የክርስትና እውነቶች


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


📖መጽሐፍ ቅዱሳዊ📖 የሆኑ መንፈሳዊ ጽሑፎችን የሚያገኙበት ቻናል ነው❗
📲Join/Subscribe📲 ብለው ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ!👥
↪Share↩ በማድረግም "የክርስትና እውነቶችን" ለወዳጅዎ ያጋሩ!👇
https://t.me/Cchristiantruth

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций




በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ወቅት የሚፈጠሩ ስህተቶች (ህጸጾች)፥
-----------------------------------------------------------

1) አማርኛ_ብቻ ህጸጽ (Amharic-only fallacy)

መጽሐፍ ቅዱስን በተርጎም ሂደት ውስጥ የቃላት ጥናት ስናደርግ የቃላት ጥናታችንን መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ቁንቁዋ መሆኑ ቀርቶ በአፍ መፍቻ ቁዋንቁዋችን ሲሆን፥ ይህ ህጸጽ ተፈጸመ እንላለን።

2)Root Fallacy

መጽሐፍ ቅዱስን በመተርጎም ሂደት ውስጥ የአንድን ቃል ፍቺ በዋናነት ቃሉ ከሚገኙበት አውድ ተነስቶ ለመረዳት ከመሞከር ይልቅ የቃሉ ስርዖ መሰረት (etymology) ላይ ብቻ ስናተኩር የሚፈጸም ህጸጽ ነው።

3) Time_Frame Fallacy

መጽሐፍ ቅዱስን በመተርጎም ሂደት ውስጥ ቃላት በዚህ ዘመን ያላቸውን ወቅታዊ ፍቺ ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ይዞ ገብቶ ፍቺ ለመስጠት በመሞከር የሚፈጸም ህጸጽ ነው።

4) Overload Fallacy

አንዳንድ ቃላት ከአንድ በላይ ትርጉም ሊኖራቸው ይችላል፥ በመሆኑም መጽሐፍ ቅዱስን በማጥናት ሂደት ውስጥ እያጠናን ባለው ንባባ ከአንድ በላይ ትርጉም ያለው ቃል ሲይጋጥመን የዛን ቃል ትክክለኛ ፍቺ ቃሉ ከሚገኝበት አውድ ተነስቶ ለመረዳት ከመሞከር ይልቅ ሁሉም የቃሉ አማራጭ ፍቺዎች ቃሉ በተገኘበት አውድ ሁሉ ውስጥ ይሰራሉ ብሎ ከማሰብ የሚመነጭ ህጸጽ ነው።

5) Word-count Fallacy

መጽሐፍ ቅዱስ በማጥናት ሂደት ውስጥ ቃላት በተገኙበት አውድ ሁሉ ሁል ጊዜ ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው ብሎ ከማሰብ የሚመጣ የህጸጽ አይነት ነው።

6) Word-concept Fallacy

ይህ የህጸጽ አይነት ተፈጸመ የሚባለው የአንድን ቃል ፍቺ በማጥናታችን ቃሉ የሚሸከመውስን ሃሳብ በሙሉ እንደ ተረዳን ስናስብ ነው።

ለምሳሌ፦ ቤተክርስቲያን በግሪኩ "ኤክሌሺያ" የሚለውን ቃል ሲወክል ትርጉሙም ለአንድ አላማ ተጠርቶ ተሰባሶ የወጣ ህዝብ ማለት ነው። ታዲያ ቤተክርስቲያን የሚለው ቃል ትርጉሙ ይህ መሆኑ ቢገባንም ቃሉ በተገኘበት ቦታ ሁሉ ይህንን ሃሳብ ይሸከማል ብሎ ማሰብ ከላይ የተገለጸውን ህጸጽ እንድንፈጽም ያደርገናል።

7) Selective-evidence Fallacy

መጽሕፍ ቅዱስን በማጥናት ሂደት ውስጥ የእኛን ሃሳብ ይደግፋል አልያም ያጎላል ብለን ያሰብነውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ ብቻ በመጠቀም በተቃራኒ ሃሳባችንን ያኮስስብናል ብለን የምናስበውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ ገሸሽ ስናደርግ ይህ ህጸጽ ይፈጠራል።

ለምሳሌ፦ ሰው መንፈስ ነው፥ ብሎ የሚያስብ ሰው የሰውን መንፈስነት ለማስረዳት መነሻ ማድረግ አለብኝ ብሎ የሚያስበው ከእግዚአብሔር መንፈስነት ነው። በመሆኑም ዘፍ.1፡26_27 ሰው በእግዚአብሔር መልክና አምሳል ተፈጠረ የሚለውን ንባብ በመፍታት ሂደት ዮሐ.4፡24 ሆነ 2ቆሮ 3፡17 የእግዚአብሔርን መንፈስነት የሚናገር በመሆኑ በዘፍ.1፡26_27 የእግዚአብሔር መልክና አምሳል የተባለው የእግዚአብሔር መንፈስነት ነው። ስለዚህም ሰው በእግዚአብሔር መልክና አምሳል ተፈጠረ ማለት መንፈስ ሆኖ መንፈስ ከሆነው እግዚአብሔር ተገኘ ማለት ነው ብለው ይደመድማሉ።
በግልጽ እንደምንመለከተው በዘፍ 1፡26_27 በሚገኘው ንባብ ውስጥ የሚገኘውን የእግዚአብሔር መልክና አምሳል የሚለውን ገለጻ በአውዱ ውስጥ ከመረዳት ይልቅ የእዚአብሔር መልክና አምሳሌ መንፈስነቱ ነው የሚል ቅደመ እሳቤ በመያዝ ይህንን የሚደግፉ እንደ ዮሐ 4ና 2ቆሮ 3 ያሉ ንባባትን ጥቅም ላይ ማዋል ከላይ ያለውን አይነት ህጸጽ እንዲፈጠር ምክንያት ይሆናል።

በመሆኑም መጽሐፍ ቅዱስን በማጥናት ሂደት ውስጥ ልንወስድ የሚገባው ከፍተኛ ጥንቃቄ የቃላትን ትርጉም ቃላቱ ከሚገኙበት አውድ ተነስቶ ለመረዳት መሞከር በእጅጉ ወሳኝ ነው።

ምንጭ፦ Scott Duvall. “Grasping God's Word: A Hands-On Approach to Reading, Interpreting, and Applying the Bible.”

✍️eyosias eyouel


Репост из: Isaiah 48 Apologetics
🚩 ክርስቶስ ሰው መሆኑ ፍጡር መሆኑን ያሳያልን?

