ከላይ መጨመር ያቆምሽ ቀን ውስጥ ያለው ወሀ ፈሶ ያልቅና ባዶ ሽንቁር ገንቦ ብቻ ታቅፈሽ ትቀሪያለሽ ማለት ነው፡፡ፍቅርም ልክ እንደዛ ነው፡፡››

ሌላ የምትለው ነገር ስለሌላት‹‹አይ ጥሩ ነው፡፡›› አለችው ፡፡

‹‹ጽዮን አሁን የሚሰማኝን ስሜት እውነቱን ነው?>>

>

‹‹ርብቃን በጣም ለምጄያታለሁ ...የወደፊቱን ላማክራት እፈልጋለሁ፤የእኔ እና ያንቺን ሁኔታ በእሷ መልስ ላይ የተመሰረተ ነው...››

‹‹እሺ ታዲዬ...ደስ የሚል ሀሳብ ነው፡፡እኔም አንድ ነገር ልነግርህ እፈልጋለሁ...አንተ የእኔ መሆን ባትችል እንኳን አይዞህ አታስብ ብቸኛ ሆኜ አልቆራመድም ፤ አንድ ከሶስት አመት በላይ የፍቅር ጥያቄ እያቀረበልኝ ያለ ሰው አለ፤ እኔ አንተን ስላፈቀርኩ ነው እምቢ ያልኩት፡፡ልጁ በጣም ጓደኛዬ ነው፡፡ባላፈቅረውም ማንነቱን በጣም አውቃዋለሁ በዛ ላይ እወደዋለሁ፡፡ ስለዚህ ከእሱ ጋር ቀሪ ህይወቴን ለመኖር ሞክራለሁ፡፡ አንዳንዴ ፍቅር በመላመድ ሊመጣ ይችላል ማለቴ ከቆይታ አብሮ ከመኖር የምፈልገውን አይነት ፍቅር ከእሱ ሊይዘኝ ይችላል ፤ ካልሆነም የምወደውን እና የሚያፈቅረኝን ሰው ማግባት መቻሌም ያን ያህል
የሚያስከፋ አይደለም፤ስለዚህ ነፃ ሆነህ ያለምንም ይሉኝታ እና ተጽዕኖ መሆን ያለበትን ትክክለኛውን ነገር አድርግ፡፡››

‹‹እሺ አመሰግናለሁ… ደህና እደሪ ፡፡››ብሎ ብርድልብሱን ተሸፋፈነና ፊቱን እንዳዞረ ተኛ፡፡

እሷም በመካከላቸውን የነበረውን ክፍተት ሙሉ በሙሉ አጥፍታ ይተጠቀለለውን አንሶላ ሰርስራ ወደ ውስጥ ገብታ ..ጅርባው ላይ ልጥፍ ብላ አቀፈችውና ተኛች ...በመካከላቻው ትንሽ የሙቀት ጎመራ መንቀልቀል ጀመረ፡፡ >>

✨ይቀጥላል✨

#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
@atronose' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@atronose


#ትንግርት


#ክፍል_አርባ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ከሆቴል ይዟት ሲወጣ ሰዓቱ ከምሽቱ 3፡55 ሆኖ ነበር፡፡‹‹ፂ በጣም እኮ ጨልሞል... በዛ ላይ የከተማው መብራት እንዳለ ጠፍቷል የግድ ቤትሽ ድረስ ልሸኝሽ ይገባል፡፡››

‹‹መብራት ባይጠፋ ኖሮስ ?››

‹‹መብራት ባይጠፋማ ነፃነት ሆቴል ድረስ ከሸኘሁሽ ከዛ ወዲያ ቅርብ ስለሆነ እንቺም ወደ ቤትሽ እኔም ወደቤቴ እንበታተን ነበር››

‹‹ተው እንጂ ?እያሾፍክብኝ ነው አይደል?››

‹‹ለምን አሾፍብሻለሁ?››

‹‹ጨልሞል መብራት ጠፍቷል ..ያ ታዲያ ለእኔ ምኔ ነው..?ሁለቱም አይመለከቱኝም እኮ፡፡ ስትተኙ ተኝቼ ስትነሱ የምነሳው እኮ መቼስ ህይወቴም ስራዬም ከዓይናማዎቹ ጋር ነዋና ሰዓቴን ከእናንተ ሰዓት ጋር አስተካክዬ ልጠቀም ብዬ ነው እንጂ፤ ቀን በምትሉበት ሰዓት ተኝቼ በማታው ብሰራ ለእኔ ለውጥ የለውም፡፡ቀንና ለሊት የጨለማ እና የብርሀን መፈራረቅ ነው አይደል በእኔ ህይወት ሁለቱም አይፈራረቁም ጭርሱኑ የሉም…››

‹‹አይ የእኔ ነገር ..!!አንቺ እኮ ሁል ጊዜ በመንፈስ ብቻ ሳይሆን በአካልም ሙሉ መስለሽ ስለምትታይኝ ነው..በዛ ላይ ካለወትሮዬ አራት ቢራ መጠጣቴን አትዘንጊ፡፡››

‹‹ሰክሬያለሁ ለማለት ነው?››

‹‹ያው እንደዛው በይው››

እያወሩ ፅዮን ቤት በራፍ ጋር ደረሱ፤የቤቷን መክፈቻ ቁልፍ ከቦርሳዋ በርብራ አወጣችና በመክፈት ወደውስጥ አልፋ ከገባች በኃላ ‹‹ግባ እንጂ >> አለችው፡፡

‹‹እንዴት ልግባ?››

‹‹እኔ እንደገባሁት ነዋ…ምን እንደህንዶቹ ፀሎት ተደርጎልህ ግንባርህን ቀለም ካላስነኩህ ደጃፉን አታልፍም?››

‹‹እሱን አላልኩም እኔ እንዳንቺ በጨለማ የመጓዝ ችሎታ የለኝም..፡፡››

‹‹ወይኔ ወይኔ…አለችና ወደ ኋላ ተመልሳ በራፉ አቅራቢያ ኮርነር ላይ የሚገኘውን ማብሪያ ማጥፊያ በዳበሳ ተጫነችው፡፡››

‹‹ይሄው ግባ››

‹‹ባክሽ አሁንም አልበራም.. እውነትም ዛሬ ሰክሬያለሁ መሰለኝ መብራት እንደጠፋ ቅድም ስነግርሽ ቆይቼ አሁን ደግሞ መብራት ውለጂ ማለቴ...፡፡››

‹‹ግዴለህም ቆይ እንደ ፓውዛ ያበራል ብለው የሚያደንቁት ባትሪ አለኝ፡፡›› ብላ ወደ ውስጥ ዘለቀችና ባትሪውን አበራችለት... እውነትም ፓውዛ እንዳለችው ቤቱን በብርሀን ሞላው፡፡ከዛ እሱም ወደ ውስጥ ገባ፡፡

ክፍሉ አንድ ክፍል ቢሆንም የመለስተኛ ሳሎን ያህል ስፋት ኖሮት በዕቃ የተሞላ ነው፡፡
‹‹የሚመችህ ቦታ ቁጭ በል››አለችውና ወደ ቁም ሳጥኑ በማምራት ከፈተችው፡፡እሱ ከአልጋው ፊት ለፊት ካለው ደረቅ ወንበር ላይ ቁጭ አለ፡፡

ፅዮን ከከፈተችው ቁም ሳጥን ቢጃማ ሱሪና ሹራብ አወጣች..ቀሚሷን ሳታወልቅ በፊት ቀድማ ቢጃማ ሱሪውን ለበሰች፤ከዛ ቀሚሷን አወለቀች.... በዚህን ጊዜ ግማሽ አካሏ ለእይታ ተጋለጠ...ጡት ማስያዣያም አላደረገች፡፡ የቢጃማ ሹራቧን አነሳችና ለመልበስ ጭንቅላቷን አስገብታ ወደ ታች እየሳበች‹‹ምነው አፍጥጠህ አየኸኝ?›› አለችው፡፡

ደነገጠ‹‹ምን አልሺኝ?››

‹‹ዓይንህ ሰውነቴን አቃጠለኝ፡፡››

‹‹መቼም ወንድ ነው... ወንዶች ደግሞ የሴት ዕርቃን ፊት ለፊታቸው ከተጋረጠ ማፍጠጣቸው አይቀሬ ነው ብለሽ ነው አይደል?››

‹‹እና እያየሁሽ አይደለም እያልከኝ ነው?››

‹‹ከጠረጴዛሽ ላይ አልበም አግኝቼ እሱን እያየሁ ነው››አላት፡፡ እውነታው ልክ እሱ እንደሚለው ቢሆንም በጎሪጥ እየሰረቀ አንድ ሁለቴ ግማሽ እርቃን ገላዋን አላያትም ማለት ግን አይደለም፡፡

‹‹እሺ ይሁንልህ ሻይ ወይስ ቡና ላፍላ ?››

‹‹ኧረ ምንም አልፈልግም… ቤትሽን እኮ ልይልሽ ብዬ ነው ወደ ውስጥ የዘለቅኩት ባይሆን ሌላ ቀን እመጣለሁ... አሁን ልሂድ››

‹‹ስንት ሰዓት ነው?››



መሽቷል እኮ ለልጆቹ ትርንጎ አለች አይደለም?

