የሞቀ ከተማ ጥለን ጫካ የገባነው ዝንጀሮ ልናግድ አይደለም‼️
ንፁህ ልብስ አጥተን አዳፋና የተቦጫጨቀ ያጠለቅነው ወጣትነታችንን ያጣነው ተስፋም ስለቆረጥን አይደለም። በእኛ ትውልድ ያጣነውን ተስፋ በቀጣዩ ትውልድ እንዳይደገም ብለን ነው እንጂ።
የቀመልነው የቀጨምነው የነፃነት ዋጋው ስለገባን እንጂ እንደ ማንኛውም ወጣት ጠፍቶንም አይደለም።
የተራብነው የተጠማነው የወንዝና የኩሬ ውሃ የጠጣነው ደረቅ ብስኩትና ቆሎ በልተን ውለን የምናድረው መገርጣት ፈልገን ሳይሆን ነፃነት ከዳቦ በላይ እንደሆነ ስለገባንም ጭምር ነው።
እስርን ግርፍን ሞትን የናቅነው መኖር ስላልፈለግን ሳይሆን በእኛ መንገላታት ቁስልና ሞት መዳን ያለበት እጅግ በጣም የብዙ ህዝብ ልጆች ስለሆንን ብቻ ነው::
አሁን ትግል ብለን በረሃ የወረድነው በየጫካው እንደ አራዊት በደረስንበት የምናድረው የመንግስትን ስርዓት ለማስጠበቅ ሳይሆን ለራሳችን ህልውና ትግል ለመጀመርና ነፃነታችንን በደማችንና በክንዳችን ልናውጅ ህዝባችንንም አንገቱን ቀና እንዲያረግ እኛ ሞተን ትውልድ ይዳን ከሚል ትልቅ መርህ ቃላችን ነው።
እናሸንፋለን ስንል በቃ እናቸንፋለን ማለታችንም ነው::
ኃይላችን ያለው "ፋኖ" ከሚለው ትልቁ ስማችን ላይ ነው
ሲሳይ ሳታናው
ለተጨማሪ መረጃዎቻችን👇
𝙩𝙚𝙡𝙚𝙜𝙧𝙖𝙢:-👇
https://t.me/+SLQ8WQR1oKDGWBY𝙛𝙖𝙘𝙚𝙗𝙤𝙤𝙠፦
https://www.facebook.com/beteamharamediaa/𝙞𝙣𝙨𝙩𝙖𝙜𝙧𝙖𝙢:-👇
https://instagram.com/beteamharamedia?
𝙩𝙬𝙞𝙩𝙩𝙚𝙧:-👇
http://twitter.com/Beteamharamedia𝙩𝙞𝙠𝙩𝙤𝙠:- 👇
@beteamaharamedia' rel='nofollow'>tiktok.com/
@beteamaharamedia𝙮𝙤𝙪𝙩𝙪𝙗𝙚:-👇
@beteamharamedia1475' rel='nofollow'>
https://youtube.com/@beteamharamedia1475