ሙስሊም ወገኖቻችን ክርስቶስ ፍጡር ነው ለማለት የማይፈነቅሉት መሬት፥ የማይደረምሱት ተራራ የለም። እነዚህ ወገኖች፥ ለዚህ እይታ ዋነኛ ነጥባችን የሚሉት የክርስቶስ ሰውነት ነው

"ሰው ፍጡር ነው። ኢየሱስ ደግሞ ሰው ነው። ስለዚህ ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጡር ነው" ከሞላ ጎደል ሀሳባቸው ይህንን ይመስላል። ከመጽሐፍ ቅዱስም፥ ክርስቶስ ሰው ተብሎ የተጠራባቸውን ስፍራዎች በመጥቀስ ፍጡር ነው ለማለት ይሞክራሉ

▶ ነገር ይህ ድምዳሜ የክርስትናን አንኳር አስተምህሮዎች ካለማወቅ የመነጨ ሲሆን፥ መሰረታዊ የሆነ የአመክንዮ ችግር አለበት

በመጀመሪያ ደረጃ፥ አንድ ነገር ፍጡር መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ ከመነሳታችን በፊት፥ የፍጡርን (creation) ትርጉም ማወቅ አለብን

ፍጡር ማለት ካለመኖር ወደ መኖር የመጣ ነገር ማለት ነው። አንድ ነገር በህልውና ያልነበረበት ጊዜ ካለና በሆነ ጊዜና ወቅት ላይ ወደ ህልውና (existence) ከመጣ፥ ያ ነገር ፍጡር ይባላል

Create:- To bring into #existence out of #nothing, without the prior existence of the materials or elements used.

[ English Dictionary 2.0 ]

✒ መጽሐፍ ቅዱስም ፍጡር ማለት ቀድሞ በህልውና ያልነበረ ማለት እንደሆነ ያስተምራል

" ምድርን በመሠረትሁ ጊዜ አንተ ወዴት #ነበርህ?
(መጽሐፈ ኢዮብ 38:4)

" እርሱም። ለብዙ አሕዛብ አባት አደረግሁህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ለሙታን ሕይወት በሚሰጥ #የሌለውንም እንዳለ አድርጎ በሚጠራ ባመነበት በአምላክ ፊት የሁላችን አባት ነው።"
(ወደ ሮሜ ሰዎች 4:17)

ስለዚህ አንድ ነገር ፍጡር ሊባል የሚችለው፤ ካለመኖር ወደመኖር መምጣቱ ሲረጋገጥ ብቻ ነው። በሆነች ጊዜ እና ቅጽበት ላይ ወደ ህልውና መምጣቱ እስካልተረጋገጠ ድረስ ፍጡር ነው የሚያስብል ምንም ነገር የለም

▶ የፍጡርን ትርጉም በዚህ መልኩ ካየን ዘንድ ወደ ክርስቶስ እንምጣ። ክርስቶስ ሰው የተባለው ለምንድነው?

ክርስቶስ ሰው የተባለው ፍጡር ስለሆነ አይደለም። ክርስቶስ ሰው የተባለው ስለተሰገወ (incarnate) ስለሆነ ነው። ስጋዌ (incarnation) ማለት ቀድሞ ሰው ያልነበረ ነገር በሆነ ጊዜና ወቅት ላይ ሰው ሲሆን ማለት ነው።

Incarnate:- invested with bodily and especially human #nature and form

[ Merriam-Webster Dictionary ]

♦ አስተውሉ! አንድ አካል ተሰገወ ማለት፥ ያ ነገር ሰው ከመሆኑ በፊት በህልውና ነበር ማለት ነው። ሰው ሲሆን አይደለም የእርሱ ህልውና የጀመረው፥ ቀድሞውንም በህልውና ነበር

መጽሐፍ ቅዱስም ነገረ ስጋዌን በተመለከተ ብጥር ያለ ትምህርት አለው። ክርስቶስ ሰው የተባለው ስለተሰገወ እንጂ ካለመኖር ወደ መኖር ስለመጣ አይደለም

" ከሥጋ የተነሣ ስለ ደከመ ለሕግ ያልተቻለውን፥ እግዚአብሔር የገዛ #ልጁን በኃጢአተኛ #ሥጋ ምሳሌ በኃጢአትም ምክንያት ልኮ አድርጎአልና፤"
(ወደ ሮሜ ሰዎች 8:3)

" #ቃልም #ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1:14)

" እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ #በሥጋና_በደም እንዲሁ #ተካፈለ።"
(ወደ ዕብራውያን 2:14-15)

" ነገር ግን የባሪያን #መልክ #ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥"
(ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:7)

▶ ክርስቶስ ሰው መባሉ ስጋዌን ያስይዛል እንጂ በፍጹም ፍጡር ነው አያስብለውም። ከላይ ያየናቸው ጥቅሶች በሙሉ፥ ሰው ከመሆኑ በፊት ህልው እንደ ነበር የሚያሳዩ ጥቅሶች ናቸው።

ስለዚህ ኢየሱስ ፍጡር ነው ለማለት ካለመኖር ወደ መኖር መምጣቱን የሚያሳይ ማስረጃ ማምጣት የግድ ይሆናል። ሰው ተብሏልና ፍጡር ነው የሚለው ትርክት ማስረጃ የሌለው ስሁት አመክንዮ ነውና

✒ ስለ ክርስቶስ የቅድመ ስጋዌ ዘመን፥ መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ በቅድመ ስጋዌ ዘመኑ ዘላለማዊው እግዚአብሔር መሆኑን በግልጽ ያስተምራል

1. " እርሱም የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው። የሚታዩትና የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት፥ በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና ከፍጥረት #ሁሉ በፊት በኵር ነው። ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል።"
(ወደ ቆላስይስ ሰዎች 1:15-16)

✒ በዚህ ስፍራ ክርስቶስ ፍጥረትን ሁሉ የፈጠረ ፈጣሪ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ይናገራል። #ሁሉን ፈጠረ ማለት ፍጡር የተባለ ነገር ሁሉ (ቀድሞም በህልውና ያልነበረ፥ በሆነ ጊዜ ላይ ወደ ህልውና የመጣ) ሁሉ በእርሱ ነው የተፈጠረው ማለት ነው።

ይህ ደግሞ እሱን ከፍጥረት ውጪ ያደርገዋል። ምክንያቱም ፍጥረትን ሁሉ እሱ ፈጥሮ፥ እሱ ራሱ ፍጡር ነው ከተባለ ራሱን ፈጥሯል ማለት ሊሆን ነው። ይህ ደግሞ ኢ-አመክንዮአዊ ነው። ስለዚህ ክርስቶስ ፍጡር አይደለም ማለት ነው