(ትርንጐ ልጆቹን እንድትንከባከብ የታዲዬስ ቤተስብ የተቀላቀለች ወጣት ልጅ ነች) >>

‹‹ብትኖርስ…? እዚህ ነው የማድረው?››

‹‹አዎ፡፡ ምን አለበት..?አልጋው እንደሆነ እንደምታየው ባለ ሜትር ከሰማንያ ነው፡፡››

‹‹እሱስ እውነትሽን ነው..እንግዲያው ለትርንጎ ደውዬ ልንገራታ.. ታውቂያለሽ ስልክ አልያዝኩም ያንቺን ስልክ ልጠቀም?››

‹‹ቦርሳዬ ውስጥ አለልህ ፤ተጠቀም፡፡››

ከተቀመጠበት ተነሳና ቦርሳውን ከጠረጴዛው አንስቶ ያለችበት ቦታ ድረስ ወስዶ ሰጣት፡፡

‹‹ምነው?››

አውጪና ስጪኛ..የሴት ቦርሳ በርብሮ ዕቃ ከማግኘት ከሙሉ መጋዘን ውስጥ የሆነ ዕቃ ፈልጐ ማግኘት ይቀላል..ግምሽ ንብረታችሁን እኮ በቦርሳችሁ ነው ይዛችሁ የምትዞሩት፡፡››

‹‹ለካ እንዲህ ነገረኛ ነህ?››አለችና አውጥታ ሰጠችው፡፡ ደውሎ እንደማይመጣ ተናግሮ ስልኩን ዘጋና ወደ መቀመጫው ተመልሶ ቁጭ እንዳለ መብራቱ መጣ፡፡

‹‹እሺ አሁንስ ማደርህ ተረጋግጧል .. ቡና ነው ሻይ?>>

‹‹እኔ ምንም አልፈልግ..መተኛት ብቻ፡፡››

‹‹የእኔ ቢጃማ ይሆንህ ይሆን?

‹‹ቅር ካላለሽ እኔ ቢጃማ ለብሼ መተኛት አልወድም... እንቅልፍም አይወስደኝም፡፡››

‹‹በፓንት ብቻ ነው ሁሌ የምትተኛው?››

‹‹ኧረ እኔ ፓንት የሚባል ኖሮኝ አያውቅም?››

ከትከት ብላ ሳቀችበት‹‹እያሻፍክብኝ ነው አይደል?››

‹‹የእውነቴን ነው ... ሰውዬውም በሰፊ ሱሪ ውስጥ በነፃነት ሲጨፍር ነው የሚውለው... ለዛሬው ግን አይዞሽ አትስጊ አንሶላውን ተጠቅልዬ እተኛለሁ››

‹‹ኧረ ያንተ ነገር ገርሞኝ ነው እንጂ ለእኔ ችግር የለውም፡፡››

ልብሱን ሙሉ በሙሉ አወለቀና መላ መላውን ወደ አልጋው ሲራመድ

‹‹አንተ በጣም ትልቅ ነው አለችው›› ደነገጠና በሁለት እጁ አፈፍ አድርጎ ሸፈነው...ትዝ ሲለው

መልሶ ለቀቀውና በሳቅ ፈረሰ፡፡

‹‹በጣም ተንኮለኛ ነሽ ..የእውነት ያየሺኝ እኮ ነው የመሰለኝ››ብሏት ወደ አልጋው ሄዶ ከውስጥ ገብቶ ተኛ ..እንዳለውም አንሶላውን ተጠቅልሎ አንደኛውን ጠርዝ ይዞ ነበር የተኛው፡፡እሷም ከደቂቃዎች በኃላ ተከተለችው ፤በመካላቸው የ5ዐ ሴ.ሜትር ክፍተት ነበር

‹‹መብራቱን ላጥፋው?››ጠየቃት፡፡

‹‹መብራት መጥቷል እንዴ ?››

‹‹አዎ መጥቷል?››

‹‹እንደፈለግክ፡፡››

‹‹አይ አንቺ የቱ ይሻልሻል?››

‹‹አንተ ልጅ ዛሬ ምን ነክቶሀል? መብራቱ እኮ ለአንተ ሲል ነው የበራው፡፡››

‹‹እውነትም የሆነ የነካኝ ነገር አለ፡፡›› አለና ተንጠራርቶ አጠፋው፤ ፊቱን አዙሮ ተኛ፤እሷም

ፊቷን ወደ እሱ አዙራ ክፍተቱን እንደጠበቀች

ከ1ዐ ደቂቃዎች ዝምታ በኃላ‹‹ታዲያ..እንቅልፍ ወሰደህ እንዴ?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹አልወሰደኝም››መለሰላት፡፡

‹‹ማውራት ትፈልጋለህ?››

‹‹አዎ እስቲ አውሪኝ ..ዛሬ ቢራው ነው መሰለኝ የወሬ አፒታይቴን ክፍትፍት አድርጎልኛል››

‹‹ወሬ አይደለም ጥያቄ ልጠይቅህ ነው?››

‹‹ጠይቂኝ››

‹‹ታዲ የዛሬው ፕሮግራም እኮ በዕቅዳችን መሰረት አይደለም የተፈፀመው፡፡የተገናኘነው የሁለታችን ጉዳይ ለማውራት ነበር፤ ጊዜው ያለፈው ግን በእኔ ያለፈ ታሪክ ትረካ ነው፡፡››

‹‹እና ጥያቄሽ ምንድነው?››

‹‹ጓደኛ አለህ እንዴ? ማለቴ የፍቅር ጓደኛ?››

‹‹እኔ እንጃ››

‹‹እኔ እንጃ ማለት እኮ አለኝምም የለኝምም የሚል አሻሚ መልስ ነው፡፡››

‹‹አዎ እንደዛው ነው፡፡››

‹‹እሺ ያለችውን ታፈቅራታለህ?››

‹‹ይመስለኛል ያለፉትን 1ዐ ዓመታት ያለመሳለቻቸት አብረን አሳልፈናል…ከእሷ ውጭ ማንም ሴት ጋር ሄጄ አላውቅም፤ባላፈቅራት ኖሮ እንደዛ አላደርግም የሚል ግምት አለኝ፡፡››

‹‹ትክክል ነህ... እሷስ ታፈቅርሀለች?››


‹‹እማዬ የልጅ ልጅ ለመታቀፍ ያላትን ጉጉትና የዘመናት ፀሎት ታውቂያለሽ..አሁን እንዳልሺው ፅንሱን አስወርደሽ በሆነ አጋጣሚ ብትሰማ ምንድነው የምትሆነው..?ቀጥታ የልብ ምቷነው የሚያከትምለት፡፡››
‹‹አንተ ካልነገርካት ከማንም ልትሰማ አትችልም…፡፡እርግጥ እንደእሷ ጉጉት ይሄንን ልጅ ወልጄ ባስታቅፋት እና በእሷ ብመረቅ ደስ ይለኝ ነበር..ግን አባት የሌለው ልጅ ማሳደግ አልፈልግም..ፈፅሞ ሲንግል ማም የመሆን እቅድ የለኝም፡፡››
‹‹አባት የሌለው ልጅ ስትይ…የሞትኩ አስመሰልሺው እኮ››
‹‹እድር ስለሌለ ነው እንጂ ከሞትክ እኮ ሰነባበትክ፡፡››
‹‹የተወሰነ ቀን ስጪኝ ..ነገሩን የምናስተካክልበት የሆነ መንገድ እንዳለ እንይ…››
ትንሽ እንደመተከዝ አለችና‹‹እሺ…አንድ ሳምንት ሰጥቼሀለው….አንድ ሳምንት ብቻ…››
ለእሷ ሆነ ነገር ለመመለስ ሳብሰለስል ስልኬ ጮኸ።ተንጠራርቼ  አነሳሁትና አየሁት።
ወይኔ ጉዴ አሷ ነች።‹‹በቃ ሞተ ማለት ነው?ነፍሰ ገዳይ ሆንኩ ማለት ነው..?እንዴት ነው ግን ከዚህ ወንጀሌና ሀጥያቴ ጋር የምኖረው?እንደምንም እራሴን አረጋግቼ  የለቅሶና ሰቅጣጭ የጩኸት  ድምፅ ለመስማት ውስጤን  አዘጋጅቼ በሚንቀጠቀጥ እጄ ላይ   ያለውን  ስልክ አነሳሁት።

