Ethiopian Digital Library


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


በዚህ ቻናል ስለ
👉ትምህርት፣
👉ሥራ እና
👉ማህበራዊ ጉዳይ
መረጃ ያገኛሉ!
Contact: @ethiodlbot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


#ባለጸጋ ያደረጉን ድሆች፣ የደስታችን ምንጭ የሆኑ ሀዘንተኞች

በዓለት መሀል የሚገኝ በመነኮሳት ፀሎት ብቻ እየተቆረጠ ለፀበልተኞች የሚሰጥ የማር እምነት መገኛ፣ ድውያንን ከመፈወስ አልፎ ሙት ያስነሳ ድንቅ የሚያደርግ ጸበል ያለበት፤ ከዘጠና በላይ መናንያን ዓለምን ንቀው የተጠለሉበት ነገር ግን ስለ ዓለምና ስለ ሀገራችን ሌት ተቀን የሚጸልዩበት ቅዱስ ስፍራ፤ ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አድነት ገዳም።

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ በለሳ ወረዳ የሚገኘው ይህ ገዳም ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በ2ኛ ቆሮንቶስ 6÷10 “ኀዘንተኞች ስንሆን ዘወትር ደስ ይለናል፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው።” ያለው ሕያው ቃል በዘመናችን በተግባር የሚታይበት ቦታ ነው፡፡

ምንም እንኳን መነኮሳቱና ገዳማውያኑ አሁንም ድረስ መንፈሳዊ ግዴታቸውን እየተወጡ በጽናት ቢቆዩም ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች እየተፈታተኗቸው ነው፡፡ ይህ ድንቅ ተአምር ያለበት ታሪካዊ የአንድነት ገዳም በአንድ በኩል አከባቢው ተፈጥሮ ፊቷን አዙራበት በድርቅ ምክንያት ምንም ዓይነት አዝርእት ያልበቀለበት በመሆኑ ጭው ያለ ምድረ በዳ ሆናል።

ወዲህ ደግሞ በአካባቢው ያለው ጦርነት በየጊዜው ይጎበኟቸው የነበሩ ፀበልተኞች ፈጽመው እንዲሸሹና ገዳማውያኑ ያለምንም ጠያቂ በትልቅ ችግርና ፈተና ውስጥ እንዲገኙ አድርጓቸዋል፡፡
ረሀብ፣ እርዛት፣ የማረፊያ ቦታ ችግር እጅግ ቢፈታተናቸውም፣ በአንድ በዓት ለሶስት ለአራት ለማደር ቢገደዱም ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው የራሳቸውን ስጋዊ መከራ ችለው፤ ሌት ተቀን ስለ ሀገር ደህንነት፣ ስለ አሐቲ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ሰው ልጅ ሰላምና ጤንነት ሳያቋርጡ በጽናት የሚፀልዩ ናቸው።

ዙሪያችንን የከበበንና በእሳት ውስጥ ያሳለፈን መከራ ያልጣለን፣ በተገፋነው እጥፍ ጸንተን የቆምነው በእነዚህና በሌሎችም ገዳማውያን አባቶቻችን የማያቋርጥ የሕብረት ጸሎት ነው፡፡ የገዳማት መፈታት የመነኮሳት ከበዓታቸው መውጣት ይህን የሕብረት ጸሎት ያስተጓጉለዋል፡፡

ድውያነ ስጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የሚፈውሰውን ስፍራና ገዳማውያኑን ዛሬ ካልታደግን ዳሩ ሲወረር መሀሉ ዳር ይሆናል የሚለው ይፈጸምብናል፡፡ የተወረወረብን ጦር፣ የተመከረብን ክፉ ምክር በግላጭ ያገኙናል፡፡ በግንብ የታጠረ ቤታችን አቅበን የያዝነው ንብረታችን አይታደጉንም፡፡

ከፀሎትና ከድካም መልስ የሚጠለሉበትን፣ ከፆም መልስ የሚቀምሱትን ነገር ልናቀርብላቸው ይገባል። ለሰማያዊ ህይወታችን ስንቅ ይሆነናል ከመነኮሳቱ ፀሎት የበረከት ተካፋይ እንሆናለን፥ ለህሊናችንም እረፍት እናገኝበታለን።

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444


የ USAID መቋረጥ ምን ያመጣብናል?

