Ethiopian Digital Library


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


በዚህ ቻናል ስለ
👉ትምህርት፣
👉ሥራ እና
👉ማህበራዊ ጉዳይ
መረጃ ያገኛሉ!
Contact: @ethiodlbot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций




የሚመለከታችሁ ሁሉ

መረጃውን ለማግኝት ይህንን ሊንክ ይጫኑ

https://forms.gle/N8uPaW7uXYTEZWQC8

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የውጭ አገር የትምህርት ዕድል ያገኘውን ጓደኛውን በመርዝ ገደለ

በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የዘንድሮ ተመራቂ የነበረው ውብሸት አስቤ ከአሜሪካ ፊሊድያ ዩንቨርስቲ ነፃ የትምህርት እድል አግኝቶ ለጉዞ እየተዘጋጀ ባለበት የቅርብ ጓደኛው ዶርም ውስጥ #በመርዝ እንደተገደለ የአስክሬን ውጤቱ ያሳያል።

ወጣት ውብሸት እጅግ በጣም ትሁትና ታታሪ መሆኑን ብዙዎች ይመሰክራሉ። ይሁን እንጂ በጉብዝናውና በመልካም እድሎቹ ላይ በመቅናት እጅግ በሚከረፋ መርዝ ህይወቱን ነጠቁት።

በአረብ ሀገር እየለፋች ያስተማረችው እህቱ በወንድሟ ፅኑ ተስፋ የነበራት ቢሆንም በምቀኝነትና በክፋት ተነሳስተው የወንድሟን ነፍስ ፣ ህልሙንና ተስፋውን በማጨናገፋቸው ከመሞት ያልተናነሰ ተስፉ መቁረጥ ውስጥ ትገኛለች። እጅግ ከባድ የመንፈስ ስብራት ደርሶባታል።

በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ይህንን ከባድ ወንጀል የፈፀመው ተጠርጣሪ ጓደኛው የህግ ጠበቃ ይዘው የተከራከሩ ሲሆን በሟች ቤተሰብ በኩል "ቸልተኛ" አቃቤ ህግ ብቻ በመሆኑ #ገዳይ ከእስር ሊፈታ ጫፍ ደርሷል።

የሟች ቤተሰብ ተስፋና ማረፊያቸው የነበረውን ወጣት ልጃቸውን መነጠቃቸው ሳይበቃ ጭራሽ የልጃቸው ገዳይ በነፃ መፈታቱ የእግር እሳት የሆነ ህመምና ለልጃቸውም ሁለተኛ ሞት ነው።

Sentayehu Hailu

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

5.5k 0 38 6 101

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ለሰራተኞቹ ከ33% -99% የደመወዝ ጭማሪ አድርጓል!

ሰራተኞቹ የደመወዝ ጭማሪው በዝቅተኛ የደመወዝ እርከን ላይ ያሉትን ከግምት ያላስገባ ነው በሚል ቅሬታ እያቀረቡ ነው።

👉የደረጃ 1 ደመወዝ ብር 1779 የነበረዉ ወደ 2949 አድጓል።
👉የደረጃ 2 ደመወዝ ብር 1838 የነበረው ወደ 3904 አድጓል።

በክልል ደረጃ የሚገኙ ከፍተኛ የሰራ ሃላፊዎችና አመራሮች 96% እና 99% ጭማሪ ተደርጓል።

👉የደረጃ 12 ደመወዝ ብር 16,021 የነበረዉ ወደ 24,583 ሲያድግ ብር 8562 ጭማሪ ተደርጓል
👉የደረጃ 13 ደመወዝ ብር 13,689 የነበረዉ ወደ 26530 ሲያድግ ብር 11,036 ጭማሪ ተደርጓል
👉የደረጃ 14 ደመወዝ ብር 14,372 የነበረዉ ወደ 26,830 ብር 14,258 ጭማሪ ተደርጓል።

አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ለሰራተኞች ያደረገው የደመወዝ ጭማሪ ዝቅተኛ የደመወዝ ተከፋይ የሆኑ ሰራተኛን ያላማከለ እና ከስራ ጫናው ጋር ተመጣጣኝ አለመሆኑን ቅሬታቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


“መምህራን እየተራቡ የትምህርትን ጥራት ማረጋገጥ አይቻልም” መምህራን

ለዩኒቨርሲቲ መምህራን እየተከፈለ ያለው ክፍያ ከአንድ የባንክ ቤት የጥበቃ ሰራተኛ ያነሰ ነው!