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


እባክሽ አትሂጂ…..
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-17

ጊዜ በቀናት፤በወርና በአመት መከፋፈሉ ዋናው ጥቅም ስልቹ ለሆነው ስነልቦናችን
መፍትሄ ለማበጀት ነው፡፡አንድ መፅሀፍ የፈለገ ምርጥ ቢሆን በርዕስ ተሸንሽኖ
በምእራፍ ካልተከፋፈለ ማንም ጀግና አንባቢ ጀምሮ ሊጨርሰው ሞራል
አይኖረውም፡፡ጊዜም እንደዛው ነው፡፡ሰኞ አልፎ ማክሰኞ  ሲመጣ  በህይወታችን ሰኞ ያልነበረ አዲስ ነገር  እንደሚከሰት ተስፋ እናደረጋለን…ዛሬም ሰኞ ነገም ሰኞ ተነገ ወዲያም ሰኞ ከሆነ ግን አእምሮችን በሁሉም ሰኞዎች አንድ  አይነት የህይወት ክስተት እደሚያስተናግድ ግምቱን የመውሰድ  እድሉ ከፍተኛ ነው….ይሄ ደግሞ ወደመሰላቸት እንድንገባና ከነበርንበት  የጨፈገገ ስሜት በቀላሉ እንዳንወጣ ሊያደርገን ይችል ነበር፡እንደውም ጊዜ ልሙጥ ይመስለኛል….መጀመሪያም ማብቂያም የሌለው አልፋኦሜጋ….ልክ  እንደእግዚያብሄር..፡፡ እንደውም ጊዜ እራሱ እግዚያብሄር ይሆን እንዴ….?እንጂማ  አሮጌ የሚባል አመት የለም አዲስም የሚባል ነገር አይመጣም፡፡እንዲህ ስለጊዜ እየተፈላሰፍኩ ምዘበራርቀው ስለጨነቀኝ ነው፡፡
ሀሳብና ስጋት  ቀረጣጥፎ ሊጨርሰኝ ነው…፡፡ሰው መግደል አይደለም ሰው ስለመግደልም አስቤ አላውቅም…፡፡ሰው እንዴት አስቦ አቅዶና ልዩ ዝግጅት አድርጎ ሰውን ይገድላል? እያልኩ ለአመታ ስገረምና ስደነቅ የኖርኩ አይነት ሰው ነኝ ፡፡አሁን ግን እኔ አድርጌዋለሁ..ለዛውም ለፍቅር ስል…፡፡ግን ለፍቅር ስል ነው ማለት እችላለሁ እንዴ? ፍቅር እንደዛ ነው እንዴ የሚተረጎመው..?ፍቅር ስግብግብነት ነው እንዴ? ፍቅር የሌላውን ሰው ደስታና ህልም መንጠቅ ነው እንዴ..?እኔ እንጃ ብቻ በህይወቴ በዚህ መጠን የተወዛገብኩበትን ጊዜ አላስታውስም ..፡፡ገና በመጀመሪያው ቀን እንዲህ አይነት ጭንቀት ውስጥ ከገባሁ ቀጣዬቹን ቀናት እንዴት ልወጣው ነው…?መድሀኒቱ እንደሆነ ቀስ ብሎ ገና በሰውነቱ ተሰራጭቶ ህይወቱን እስኪነጥቀው ከፈጠነ ሶስት ቀን ካልሆነ ደግሞ አራት ቀን ይፈጃል….፡፡አራት ቀን በእንደዚህ አይነት ስጋት…?እንደእዚህ አይነት ጭንቀት እንዴት ላሳልፍ እችላለሁ…?፡፡ስራዬን እንኳን ተረጋግቼ መስራት ስላልቻልኩ አሞኛል ብዬ በማስፈቀድ እቤት ተኝቼያለሁ፡፡ ለነገሩ ከዚህ በላይ ምን መታመም አለ..?ከታመምኩእማ ቆየሁ..፡፡
ቆይ ደወለች….አሁን አንስቼ ምንድነው የምላት…?ሰውነቴ በጠቅላላ የእሌክትሪክ ወንበር ላይ እንዳስቀመጡን ወንጀለኛ ተንዘረዘረብኝ….ሊዘጋ አንድ ጥሪ ሲቀረው እንደምንም አነሳሁት፡፡
‹‹ሄለ ዶ/ር ሰላም ነህ?››ቅልጥልጥ የሚያደርግ አዚማም ድምፅ፡፡
‹‹ሰላም ነኝ..አንቺስ…?መስፍኔ ሰላም ነው..?አላመመውም አይደል?››
‹‹አይ ሰላም ነው …ምንም ችግር የለም…እናንተ ሆስፒታል አካባቢ ነበርኩ፡፡ ጎራ ብዬ ሰላም ልልህ ፈለኩና ብዙ ታካሚ ካለ እንዳረብሽህ ሰጋሁ..ለዛ ነው ቀድሜ የደወልኩልህ››
‹‹በጣም ደስ ይለኝ ነበር..ዛሬ ግን ትንሽ ጉንፋን ነገር ይዞኝ አልገባሁም..እቤት ነኝ፡፡››አልኳት፡፡
ደነገጠች‹‹ውይ ዶ/ር..መቼ ጀመረህ? ትናንት ሰላም አልነበርክ እንዴ?››
‹‹አዎ ለሊት ነው የጀማመረኝ…እንዲሁ ድካም ሰለተሰማኝ እንጂ ብዙም የሚያስጨንቅ ህመም አይደለም..፡፡››
‹‹እሱማ የህመም ቀላል አለው ብለህ ነው….?አንተን ከስራ አስቀረህ ማለት እኮ…መጥቼ ልይህ ሰፈርህ የት ነው?››
‹‹አረ አያስፈልግም…ባይሆን ካልተሻለኝ ነገ ትጠይቂኛለሽ፡፡››
‹‹ይሻላል ብለህ ነው?››
‹‹አዎ …ይሻላል፡፡ለመሆኑ እኛ ሰፈር ምን እግር ጣለሽ?››
‹‹ያው ለመስፍኔ ጉዳይ ነዋ….እኔማ ደስታዬን ነግሬህ የደስደስ መክሰስ ልጋብዝህ ነበር፡፡››
‹‹ምን ተገኘ?››
‹‹በቃ የውጭ ፕሮሰሱን ወደመጨረሱ ነኝ፡፡ትንሽ ነገር ብቻ ነው የቀረኝ ፡፡የዛሬ ሳምንት ከበዛ ከአስራአምስት ቀን በኃላ ወደህንድ ይዤው እሄዳለው››ብላ እጥዬን ድብ አደረገችው፡፡እሱ የሳምንት ዕድሜ እንደሌለው ነገ ወይ ተነገ ወዲያ እንደሚሞትና ይሄ አሁን የምትፈነጥዝለት የውጭ ጉዞ እንደማይከናወን እርግጠኛ ሆኜ እንኳን በሀሳቧ ስላሰበች ብቻ አስደነገጠኝ፡፡እንደምንም እራሴን አረጋግቼ‹‹በእውነት በጣም ደስ ይላል….ለመሆኑ ልጆቹን እንዴት ልታደርጊ ነው…?››ስል ጠየቅኳት፡፡
‹‹እነሱ ምን ይሆናሉ ብለህ ነው….ከሞግዚቷ ጋር አድርጌ እናቴ ጋር ተዋቸዋለው››
‹‹አይ ጥሩ ነው፡፡በቃ ከተሻለኝ ነገ ብቅ ብዬ እናወራለን..በዛውም መስፍንን አየዋለሁ፡፡››
‹‹እሺ ..ካልተሻለህ ደግሞ እኔ መጥቼ ጠይቅሀለው…ለማንኛውም እራስህን ተንከባከብ …እግዜር ይማርህ፡፡››
‹‹አሜን ደህና ሁኚ››ስልኩ ተዘጋ…ድካሙ ባሰብኝ….ልፋቷ ጉጉቷና መስዋዕት የከፈለችበትን ነገር በአንድ ብልቃጥ መድሀኒት መሰል መርዝ ገደል መከተቴ ፀፀት ውስጥ ከተተኝ፡፡ግን ደግሞ ጥፈቴን ለማስተካከል ምንም አይነት ፍላጎት የለኝም ፡፡እንጂማ..መዲሀኒቱ በተሰጠ በ48 ሰዓት ውስጥ እሱን የሚያረክስ ሌላ መድሀኒት መስጠትና ስህተቴን ማስተካከል እችል ነበር….ግን አሁንም በአቋሜ እንደፀናሁ ነው፡፡
///
ሶስት ቀን አለፈው፡፡ እኔም መኝታዬን ለቅቄ አልተነሳውም ልዕልትም አልደወልችልኝም፡፡በቃ  እራሷን ስታ ነው የሚሆነው፡፡..ምንድነው የማደርገው፡፡ ደውዬ እንዳላረጋግጥ ፈራሁ ….የምሰማውን ዜና ፈራሁ፡፡ እርግበ ከአልጋው ጠርዝ ቁጭ ብላ ነገረ ስራዬን እያየች በዝምታ እየታዘበችን ነው፡፡
‹‹ቆይ ግን ምንድነው የሚበጅህ?››
‹‹ይሻለኛል..አሁን መድሀኒት ወሰድኩበት አይደል? ምንም አይለኝም፡፡››
‹‹በሽታህ እኮ በመድሀኒት የሚድን አይደለም፡፡››
‹‹ምን ማለትሽ ነው…?››በተኛሁበት ፊቴን አጨመዳድጄ ጠየቅኳት፡፡
‹‹…ባሎን ለማሳከም ውጭ ሄደች ማለት እኮ ለዘላለም በዛው ትቀራለች ማለት አይደለም…ነው ወይስ ሰውዬው ድኖ ከመጣ በኃላ እንዴት አገኛታለሁ? የሚለውን ነው እንዲህ ያስጨነቀህ፡፡››
‹‹ስለማን ነው የምታወሪው?››
‹‹ስለማን እንደማወራማ በትክክል ታውቃለህ….እኔ ማወራው አእምሮህን በምስሎቾና በትዝታዎቾ ስለሞለችው ባለትዳር ሴት ነው…..ለማንኛውም ምረዳህ ነገር ካለ ንገረኝ፣…ቢያንስ ጓዳኛዬ እንዲህ ሲሆን ዝም ብሎ የማየት ሞራል የለኝም››
ምንም ልመልስላት አልቻልኩም..ዝም አልኩ….፡፡
‹‹በነገራችን ላይ አርግዤለሁ››
እባብ አንገቴ ላይ እንደተጠመጠመ ተልፈስፍሼ ከተኛሁበት አልጋ ላይ ተፈናጥሬ ተነሳሁ….‹‹ምን..?አርግዤለሁ?…እንዴት?››
‹‹ኸረ ተረጋጋ..አሁን እንዴት ሊረገዝ እንደሚችል ለአንድ ዶ/ር ማስረዳት አለብኝ?››
እልክ እየተናነቀኝ‹‹እየቀለድኩ አይደለም?››አልኳት፡፡
‹‹በደንብ እየቀለድክ ነው እንጂ…መቼስ ወንዶች ተንሰፍስፋችሁና ላሀጫችሁን አዝረክርካችሁ በጥድፊያ ታደርጉና ተረግዞላችኃል ስትባሉ በድንጋጤ ጭራችሁን ሸጉጣችሁ መደበቂያ ቦታ ትፈልጋላችሁ….ለማንኛውም አታስብ ላስወርደው ነው፡፡››
‹‹ምን?››አርግዤላሁ ብላ ከነገረችኝ ዜና በላይ ላስወርደው ነው ብላ የነገረችኝ ይበልጥ አስደነገጠኝ፡፡
ፍፅም መወሰኗን በሚያሳብቅ ጥብቅ ንግግር ‹‹ምነው…ችግር አለው? ››አለችኝ፡፡
‹‹ማለቴ ለእንደዚህ አይነት ውሳኔ ምን አስቸኮለሽ?››
‹‹ምን አስቸኮለሽ? ትቀልዳለህ….?የማልወልደውን ልጅ በውስጤ ተሸከሜ ለምን ዞራለው…?የነገርኩህ እንዲህ እንድታመር  እና እንድትጨነቅበት ፈልጌ ሳይሆን ለጠቅላላ እውቀት እንዲሆንህ ነው፡፡››