ሙሉ ለሙሉ አይተውንም እንጂ ከተረጂነት መንፈስ እንወጣ ነበር:: ሀገራችን ላይ ከ3 ሜትር ጀምሮ ውኃ አለ:: ግን በውኃ ጥም እንደኛ የሚሰቃይ የለም:: ማዕድናት እንደኛ ያለበት ሀገር መጥቀስ ይከብዳል:: አዲስ አበባ ውስጥ ሳይቀር ብዙ ማዕድናት አሉ:: የጫካውን ... (ሌላ ነገር ውስጥ አታስገቡን):: ሶማሌ ክልል ያለው የእርሻ መሬት አፍሪካን መቀለብ ይችላል:: ከጥልቅ ዳሎል እሳት እስከ ራስ ደጀን በረዶ ዐለም ያለው የአየር ንብረት ሁሉ አለን:: የአዲስ አበባ አየር በሹካ ተጠቅልሎ በማንካ የሚጎረስ የሚመስል እኮ ነው:: ሁሉንም ነገር ተሰጥቶን ሁሉንም ነገር ያጣን የነጣን ሆነን ነው::

ኑሮአችን አኗኗራችን ቀርቶ ሕግ ሁላ የሚወጣው በምቀኝነት ነው:: በስንት ልፋት, እንቅልፍ ማጣት እና ጥበብ የሆነ ሥራ ከሠራህ "በየት በኩል አምልጦን ከበረ?" ብለው ይከቡሃል:: ሳትወድ በግድ የማልመጡን መንገድ ትለማመዳለህ:: ብዙ ከሠራህ ብዙ የምትቀጣበት ሲስተም ውስጥ ነን:: አሜሪካ ዕርዳታ ብትቀንስ የለማኝ ነገር ወደ ቻይናና ራሽያ እንጠጋለን::

እንደው በምታምኑበት ይዣችሗለሁ:- ድንጋይ ለመፍለጥ, መሬት ለማረስ የትኛው የውጭ እርዳታ ያስፈልጋል? ብር ቸግሮን? በፍጹም:: ብር እኮ በነጻ የሚፈጠር ጸጋ ነው:: መንግሥት በማንኛውም ሰከንድ ያሻውን ያህል ብር መፍጠር ይችላል:: የውጭ ዕርዳታ የሚጠቅመን የውጭ ምንዛሪ ስለሆነ ከውጭ ለሚገባ ምርት እና ለዕዳ ክፍያ ነው::

ያው የፈረደባትን ቻይናን ምሳሌ ላድርግና 1959-1961 ጫማ ያስበላ ረሃብ ውስጥ የገባችው ቀደም ብላ የውጭ እርዳታ አስቁማ ወደ ኢንደስትሪ ገብታ ነው:: በኢንደስትሪው ምክንያት ብረት ተወደደና ገበሬው ማረሻውን ሁላ በኪሎ ሸጠ:: ግብርና ቀነሰ:: ረሃብ መጣ:: ሕዝቡ ለአመጽ ወጣ:: መንግሥት ወጥሮ ያዘ:: የግብርናና የኢንደስትሪ ባንክ አቋቁሞ, ታክስ ቆርጦ ጥሎ ዘመቻ ገባበት:: ታክስ መንግሥትን አስንፎ ሙሰኛን ይቀፈቅፋል::

የኢንደስትሪ ባንኳ ከዓለም 2ኛ ሲሆን የግብርና ባንኳ ከዓለም 4ኛ ነው::
ከስምንት ዓመታት በላይ በዕርዳታ ድርጅት ውስጥ ሠርቻለሁ:: የዕርዳታ ድርጅቶች የስለላ ሰንሰለቶች ናቸው:: እኛ በሁለቱም እግራችን ማጥ ውስጥ ስለገባን ቶሎ መውጣት ያዳግተን ይሆናል:: ግን መውጣት የግድ ይለናል::

Abdulkadir Hajj Nureddin

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል በታላቅ ድምቀት ተጠናቀቀ

"ስፖርት ለአንድነት እና ለጋራ ዕድገት"በሚል መሪ ቃል አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከጥር 17-27 /2017 ዓ፣ም ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል ዛሬ ተጠናቋል።

አጠቃላይ አሸናፊ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን የፀባይ ዋንጫ አዲግራት ዩንቨርሲቲ ወስዷል ።

በፌስቲቫሉ በባህላዊ ስፖርት
✔️ ቡብ ጨዋታ ሴት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፣
✔️በቡብ ወንድ ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ፣
✔️በገበጣ ሴት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፣
✔️በገበጣ ወንድ ወልዲያ ዩንቨርሲቲ ፣
✔️በወርልድ ቴኳንዶ  ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ፣
✔️በእግር ኳስ ወሎ ዩንቨርሲቲ፣
✔️በቼዝ ሴት አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣
✔️በቼዝ ወንድ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣
✔️አትሌቲክስ ወንድ ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ እና
✔️አትሌቲክስ ሴት የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ  የዋንጫ አሸናፊ ሆነዋል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሦስት ዘመናዊ የመምህራን መኖሪያ አፓርትመንቶችን አስመርቋል