2. “እርሱ የእግዚአብሔር ክብር ነጸብራቅና የባሕርዩ #ትክክለኛ_ምሳሌ ሆኖ፣ በኀያል ቃሉ ሁሉን ደግፎ ይዞአል፤ የኀጢአት መንጻት ካስገኘ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ።”
— ዕብራውያን 1፥3 (አዲሱ መ.ት)

✒ በዚህ ስፍራ ወልድ የአብ ባህሪ ትክክለኛ ምሳሌ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። "ትክክለኛ ምሳሌ" የሚለው የግሪክ ቃል karakteir የሚል ሲሆን "exact imprint: exact representation" ማለት ነው። ማለትም የአንድ ነገር ቁጭ አምሳያ ማለት ነው። ያ ነገር የሆነውን በሙሉ አንድም እንኳ ሳይሸረፍ፥ ሳይቀነስ የሆነ ማለት ነው

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን፥ አብ በባህሪው ዘላለማዊ ነው። (ሮሜ 1:20) ማለትም አብ በባህርይው ፍጡር አይደለም። ይህ ማለት የእርሱ ባህርይ ትክክለኛ ምሳሌ የሆነው ወልድም፥ ፍጡር አይደለም ማለት ነው

3. “ኢየሱስም፣ “እውነት እላችኋለሁ፤ አብርሃም ከመወለዱ በፊት እኔ፣ እኔ ነኝ” አላቸው።”
— ዮሐንስ 8፥58 (አዲሱ መ.ት)

✒ በዚህ ስፍራ ጌታ ኢየሱስ አብርሃም ሳይወለድ በፊት እሱ እንደነበር ሲናገር እንመለከታለን። "ሳይወለድ" የሚለው የግሪክ ቃል "genesthai" ሲሆን "ወደ ህልውና መምጣት" ማለት ነው። "እኔ ነኝ" የሚለው ቃል ደግም "eigo emi" ሲሆን በimperfect tense ነው የገባው

ይህ ቃል "የክርስቶስ ህልውና የጀመረው በድንግል ማርያም ማህጸን ነው" የሚለውን ሀሰት ከማፈራረስ ባሻገር የክርስቶስን ዘላለማዊነት የሚያጸና ነው። ምክንያቱም ጌታ፥ እያነጻጸረ ያለው የአብርሃምን ካለመኖር ወደ መኖር መምጣት ከእሱ ጅማሬ አልባነት ጋር ነው። አብርሃም ሳይወለድ እርሱ ነው። ይህ አተራረርክ በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ሲተረክበት የነበረው አተራረክ ነው። (መዝ 90:2)

▶ መደምደሚያ

ክርስቶስ ሰው የተባለው ስለተሰገው እንጂ ወደ ህልውና ስለመጣ አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረው፥ መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው ዘላለማዊ ነው። ሰው መባሉ ፍጡር መሆኑን አያሳይምና

ስለዚህ ፍጡር ነው የምትሉ ከሆነ፥ ካለመኖር ወደ መኖር መምጣቱን የሚያሳይ ማስረጃ ይዛችሁ መቅረብ ይኖርባችኋል።

ጌታ ይርዳን!


“ሕጉ ድካም ያላቸውን ሰዎች ሊቀ ካህናት አድርጎ ይሾማልና፤ ከሕግ በኋላ የመጣ የመሐላው ቃል ግን ለዘላለም ፍጹም የሆነውን ልጅ ይሾማል።”
— ዕብራውያን 7፥28






