የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ
ማክሰኞ ነሐሴ 23 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ከዛሬ ጀምሮ ለአንድ ወር የሚቆይ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋን ይፋ አድርጓል፡፡
ሚኒስቴሩ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ የዓለም ነዳጅ ዋጋ ከሚያዝያ ወር 2015 ጀምሮ እስከሰኔ ወር መጨረሻ ድረስ አንጻራዊ መረጋጋት እንደታየበት ገልጿል።
በዚህም፤ ላለፉት አራት ወራት በችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ለውጥ ሳይደረግ መቆየቱን አስታውሷል።
ሆኖም ግን የዓለም ነዳጅ ዋጋ ከሐምሌ ጀምሮ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እያሳየ በመምጣቱ ዋጋውን ማሻሻያ ማድረግ ማስፈለጉ ተገልጿል፡፡
በዚሁ መሰረት:-
1. ቤንዚን ----------ብር 74.85 በሊትር
2. ነጭ ናፍጣ -----------ብር 76.34 በሊትር
3. ኬሮሲን ብር ------------76.34 በሊትር
4. የአውሮፕላን ነዳጅ ---------ብር 68.58 በሊትር
5. ቀላል ጥቁር ናፍጣ -----------62.22 በሊትር
6. ከባድ ጥቁር ናፍጣ -----------61.07 በሊትር መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡
@cnn_amharic1@cnn_amharic1