ዩኒቨርሲቲው ሦስት አፓትርትመንቶችን በ677 ሚሊዮን ብር ወጭ አስገንብቶ ለመምህራኑ አስረክቧል፡፡ መኖሪያ ቤቶቹ ባለ አንድ፣ ባለ ሁለት እና ባለሦስት መኝታ ዘመናዊ ቤቶች መሆናቸውን የገለፁት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) ፤ መኖሪያ ቤቶቹ ከ200 በላይ የተቋሙ መምህራንን ተጠቃሚ ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡

መኖሪያ ቤቶቹ ውሃ፣ ኤሌክትሪክ፣ ዘመናዊ ሻወርና ሽንት ቤት፣ ማዕከላዊ የቴሌቪዥን እና የዲሽ መቆጣጠሪያ፣ የእሳት አደጋ መከላከያ፣ ዘመናዊ የፍሳሽ አገልግሎት ማስወገጃ እና የውስጥ ለውስጥ የእግረኛ መንገዶች እንደተሟላላቸውም አብራርተዋል፡፡

በቀጣይ የተጨማሪ ሁለት አፓርትመንቶች ግንባታ ለማከናወን እየተሠራ መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ፤ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የጤና ኮሌጅን ለመገንባት ከከተማ አስተዳደሩ ቦታ መጠየቁንም አንስተዋል፡፡

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


#Inbox

በ AnyDesk ሶፍትዌር እና ሌሎችም በመጠቀም የመውጫ ፈተና ለተማሪዎች በውጭ እየተፈተኑላቸው ነው። ለመፈተን ከ 7,000 እስከ 20,000 ብር እየተቀበሉ ነው የሚፈተኑላቸው ለህክምና ተማሪዎችም ጭምር ። ባስቸኳይ መፍትሄ ቢደረግ !!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ወሎ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች የስፖርት ውድድር የእግር ኳስ ሻምፒዮን ሆነ

የዩኒቨርስቲዎች የስፖርት ውድድር ከዘጠኝ ዓመታት መቋረጥ በኋላ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ነው፡፡ ውድድሩ በአምስት የስፖርት ዓይነቶች ሲካሄድ ሰንብቶ አብዛኞቹ ተጠናቀዋል፡፡ ከእነዚህ ውድድሮች መካከል 45 ዩኒቨርስቲዎች የተሳተፉበት የእግር ኳስ ውድድር በወሎ ዩኒቨርስቲ አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡

ዛሬ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ሜዳ ከዋቻሞ ዩኒቨርስቲ ጋር የፍጻሜ ጨዋታውን ያደረገው ወሎ ዩኒቨርስቲ 1ለ0 አሸንፎ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡ በሁለቱም ቡድኖች በኩል ተመጣጣኝ እንቅስቃሴ የታበትን የፍጻሜ ጨዋታ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንት ደረጄ እንግዳ( ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች የስፖርት ማህበር ፕሬዚደንት አቶ አባይ በላይሁንን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተከታትለውታል፡፡

ከፍጻሜው ጨዋታ ቀደም ብሎ በተደረገው የደረጃ ጨዋታ ጎንደር ዩኒቨርስቲ አርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲን 3ለ2 አሸንፎ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ውድድሩን አጠናቋል፡፡

የ2017 የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች የስፖርት ውድድር ነገ ረፋድ ለአሸናፊዎች እውቅና፣ ሜዳሊያና ዋንጫ በመስጠት እንደሚጠናቀቅ አዘጋጆቹ አሳውቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች የስፖርት ውድድር ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ በክላስተር ደረጃ በአምስት ዞኖች ለማካሄድ ዝግጅት መደረጉን መገለጹ የሚታወስ ነው፡፡ #AMN

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


Exit Exam

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ Exit Exam ላይ ተማሪዎች በጥበቃ ሰራተኞች በተደረገ ፍተሻ ስልኮችን ይዘው ሊገቡ ሲሉ በቁጥጥር ስር ውለዋል:: በዚህም ምክንያት ተማሪዎቹ ወደ ፈተና እንዳይገቡ ታግደዋል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


Examination Tips

Before the Exam

👉Revise Smartly – Focus on key topics, summaries, and important points rather than trying to read everything.
👉Get Enough Sleep – A well-rested mind performs better. Avoid staying up all night.
👉Stay Hydrated & Eat Well – Have a balanced meal before the exam to maintain energy levels.
👉Organize Your Materials – Carry required items like pens, pencils, erasers, a calculator (if allowed), and your ID card.
👉Arrive Early – Reach the exam hall with enough time to settle down and stay calm.