“የመምህራንን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ትምህርትን ለማሻሻል በጣም ወሳኝ ነው” የትምህርት ሚኒስቴር


ትውልድ ፊደል ቆጥሮ ከህልሙ እንዲደርስ መንገድ ጠራጊው፣ አቅጣጫ ጠቋሚው መምህር ለሞያው የሚከፈለው ክፍያ ዝቅተኛ በመሆኑ ለማስተማር ፍላጎት እንዲጣ ምክንያት እንደሆነ ጥናት አሳይቷል፡፡ በደባርቅ ዩኒቭርሲቲ መምህር የሆኑት አቶ ፈለቀ ወርቁ “የዩኒቭርሲቲ መምህራን ሀገር እንድትቀጥል የማድረግ ሃላፊነት እንዳለባቸው ተናግረው ይህን ማድረግ የሚችሉት ግን ሳይርባቸው ማስተማር ሲችሉ ነው” ብለዋል፡፡

“የዩኒቨርሲቲ መምህራን እየተራቡ ሀገርን አያስቡም ያሉት መምህሩ አሁን ለመምህራን እየተከፈለ ያለው ክፍያ ከአንድ የባንክ ቤት የጥበቃ ሰራተኛ ያነሰ ነው” ሲሉ ነግረውናል፡፡ በዚህም ምክንያት መምህሩ ሞያውን ለቆ ወደ ሌላ ስራ እየገባ ነው ያሉት አቶ ፈለቀ ወርቁ ‘’መምህሩ ኑሮ አይደለም እየኖረ ያለው  ከኑሮ በታች ነው’’ ብለዋል፡፡ የመምህር ኑሮ በቃል የሚገለጽ አይደለም ከሚያስተምረው የሚማረው ተማሪ የተሻለ ለብሶ እየገባ፣ የተሸለ ኑሮ እየኖረ በሁሉ ነገር ዝቅ ያለ መምህር እንዴት ተማሪ ፊት ቆሞ ነው ማስተማር የሚችለው? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ‘’መምህሩ ዛሬ የተቀደደ ሱሪ ነው ልብሶ የሚሄደው ካለሲ መቀየርያ አጥቷል’’ ሲሉ መምህሩ ተናግረዋል፡፡

ባለፈው ሳምንት የትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፍተና ውጤት ማሽቆልቆልን ምክንያት ለማውቅ ያስጠናው ጥናት መምህራን የሚከፈላቸው ክፍያ ዝቅተኛ መሆኑ የማስተማር ፍላጎታቸው ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩን የጠቆመ ነበር፡፡ ጥናቱ ለውይይት በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በቀረበበት ወቅትም በወይይቱ የተሳተፉ የትምህርት ተቋማት የስራ ኃላፊዎች፣ መምህራን እና የምክርቤት አባላት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የመምህሩን ኑሮ ማሻሻል ተገቢ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

በወቅቱ የተገኙት እና ማብራሪያ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የመምህራንን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ከፋይናንስ ሥርዓት ጋር ለማስተሳሰር እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ይሁንና የመምህራን የደመወዝ ጥያቄ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድረስ ቢደርስም ለዓመታት እልባት ሳያገኝ የቀጠለ ጉዳይ ሆኗል፡፡

ሸገር ኤፍኤም

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

8.4k 0 20 16 111

ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ ማሳሰቢያ ተሰጠ

ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ የኢንፎርሜሽን መረብ አስተዳደር ኤጄንሲ አሳስቧል።

አስተዳደሩ የኢንተርኔት አጠቃቀም በየቀኑ እየጨመረ በሄደበት በዚህ ዘመን፤ ከዚህ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ስጋቶችም እየተስፋፉ መሆናቸውን ገልጿል።