ሕይወት ገፍታ ገፍታ ከነፍሱ ጥሪ ጋር አገናኘቺው፤ የሙሉ ጊዜ ጸሐፊ ሆኖ አረፈው፡፡ በሴኩላሩ ዓለም ግን የሚታወቀው በገጣሚነቱ ነው፡፡ አልፎ አልፎ በመገናኛ ብዙኃን ብቅ ሲል፡- ታሪኩን ያጠኑ ጋዜጠኞች፡-
‹‹ማን ብለን እንጥራህ?›› ይሉታል፡፡
“የሥነ ጽሑፍ ወዛደር” የሚል ነበር አጭር መልሱ፡፡
ገጣሚ ብቻ፣ ደራሲ ብቻ፣ ባዮግራፈር ወይንም ኤዲተር … ብቻ መባል፡- ሥነ ልቡናዊ ጥበት ስለ ሚፈጥርበት ወይንም ያው ‹‹ልክ ያለፈ ትህትናው›› ድምር ተፅዕኖ ይመስላል፡፡
ወንድዬ በሥነ ጽሑፍ ወዛደርነቱ የሚያስታውቸውን ኹነኛ ሥራዎቹን አባሪ ማድረጉ ይሻላል፡፡ ዝርዝሮቹን ያነበበ ብቻ ነው፡- ገጣሚ ብቻ፣ ባዮግራፈር ብቻ፣ ኤዲተር ብቻ፣ ሪሰርቸር ብቻ መሆኑን መበየን የሚችለው፡፡
ከማስታውሳቸው ሥራዎች መካከል …
የሥነ ግጥም ሥራዎች
1. ወፌ ቆመች፤ 1984 ዓ.ም፤ (በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ በኮቴቤና በሌሎችም የአካዳሚያ ተቋማት ካሪኩለም ውስጥ የተካተተች)፡፡
2. ውበት እና ሕይወት፤ 1998 ዓ.ም (ወፌ ቆመች ቅጽ 2 እንደ ማለት ናት)፡፡
አጭር ልቦለድ
3. ከሚላ፤ 1998 ዓ.ም፤ (ፖፑሌሽን ሚዲያ ሴንተር፣ ‹‹ወንዞች እስኪሞሉ›› መድብል ውስጥ ያሳተማት) ተሸላሚ ነበረች፡፡
የቤተ ክርስቲያን ታሪክ
4. በመከራ ያበበች ቤተ ክርስቲያን፤ 1990 ዓ.ም፤ (የኢትዮጵያ ቃለ ሕወት ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ 1920 – 1933)፡፡
5. የእኩለ ሌሊት ወገግታ፤ 1992 ዓ.ም፤ (የኢትዮጵያ ቃለ ሕወት ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ 1934 – 1966)፡፡
የሕይወት ታሪክ (ባዮግራፊ)
6. ፈለገ ብርሃኑ፤ 2002 ዓ.ም፤ (የዶ/ር ብርሃኑ ሃብቴ የሕይት ታሪክ)፡፡
7. የሕይወት ጉዞዬ፤ 2010 ዓ.ም (የጀ/ል ታዬ ጥላሁን የሕይወት ታሪክ)፡፡
8. በእሳት የተፈተነ ሕይወት፤ 2012 ዓ.ም (የወይዘሮ በቀለች ባቾሬ ትዝታዎች)፡፡
9. ትዕግሥት በቁመናው፤ 2013 ዓ.ም (የሲዳማው አቶ ቲቦ የሕይወት ታሪክ)
10. ሺፈራው፡ በፊደላት ሥዕል፤ 2013 ዓ.ም (የአቶ ሺፈራው ወ/ሚ የሕይወት ታሪክ)፤ ምናልባት የኔ ዋናዬ (ማስተርፒስ) የምለው ሥራዬ ነው፡፡
11. ያልባከነ ዕድሜ 2015 ዓ.ም (የወ/ሮ ዐመለወርቅ አበበ) የሕይወት ታሪክ፡፡
በ‹‹ኤዲቲንግ›› ስም ያዘጋጀኋቸው ወይንም ዳግም የጻፍኳቸው እና የታተሙቱ
12. ተስፋዬ በእግዚአብሔር ጥላ ሥር፣ 2014 ዓ.ም (የቄስ ተስፋዬ ዲነግዴ የሕይወት ታሪክ) በኦሮሚኛ ተተርጉሟል፡፡ የተመረቀው አሜሪካን አገር ነው፡፡
13. ትውስታዬ፤ 2010 ዓ.ም (የአቶ ሚሊዮን በለጠ የሕይወት ታሪክ)፡፡
14. BEYOND THE FAIRY Tale “ከገራገር ወጎች ማዶ ብዬ እንደገና የተረጎምኩት” 2009 ዓ.ም (የዶ/ር መስከረም ክፈተው መጽሐፍ)፡፡
15. ሕይወቴና ጰንጠቆስጤአዊ እንቅስቃሴ አጀማመር፤ 2009 ዓ.ም (የዶ/ር ዘለቀ ዓለሙ የሕይት ታሪክ)፡፡ (እምብዛም የማልደሰትበት ሥራ)
16. የታምራት አምላክ ታምረኛ፤ 2008 ዓ.ም (የታምራት ኃይሌ የሕይወት ታሪክ)፡፡
17. የማኅበር አህያ ፤ 2007 ዓ.ም (የአቶ ተክሌ ወልደ ጊዮርጊስ የሕይወት ታሪክ)፡፡
18. የምድረበዳው እረኛ ፤2005 ዓ.ም (የዶ/ር ጥበበ የሕይወት ታሪክ) በጣሙን የምኮራበት ሥራ ነው፡፡
19. ጥበበ ሕጥወት፤ 1996፣ (የሕይወት ክኅሎት መመሪያ/ማኑዋል)
ያልታተመ
20. ድምፅ ዐልባው ሞገድ፤ 2009 ዓ.ም (የኢቫሱ ታሪክ፤ ምናልባት ‹ሺፈራው በፊደላት ሥዕል›ን ሊያስከነዳ የሚችለው ይህ መጽሐፍ ብቻ ነው፡፡)
አርትዖት ብቻ፡-
21. መንፈስ ቅዱስ ፤ 1989 ዓ.ም (የቢሊ ግራሃም የአማርኛ ትርጉም መጽሐፍ)፡፡
የፊልም ጽሑፎች፡-
22. የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጉዞ፤ 2011 ዓ.ም፡፡
23. ትውልድም እንደ ዐባይ (ለልዕሥምማ - 2000 ዓ.ም) ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ከመጀመሩ በፊት የተሠራ ዶኪዩመንተሬ፡፡
24. ሰው ማለት ምንድነው? (2005 ዓ.ም)
በመጠናቀቅ ላይ ያሉ መጻሕፍት
25. ብርሃን ይሁን፤ (የቤተ ክርስቲያን ታሪክ)
26. የግንባር ሥጋው፤ (የሕይወት ታሪክ)