ትመጫለሽ ብዬ ፣ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ
የማውቀው ሰው ሁላ ፣ አረብ ሀገር ሔዶ
አንቺ ሳትመጪ ፣ ለመመለስ ቃጣ
በመጪ መዳፍ ላይ....
ተጎትቶ አለፈ ፣ እድሜዬ እንደሻንጣ
"ትመጫለሽ እያልኩ"
ደርግ ስልጣን ለቆ ፣ ሌላ ደርግ መጣ

🎴በላይ በቀለ ወያ🎴

#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
@atronose' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@atronose


እባክሽ አትሂጂ
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-16


በጭንቀት በተወጠረ ጨፍጋጊ ስሜት በእኔ መኪና ተያይዘን ከጊቢ ወጣን፡፡

ግቢዋን ለቀን ትንሽ እንደተጓዝን ያላሰብኩት ነገር ተከሰተ፡፡ያቺ አበባ የምትረከበኝ እብድ ዘላ መኪናዬ ፊት ለፊት ተጋረደች፡፡ለትንሽ ወጥቼባት ነበር፡፡ሲጢጢ አድርጌ ነው በመከራ ያቆምኩት…ንግስት በድንጋጤ ጩኸቷን ለቀቀችው….እኔ በፊትም ድንዝዝ ብዬ ነበር ይበልጥ ደነዘዝኩ፡፡ልጅቷ ምንም እንዳልተፈጠረ ከፊት ለፊቱ ለቃ በመስኮት በኩል መጣች፡፡
‹‹ምን እየሰራሽ ነው..?ተጎዳሽ?››
‹‹አይ አልነካኝም….አይዞህ ብጎዳም አሳክመኝ አልልህም››
‹‹አይ ጥሩ ነው…››ኪሴ ገባሁና የተለመደውን 50 ብር አወጣሁ‹‹‹ለሌላ ጊዜ ግን እንዲህ ዘለሽ መኪና ውስጥ አትግቢ፡፡››
‹‹አንተም ለሁለተኛው እሷን አገኘሁ ብለህ ሳታናግረኝ ዝም ብለህ እንዳትሄድ››ብላ መለሰችልኝ፡፡
ልዕልትን ሳያት በንግግራችን ግራ እንደተጋባች ያስታውቃል…ምን ብዬ እንደማስረዳት ግራ ስለገባኝ እሷን ዝም አልኳትና 50 ብር የያዘውን እጄን ወደልጅቷ ዘረጋሁ…እሷ ወደ ልዕልት እየች‹‹አበባውን ስለተቀበልሺው ጥሩ አድረግሻል…ይሄን የመሰለ መልከ መልካምና ሸበላ ወንድ ያን ያህል ማሰቃየት አልነበረብሽም…ሁሌ ይዞልሽ ሚመጣውን አበባ አንቺ አልቀበል ስትይው በሀዘን ስብር ይልና መጥቶ ለእኔ ይሰጠኝ ነበር…እኔም አበባውን ስለተቀበልኩት ሀምሳ ብር አስከፍለዋለሁ….›› ሁሉንም በዝርዝር ማስረዳቷን እንደቀጠለች..በእፍረትና በላብ ተጠምቄ 50 ብሩን እላዋ ላይ ወረወርኩና ገፍተር አድርጌ ከመንገዱ የተወሰነ  አራቅኳትና መኪና ውስጥ ገባሁ፡፡ ነዳሁት..እየተከተለችኝ..‹‹እንዳያመልጥሽ…..በጣም ነው የሚያፈቅርሽ፡›› ማለት ጀመረች፡፡
በዝምታ የተወሰኑ ርቀት ከተጓዝን በኃላ  የልዕልት ዝምታዋ አስፈራኝና …‹‹የእብድ ነገር››አልኩ፡፡
‹‹አይ ምታወራው ግን የእብድ ወሬ አይመስልም…በደንብ የምትተዋወቁ ነው የሚመስለው››
‹‹እሱማ አንቺ ቤት ስመጣ እዚህ አካባቢ ስለማገኛት ሳንቲም ሰጣታለሁ፡፡››
የሆነ ነገር ልትመልስልኝ ካለች በኃላ ድንገት በእስፖኪዬ ውስጥ እትኩራ አየች ..ከዛ ወደኃላ ወንበር ዞረች….በድንጋጤ ይሆን በአድናቆት አይኖቾ ፈጠጡ፡፡ተንጠራራችና ቅድም ለእሷ ገዝቼ ግን እንደሁልጊዜው ሁሉ ያልሰጠኋትን አበባ አነሳችና..በእጆቾ እያፍተለተለች ታየው ጀመር….ወደአፍንጫዋ አስጠግታ አሸተተች..ስታሸት ደግሞ አይኖቾን ጨፈነች……
‹‹ዶ/ር  ማነች በክህ እንዲህ የታደለች ተፈቃሪ..?››
‹‹እሷ ሳትሆን እኔ ነኝ እድለኛው….››
‹‹አረ..አንተን ያገኘችማ በጣም የታደለች ነች….ግን ልጅቷ አልቀበልህ እያለች እንዳስቸገረችህ ስትናገር ነበር…እውነቷን ነው?፡፡››
‹‹በከፊል አዎ..እውነቷን ነው››
‹‹አስተዋውቀኝ…ምን ያህል እንቁና ውድ ሰው እየገፋች እንደሆነ እንዲገባት አድርጌ ነግራታለሁ…አንተ እኮ ከሚሊዬን ወንዶች መካከል እንደሎተሪ የምትገኝ እንቁ ስርዓት ያለህ፤ተንከባካቢና አሳቢ ወንድ ነህ…፡፡››
በአድናቆቷ አይኖቼ ፈጠጡ….‹‹ዝም ብለሽ አጉል እየካብሺኝ ነው፡፡››
‹‹አይደለም..የምሬን ነው እያወራሁህ ያለሁት…እርግጥ ይሄ ፍቅር የሚባለው ነገር ግራ አጋቢ ነው፡፡መስፈርቱ ምን እንደሆነ እራሱ አይታውቅም…አንተ ስታፈቅር ከሌላው በተሻለ ውበትም እውቀትም ያለውን ሰው መርጠህ አይደለም…ልብህ ይምታ እንጂ ሌላው  አያሳስብህም…መምሁሩን ትተህ መሀይሙን..ውብን አልፈልግም ብለህ ፉንጋውን …ትሁትና ተንከባካቢውን አባረህ ተደባበዳቢና ጠጪውን ልትፈቅድ ትችላለህ፡፡ለዚህ የምርጫ መፋለስ ምንም የሚሰጥ ማብራሪያ የለም፡፡ፍቅርን የተለየ የሚያደርገውም ይሄ ባህሪው ነው…እና ለማለት የፈለኩት ያንትም ሴት አንተን ገፋ ገፋ ብታደርግህ ችግሩ ካንተ ሳይሆን ከራሱ ከፍቅር ባህሪ መሆኑን እንድታውቀው ነው፡፡››
መሪዬን እያሽከረከርኩ በፍፅም መመሰጥ እያዳመጥኳት ሳለ በመሀከል ወሬዋን አቋመችና ከትከት ብላ ሳቀች…ደነገጥኩና የአስፓልቱን ጠርዝ አስይዤ መኪናዬን አቆምኩ‹‹ምነው ምን አሳቀሽ ?›ጠየቅኳት
‹‹አይገርምም..አሁን እኔ የፍቅር ኤክስፐርት ሆኜ ለአንተ ለዛውም ለዶክተሩ ሰውዬ ሳብራራልህ…..››
‹‹አይ አንቺ..ጠንቋይ ለራሱ አያውቅም ሲባል አልሰማሽም…ደግሞ ማብራሪያሽ ምንም እንከን የማይወጣለት ነው፡፡››
‹‹እሱስ አዎ..ፍቅር ምክንያታዊ ቢሆን ኖሮ እኔና መስፍኔ ተጋብተን ይሄን ሁሉ አመት አብረን በመኖር እነዚህን ልጆችም አናፈራም ነበር…በቃ አሁን ቸው ሰሞኑን ልጅቷን ታስተዋውቀኝና ልክ ልኳን እንግራታለው፡፡››ብላ ልትወርድ የጋቢናውን በራፍ ከፈተች፡፡
‹‹እንዴ…ምትሄጂበት ላድርስሽ፡፡››
‹‹ደረስኩ እኮ.. እንደውም ወሬ ይዤ ትንሽ ወደፊት መጥቼለሁ፡፡››
‹‹እኮ የማያቆይሽ ከሆነህ ጠብቄ ልመልስሻ››
‹‹አይ ..እቆያለሁ..ደግሞ ወንድሞቼ አሉ …እንሱ ይመልሱኛል፡፡››አለችና ከወረደች በኃላ በእጇ ይዛ የነበረውን አበባ የተነሳችበት ወንበር ላይ ቀስ ብላ አስቀመጠች፡፡ወዲያው አነሳሁና…እባክሽ ለሚቀጥሉት ሶስት ቀናት እሷና ማግኘት አልችልም..እኔው እጅ ቆይተው ከሚረግፉ አንቼ ውሰጂያቸው››አልኩና አነሳሁና እንድትወስድ ዘረጋሁላት፡፡
እንደማሰብ አለችና‹‹እሺ በጣም ደስ ይለኛል….ግን ለእኔም እንደእብዷ ልጅ ስለተቀበልኩህ 50 ብር ትሰጠኛለህ?››ብላ ሳቀችብኝ፡፡
‹‹ተስማምቼያለሁ፡፡››
‹‹በል ቸው..እንደውም ለመስፍኔ ሰጠዋለው..በሰላሙ ጊዜ አበባ ይወድ ነበር፡፡ ››ብላ ኩም አድርጋኝ መንገዷን ቀጠለች…እኔም በተረማመሰ ስሜት  ስለእሷ እና ስለመስፍኔ ጥምረትና የጋብቻ ሁኔታ እያሰብኩ መንገዴን ቀጠልኩ፡፡

