ኢትዮ ሪያል ማድሪድ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


El Real Madrid Es Mi Corazon ⚪️⚪️
ይህ በኢትዮጵያ የመጀመሪያዉ እና ትልቁ የሪያል ማድሪድ የቴሌግራም ቻናል ነው። ስለ ሪያል ማድሪድ አዳዲስና ትኩስ መረጃዎች የዝውውር ዜናዎች ፣ ኃይላይቶች ፣ ቪዲዮች ፣ ትንታኔ በቀጥታ ያገኛሉ !
⚪️HALA MADRID Y NADA MAS⚪️
________________________________
📢 ለማስታወቂያ ስራ @LeulaRamos

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


ከመጪዉ ቅዳሜ ጀምሮ ሪያል ማድሪድ የሚያደርጋቸዉ ቀጣይ ጨዋታዎች። 😱

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


ከትላንቱ ጨዋታ በኃላ ሊዮኔል ሜሲ ስለ ኒኮ ፓዝ ፦

"እድሜው ምንም ይሁን ምን አስደናቂ አስተሳሰብ አለው ፥ በዚህ ቡድን ውስጥ ያለው ለዚህ ነው የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል እናም ጥሩ ደቂቃዎችን አሳልፏል። በዚህ ቡድን ውስጥም ምቾት ይሰማዋል ብዬ አስባለሁ። ፓዝ ጥሩ ኳሊቲ ያለው እና ጨዋታውን በሚገባ የሚረዳ ልጅ ነዉ። አሁን ጓደኛዬ ስለሆነ እንዲያድግ እረዳዋለዉ።"

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


❗️አለም አቀፍ የሀገራት የማጣሪያ ጨዋታዎች ተጠናቀዋል!

ተወዳጁ ክለባችንም ከ3ቀናት በኋላ ወደ ጨዋታ የሚመለስ ይሆናል!🤍😊

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


እንደምን አደራችሁ ማድሪዲስታስ ?

መልካም ቀን ይሁንላችሁ ! 🙏🏽

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


መልካም አዳር ማድሪዲስታስ 🤍

የነገ ሰዉ ይበለን 😉

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


ታዳጊው ተጨዋች ማኑኤል አንሄል ጉዳት አስተናግዷል!

ማኑኤል አንሄል በጉልበቱ ላይ ጉዳት ያስተናገደ ሲሆን ምናልባት ከ4 እስከ 6 ሳምንታት ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ስፔኑ ጋዜጣ Relevo ዘግቧል።

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


ቲቦ ወደ ልምምድ ተመልሷል። 🔥👏

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


ለስፔን ከ 21 አመት በታች የሚጫወተዉ ይህ ተጨዋች ከቤኔፊካ ጋር ባለው ኮንትራት ዉስጥ €50 ሚሊየን ዩሮ የሚያወጣ አጠቃላይ የውል ማፍረሻ አለው። እንደ ዘገባው ከሆነ አልቫሮ ክለቡን የሚለቅ ከሆነ ቤኔፊካ ለማንቸስተር ዩናይትድ በ €20 Million ከመሸጥ ይልቅ በዉል ማፍረሻዉ ገንዘብ መጠን ለሪያል ማድሪድ መሸጥን እንደሚመርጥ ተነግሯል።

ነገር ግን ብዙሀኑ የስፖርት ሚዲያዎች እንደጠቀሱት መረጃ ከሆነ ክለባችን ሪያል ማድሪድ ለአዲሱ የግራ ተከላካይ ይህን ያህል ገንዘብ ለማዉጣት ፈቃደኛ አደለም። ክለባችን በዚህ ግዜ ከሜንዲ እና ጋርሲያ በተጨማሪ ሌላ የግራ ተመላላሽ ለማስፈረም በሚፈልግበት ግዜ በ 2025 ከባየር ሙኒክ ጋር ያለዉ ኮንትራት የሚጠናቀቀዉን ትልቅ ልምድ ያለዉኖ አልፎንሶ ዴቪስን በነፃ ሊያስፈርም የሚችልበት እድል ሊረሳ አይገባም። ስለዚህ ሪያል ማድሪድ ለቤኔፊካ የሚጫወተዉን የአልቫሮን Performance በይነ ቁራኛ እየተከታተለ ቢሆንም ከዴቪስ ይልቅ ይህን ተጨዋች የማስፈረሙ እድል አነስተኛ እንደሆነ ተነግሯል።