✅ During the Exam

👉Read Instructions Carefully – Ensure you understand the rules, question formats, and any special instructions.
👉Manage Your Time – Allocate time for each question based on marks and difficulty. Keep an eye on the clock.
👉Start with Easy Questions – Answer familiar questions first to build confidence and secure marks early.
👉Stay Calm & Focused – If you get stuck, take deep breaths and move to the next question. You can return to it later.
👉Answer in a Structured Manner – Use bullet points, subheadings, and diagrams where applicable for clarity.
👉Show Your Work – In calculations or problem-solving questions, write down steps to get partial marks even if the final answer is incorrect.
👉Review Your Answers – If time permits, go through your answers to correct mistakes and add missing points.

After the Exam

👉Avoid Overthinking – Don't stress about what went wrong; focus on your next exam.
👉Learn from Mistakes – If possible, review answers to understand what you can improve for future exams.
👉Stay Positive – A single exam doesn’t define your abilities. Stay motivated for the next challenge!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library




የሐዘን መግለጫ
============
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽት እና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊት ሃኪም፣ ተመራማሪ እና መምህር እንዲሁም በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር የነበሩት ዶ/ር አንዷለም ዳኘ ጠብቀው በተወለዱ በ37 አመታቸው በደረሰባቸው ድንገተኛ ሞት የተሰማንን መሪር ሃዘን እየገለፅን ለሟች ቤተሰቦች፣ ጓደኞች፣ የሥራ ባልደረቦች እና ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ መፅናናትን እንመኛለን።

ዶ/ር አንዷለም በዩኒቨርሲቲያችን፣ ብሎም በአገራችን አሉን ከምንላቸው በቁጥር ትንሽ የዘርፉ ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞቻችን ውስጥ አንዱ የነበሩ ሲሆን ከስራ ውለው ወደቤታቸው ሲመለሱ በአጋጠማቸው ግድያ ህይወታቸውን አጥተዋል። በሐኪማችን ላይ ያጋጠመውን ግድያ እና በተደጋጋሚ በዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች ላይ እየደረሰ ያለውን ተደጋጋሚ ያልተገባ መሰል ድርጊት ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ በጥብቅ ያወግዛል። በየትኛውም አካል ሊሰነዘር የሚችል ይሄን አይነት መሰል ድርጊትም ለአገርም ሆነ ለወገን አጉዳይ እንጅ አንዳች የሚጨምር ነገር እንደሌለ ሁሉም ሊገነዘበው የሚገባ ጉዳይ ነው።

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ከCGPA በላይ Exit Exam ውጤት ተመራጭ እየሆነ ነው

Exit Exam ማለፍ ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ ውጤት ማምጣት ለቅጥር ተመራጭ እየሆነ ነው ።

የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ አንዳንድ ቀጣሪዎች CGPAን ትተው የExit Examን ውጤት ሰራተኛ ለመቅጠር እያዩ ነው ።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


🌟 Exciting News, GLOBEDOCK ACADEMY Family! 🌟

We are thrilled to announce that GlobeDock Academy has been selected for the Legacy Builders Award at the Great Rift Valley Innovation Summit! 🎉

This recognition is a testament to the power of education and the incredible learning community we’ve built together. But now, we need your support to win!

🗳 Vote for GlobeDock Academy and help us make history!

👉 Click here to vote : https://vote.grvsummit.com/dashboard


📢 Spread the word! Share this with your friends, classmates, and family so we can achieve this milestone together.