መልካም እረፍት


የወፌ ቆመች መታተም እና ዝና ኋላ ላይ ፍቅሩም፣ እንጀራውም ወደ ሆነው የሥነ ጽሑፍ ሙያ ይቀላቀል ዘንድ መንገድ ጠረገለት፡፡ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት የሥነ ጽሑፍ ድርጅት ባልደረባ ይሆን ዘንድ ጋበዘው፡፡ (በዚህ ረገድ የአቶ ጌታቸው በለጠ ድርሻ ትልቅ ነበር፡፡ ግብርና ምኒስቴርን ለቆ (ሞፈሩን ሰቅሎ፣ ቀምበሩን ሰብሮ) በትንሽ ደመወዝ በረዳት መጽሔት አዘጋጅነት ተቀጠረ፡፡
‹‹መጽሔት፡- እንደ ‹ቡፌ› ገበታ የተለያዩ መልእክቶች፣ በተለያዩ አቀራረቦች፣ በተለያዩ የአቀራረብ ቀለሞች፣ የሥነ ጽሑፍ ዘውጎች መከሸን ይገባዋል፤›› ብሎ የሚያምነው
ወንድዬ የቃለ ሕይወትን መጽሔት እንደ ልቡ ናኘባት፡፡ እያንዳንዷን ቅጽ፡- የመጣጥፍ፣ የታዋቂ ሰዎች ፕሮፋይል፣ የቃለ ምልልስ፣ የግጥሞች . . . ገበታ አደረጋት፡፡ (እንዳሰኘው ይጽፍ ዘንድ ሙሉ ነፃነት ያጎናጸፉትን የቅርብ አለቆቹን ያመሰግናል)፡፡
በዚህ ወቅት ነበር ከሥነ ግጥም በተጨማሪ በሌሎችም የሥነ ጽሑፍ ዘውጎች ለመጻፍ ተሰጥዖ እንዳለው ራሱን ያሳመነው፡፡ በተለይም በታሪክ እና የሕይወት ታሪኮች አተራረክ ረገድ ብዙ እርምጃ ተራመደ፡፡
ለዚህም ነበር፣ ከመደበኛ ሥራው ጎን ለጎን የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያንን ከፊል ታሪክ የሚሸፍነውን (1920-1966 ዓ.ም) ለመጻፍ የቻለው፡፡
በሁለት ቅጽ የተዘጋጁት መጻሕፍት “በመከራ ያበበች” እና “የእኩለ ሌሊት ወገግታ” ይሰኛሉ፡፡ እንደ ቅደም ተከተላቸው በ1990 ዓ.ም እና 1992 ዓ.ም የታተሙ ናቸው፡፡ መጻሕፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በአማርኛ ቋንቋ የተጻፉ የፕሮቴስታንት (ወንጌላውያን) ቤተ እምነት ታሪክ በመሆናቸው በርካታ የሥነ መለኮት ኮሌጆች ሥርዓተ ትምህርት (ካሪኩለም) ውስጥ ተካተቱለት፡፡
በዚህ ደስ የተሰኙት አለቆቹ Tear fund England ከሚባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት ጋር በመተባበር ኬኒያ - ናይሮቢ በሚገኘው Daystar ዩኒቨርስቲ የትምህርት ዕድል አመቻቹለት፡፡
በ40 ዓመቱ ተመልሶ ትምህርት ቤት ገባ፡፡ በአራት ዓመት ቆይታ ለመጀመሪያ ድግሪ መርሐ ግብር የተላከው ወንድዬ፣ በሦስት ዓመት ቆይታ የማስተርስ ዲግሪውን ይዞ ተመለሰ፡፡ ይህ ለብዙዎች ታምር ያህል እውነት ነው፡፡ ጥያቄም ነው፡፡
‹‹ሰው እንዴት ከveterinary ዲፕሎማ ተነስቶ በሦስት ዓመት፣ ለዚያውም ለMature Students የሚሰጠውን መሸጋገሪያ ኮርስ (Bridging Course) ሳይወስድ፣ ሁለተኛ ዲግሪውን ለዚያውም በሦስት ዓመት ብቻ ሊያጠናቅቅ ይችላል?›› ይህን ዝርዝር ለመዘርዘር ውጥኔ አይፈቅድልኝም፡፡
የወንድዬን የአዕምሮ ጉልበትና ሥራዎቹን በደንብ የተረዱ ሰዎች ‹‹ይህን ሰው ለመጀመሪያ ድግሪ ማስተማር “ማባከን ነው” በማለት ከዩኒቨርስቲው ጋር የተሟገቱ እንደ ነበሩ ወንድዬ ያስታውሳል፡፡ የአቶ ወርቁ ኃይለ ማርያምን ግትገታ (ውትወታ) ግን ከሁሉ የበለጠ ነበርና ወንድዬ ሁሌም ያስታውሰዋል፡፡
ወርቁን እና ወዳጆቹን አላሳፈራቸውም፡፡ የመመረቂያ ወረቀቱን፡, “THE CONTRIBUTION OF ORAL LITERATURE IN COMMUNICATING THE GOSPEL TO THE OMOTIC PEOPLE OF SOUTHERN ETHIOPIA: A CASE STUDY OF THE WOLIATE PIONEER EVANGELISTS” በሚል ርእስ ሠርቶ በ2003 (እኤአ) በማስተርስ ድግሪ ተመረቀ፡፡
***
ከናይሮቢ እንደ ተመለሰም የቃለ ሕይወት ሥነ ጽሑፍ ክፍል ኃላፊ ሆኖ ተመደበ፡፡ ግና ምን ያደርጋል? ሹመቱን ሰጥተው የቀድሞውን ነፃነቱን ነፈጉት፡፡ ከሁለት ዓመት መፍገምገም በኋላ ሥራውን ለቆ Population Media Center (PMC) በኤክስፐርትነት ተቀጠረ፡፡ ጥቂት፣ ግን መልካም የፊደላት የምርት ዘመን አሳለፈ - 2 ዓመት ብቻ፡፡ በክብር ተሰናብቶ የሙሉ ጊዜ ጸሐፊ ሆነ፡፡
ሁለተኛዋን የግጥም መድበል “ውበትና ሕይወት” (ወፌ ቆመች - ቅጽ -2) የታተመችው በ1998 ዓ.ም (2005 - እኤአ) ነበር፡፡ ይህም ማለት በ1ኛዋ እና በ2ኛዋ የግጥም መድበል መካከል የ15 ዓመት ግድም ክፍተት አለ ማለት ነው፡፡ በስሎ፣ ሰክኖ፣ ነትሮ ራሱን የገለጠባት መድብል ሆነች፡፡
ከሌላ 17 ዓመት ቆይታ በኋላ 3ኛ ቅጹን ለማሳተም ኮምተራይዝ እያደረገ ይገኛል፡፡ አልፎ አልፎ በፌስ ቡክ በሚለቃቸው ያልታተሙ ግጥሞቹ፣ የወፌ ቆመች 3ኛ ቅጽ አቀማመር ካለፉት ሁለቱ ለየት እንደሚል ያመላክታሉ፡፡ ለኅትመት ጉድ ጉድ ማለቱን የሰማ አንድ ወዳጁ ‹‹የማያርጠው ገጣሚ›› በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡ ሳያሳትማት ዘገየች፤ ‹‹እየታመምን እንጽፋለን፣ እየጻፍን እንታመማለን›› ይላል በራሱ ሲቀልድ፡፡ አሁንም እየጻፈ፣ እየታተመም ነው፡፡ ከህመሙ በኋላ እንኳን አራት መጽሐፎች ታትመውለታል፡፡
***
ስለ ግጥሞቹ ውበትና ለዛ፣ ይዘትና ቅርጽ አብዝተው ከጻፉት መካከል፡- አቶ ዘሪሁን አስፋው (በሥነ ጽሑፍ መሠረታውያን መጽሐፉ)፣ እንዲሁም ረዳት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ገበየሁ (በሥነ ግጥም ማኑዋል መጽሐፉ) ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡ ሁለቱም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህራን ናቸው፤ (ብርሃኑ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ያስታውሷል)፡፡ በህትመትሚዲያው ደጋግመው ከጻፉት መካከል ደግሞ፡- ደረጀ በላይነህ፣ ተሻገር ሺፈራው (ዶ/ር) እንዲሁም ወጣቱ ገጣሚ መዘክር ግርማ ይገኙባቸዋል፡፡
ከሁሉም በላይ ሥራዎቹን ተመርኩዘው የመመረቂያ ጽሑፎቻቸውን የጻፉ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች 15 ያህል እንደሆኑ አንድ ወዳጁ ለወንድዬ ነግሮታል፡፡
ታዲያ ምን ያደርጋል፤ ገጣሚውና ሐያሲው ደረጀ በላይነህ ‹‹ዓይናፋሩ ገጣሚ›› ሲል እንደ ገለጸው፣ በእርሱ ዙሪያ የተጻፉትን የትውልድ ቅርሶች ቢያንስ ለልጆቹ እንኳ ሲል ያሰባስባቸው ዘንድ ጥረት አላደረገም፡፡ ይህ ልክ ያለፈ ትህትናው (Humility)፣ ምናልባት ልክ ያለፈ ድካሙ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ጋባዡ ብዙ ቢሆንም፣ በመድረክ፣ በቴሌቪዥን፣ በሬዲዮ . . . ትዕይንታት አይሳተፍም፡፡ ከተሳተፈም በጥንቃቄ መርጦ ነው፡፡ ውካታና ሆያ-ሆዬ አይወድም፡፡
***
ወንድዬ፡- ገጣሚ? ደራሲ? Church Historian? Biographer? Researcher? ኤዲተር?
ጥሩ ደመወዝ የሚከፍለውን PMCን በወዙ (1999 ዓ.ም) የተሰናበተው የራሱ ጌታ ‹‹Self-employed›› ሆኖ፣ ከአለቃ የሚሰጠውን ብቻ ሳይሆን የሚወደውን ሥራ ለመሥራት ነበር፡፡ ከኮንሰልታንሲ ተቋማት ጋር ሕብረት ፈጥሮ አንድ ዓመት ያህል የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ሠራ፡፡ ነባራዊውን እውነት ዘወር ብሎ ሲያጤነው ይህኛውም ዓለም “ዘመናይ መሸቀጫ” ሆነበት፡፡ (ጥቂቶቹን የምርምር ሥራዎቹን ጉጉል ያውቃቸዋል)፡፡
ደግነቱ ገና PMCን ሳይለቅ ‹ሁሉን የታደሉ›፣ ነገር ግን ‹ሃሳባቸውን ወደ ፊደል መለወጥ› የማይችሉ ተቋማት እና ግለሰቦች በዝናው አፈላልገው፣ የትርጉም፣ የግለ ታሪክ ዝግጅት፣ የኤዲቲንግ የቤት ሥራዎች ይሰጡት ነበር - ለወንድዬ፡፡
ከደጋግ ወዳጆቹ መካከል አንዱ ‹የቤት ሥራ› በታተመ ቁጥር ሌላውን እየጎተተ ‹‹ሥራ ሲበዛለት›› የኮንሰልተንሲውን ‹‹ሽቀጣ›› እርግፍ አድርጎ ተወው፡፡ ወደ ታሪክና ግለ ታሪክ ዝግጅት ፊቱን አዞረ፡፡