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


የሳቅኩት ሳቅ፣አቤት ያፈሰስኩት የደስታ እንባ ….፡፡

‹‹እኔ ደግሞ ይህቺን ዓይነ-ስውር እስከመቼ ስመራ እኖራለሁ? ብለህ ችላ ያልከኝ መስሎኝ፡፡››

‹‹አንቺ እኮ መቼም መሪ ፈልገሽ አታውቂም ፤ ከማውቃቸው ዓይናማ ሴቶች ሁሉ በተሻለ ሁኔታ ጠንካራ ነሽ ፡፡ ደግሞ መሪ የሚያስፈልገው ዓይኑ ለታወረ ሰው ሳይሆን ልቡ ለታወረ ሰው ነው፡፡››

‹‹..እና ከዛሬ ጀምሮ ፍቅረኛሞች ነን አይደል?

‹‹ወደፊት አልፀፀትም ካልሽ አዎ የእኔ ፍቅር፡፡››

‹‹ምንም የሚያፀፅተኝ ነገር የለም፤ የአለም ቁጥር አንድ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴት የመሆን እድሉ እንኳን ቢኖረኝ አንተን አይተካልኝም..አንተን የሚያሳጣኝ ከሆነ በህይወቴ ምንም የማልሰዋው እና የማልተወው ነገር የለም፡፡››

ያንን በተስማማንበት ቀን አልጋ ለየን …፡፡

‹‹ምነው?›› ብዬ ስጠይቀው፡፡

>ብሎ አሾፈብኝ ፡፡
ያቀረበው የመከራከሪያ ሀሳብ ባያሳምነኝም ዋናው በዓለም ላይ እጅግ የማፈቅረውን ሰው ለዘላለም የራሴ እንዲሆን ማሳመኔ ነው ፤ሌላው የቀናት ጉዳይ ነው ይደረስበታል ብዬ ተፅናናሁና የደስታ ኑሮዬን መኖር ቀጠልኩ፡፡

ከዛ ያሬድ የአራት ዓመት ትምህርቴን ጨርሼ ለመመረቅ አንድ ወር ሲቀረኝ ..ምርቃቴንና ሰርጌን በአንድ ቀን ለማድረግ ዝግጅት ሁሉ ጀምረን ሳለ ደፎ ለሁለት ቀን ፊልድ አለቃውን ይዞ ወደ ደብረማርቆስ ሄደ፡፡እንዳለውም በሁለተኛው ቀን ተመሶ መጣ….ግን እንዴት ሆኖ እንደመጣ ታውቃለህ.... ? በሳጥን ታሽጎ እሬሳ ሆኖ…. ሙሽራዬን የመኪና አደጋ እስከመጨረሻው ቀማኝ እልሀለው፡፡

ታዲዬስ ከተቀመጠበት ተነሳና ከጎኗ ካለው ወንበር ላይ ተቀመጠ ፡፡እጁን በትከሻዋ አዙሮ አቀፋት እና ወደ ደረቱ አስጠግቶ ጉያው ሸጎጣት....


#ትንግርት


#ክፍል_አርባ_አምስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


እሁድ ቀን ነው 8 ሰአት ከካባቢ ደደፎ እንግዳ ይዞ ቤት መጣ፤ምን ዓይነት እንግዳ መሰለህ ? ... የሚያስጠላ ቀፋፊ ድምፅ ያላት፤ሾካካ አረማመድ የምትራመድ፤ባለ ሻካራ ድምፅ ሴት፡፡ ምን አልባት ያልኳትን አይነት ሴት ላትሆን ትችላለች፤በወቅቱ ለእኔ የተሰማኝ ግን እንደዛ ዓይነት ሴት እንደሆነች ነበር፡፡››

‹‹ኪያ ተዋወቂያት ፀዳለ ትባላለች..ፀዳለ እሷ ደግሞ ጽዮን ትባላለች እህቴ ነች፡፡ ››አላት፡፡

‹‹ተዋወቅንና ቁጭ አሉ…ውይ ኪያ ሳልነግርሽ ….ከፀዳለ ጋር አንድ መስሪያ ቤት ነው
የምንሰራው አሁን ግን….››ብሎ ንግግሩን አንጠልጥሎ ተወው፡
እኔም የልጅቷን ድምጽ ከሰማሁበት ደቂቃ ጀምሮ የሆነ ቅፍፍ ብሎኛልና‹‹አሁን ግን ምን…?››ብዬ ጠየቅኩት፡፡

‹‹ፍቅረኛዬ ሆናለች….እሺ ካለቺኝ በቅርብ እንጋባና ትቀላቀለናለች፡፡››አለኝ፡፡

መሀከል ወለል ላይ ቆሜ ነበር የሚያወራውን ሳዳምጥ የነበረው ... ወዲያው ግን ብዥ አለብኝ...ልቤን ሲያጥወለውለኝ ወደ ጓዳ ለመግባት ቀኝ እግሬን አነሳሁና መልሼ መሬት ለማሳረፍ ስሞክር መሬቱ የጥልቅ ገደል ያህል በኪሎ ሜትሮች ራቀብኝ፡፡ከዛ ዥው ብዬ ወደ ኃላዬ እየወደቅኩ ሳለ ደፎ ተንደርድሮ ከመሬቱ ከመላተሜ በፊት ሲታደገኝ..ከዛ ማንነቴም ሲጠፋኝ፡፡

ከደቂቃዎች በኃላ ስነቃ ደደፎ በድንጋጤ በፎጣ ውሃ እየነከረ እራሴን ልቤን ሲያቀዘቅዝልኛል ሴትዬዋ በዛ ቀፋፊ ድምጿ < አይዞህ ይሻላታል …አትደንግጥ፡፡›› እያለች ስታፅናናው ሰማሁ ፡፡ የእሷን ድምጽ
የማልሰማበት የት ልሂድ....? ደሞ ያበሳጨኝ የእኔ መታመም ሳይሆን የእሱ ለእኔ መጨነቅ ስላስጨነቃት ነበር ፡፡ እንደምንም አንደበቴን አላቅቄ‹‹.. ደፍ ሰላም ነኝ እራሴን ስላመመኝ ትንሽ ልተኛበት ..ይተወኛል› አልኩት፡፡

በመናገሬ ደስ እያለው ብርድልብሱን አለባበሰኝና ያቺን ባለቀፋፊ ድምፅ ሴት
ከመኝታ ቤት ይዞልኝ ወጣ፡፡እኔም የምፈልገው

እሱን ነበር፡፡ግን ምን ነካኝ….?የእሱ ፍቅረኛ
መያዝ እኔን እራሴን እስክስት ድረስ እንዴት
ሊያደርሰኝ ቻለ... ? ለእኔ ወንድሜ አይደል እንዴ..?አይደለም፡፡ ለእኔ ዘመዴ አይደለ እንዴ….? አይደለም፤እና አፈቅረዋለው ማለት ነው...?. መጠርጠሩስ፡፡ በቃ የልቤን ጥያቄ እና የአዕምሮዬን መልስ ስሰማ ሰማይ ምድሩ
ተደበላለቀብኝ፤ምን ይሻለኛል….?እንዴት ነው
ለዓመታት እሱን አቅፌ የሰላም እንቅልፍ
በተኛሁበት አልጋ ላይ ሌላ ሴት መጥታ እኔን
ሳሎን ወዳለው ፍራሽ ላይ ወርውራኝ እሷ እሱን
አቅፋ የምትተኛው…? በፍፅም አይሆንም፡፡
ይሄንን ቤት ለቅቄ መውጣት አለብኝ…? ወጥቼ ወዴት ነው የምሄደው? አለሜ ጠቅላላ ..ዘመዴ መሸሸጊያ እሱው ነው፡፡ ቢሆንም እሱን ከሌላ ሴት ጋር እያየሁ መኖር አልችልም ::

