Фильтр публикаций






በገቢው ዘርፍ የሚደረገው የፀረ ሙስና ትግል የተቀናጀ ጥረትን የሚጠይቅ ነው፤ ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ፣ የገቢዎች ሚኒስትር
#########################
(ጉምሩክ ኮሚሽን፣ መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም)
ለገቢዎች ሚኒስቴር እና ለጉምሩክ ኮሚሽን ዳይሬክተሮች፣ አማካሪዎች፣ ፅ/ቤት ሀላፊዎች፣ ስራ ሂደት መሪዎች እና ቡድን አስተባባሪዎች ሥነ ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልእኮ ስኬት በሚል መሪ ቃል በፌደራል ስነምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡
ለሁለት ቀናት በሚካሄደው በዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ፣ የታክስ ስርዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ መስከረም ደበበ እና የፌደራል ስነምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ ተገኝተዋል፡፡

ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ፤ ሙስና ለዘላቂ ልማት፣ ለዴሞክራሲና ለመልካም አስተዳደር ማነቆ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ሚንስትሯ አክለውም በገቢው ዘርፍ የሚደረገው የፀረ ሙስና ትግል የተቀናጀ ጥረትን የሚጠይቅ እንደሆነ ገልፀው ከፌደራል ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

በገቢው ዘርፍ ሙስና እና ብልሹ አሰራር ሥር ከመስደዱ በፊት ተጋላጭነትን የመለየት፣ ክፍተቶችን የመዝጋት እና አሰራሮችን የማሻሻል ስራዎች እየተሰሩም ነው ብለዋል ሚንስትሯ፡፡

የፌደራል ስነምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው፣ ሙስና እና ብልሹ አሰራር የአስተሳሰብ መበላሸት እና የማህበራዊ እሴቶች መሸርሸር ውጤት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ሥነ ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልእኮ ስኬት በሚል መሪ ቃል እየተሰጠ የሚገኘው ስልጠናም ዘርፍ ተኮር እና በገቢው ዘርፍ ያለውን የሙስና ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena
በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et
በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopianCustomsCommission




ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8 በጉምሩክ ኮሚሸን ዋና መ/ቤት ተከበረ
*****************************************************
(ጉምሩክ ኮሚሽን፣ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም )
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች8በጉምሩክ ኮሚሸን ዋና መ/ቤት "ፈጣን እና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል” በሚል መሪ ቃል ተከብሯል፡፡

በአከባበር መድረኩ የጉምሩክ ኮሚሽን ዋናው መስሪያ ቤት፣ የቃሊቲ እና የአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ አመራሮች እና ባለሙያዎች ተገኝተዋል፡፡

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት፣ በጉምሩክ ኮሚሽን የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ማንጠግቦሽ ከበደ፣ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8 በያዝነው አመት በኢትዮጰያ ለ49ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ 114ኛ ጊዜ" ፈጣን እና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ የሚገኝ መሆኑን ገልፀዋል።

ማርች 8 ሴቶች ለመብታቸው የታገሉበት፣ ነፃነታቸውን ለማስከበር ትግል የጀመሩበት እና የትግል ውጤታቸው የሚዘከርበት ቀን በመሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል፡፡

በየዓመቱ በዓሉ ሲከበር የተገኘውን ድል የምንዘክርበት ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለሚገኙ እንዲሁም በፆታዊ ጥቃት ተጎጂ የሆኑ ሴቶችን የምንረዳበትና የምናስብበት ቀንም ነው ብለዋል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽን በየደረጃው የሚገኙ ሴቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ እና ወደ አመራር እርከን እንዲመጡ የሚስችሉ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም ወ/ሮ ማንጠግቦሽ አስገንዝበዋል፡፡

ከመክፈቻ ንግግሩ በኋላ የሴቶችን የእኩልነት ትግል የሚዘክር እና የስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማምጣት የሚያስችል የመነሻ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena
በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et
በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopianCustomsCommission



Показано 6 последних публикаций.