አንጋፋው የሥነ ጽሑፍ ሰው አረፈ

#Ethiopia | ከ25 በላይ መጽሐፍትን ለአንባብያን ያደረሰው፣በበርካታ ግጥሞች እና የግለታሪክ አሰናጅነት የሚታወቀው ወንድዬ ዓሊ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ደራሲ ወንድዬ ዓሊ በ1950 ዓ.ም በቀድሞው የወሎ ጠቅላይ ግዛት ወረኢሉ አውራጃ ካቤ በምትባል መንደር ታክል ከተማ እንደተወለደ ከአንድ ዓመት በፊት ከኢቴቪ መዝናኛ ቻናል ጋር ካደረገው ቃለመጠይቅ ገልጿል፡፡የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን ደሴ በሚገኝው ወ/ሮ ስሂን ትምህርት ቤት፣የኮሌጅ ትምህርቱን በደብረዘይት የእንስሳት ህክምና ኮሌጅ ተከታትሏል።

"ወፌ ቆመች" የተሰኝው የግጥም መድብል እጅግ ተዋቂ መጽሐፉ ሲሆን በዩንቨርስቲ የሥነጽሑፍ ትምህርት ክፍል ማጣቀሻ ማስተማሪያ በመሆን ያገለግላል።

ደራሲ ወንድዬ ዓሊ በመካነ ኢየሱስ እና በቃለ ሕይወት ቤተክርስትያናት የሚዘመሩ ከ500 በላይ የመዝሙር ግጥሞችን ጽፏል።የበርካታ ግለሰቦች እና ተቋማትን ታሪኮችን በማዘጋጀትም ይታወቃል።

ደራሲ ወንድዬ ዓሊ በ2013 ዓ.ም የካንሰር ታማሚ እንደሆነ ካወቀ ጀምሮ ህክምና ሲከታተል ነበር። በተወለደ በ66 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

የአስክሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓቱ በሕብረት አምባ ቃለ ሕይወት ዛሬ የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ አምስት ሰዓት ጀምሮ የሚካሄድ ሲሆን፣ የቀብር ሥነ ሥርዓቱም በቅዱስ ዮሴፍ መካነ መቃብር ይፈፀማል።

***
ወንድዬ አሊ

ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን በስነጽሁፍና በመዝናኛው ኢንዱስትሪ ያሉ ባለሙያዎች የህይወት ታሪክን እያፈላለገ ለንባብ እያበቃ ይገኛል፡፡ የብዙ በሳል የስነጽሁፍ ሰዎች የህይወት ታሪክ በቀላሉ በማይገኝበት በዚህ ሀገር ተግባሩ መአድንን የመቆፈር ያህል ፈታኝና ከባድ ነው፡፡ ታሪካቸውን ከምንሰንድላቸው የግለ-ታሪክ አሰናጅ እንዲሁም ብርቱ ገጣሚዎች ውስጥ ወንድዬ አሊ ይገኝበታል፡፡ በአሁኑ ሰአት 65ኛ አመቱ ላይ የሚገኘው ይህ ታላቅ ሰው ከ25 በላይ መጽሀፎችን ወደ አንባቢ አድርሷል፡፡ ጥር 27 2015 ደግሞ ወንድዬን ለማክበር በሀገር ፍቅር ቴአትር ጠዋት ላይ አንድ መሰናዶ ይደረጋል፡፡ ይህ አንዱ በጎ ጅምር ስለሆነ ይበል እንላለን፡፡ የህይወት ታሪኩን አረጋ ጋሻው እንደሚከተለው ሰንዶታል፡፡