መቻል አለብሽ... እሱ እኮ እንደ ታናሽ እህቱ አይቶሽ ነው በህይወቱ ሙሉ ሲንከባከብሽ የኖረው ፡፡ታዲያ ውለታውን እንዲህ ነው እንዴ የምትመልሺው..… ?ዕድሜሽን በሙሉ ያንን ሁሉ በምንም የማይለካ ደስታ ሲመግብሽ ቆይቶ ዛሬ አንቺ ውለታውን እንዲህ ነው የምትመልሺው...? የእሱ ደስታ እንዴት ነው እንዲህ ሊያበሰጭሽ የቻለው..? እስከመቼ ሳያፈቅር እና ሳያገባ ላንቺ ሲል ተቆራምዶ ይኖራል…?››አይምሮዬና ልቤ ጦርነት ጀመሩ ግን ቆረጥኩ… በቃ፡፡

ቢያንስ አሁን ትልቅ ሰው ነኝ.. ከአያቴ ቤት ኪራይ ለዓመታት የተጠራቀመልኝ 5ዐሺ ብር ባንክ ቤት አለኝ ፤ በዛ ላይ ከቸገረኝ የአያቴን ቤት እሸጠዋለሁ፡፡ያ ደግሞ ትምህርቴን እስክጨርስ በርግጠኝነት ይበቃኛል.. ለጊዜው
የሚከራይ ቤት እስካገኝ ጓደኞቼ ጋር አርፋለሁ ፡፡ከዚህ ቤት ግን ዛሬውኑ መልቀቅ አለብኝ፡፡ አዎ አሁን ሊሸኛት ሄዷል ፤ ከመምጣቱ በፊት መፍጠን አለብኝ > አልኩና ከተኛሁበት ተነስቼ ሻንጣዬን በዳበሳ ፈለግኩና ፊት ለፊት ያገኘሁትን እና መሰብሰብ የቻልኳቸውን የእኔ የሆኑ እቃዎችን ከታተትኩና ሻንጣዬን በአንድ እጅ የገንዘብ ቦርሳዬን በትከሻዬ፤ ዘንጌን በሌላው እጄ ይዤ ከመኝታ ቤት አልፌ የሳሎኑን ደጃፋ በጥበብ ተሸግሬ ቤቱን ሙሉ በሙሉ ለቅቄ ልወጣ ስል‹‹እንዴ ወዴት ነው?››የሚለው የደደፎ ድምጽ አንዱን እገሬን በአየር ላይ ተንከርፍፎ እንዲቀር አደረገው፡፡ ተንደርድሮ መጣና ክንዴን አጥብቆ ያዘኝ፡፡

‹‹ኪያ ምን እየሰራሽ ነው?›› ሲጠይቀኝ ሰውነቱ ሁሉ እየተንቀጠቀጠ እንደሆነ በያዘኝ እጆቹ ንዝረት ተረዳሁ፤ አሳዘነኝ፡፡

‹‹ንገሪኝ እንጂ የት ነው?››

‹‹በቃ ልታገባ አይደል እንዴ? ቤቱን ልለቅልህ ነዋ፡፡››

በጥፊ አላሰኝ... አቤት የደነገጥኩት ድንጋጤ ..አቤት የተደሰትኩት መደሰት..አቤት የተሰማኝ ቅብዥርዥር ስሜት፡፡ ከተዋወቅንበት ቀን አንስቶ እንኳን ሊመታኝ ክፉ ቃል እንኳን ተናግሮኝ አያውቅም ...የደነገጥኩት ለዛ ነው፡፡ የተደሰትኩት ደግሞ የመታኝ ስለሚፈልገኝ ነው የሚል ስሜት ስለተሰማኝ ነበር፡፡ከዛ ቦርሳውንም ሻንጣውንም ነጥቆኝ እየገፈተረ ወደ ውስጥ አስገባኝ እና ወንበር ላይ ገፍትሮ አስቀመጠኝ..››

‹‹እየሰማኸኝ ነው አይደል ታዲ?››

‹‹በጣም እየሰማሁሽ ነው.፡፡ በሰው ወሬ መካከል እሺ ..ከዛስ ..ምናምን ማለት ስለማልወድ ነው..፡፡››

ከዛ እየተንዘረዘረ‹‹እኔ አንቺን ከቤት አስወጥቼ ነው ሚስት የማገባው?እንዴት እንዴት ነው የምታስቢው…? በቀላሉ እንድታገባ አልፈልግም አትይኝም?››

‹‹እንድታገባ አልፈልግም ብልህ እሺ ትለኛለህ?››

‹‹በትክክል እልሻለው፡፡››

‹‹እንግዲያው እንድታገባ አልፈልግም..አንተን ከሌላ ሴት ጋር እንዳይህ ፈጽሞ አልፈልግም››አልኩት፡፡ ፀጥ አለኝ ፡፡ ፀጥታው አስር ለሚሆኑ ደቂቃዎች ነው የቆየው... ግን የአስር ሺ አመትን ያህል ርዝመት ነበረው፡፡ ግራ የሚያጋባ የሚያስደነግጥ ፀጥታ….ነፍስን የሚያፍን ፀጥታ እንደምንም ያለኝን ጉልበት አጠራቅሜ‹‹ይሄው አላልኩህም… እሺ አትልም አላልኩህም .. ?እኔ እዚህ ቤት መኖር አልፈልግም በቃ…››ተንጣጣሁበት፡፡

‹‹ባክሽ ዝም በይ፤እሺ ብዬሻለሁ፤በቃ ትቼያታለሁ፡፡ ፍቅረኛዬም እንዳልሆነች
እንደማላገባትም ነገ እነግራታለሁ...አሁን ለምቦጭሽን አትጣይብኝ፡፡›› አለኝ፡፡

ከተቀመጥኩበት ተንደርድሬ በመነሳት ተጠምጥሜበት ልስመው ስል አንድ ኩርሲ ነገር አደናቀፈኝና ልዘረገፍ ስል በአየር ላይ ተቀበልኝ ...በአንድ ቀን ለሁለተኛ ጊዜ ከመፈጥፈጥ ታደገኝ፡፡ ለዛም ምስጋና እንዲሆንልኝ ወደራሴ ጎትቼ ጉንጩን ሳምኩት…፡፡

ከዛ .... ከአንድ ወር በኋላ ነበር ነገሩን አንስተን ዳግም የተነጋገርንበት፡፡

እንዲሁ ከመሬት ተነስቶ‹‹ኪያ ታፈቅሪኛለሽ እንዴ?›› አለኝ፡፡

‹‹አንተ ምን ይመስልሀል?››

‹‹እኔ እንጃ ግራ ገብቶኝ እኮ ነው የጠየቅኩሽ .. ምን አልባት አንቺ ድሮ አይንሽ በሚያይበት ወቅት ጎረምሳ ስለነበርኩ አሁንም ልክ እንደዛው አድርገሽ ስለሺኝ ተሸውደሽ  እንዳይሆን ....ቢያንስ ከአስር አመት በላይ በዕድሜ እበልጥሻለሁ... አረጅብሻለሁ፡፡››

‹‹እንጂ ታፈቅረኝ ነበር.?

‹‹.እኔማ በጣም ነው ማፈቅርሽ….ግን ደግሞ ሳስብ በብዙ ነገር የምገባሽ አይደለሁም፡፡ እኔ አንድ ተራ ሹፌር ነኝ..አንቺ ደግሞ ነገ ብሩህ ሕይወት የሚጠብቅሽ በጣም ዝነኛ የመሆን ዕድል ያለሽ ሴት ነሽ፡፡ አየሽ ነገ ይሄ በውለታ አስሯት አታሏት ህይወቷን አበላሸባት፤ደግሞ ሽማግሌ እኮ ነው!!! በዛ ላይ፤ እያሉ እንዲሳለቁብኝ እና አንቺም ወይኔ ብለሽ እንድትፀፀቺ ስለማልፈልግ እንጂ እኔማ መች አንቺን ሳላፈቅር ቀርቼ አውቃለሁ፡፡››ብሎ ቁጭ አለ፡፡… አቤት የዛን ቀን የተደሰትኩት መደሰት፣አቤት


‹‹እሱ እቴ ብጠብቅ..አንድ ወር...ሁለት ወር...ሶስት ወር....በስጋት ልሞት .....በየቀኑ የሆነ ኪሎ ያህል እየቀነስኩ ሄድኩ...እንዳልጠይቀው ደግሞ የሴትነት ኩራቴ ተናነቀኝ...።ብቻ አንድ ተስፋ የሠጠኝ ነገር ቢኖር ከንፈሬን ከሳመበት ከልደት ቀኔ በኃላ አንድም ሴት እዛ ግቢ ደርሳ አታውቅም...እሱን ፍለጋ በራፉ አንኳኩተው ሲመጡ እንኳን "የለም በሉ" ብሎ ከበራፍ ያባርራቸው ነበር...።
ከአራት ወር ጭንቀት በኃላ ግን አንድ ቀን ማታ ከስራ ሲመለስ እኔ ነበርኩ በራፍ የከፈትኩለት።
‹‹እፈልግሽ ነበር እንኳን አገኘሁሽ››አለኝ።
‹‹ለምን?››
‹‹እቤቱን ልለቅ ነው››አለኝ፡፡ በእግሮቼ መቆም አቃተኝ። እጄን ዘረጋሁና የአጥሩን ግንብ ተደገፍኩ‹‹ምን አደረኩህ?ጓደኞቼ ሲሉ እንደነበሩ ጥለኸኝ ልትሄድ ነው››

