ኮሚሽነር ደበሌ ከጣሊያን ጉምሩክ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በጉምሩክ ዘርፍ በቅንጅት ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ
*******************************************
(ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የካቲት 27 ቀን 2017 ዓ.ም )
የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ከጣልያን ጉምሩክ ኤጀንሲ የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር ጀኔራል Andrea Mazzella እና በጣልያን ጉምሩክ የአውሮፓ እና የዓለም አቀፍ የጉምሩክ ጉዳዮች ኃላፊ Dr. Raffaelle Capuano ጋር የሁለቱ ሀገራት የጉምሩክ ተቋማት በጋራ ለመስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡
በውይይታቸውም የጉምሩክ አገልግሎቶች ድንበር ዘለል፣ ዓለም አቀፍ እና በርካታ ሀገራትን የሚያስተሳስር መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ለዘርፉ እድገትም የሀገራት ቅንጅት ወሳኝ መሆኑም ተመላክቷል፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚስተዋለው የንግድ እንቅስቃሴ ፈጣን እና ተለዋዋጭ ባህሪ ያለው በመሆኑ ይህን ታሳቢ ያደረገ አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻልም የጉምሩክ ተቋማትን ማጠናከር እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን እና የጣልያን ጉምሩክ ኤጀንሲም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ግንኙነት የሚመጥን የጉምሩክ አገልግሎት ለመስጠት በቅርበት እንደሚሰሩ ተገልጿል፡፡
በተለይም በቴክኖሎጂ እና በዓቅም ግንባታ ስራዎች የሁለቱ ሀገራት የጉምሩክ ተቋማት ያላቸውን ልምድ እና ተሞክሮ ለመለዋወጥ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም በውይይቱ ወቅት ተነስቷል፡፡
ጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/ecczenaበድረ ገጽ፦
www.ecc.gov.etበቴሌግራም፦
https://t.me/EthiopianCustomsCommission