ጠቅላላው ቤተዘመዱ እና የልቡ ሰዎች ‹‹አባት ወንድዬ›› ነው ብለው የሚጠሩት፡፡ ይህም አንድ ቁምነገር ያስገነዝበናል ብዬ አስባለሁ፡፡ እንኳን በቅርበት ለሚያውቁትና ለታናናሾቹ ቀርቶ በዕድሜ አቻዎቹና ታላላቆቹ ሁሉ የአባትነት መንፈሱ ስለሚገዝፍባቸው ይመስለኛል፤ ‹‹አባት ወንድዬ›› እያሉ የሚጠሩት፡፡
ደረጀ በላይነህ ባንድ ወቅት እንዳለው ‹‹ወንድዬ ዓይናፋር ገጣሚ ነው››፡፡ ከዚያ በላይ ግን ወንድዬ ዓይናፋር ደራሲ፣ አርታኢ፣ ባዮግራፈር፣ የምርምር ሰው፣ ፊልም ስክሪፕት ጸሐፊ … ወዘተም ነው፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ራሱን ‹‹የሥነ ጽሑፍ ወዛደር›› እያለ የሚጠራው፡፡ለዚህም ምክንያቱም፡- ራሱን በገጣሚነት ወይ በደራሲነት፣ አለዚያም በሕይወት ታሪክ ጸሐፊነት … አጥሮ መሰየምን አልወደድም ይሆናል ብዬ እገምታለሁ፡፡
አባት ወንድዬ በእውነትም ‹‹የሥነ ጽሑፍ ወዛደር›› ነው፡፡ ላለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት ‹‹የሙሉ ጊዜ ጸሐፊ›› ብቻ ሆኖ ነበር የሰከነ ሕይወት እየመራ ያለው፤ (የአብራኩ ክፋይ የሆኑ ልጆቹንና ዘመዶቹን እያስተማረ፣ ቤት ኪራይ እየከፈለ፣ ችግረተኞችን እያገዘ) . . .፡፡ የሙሉ ጊዜ ጸሐፊ ሆኖ ሃያ ያህል ዓመታት የዘለቀ የሥነ ጽሑፍ ሰው የማውቀው ወንድዬን ብቻ ነው፤ ሌላ ሰው ካለ ለመታራም ዝግጁ ነኝ፡፡
የመዘገባቸው ሥራዎቹ ሃያ አምስት ይህል ናቸው፤ ያልመዘገባቸው በርካቶች እንዳሉ ምንም አያጠራጥርም፡፡
አንድ ልጨምር፡- በአባትነት መንፈሱ፣ የኮተኮታቸው፣ ፅንሳቸውን ያዋለዳቸው፣ የጥበብ መንገዱን ያሳያቸው ወጣት ደራሲያን በርካቶች ናቸው፡፡ ለሚተማመንባቸው ለአንዳንዶቹ የጀርባ ጽሑፍ እና መቅድም እንደጻፈላቸው አውቃለሁ፡፡
እንግዲህ የዚህን ሰው እና ‹‹የዚህን ብዙ ሰው›› አጭር ታሪክ ለመጻፍ የተነሳሁት፡፡ ይለናል አረጋ ጋሻው ፡፡
ወንድዬ ዓሊ በ1950 ዓ.ም (እኤአ 1957) በቀድሞው የወሎ ጠቅላይ ግዛት፣ ወረኢሉ አውራጃ ካቤ በምትባል መንደር ታክል ከተማ ተወለደ፡፡ ለወላጆቹ አምስተኛ ልጅ የሆነው ወንድዬ በእናቱ ፍቅር ተምበሽብሾ፣ ወደ ጫና በሚያደላው በአባቱ ጥብቅ ሥነ- ምግባር ተኮትኩቶ አደገ፡፡
ግጥም መግጠም የጀመረው ገና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሳለ ነበር፡፡
‹‹የእናትና አባቴ ትዳር ከፈረሰ በኋላ አባቴ ሌላ ሚስት አገባ፡፡ የእንጀራ እናቴ - በራሷ “ክፉ ቀን! ክፉ ሰው!” ሆነችብኝ፡፡ ፊቷ በገረፈኝ ቁጥር ቁጭቴን የምወጣው ወረቀት ላይ ነበር፡፡ አምስተኛ ክፍል ስደርስ እንጉርጉሮዎቼ አንድ ደብተር ሞሉ፡፡ ጥራዟን “ሲከፉ” የሚል ርእስ አወጣሁላት›› ይላል ወንድዬ አጀማመሩን ሲያስታውስ፡፡
ግጥሞቹ ግን ከባድማ ልቡ ብቻ የወጡ አልነበሩም፤ ከማንበብና መጻፍ በስተቀር ምንም ዘመናዊ ትምህርት ያልቀሰሙት አባቱ ለሕክምናም ሆነ ለፍርድ ቤት ጉዳይ ወደ አዲስ አበባ ጎራ ባሉ ቁጥር ብርቅዬ ጫማ እና አልባሳት ሳይሆን መጻሕፍት ገዝተውለት ነበር የሚመጡት፡፡ ጦቢያ (የመጀመሪያው ልቦለድ በአፍሪቃ)፣ ወዳጄ ልቤ፣ አልሞትኩም ብዬ አልዋሽም፣ ፀሐይ መስፍን፣ እንቅልፍ ለምኔ ወዘተዎቹን. . . ያነበበው ካቤ መንደሩ ሳለ በኩራዝ ነው፡፡ የንባብ ፍቅር በዚያው ተጠናውቶት ቀረ፡፡
***
በጠቅላይ ግዛቱ ዋና ከተማ በሚገኘው በታዋቂው የወይዘሮ ስኅን ትምህርት ቤት የሁለተኛ ከፍተኛ ደረጃ ትምህርቱን ለመከታተል ወደ ደሴ ከተማ በ1965 ዓ.ም (1972 እኤአ) ሲሄድ እንጀራ እናቱ ከሚያደርሱበት ሃበሳ ተገላገለ፡፡ እንጉርጉሮ - ጎርጉሮ የመክተቡም ነገር አብሮ ቀጥ አለ፡፡
ኪነ-ጥበባዊው ደመ-ነፍሳዊ አደራ ግን እንደ ጪስ (ጢስ) መውጪያ ስንጥቅ አታጣምና መንፈሳዊ ግጥሞችን መጫጫር ጀመረ፡፡ በደብረ ዘይት የእንስሳት ሕክምና ኮሌጅ በ1971 ዓ.ም (1978 እኤአ) ገበቶ የደብረ ዘይት መካነ ኢየሱስ ኳየር ሲቀላቀል አምሮቱን ተወጣ፤ 200 ግድም ዜማ-ግጥሞችን (Lyrics) ዘመረ፤ አዘመረ፡፡ ስለ ዜማ-ግጥም ሥራዎቹ ሲናገር እንዲህ ይላል፡-
‹‹እነሱ እኮ! … ግጥሞቼ ሳይሆኑ፣ የዐውደ ዕለት ማስታወሻዎቼ (Diary) ናቸው፤ ግጥሞቼ ደግሞ - ታሪኮቼ››፡፡
ከነፍሱ ጥሪ በተቃራኒ እንስሳት ሕክምና ኮሌጅ የገባው በጊዜው ከነበረው ቀይ ሽብር አደጋ ለመሰወር ያህል ብቻ እንደ ነበረ - ያስታውሷል፡፡
***
ከኮሌጅ ሲመረቅ በሐምሌ 1972 (1980 እኤአ) አርሲ ተመደበ፡፡ በእንስሳት ሐኪምነትና በእንስሳት እርባታ ማኔጀርነት ዘጠኝ ዓመት ተኩል በሠራባቸው ዓመታት እውነተኛ ገጣሚነቱ ተፍለቀለቀ፡፡ በ1984 ዓ.ም (እኤአ 1992) በታተመቺው የመጀመሪያ መድበሉ “ወፌ ቆመች” ውስጥ የተካተቱት ግጥሞች አብዛኛዎቹ የተጻፉት በአርሲ ቆይታው ነበር፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እና ኮተቤ ኮሌጅን ጨምሮ በተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት “በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ ጽሑፍ” ክፍል ለማስተማሪያነት ካሪኩለም ውስጥ ለመካተት የበቃቺው “ወፌ ቆመች” እንግዲህ የእንስሳት ሐኪሙ - የቅኔ ዛር ምጥ ናት ማለት ነው፡፡


ሀሌ ሉያ !!