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


ባሳለፍነው ሳምንት ሪያል ማድሪድ የ La Fabrica ምርት የሆነዉን የቀድሞ ተጨዋቹን አልቫሮ ካሬራስ ላይ ፍላጎት እንዳለው የሚገልፁ ሪፖርቶች ወጥተዋል።

የ 21 አመቱ የግራ መስመር ተከላካይ ሪያል ማድሪድን ለቆ የፖርቹጋሉን ክለብ ከመቀላቀሉ በፊት በ 2020 ለማንቸስተር ዩናይትድ የመጫወት እድልን አግኝቶ ነበር ፣ አልቫሮ ከፖርቹጋሉ ክለብ ቤኔፊካ ጋር ባደረገው አጭር ቆይታ እንደ ሪያል ማድሪድ ፣ ሊቨርፑል ፣ ባርሴሎና እና ማንቸስተር ዩናይትድ ባሉ ክለቦችን አይን ትኩረት እንዲደረግበት አድርጓል።

ሆኖም አሁን ላይ ከፖርቹጋል እየወጡ እንዳሉት ዘገባዎች ከሆነ አልቫሮ ካሬራስ ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ የመመለስ እድል ቢኖረውም ወደ ሪያል ማድሪድ መመለስን አጥብቆ እንደሚፈልግ እና እንደሚመርጥ ተዘግቧል። ማንችስተር ዩናይትድ የ 21 አመቱን የግራ መስመር ተከመላላሽ መልሶ ወደ ኦልትራፎርድ የማምጣት አንቀፅ በእሱ እና በተጨዋቹ መካከል ቀደም ሲል በተፈራረሙት ዉል መሰረት የሰፈረ ሲሆን ዩናይትድ ተጨዋቹን መልሶ ማምጣት ከፈለገ ወደ €20 ሚሊዮን ዩሮ መክፈል እንዳለበት ሪፖርቶች ጠቁመዋል።

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


እማይቻል የሚመስለዉ የዊሊያም ሳሊባ ፊርማ !

በብዙ ዘገባዎች ላይ እንደጠቀስነዉ ክለባችን ሪያል ማድሪድ በሳሊባ ላይ ከፍተኛ ፍላጎት ቢኖረውም አርሰናል ተከላካዩን የመሸጥ ሀሳብ ማስተናገዱ የማይመስል ነገር ነው። Mundo Deportivo እንደዘገበው መድፈኞቹ ሳሊባ እስከ 2027 ድረስ የሚቆይ የረጅም ግዜ ኮንትራት ስላለዉ በተጨዋቹ ዙሪያ የሚመጡ ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ፍቃደኛ እንዳልሆኑ ዘግቧል።

ዘገባዉ አያይዞ አርሰናል በሳሊባ ጉዳይ ከክለባችን ሪያል ማድሪድ ጋር እና ተከላካዩን ይፈልገዋል ከተባለዉ ከሌላኛዉ ክለብ ፓሪስ ሴንት ዠርመ ጋር ምንም አይነት ንግግር የማድረግ ፍላጎት እንደሌለዉ ዘግቧል። አርሰናሎች በጉዳዩ ላይ ያላቸው አቋም ግልፅ ነው ፣ እሱም ሳሊባ አይሸጥም የሚል አንድምታ አላቸዉ።

ሪፖርቱ አክሎም ሪያል ማድሪድ የተጨዋቹን አገልግሎት ለማግኘት ፍላጎት ቢኖረውም ሳሊባ ራሱ አርሰናልን መልቀቅ አይፈልግም ሲል አትቷል። ከሁኔታዎች አንፃር በ 2025 የክረምቱ መስኮት የባሎንዶር ስጩ ዉስጥ ስሙ የሰፈረዉን ይህን ተከላካይ አገልግሎት ለማግኘት ለፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ ከባድ እንደሆነ ሙንዶ ዲፖርቲቮን ጨምሮ ብዙሀኑ የእንግሊዝ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


ሉካ ሞድሪች በክሮሺያ በኩል ቋሚ ሆኖ ተሰልፏል!

