EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


Ethiopian Broadcasting Corporation (EBC)

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций








የወሎ ማህበረሰብ ድንቅ እሴት፡- "ፋጡማ ቆሪ"
****************

"ፋጡማ ቆሪ" በወሎ አካባቢ ለነፍሰጡር ሴቶች የሚዘጋጅ ባህላዊ በገንፎ የታጀበ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ነው፡፡

በትውልድ ቅብብሎሽ ዛሬ ላይ የደረሰው ስርዓቱ የወሎ ነፍሰጡር ሴቶች እርግዝናቸው 9 ወር ሲደርስ እናቶች የገንፎ እህል አዘጋጅተው በባህላቸው መሰረት ደግሰው አብረው እየበሉ የሚመራረቁበት ነው፡፡

የኢቢሲ ሪፖርተር መታሰቢያ ደረጀ ወደ ወሎ ደጋን አካባቢ ባቀናችበት ወቅት አንድ ለመውለድ የተቃረበች ነፍሰጡር ሴት ከመውለድዋ በፊት በባህሉ መሰረት ምን ዓይነት ቅድመ ዝግጅት ይደረግላታል የሚለውን ቅኝት አድርጋለች፡፡

ድሪያ የለበሱ እናቶች ቀድሞ ከተዘጋጀው ዱቄት ላይ እየወሰዱ ለብዙኃኑ እንዲበቃ አድርገው በትልቅ ድስት ገንፎ ሰርተው ያቀርባሉ፡፡ ሰብሰብ ብለውም ለነፍሰጡሩዋ ሴት በሰላም ተገላገይ፣ ልጅሽን ወልደሽ እቀፊ እያሉ ይመርቃሉ፡፡
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02YhQGUQM2xr9Tm9jMeEJFv2WWXHKRcj7eZqAm14RwdNm3NHoSVNXFLjgHBEPyJYXjl


አስቶንቪላ ቪላ ማርከስ ራሽፎርድን በውሰት ውል አስፈረመ
**************

አስቶንቪላ የማንቸስተር ዩናይትድ አጥቂ የነበረውን ማርከስ ራሽፎርድን በውሰት ውል ማስፈረሙ ተገለጸ።

በውሉ መሰረት የ27 አመቱ ተጫዋች እስከ የውድድር ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በሚኖረው ቆይታ 75 በመቶው የተጨዋቹ ደሞዝ በአስቶን ቪላ ይሸፈናል ተብሏል፡፡

በውሉ ላይ አስቶን ቪላ በሰኔ ወር በ40 ሚሊየን ፓውንድ ተጫዋቹን የግሉ የሚያደርግበት የግዢ አማራጭ እንዳለውም ተገልጿል።

ራሽፎርድ በኢንስታግራም ገፁ ላይ “ይህ የብድር ውል እንዲፈፀም በማድረጋቸው ማንቸስተር ዩናይትድን እና አስቶን ቪላን ማመስገን እፈልጋለሁ” ሲል ሀሳብን ጠቅሷል።

ተጨዋቹ በማንችስተር ዩናይትድ የ20 አመታት ቆይታው በ426 ጨዋታዎች 138 ግቦች እና አምስት ዋንጫዎች አሳክቷል።

በሴራን ታደሰ


"የትግራይ ህዝብ ከትላንት ቁስሉ ሳያገግም ዛሬም በጦርነት ወሬ በፍርሃት እንዲኖር ሊፈረድበት አይገባም" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
****************

የትግራይ ህዝብ ከትላንት ቁስሉ ሳያገግም ዛሬም በጦርነት ወሬ በፍርሃትና በሰቀቀን እንዲኖር በፍጹም ሊፈረድበት አይገባም ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው በትግርኛ ቋንቋ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የትግራይ ህዝብ ኢትዮጵያን በመፍጠርና በመንከባከብ ውስጥ ያለው ሚና ጥልቅ ነው ብለዋል።

ትግራይ የስልጣኔ መነሻ እና የኢትዮጵያ የግዛት አንድነት ዋልታ ማገር መሆኑንም እንስተዋል::

የትግራይ ህዝብ በማይፋቅ ቀለም የተፃፈ ብሩህ ታሪክ ያለው ህዝብ ብቻ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከምንም በላይ ደግሞ የአገሩ ወዳጅ፣ የሰላምና የብልጽግና ወዳጅና ሥራ ወዳጅ ህዝብ ነው ብለዋል።

ትግራይ የመንግስት አስተዳደር እና ሃገረ መንግስት ግንባታ የተጀመረበትና ተጠበቆ የቆየብትም ምድር ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ::