1ኛ ጢሞቴዎስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤
⁶ ራሱንም ለሁሉ ቤዛ ሰጠ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ፤










መፅሐፍ የሚለውን ብቻ እንላለን !!

ማደግህ በነገር ሁሉ !!

የዛሬው ስልጠናችን በሾኔ ከአብያተ ክርስቲያናት ወጣቶችና መሪዎች ጋር

“ማደግህ በነገር ሁሉ እንዲገለጥ ይህን አስብ፥ ይህንም አዘውትር።”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥15

በርናባስ ዩዝ ሚኒስትሪ!!


Dr. Justin Capes, አናሊቲክ ፊሎሶፊላይ ለካልቪኒዝም ያቀረባቸው ሶስት ተቃዎሞዎች።

1 on the value of freedom to do evil የሚለውን የ Josh Rasmussenን ጽሁፍ መነሻ በማድረግ፤ መለኮታዊ ውሳኔ ያለ ነጻ ፍቃድ የፍቅርን ትርጉም ሊያሳንስ ይችላል በማለት በማስገደድ የሆነንና በነጻ ፍቃድ የሆነን ፍቅር በሚከተለው ምሳሌ ያሳየናል።

ሳሊ የተባለች ሴት፤ ባለቤቷ እርሷ የምትወድደውን አበባ እንዲገዛለት ፈልጋ እርሱ በሚበላው ሾርባ ውስጥ፤ እሷ የምትወድደውን አበባ እንዲያስገዛው የሚያስችለው ወይም የሚያስገድደው አልያም ፍላጎት የሚፈጥርበት፤ መዳኒት ሰጠጭው። ከዛ ሳም(ባለቤቷ) ሾርባውን ከጠጣ በኋላ፤ በውስጡ አበባውን እንዲገዛ የሚያደርግ ፍላጎት ስላደረበት ገዛለት።

ይህኑ ምሳሌ ቀይረነው፤ ሳሊ ይህን አበባ ባለቤቷ እንዲገዛላት ስለፈለገች፤ ሂዳ በግልጽ ባለቤቷ ሳም፤ አበባውን እንዲገዛላት ጠየቀችው እና በፍቃዱ ገዛላት። ከመጀመርያው ይልቅ የኋለኛው ፍቅርን በተሻለ አይገልጽም?

2. እግዚአብሔር አንድ ነገር እንዲሆን ወስኖ ከሆነ፤ ያለምንም ጥያቄ ይህ እንዲሆን አቅዶታል ወይም ሁሉንም ነገር አመቻችቷል ማለት ነው። ይህም ፍቃዱ በምንም ሊከለከል አይችልም ማለት ነው። ስለዚህ ምንም እናምጣ ምን፤ ከተጻፈው ስለማናመልጥ፤ እንደፈለገው እያረገው ነውና። ተጠያቂም ልንሆን አይገባም፤ እንደየውም ምንም እንደሚጠበቅብንም ማስብ ላይኖርብን ነው።

አንድ ሰው በሚያምር ፓርክ ውስጥ ሲዝናና ሳለ፤ አንዲት ህጻን ወደ ጥልቅ ጉድጓድ ልትወድቅ ስትል አየ። ከዚህም ሊታደጋት ወደ ጉድጓዱ አፋፍ ቀርቦ እጁን ሊዘረጋላት ሲል፤ እጁ ወደሷ እንዳይዘረጋ የሚከለክለው ጠንካራ ሀይል ወደ ኋላ ይገፋዋል። በርግጥ ይህ ግለሰብ ህጻኗን ባለመርዳቱ ተጠያቂ ሊሆን ይችላል?

3. እግዚአብሔር እኛን በጥፋታችን የሚፈርድብን ከሆነ፤ አንደኛ የሚፈርድብንን ራሱ እንድናጠፋ አድርጎን ነው እና ለመቀበል ይከብዳል። ይሁን ብለን እንኳን ብንቀበለው፤ እግዚአብሔር እኛን እንድናጠፋ ሲያደርገን፤ ከዛም ሲፈርድብን፤ ግብዝ አያደርገውም ወይ? ለራሱ ያጠፋውን ስናጠፋ እንዴት ይፈርድብናል? በምንስ መለክያ? ለዚህ ፈላስፎቹ የሚያቀርቡት ምሳሌ፤ አሊስ የተባለች ሴት ባሏ ላይ አመነዘረች። ከዛ ወደ ቤት ስትመለስ፤ የእህቷ ባል፣ እህቷ/ጄን ላይ ሲማግጥ እጅ ከፍንጅ ያዘችው። ጥያቄው የሚሆነው፣ አሊስ በጄን ባል ላይ መፍረድ ወይም መቆጣት ትችላለች ወይ?

ሌላም ምሳሌ ለመጨመር። ጄን ልጇ ይታገትባታል። አጋቾቹ ልጇ እንዲለቀቅ፤ ቀለል ያለ ነገር ጠየቋት። ይህም አንድ ሰው በቦክስ ፊቷን ቢመታት፤ ልጇን ሊለቁላት። ይህን ግን የሚመታት ግለሰብ ማወቅ የለበትም። ስለዚህ አንድ ምታውቀውን ጆርጅ የተባለ ግለሰብ፤ ፉንጋነቱን ነቅፋ ሰደበችው። በፉንጋነቱ ሲመጡበት ጆርጅ ቶሎ ብሎ ቱግ የሚል በቦክስም የሚማታ መሆኑን ታውቅ ነበርና። በዚህም ጆርጅ ተናድዶ፤ ጄንን በቦክስ መታት። ልጇም ተለቀቀላት። ኋላ ላይ ግን ጄን በጆርጅ ድርጊት ተናድዳ ከሰሰችው። ቪዲዮም ተቀርጾ ነበርና ተፈረደበት። በርግጥ ጆርጅ አጥፍቷል እንኳን ብንል፤ የጄን ፍርድ ትክክል ነውን?

ምን ታስባላቹህ? ✍️Girum fida




በልሁ ደሳለኝ


የቄስ ኮሊን ትምህርተ ክርስቶስ መፅሐፍ 👆

Показано 20 последних публикаций.