ክሮሺያ በዛሬው ዕለት በአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ማጣሪያ ምሽት 03:45 ሲል ፖላንድን የምትገጥም ሲሆን በቡድኑ በኩል አንጋፋው አማካኝ ሉካ ሞድሪች ቡድኑን በአምበልነት እየመራ የሚጫወት ይሆናል።

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


ቀደም ሲል እንደተዘገበው ክለባችን ሪያል ማድሪድ በ 2025 የክረምቱ የዝውውር መስኮት የመሀል ተከላካይን በጥብቅ ሁኔታ ለማስፈረም አስቧል።

ክለባችን በተከላካይ ክፍል እጥረት ምክንያት ዘንድሮም ለሁለተኛ ተከታታይ ሲዝን ተጋልጧል። ይህን የተመለከተዉ ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ የተለያዩ ማጠናከሪያዎች በመጪዉ ክረምት ማስፈረም አስፈላጊ እንደሆነ ያምናል።

አንዳንድ ሚዲያዎች ፔሬዝ በ January ወር ወደ ገበያ ሊወጣ እንደሚችል ቢጠቅሱም ሪያል ማድሪድ ሁነኛ የመሀል ተከላካይ ተጨዋችን ለማስፈረም እስከ ክረምቱ መስኮት ድረስ የሚጠብቅ ይመስላል። በዚህ ዝዉዉር ላይ ሁሉም ምልክቶች እንደሚመሩን ከሆነ ክለባችን አሁንም የአርሰናሉን እና የፈረንሳይ ብሄራዊ ቡድን ተጨዋች የሆነዉን ዊሊያም ሳሊባን በዚህ ስፍራ ላይ ተመራጭ ኢላማ እንደሆነ ነዉ።

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


🏆 አሸንፉ ወይም ተሸንፉ፣ Betwinwins ሸፍኖታል! 🏆

ውርርዶችዎን በተወዳጅ የእግር ኳስ ቡድንዎ ላይ ያስቀምጡ እና ውርርድዎ ከተሸነፈ እስከ 10% ድረስ እንደ ነጻ ውርርድ ይዝናኑ። በ Betwinwins ፣ ሁል ጊዜ ወደ ኋላ መመለስ እና ደስታውን መቀጠል ይችላሉ!

🎯https://t.betwinwins.net/y7jcwrsy

📱 t.me/betwinwinset


የሪያል ማድሪድ ቡድን በዛሬው እለት ልምምዱን ያከናወነ ሲሆን በልምምዱም ላይም ዴቪድ አላባ ተገኝቶ ነበር።

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


በአንድሪክ ላይ በብራዚል ብሄራዊ ቡድን ቆይታው ቋሚ የመሆኑ ጉዳይ ጥራጥሬዎች እየተነሱበት ነው!

ብራዚላዊው እንቁ ታዳጊ አንድሪክ በብራዚል ብሄራዊ ቡድን በአብዛኛው ጊዜ የመጫወቻ ደቂቃ ሲሰጠው እየተመለከትን አይደለም። አሰልጣኝ ዶሪፋል ጁንዬር ሄጎር ሄሱስን ከአንድሪክ ይልቅ ያስበልጣል። ይህም በቺሊ ጨዋታ ተመልክተናል።

አንድሪክም ቢሆን በብራዚል ብሄራዊ ቡድን የነበረው አቋም እየፈረሰ ወይም እየወረደ ነው። ምንም ያህል በመጀመሪያዎቹ በብራዚል ብሄራዊ ቡድን ቆይታ ጎሎችን እያስቆጠረ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን አሰልጣኝ ዶሪፋል ጁንያር ታዳጊው በሎስ ብላንኮቹ እያስመዘገበ ያለው ውጤት እየመረኩ አይደለም። በዚ ጥላ ስር ካርሊቶ ለታዳጊው የመጫወቻ ደቂቃ ሲሰጥ መመልከት የተለመደ ሆኗል።

በሳንቲያጎ ዴ ቺሊ ስታድየም በተረደገው የቼሊ ጨዋታ ኢጎር ሄሱስ ለቦታው ለሚደረገው ትግል ወይም ፉክክር አሸንፏል። በጨዋታው ድንቅ እንቅስቃሴ + ጎል ማስቆጠር ችሏል። ይህም በብራዚል ብሄራዊ ቡድን ክርክር እንዲፈጠር አድርጓል። እሱም አንድሪክ በብራዚል ብሄራዊ ቡድን ከዚ በላይ ቋሚ ተሰልፎ የመጫወቻ ደቂቃ እንዲያገኝ ነው።

[ AS ]

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


አመለ ሸጋውና ደጉ ባለተጥኦ ተጨዋች ጉለር!

