አርሰናል ኬፓን እንዴት ለማስፈረም አሰበ ?
ኬፓ አሪዛባላጋ በውሉ ያለው አነስተኛ የኮንትራት ማፍረሻ ክፍያ ምክንያት የተለያዩ አማራጮች እንደሚቀርቡለት ተጠብቆ ነበር።
በአርሰናል ቤት የቡድኑን ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያን ሊያስቀምጥ እንደማይችል እንደሚረዳ የተገለጸው ኬፓ ይሁን እንጂ ለቦታው መፋለም እንደሚፈልግ ተነግሯል።
መድፈኞቹ ኬፓ በሪያል ማድሪድ እና ቼልሲ ቆይታው የቡድኑን ቁጥር 1 ግብ ጠባቂ የመርዳት አቅም እንዳለው አሳይቷል ብለው እንደሚያምኑ ተነግሯል።
ኬፓ አሪዛባላጋ ከዚህ በፊት በሁለቱ ክለቦች ኤድዋርድ ሜንዲ እና አንድሬ ሉኒንን እየተካ ሲያገለግል እንደነበር የሚታወስ ነው።
#𝗘𝗣𝗟 𝗘𝗧𝗛𝗜𝗢𝗣𝗜𝗔
@PREMIER_LIGU | #𝗘𝗣𝗟