ወንዲ ማክ ከ15 ነጠላ ዜማዎች በኋላ የመጀመሪያ አልበሙን ሊያወጣ ነው።
#FastMereja
አዲስ አበባ ኮልፌ ነው ተወልዶ ያደገው፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በኮልፌ ሰላም በር፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በቦሌ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሏል። የኮሌጅ ትምህርቱን በንፋስ ስልክ ቴክኒክ ተከታትሎ ተመርቋል።
ድምፃዊ ወንዲ ማክ መጀመሪያ ከህዝብ ያስተዋወቀው የሙዚቃ ስራ የቀድሞው አንጋፋ ድምጻዊ የጋሻው አዳል የሆነውን ግጥም ከራሱ በመጨመር "ምን ይጥራሽ" ወይም "ኮለል በይ" የተሰኘ ስራ ነው።
ወንደወሰን መኮንን (ወንዲ ማክ) 15 ነጠላ ዜማዎችን በመስራት ለህዝብ አድርሷል። በዚህም በተለያዩ የአለማችን ሀገራት በመሄድ የሙዚቃ ስራውን አቅርበዋል።
አሁን ከዘጠኝ አመት በኋላ "ይንጋልሽ" የተሰኘ የራሱን የመጀመሪያ አልበም አጠናቆ አርብ ሰኔ 14/2016 ዓም በራሱ ዩቲዩብ ቻናል እንደሚለቅ ፋስት መረጃ ሰምቷል።
14 ሙዚቃዎችን የያዘው ይንጋልሽ አልበም ግጥም እና ዜማ ራሱ ወንዲ ማክ የሰራው ሲሆን በፍቅር፣ በማህበራዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥን እንደሆነ ሰምተናል።
🎭#To Download Mp3👇👇
🥕🥕
@CAROTMUSICS 🥕🥕
◌◌◌🎸🎸🎸🎸🎸◌◌◌