በትላንትናው ዕለት በአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ማጣሪያ ጨዋታ ቱርክ ከ አይስላንድ ጨዋታ መጀመር በፊት ተጨዋቾች ወደ ሜዳ ልጆች ይዘው በገቡበት ወቅት አርዳ ጉለር ከነዛ ይዟቸው ከገቡት ልጆች ውስጥ ይዞት የገባው ልጅ ብርድ ሲበረደው ለብሶት የነበረው ጃኬት አውልቆ ለልጁ ሲያለብስ ታይቷል! ከዛም የቡድኑ ተጨዋቾች እሱን ተከትለው አልብሰዋል። ❤👏

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


አንዳንድ የክለባችን ተጨዋቾች የኢንተርናሽናል ብሬክ ጊዜያቸውን አጠናቀዋል!

የኢንተርናሽናል ብሬክ ጨዋታዎች ሊጫወቱ ለብሄራዊ ቡድኖቸው ከተላኩ ዘጠኝ ተጨዋቾች ውስጥ በአሁኑ ሰዓት ተጫውተው ጨርሰው ጉዳት ያለስተናገዱ የክለባችን ተጨዋቾች አራት ሆነዋል። (አምስት ተጨዋቾች ገና አልጨረሱም)

✅ ኤድዋርዶ ካማቪንጋ
✅ ኦሪያን ቹአሚኒ
✅ አርዳ ጉለር
✅ አንቶኒ ሩዲጋር

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


#ቁጥራዊ_መረጃ ....

ቱርክ በአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ማጣሪያ አይስላንድን 4ለ2 በሆነ ውጤት ባሸነፈቺበት ጨዋታ ቱርካዊው የክለባችን ባለተሰጥኦ አማካኝ አርዳ ጉለር በጨዋታው የነበረው ቁጥራዊ መረጃ ይህንን ይመስላል። 😌👌

- 88 ደቂቃዎች ተጫውቷል
- 1 ግብ ከመረብ ጋር መዋሀድ ችሏል።
- 46/42 (91%) የተሳኩ ኳሶች አቀብሏል
- 3/3 (100%) የተሳኩ ረጅም ኳሶች አቀብሏል
- 2 ኳሶችን በግብ ላይ ሞክሯል
- 70 ጊዜ ኳስን ነክቷል
- 3 እድሎች ፈጥሯል
- 2 የተሳኩ ድሪቢሎችን አድርጓል

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


ቹአሚኒ ከዚኒዲን ዚዳን በመቀጠል ቀይ ካርድ የተመለከተ የመጀመሪያው ተጨዋች ነው!

የክለባችን ኮከብ የሆነው ኦሪያን ቹአሚኒ ከሌጃንዳችን ዚኒዲን ዚዳን (እ.ኤ.አ በ2006 July 9) በኋላ የፈረንሳይ ብሄራዊ ቡድን አምበል ሆኖ በቀይ ካርድ ሲወጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15


❗️በዛሬው ዕለት 36ኛ አመት የልደት በዓሉን በማክበር ላይ የሚገኘው ጀርመናዊዉ ድንቅ አማካኝ ሜዙት ኦዚል በሪያል ማድሪድ ቆይታው ያስመዘገባቸው ቁጥሮች!

🎽159 ጨዋታ

⚽️ 27 ጎል

🅰 80 አሲስት

🏆1 የስፔን ላሊጋ ዋንጫ

🏆1 ኮፓ ዴልሬይ ዋንጫ

🏆የስፔን ሱፐር ካፕ ዋንጫ

በድጋሜ መልካም ልደት ሌጀንድ🤩🥳

@ETHIO_REAL_MADRID_15
@ETHIO_REAL_MADRID_15

Показано 20 последних публикаций.