Thank you for being part of our journey! Let’s keep shaping the future of education! ✨


በሜታ ወልቂጤ በአንዲት ታዳጊ ህጻን ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ሜታ ወልቂጤ ወረዳ አንዲት ህጻን ከቤት ተወስዳ ከተደፈረች በኋላ ተገድላ መገኘቷ ቁጣ ቀስቅሷል። “በኛ የደረሰ በማንም አይድረስ” የሚሉት የተጎጂ ቤተሰብ በታዳጊ ልጃቸው ላይ ለደረሰው ቀሰቃቂ ወንጀል ፍትህ እንሻለለን ብለዋል።

ሲምቦ ብርሃኑ ትባላለች፡፡ የስምንት ዓመት ታዳጊ ህጻን ናት፡፡ የአንደኛ ክፍል ተማሪ፡፡ በዚሁ ባሳለፍነው ሳምንት ባለፈ ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ከትምህርት ቤት ተመልሳ ምሳ እንደበላች ከመኖሪያ ቤቷ የደረሰችበት ሳይታወቅ ቀርቷል ፡፡ በዕለቱ ፍለጋ የወጣው ቤተሰብ ታዳጊዋን ከነሙሉ ጤንነትና በህይወት ለማግኘት ግን አልታደሉም፡፡

ሮጣ ያልጠገበች ታዳጊዋ ለአዕምሮም በሚከብድ ሁኔታ ከተደፈረች በኋላ “እንዳትናገር በሚል” ከመኖሪያ ቤታቸው ጀርባ በቅርብ ርቀት ላይ ህይወቷ አልፎ መገኘቱን አንድ የቤተሰቧ አባል ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል። ታዳጊዋ ከተገደለች በኋላ ተሰቅላ መገኘቷን የገለጹት የቤተሰብ አባሉ “ጫማዋን ያወለቁባትና የሰቀሏት ቦታ አንድ አይደለም የ50 ሜትር ገደማ ርቀት አለው” ብለዋል።

በወረዳው የኤላ ከተማ በታዳጊዋ ላይ የተፈጸመው ጥቃት አባት የመንግስት ሰራተኛ መሆናቸው እና በስራ ቦታ መሆናቸው እንዲሁም እናት የ2 ወር እመጫት በመሆናቸው አጋጣሚውን በመጠቀም እንደነበር የቤተሰቡ አባል ተናግረዋል።

የተጎጂ ቤተሰብ አባል የሆኑት አስተያየት ሰጪ ቀጥለው፤ “የታዳጊዋ ቤተሰብ ቤት በፊት ለፊት በኩል ሆቴል በመሆኑ የሚገባውና የሚወታው ብዙ ነው፡፡ በጓሮ በኩል ፑል መጫወቻም አለ፡፡

ደፋሪዎችም በዚያው በጀርባ በር እንደወሰዷት ነው የቤተሰብ ስጋት” ያሉን አስተያየት ሰጪው፤ 2009 ዓ.ም. የተወለደችው ታዳጊዋ ሲምቦ ገና በ8 ዓመቷ ለዚህ ለአሰቃቂው ድርጊት ሰለባ መሆኗን በቁጪት ተናግረዋል፡፡

“ባለሙያዎች በሰውነቷ ላይ የታየውን ፈሳሽ በመውሰድ ምርመራ እያደረጉ ነው” ያሉን የቤተሰብ አባል እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋለ ተጠርጣሪ አለመኖሩንም ገልጸዋል፡፡ ባለፈው ረቡዕ ከሰዓት በኋላ 9 ሰዓት ተኩል የተገኘው የታዳጊዋ አስክሬን በትናንትናው እለት ስርዓተ ቀብሩ መፈጸሙን የአዲስ አበባው ወኪላችን ስዩም ጌቱ ዘግቧል።

ዶቼ ቬለ በታዳጊዋ ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ድርጊት እና ቀጣይ እርምጃዎች ለመጠየቅ ለወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ አጀማ በእጅ ስልካቸው ላይ ቢደወልም ስልካቸው ስለማይነሳ አስተያየታቸውን በዚህ ዘገባ ማካተት አልተቻለም፡፡
ምስል ፤ ከቤተሰብ አባል የተገኘ
#DW #ዶቼ_ቬለ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

9.3k 0 15 7 100

GlobeDock Academy is honored to be recognized at the Great Rift Valley Innovation Summit! 🎉 Now, we need your support to win the People’s Choice Award! 🏆

📚 Support GlobeDock at the GRV Summit and help us continue transforming education in Ethiopia.

🗳 Cast your VOTE NOW! 👇
🔗 https://vote.grvsummit.com/dashboard


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library








Mekdela Amba University Vacancy

Experience: 0 year

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የቻይና ሲሆን ደህንነት ምናምን ይላሉ...አይ አለም

ጣሊያን ከሰሞኑ መነጋገሪያ የነበረውን የAi app Deepseek ን ከደህንነት ስጋት ጋር በተገናኘ ምክንያት አግዳለች::

ያም ሆነ ይህ ቻይና አሜሪካን መገዳደር ጀምራለች::

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

Показано 20 последних публикаций.