ተንከትክቶ ሳቀ‹‹ምን ያስቅሀል?››
‹‹ገርመሺኝ ነዋ...ሳምንት ሽማግሌ ልልክ አዘጋጅቼያለሁ...ወዲያው እንድንጋባ ነው የምፈልገው።ስለዚህ የቤት ዕቃዎች መገዛዛት አለብኝ...አሁን ያለሁባት ክፍል ደግሞ አትበቃም..ሶስት ክፍል ቤት ተከራይቼ ቀብድ ከፍያለሁ...ቀድሜ ወጣና ዕቃ አሟልቼና እቤቱን አደራጅቼ እጠብቅሻለሁ። አንቺ ደግሞ ከሶስት ወይም ከአራት ወር በኃላ ጠቅልለሽ ትመጪያለሽ..እስከዛ አንዳንድ ቀን ሹልክ እያልሽ ተመጪና አንዳንድ ነገሮችን ታስተካክያለሽ"
ተንደርድሬ ሄጄ ተጠመጠምኩበት...ግንባሩን ጉንጩን እየሳምኩ‹‹በጣም ነው የማፈቅርህ እሺ...ግን ከዚህ ቤት አትወጣም...አያቴ በሽተኛ እንደሆነች ታውቃለህ ከተጋባን በኃላም የምንኖረው እዚሁ ነው...ዕቃም መግዛት አይጠበቅብህም።››
በስንት ጭቅጭቅ ልመናና ለቅሶ ሀሳብን አስቀየርኩትና የእኛን ጊቢ ለቆ መውጣቱን ሀሳብ ሰረዘው።አንድ ወር ጠበቀና አያቴ ጋር ሽማጊሌ ላከ...ወንድሞቼ አበድ..ወልጆቼ እንዴት ታስቦ ብቸኛ ሴት ልጃችንን አንድ ስሜቱን መቆጣጠር ለማይችል ሰው  አሳልፈን አንሰጥም..አሉ።አያቴ ብቻ በምን ያህል መጠን  እንደማፈቅረው ስለምታውቅ ገለልተኛ አቋም  ያዘች።
ለማንኛውም መጨረሻ  እሱን ካላገባሁ በህይወት መኖር እንደማልፈልግ ቁርጥ ያለውን ውሳኔዬን ስነግራቸው  ባይዋጥላቸውም ያው ስለሚሳሱልኝ ብቻ እንዳገባው ፈቀድልኝ።ይሄው በጋብቻም አስር አመት ኖርን 3 የሚያማምሩ ልጆችም ወለድን እልሀለው››በማለት ገራሚ የፍቅር ታሪኳን  አጠናቀቀች።
መወሰን አለብኝ….ይህ ሰውዬ ከዚህ በላይ በህይወት መቆየት የለበትም..ለእሱ ርህራሄ የማሳይበት ምንም አይነት ምክንያት እየታየኝ አይደለም…፡፡እሷ እራሷ በቀናቶቹ ውስጥ ቆራርጣ በነገረችኝ ታሪክ ውስጥ እሱ የእኩይ አፍቃሪን ገፅ ባህሪ ወክሎ ነው ያገኘሁት፡፡ ይበልጥ እንድጨክንበት የሚያደርግ እንጂ እንድራራለት የሚያደርግ አንድ ገጽ የህይወት ታሪክ የለውም፡፡ምን አልባት እሱ መኖር አለበት እንኳን ቢበባል አንድ ሊያኖረው የሚችል መክንያት የሶስት ልጆቾ አባት መሆኑ ነው፡፡ለዛም ቢሆን እኔ ኃላፊነቱን ወስዳለሁ…በህይወት እስከኖርኩ ልጆቹን እንደገዛ ልጆቸ አድርጌ አሳድጋለሁ..በቃ ላደርግ የምችለው ያንን ብቻ ነው፡፡
‹‹የሚገርም ታሪክ ነው የነገርሽኝ..አሁን መስፍኔን የምወጋው አንድ መርፌ አለ እሱን ልውጋውና ልሄድ›› ብያት ከመቀመጫዬ ተነሳሁ..
‹‹ጥሩ እንደውም እኔም የሆነ ጉዳይ ስላለኝ አብረን  እወጣለን እስከዛ ልዘገጃጅ›› አለችኝና ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡በኮሪደሩ እየተጓዝን ፊትና ኃላ ወደውስጠኞቹ ክፍሎች መራመድ ጀመርን፡፡ እኔ የመስፍኔን መኝታ ክፍል ከፍቼ ስገባ እሷ ወደሚቀጥለው ክፍል መራመዷን ቀጠለች…እንደገባሁ ክፍሉን ከውስጥ ቀረቀርኩት…ምን ማድረጌ ነው…?ቀረቀርኩ አልቀረቀርኩ የማደርገውን ነገር ማንም ቢያይ ምን የሚያመጣው ነገር የለም…?እኔ ለዚህ ሰው የምሰጠውን መድሀኒት  እሱን ለማዳን እንጂ ለመግደል ይሆናል?ብሎ የሚጠረጥር ሰው እንዴት ሊኖር ይችላል ?፡፡ይሄንን የሚያውቀው የሰማይ አምላክ ብቻ ነው፡፡እሱን ደግሞ በራፉን በመዝጋት የምሰራውን ልሸሽገው አልችልም፡፡…..
ከኪሴ ውስጥ ሁለት ብልቃጦች አወጣሁና በስሪንጅ ከአንደኛው እየወሰድኩ ሌለኛው ውስጥ በመጨመር አዋሀድኩትና በመስፍን ክንድ ውስጥ ጨመርኩት…እነዚህ መድሀኒቶች ምንነታቸውን ልነግራችሁ አልችልም..ግን ያደረኩት የመስፍኔ አይነት ህመም ያለባቸው ሰዎች ፈፅሞ መውሰድ የሌለባቸው መድሀኔቶች ሲሆኑ አንደኛው ደግሞ መድሀኒቱ በሰውነቱ ውስጥ መግባቱን ፈጽሞ እንዳይታወቅ የሚያደርግ ነው….ሁሉን ነገር አጠናቅቄ የተጠቀምከባቸውን የመድሀኒት ብልቃጦች ኪሴ ውስጥ ጨመርኩና በቆምኩበት ፍዝዝ ብዬ በሽተኛውን እመለከተው ጀመር…
የድካም እንቅልፍ የተኛ ሰላማዊና ጤነኛ ሰው ነው ሚመስለው፡፡ያኔ እዚህ ጊቢ ብዙ ልጃገረዶችን በማመላለስ ስንት ቀናት የልዕልትን ልብ በቅናት እንደሸረካከተው አሰብኩ‹‹..በቃ ደህና ሁን ፡፡››አልኩና በራፍን ከፍቼ ስወጣ ልዕልትን ዝግጁ ሆና ሳሎን ስትጠብቀኝ አገኘኋት….በጭንቀት በተወጠረ ጨፍጋጊ ስሜት በእኔ መኪና ተያይዘን ከጊቢ ወጣን፡፡