የትግራይ ህዝብ ከምንም በላይ ሃገሩን ወዳድ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለሰላምም ትልቅ ዋጋ የሚሰጥ ህዝብ መሆኑ የአደባባይ ሃቅ ነው ብለዋል::
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid026YN4Vugb96GMKN94kgo66irGu1Q56nrLkuFjhXDUcQvpB2Pi81jx3gdYizfoNjThl


38ኛውን የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ካለፉት ጊዚያት በላቀ ደረጃ ለማስተናገድ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ
**********************

በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ እየተደረገ ያለውን ዝግጅት የተሳታፊ አገራት ቀዳሚ ልዑካን ቡድን አባላት ጎብኝተዋል።

የቡድኑ አባላት በጉብኝታቸው፤ ብሔራዊ ቤተመንግሥት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የክብር ሳሎን፣ አዲስ አፍሪካ ኮንቬንሽን ሴንተር እና የአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤትን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮቶኮል ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄነራል አዚዛ ገለታ (ዶ/ር) ጉብኝቱ ለጉባኤው ኢትዮጵያ እያደረገች ስላለው ዝግጅት ተሳታፊ አገራት በቂ መረጃ እንዲያገኙ ያስችላል ብለዋል።

ለዘንድሮው የሕብረቱ ጉባኤ ኢትዮጵያ በላቀ ደረጃ ዝግጅት በማድረግ የተሳካ መስተንግዶ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተር ጄነራሏ ተናግረዋል።

በጉብኝቱ የተሳተፉ እንግዶች ኢትዮጵያ ስኬታማ ጉባኤን ለማካሄድ የሚያስችል ዝግጅት ማድረጓን እንደተገነዘቡ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።


በዳውሮ ዞን በትራፊክ አደጋ የ 2 ሰዎች ህይወት አለፈ
******************

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን ሎማ ቦሳ ወረዳ ከገሣ ከተማ ወደ ሎማ ባሌ ይጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ አይሱዚ ተገልብጦ የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡

በደረሰው አደጋ 10 መንገደኞች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት እንደደረሳባቸውም ተገልጿል፡፡

ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በአቅራቢያ ወደሚገኙ የጤና ተቋማት ተወስደው ህክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ተጠቅሷል።

የአደጋዉን መንስኤ የትራፊክ ፖሊስ እየተጣራ እንደሚገኝም የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን መረጃ አመልክቷል።


የኢትዮጵያ እና የቼክ ሪፐብሊክ 8ኛ የፖለቲካ ምክክር በፕራግ ተካሄደ
****************

የኢትዮጵያ እና የቼክ ሪፐብሊክ ስምንተኛው የፓለቲካ ምክክር መድረክ በዛሬው ዕለት በቼክ ሪፐብሊክ ፕራግ ተካሂዷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ የኢትዮጵያን ልዑክ የመሩ ሲሆን፤ በቼክ ሪፐብሊክ በኩል የሀገሪቱ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጂሪ ኮዛክ ቡድኑን መርተዋል።

በውይይቱ የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር፣ የቼክ ልማት ትብብር ኤጀንሲ እንዲሁም የቼክ ንግድና ኤኮኖሚ ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

አምባሳደር ምስጋኑ በዚሁ ወቅት፤ ቼክ ሪፐብሊክ ከኢትዮጵያ ጋር ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላት ሀገር መሆኗን አንሰተው፤ ይህን ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀና ሁሉን አቀፍ ትብብር ማሳደግ እንደሚገባ ገልፀዋል።

አምባሳደር ምስጋኑ በኢትዮጵያና በቼክ ሪፐብሊክ መካከል የተካሄዱ የከፍተኛ መንግስት ባለሥልጣናት የጉብኝት ልውውጦች መጨመር በሁለቱ ሀገራት መካከል እያደገ የመጣው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።

አምባሳደር ምስጋኑ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና አህጉራዊ ወቅታዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ገለፃ አድርገዋ፤ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለውም የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራሞች በፈጠሯቸው አመቺ የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎች የቼክ ባለሀብቶች እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።

ምክትል ሚኒስትር ጂሪ ኮዛክ በበኩላቸው ኢትዮጵያ እና ቼክ ሪፐብሊክን የጋራ ተጠቃሚነት ያማከሉ በርካታ የትብብር ዕድሎች እንዳሉ ጠቅሰው፤ ሀገራቸው ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጁነቷን መግለፃቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

Показано 9 последних публикаций.