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


እባክሽ አትሂጂ…..
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-15


///
ዛሬም እንደወትሮዬ  የተለመደው  ሱፐርማርኬት ጎራ ብዬ ለልጆቹ ቸኮሌት ለእሷ ደግሞ ትኩስ እንብጥ ፅጌረዳ አበባ ገዝቼ በሚንቀጠቀጥ ሰውነትና በራደ ልብ ጉዞዬን ቀጠልኩ።ሰራተኛዋ የውጩን በራፍ ከፈተችልኝና መኪናዬን ወደውስጥ በማስገባት  እንደተለመደው አበባውን እዛው ባለበት ቦታ ትቼ የልጆቹን  ቸኮሌት ይዤ ወደውስጥ ስገባ ልዕልትን ሳሎን ሶፋ ላይ ቁጭ ብላ ልጇን ጡት እያጠባች አገኘኋት...ገና ሳሎኑን ከፍቼ ስገባ በአስደንጋጭና ብርሀናዊ ፈገግታ ተቀበለችኝ...እየተንደረደርኩ ወደእሷ ቀረብኩና በተቀመጠችበት ሳላምታ ሰጥቼያት እያጠባች ያለችውን  ልጅ ግንባር ስሜ ከፊት ለፊቷ ተቀመጥኩ።
‹‹ዶ/ር ይሄን ቸኮሌት አቁም ማለት ሰለቸኝ እኮ››
‹‹ከሰለቸሽ  አቁም ማለቱን  አቁሚያ..››
ፈገግ አለች‹‹በጣም እልከኛና የሠው ነገር የማትሰማ ሰው ነህ።››
‹‹ከዚህ በፊት እንዲህ አይነት አስተያየት ማንም ሰጥቶኝ አያውቅም።››
‹‹እንደአንተ አይነት የተሳካለትን ስፔሻል ዶ/ር ን ማን ነው ደፍሮ ተሳስተሀል የሚለው?..ስትሳሳት ቢያዩህ እራሱ አይ የገዛ አይኔ ነው የተሳሳተው ብለው አይናቸውን ነው የሚጨፍኑት።››ብላ አሳቀችኝ።
‹‹እሺ መስፍን እንዴት ነው?››
‹‹ሰላም ነው...አሁን ሰውነቱን አጣጥቤው  ተኝቷል...ትቸኩላለህ እንዴ?››
‹‹አይ ...አረ አልቸኩልም...ግን ማልቸኩለው ያንን ታሪክሽን ምትነግሪኝ ከሆነ ነው።››
‹‹የቱን?››
‹‹እየሰሰትሽ እና እየቆነጣጠርሽ የምትነግሪኝን የፍቅር ታሪክ ነዋ።››
‹‹እ...እንግዲያው ትንሽ ታገስ መጣሁ›› ብላ ልጆን አንጠልጥላ ከተቀመጠችበት  ተነሳች።ስትነሳ  ልጇ አፍ ውስጥ ተመስጎ የነበረው ጡቷ አፈትልኮ ወጣና  ሙሉ በሙሉ ለእይታ ተጋለጠ...ተንደርድረህ በመሄድ ለቀም አድርገህ ያዝና አፍህ ውስጥ ጨምረው የሚል ስሜት ተናነቀኝ።እንደምንም ስሜቴን ተቆጣጠርኩ....።እሷ ስለእኔ የስሜት መደፍረስ ልብ ሳትል  ጡቷን በግራ እጇ ወደውስጥ መለሰች እና ልጇን  ይዛ ከፊቴ ዞር አለች ...እኔም ተንፈስ አልኩና ስሜቴን ወደነበረበት ለመመለስ ጥረት አደርግ ጀመር።ከ5 ደቂቃ በኃላ ልጇን አስቀምጣ  አንድ ቢራ  ከብርጭቆና ከመክፈቻው ጋር  አመጣችና ከፍታ ከፊት ለፊቴ ቁጭ አለች።
‹‹እሺ ዶ/ር እንዴት ነህ..?››
‹‹ያው እንደምታይኝ ደህና ነኝ...ይልቅ ጊዜ ሳታባክኚ ወደታሪክሽ ግቢ።››
ፈገግ አለችና‹‹እሺ የት ላይ ነበር ያቆምኩት?››
‹‹ቤትሽን ተከራይቶ እቃውን ካስገባ……። ››
‹‹አዎ ..ገባ ።ጥዋት ወደስራ ሲሄድና ማታ ከስራ ሲገባ እየጠበቅኩ እሱን ማየት ጀመርኩ።ባንክ ስለሚሰራ ዘወትር ሙሉ ልብስ ለብሶ ሽክ እንዳለ ነበር...።››
‹‹ቆይ የእውነት..ሚስት አልነበረው? ››
‹‹አረ የምን ሚስት...ገና ሮጦ ያልጠገበ ነበር...ሚስት አልነበረውም...ግን በየሶስት አራት ቀኑ ነበር የተለያዩ ሴቶችን የሚያመላልሰው ።አንዴ የመጣች ሴት ተመልሳ ሌላ ጊዜ አትመጣም።..ያንን ሳይ ይበልጥ እያሳዘነኝ መጣ...?››
‹‹እያሳዘነኝ...?››
‹‹አዎ...እያሳዘነኝ።መቼስ ሰው ወዶ እንደዛ አይሆንም..።አንድ የምትመቸውና የምትረዳው ሴት ቢያገኝ  እንደዚህ ከዚችም ከዛችም ጋር አይንገላታም ነበር ብዬ አሰብኩና እንዴት እንደምረዳው ማሰላሰል ጀመርኩ...።በዚህ መካከል የራሴን ጓደኛ እኔ ጋር ስትመላለስ አያትና ቀጥታ ወደእኔ መጥቶ  ‹‹ጓደኛሽን አጠብሺኝ. ..ወድጄታለሁ።››አለኝ…በጣም ደነገጥኩ...‹‹እሺ ጠይቅልሀለው ..ግን ታገባታለህ?››ስል የሞት ሞቴን ጠየቅኩት።

ፍርጥም ብሎ ‹‹ምን ነካሽ ....እንዴት ታገባታለህ ብለሽ ትጠይቂኛለሽ?››አለኝ።
የውስጤን በውስጤ አፍኜ ‹‹ከወደድካት ብታገባት ምን አለበት..?››አልኩት።
‹‹ቆይ አንቺ ትወጂኝ የለ እንዴ?››ሲል ግራ አጋቢ ጥያቄ ጠየቀኝ።
ደነገጥኩ...ሰውነቴ ሁሉ ሲንቀጠቀጥ ይታወቀኝ ነበር...አንገቴን ደፍቼ‹‹ እሱማ አዎ...እወድሀለው››ስል መለስኩለት።
‹‹እሺ ስንት አመትሽ ነው?››
‹‹17 ››
‹‹በቃ ልክ አስራ ስምንት ሲሞላሽ ሽማግሌ ልካለሁ።››አለኝ።
‹‹የምን ሽማግሌ?››ስል መልሼ ጠየቅኩት።
‹‹ላገባሽ ነዋ...ምነው አንቺ ልታገቢኝ አትፈልጊም?››
‹‹እሱማ ፈልጋለው።››
‹‹በቃ ዕድሜሽ እንደሞላ አገባሻለሁ...እስከዛ ግን ከሌሎች ሴቶች ጋር እደሰታለሁ..አይከፋሽም አይደል?››
‹‹አረ አይሰከፋኝም።››አልኩት የእውነቱን ግን ጥልቅ ድረስ ልቤን በሚሸረካክት መልኩ ነበር የሚከፋኝ ።ግን እሱን ካስደሰተው እኔ ብሰቃይም ችግር የለውም ብዬ ወሰንኩ..፡፡
‹‹እሺ በቃ እንዳልክ...አሁን 17 ዓመት ከሶስት ወሬ ነው።ከዘጠኝ ወር በኃላ ትልካለህ።››አልኩት።
‹‹ተስማምቼለሁ...አሁን ግን እንደአልኩሽ ጓደኛሽን አሳምነሽ አምጪልኝ››አለች።
እንዳለኝም ሳምንት ሙሉ ለምኜና እግሯ ላይ ወድቄ እቤቱ ድረስ አመጣሁለት ...።ከዛ በኃላም እሱ ለሚያመጣቸው ሴቶች ሻይ እያፈላሁ… የሚፈልጉትን ነገር እያቀረብኩ እየተንከባከብኩ ስሸኝ...18 ዓመት እስኪሞላኝ እያንዳንዶን ቀን አልደርስ ብላኝ ስቆጥር  ከረምኩ።..ጓደኞቼ ይሄ ሸርሙጣ ውሸቱን ነው ዞር ብሎ አያይሽም ሲሉኝ ...እኔም እውነት አፍንጫሽን ላሺ ይለኝ ይሆን እንዴ ? ብዬ ስሰጋ አይደርስ  የለ ደረሰ...እሱንም ለማስታወስ እንዲያግዘኝ አያቴን አሳመንኩና የ18 ዓመት ልደቴን ድል አድርጌ ደገስኩ..።.ወንድሞቼ ዘመድ ወዳጅ ፤ጓጀኞቼ አንድ ሰው አልቀረም...መለስተኛ ሰርግ በለው፡፡በእለቱ  ዝግጅቱ ላይ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ቢኖርም ምንም አላለኝም...።እያንዳንድ ሰው የራሱን ስጦታ ሲሰጠኝ ቢውልም እኔ ግን ከእሱ የሆነ  አይነት ስጦታ አዘጋጅቶልኝ ይሆን ብዬ እጅ እጅን ሳይ ነበር የዋልኩት...እሱ እቴ ምንም እንዳለሰበበት ሳውቅ ከፋኝ...ጓደኞቼ ሲያስፈራሩኝ የነበረው እውነት ይሆን እንዴ...?የሚል ስጋት መተንፈስ እንዳልችል ጉሮሮዬን አነቀው። እንዲሁ ስጨነቅ ውዬ ማታ አካባቢ ለሆነ ጉዳይ ወደጓሮ ስሄድ ከየት መጣ ሳልለው አፈፍ አድርጎ ወደቤቱ አስገባኝ...።
በጣም ደነገጥኩ...እዛ ቤት ከገባ አመት ቢያልፈውም አንድ ቀን እንዲህ አድርጎ አያውቅም። በራፋን ቀረቀረና ከግድግዳ ጋር አጣብቆኝ ከንፈሩን ከንፈሬ ላይ አጣበቀው..መተንፈስ አቃተኝ...፡፡በአየር ላይ ሁሉ የምንሳፈፍ ሁሉ መሠለኝ..።ሲረበሽና ሲናወጥ የሠነበተው ውስጤ በደስታ ሲረሰርስ ተሰማኝ...።ምን ያህል ደቂቃ ወይም ሰዓት በመሳሳም እንዳሳለፍን አላውቅም ግን ድንገት ከንፈሩን ከከንፈሬ አላቀቀና በራፉን ከፍቶ..
‹‹የእኔ ፍቅር እንኳንም 18  ዓመት የልደት በአልሽ አደረሰሽ...መልካም ልደት...ይሄ መሳም እንደልደት ስጦታ ተደርጎ ይወሰድልኝ››አለና የመገፍተር ያህል ከደነዘዝኩበት አንቀሳቅሶ ከክፍሉ አስወጣኝና እሱ እዛው ውስጥ ቀርቶ በራፍን ቀረቀረብኝ..።.ድንዛዜዬ በቀላሉ ጥሎኝ ሊሄድ አልቻለም...።ከቤቱ ባያስወጣኝና ለዘለአለምም መሳሙን ባያቋርጥ ደስ ይለኝ ነበር...። እንደምንም በድኔን እየጓተትኩ ወደቤቴ ተመለስኩ..።የእለቱ ዝግጅትም በዛው ተጠናቀቀ።
‹‹እና  ሽማግሌ ላከ?››እኔ ነኝ ጠያቂው።

Показано 20 последних публикаций.