በቅርቡም በርካታ አደገኛ የኢንተርኔት አድራሻዎችን (URLs) መርምሮ፣ እነዚህ አድራሻዎች የኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በይበልጥ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች አካውንቶችን በመንጠቅ ከፍተኛ ስጋት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ ማረጋገጡን አስታውቋል።

እነዚህም ከተለያዩ አካላት በቴሌግራም የሚደርሱ ሊንኮች በርካታ አደጋዎችን የሚይዙ ሲሆን፤ የሚከተሉት አደጋዎች በዋናነት ይገኙበታል።

👉 የግል መረጃ መጠለፍ፦ እንደ የባንክ መለያ ወይም የይለፍ ቃል ያሉ መረጃዎችን መሰረቅ፤

👉የማልዌር ስርጭት፦ ስልኮችን ወይም ኮምፒውተሮችን የሚጎዱ ቫይረሶች፤

👉ማጭበርበሪያ፦ ተጠቃሚዎችን በሀሰተኛ ተስፋዎች (እንደ ውርርድ ወይም ኢንቨስትመንት) መታለል እንደሚገኙበት ገልጿል።

በመሆኑም ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ ያሳሰበው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር፤ ሰሞኑን በቴሌግራም ከሚላኩና ማኅበረሰቡ በፍጹም ሊከፍታቸው ከማይገቡ ሊንኮች መካከል ጥቂቶቹን ይፋ አድርጓል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ማኅበረሰቡ በቴሌግራሙ ላይ አጠራጣሪ የሆኑ ሊንኮች ሲያጋጥሙት፤ ለኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር  e-mail: ethiocert@insa.gov.et
ወይም ነጻ የስልክ መስመር፡ 933 ማሳወቅ የሚችል መሆኑን አስታውቋል።

ሰሞኑን በቴሌግራም ከሚላኩና በፍጹም ልንከፍታቸዉ ከማይገቡ ሊንኮች መካከል ጥቂቶቹ ከላይ በምስሉ ተያይዘዋል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library




ደደብ በመሆኔ ተመስገን

ጎበዝ ተማሪ ብሆን ኖሮ በ 9000 ብር ደሞዝ አማርር ነበር። ትምህርቴን ከ9 ነው ያቋረጥኩት አሁን ላይ የዶክተሮችን የወር ደሞዝ በቀን ላገኘው እችላለሁ :: ብቻ ደደብ በመሆኔ ፈጣሪን የማመስግንበት ቀን ይመጣል ብዬ አስቤ አላውቅም። ተመስገን!

Credit: Gursha Page

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

9k 0 35 27 188

በዚህ ስልክ ደውለው ያግኙ፡- 0926708054/ 0921113942

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ የዩኒቨርስቲ መንደር እንዲመሰረት ተወሰነ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓ.ም. ባደረገው የ4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ስብሰባ በአዲስ ከተማ ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ ባለው የከተማው ክፍል የዩኒቨርስቲ መንደር እንዲመሰረት ወስኗል፡፡

ውሳኔው በዚህ ኮሪደር ወስጥ አምስት ካምፓሶች፣ ኮሌጆችንና ምርምር ኢንስቲትዩቶችን፣ ዋናው መሥርያ ቤትና ሁለት ሙዚዬሞች ላሉት አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከፍ ያለ ጥቅም እንደሚያስገኝ ይጠበቃል፡፡

በቀጣይ ኮሪደሩ የትምህርት ፣ ምርምር፣ ባህልና ተጓዳኝ ጉዳዮችን ማዕከል በማድረግ ሲለማ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከዓለም አቀፍ የምርምር ተቋማት፣ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችና አገር ውስጥ አልሚዎች ጋር ለመሥራት የተመቸ ሁኔታ ስለሚፈጠርለት በተልዕኮው ልቆ ለመውጣት በእጅጉ ያግዘዋል፡፡

በተጨማሪም አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጀመራቸውን ፕሮጄክቶችና ወደፊት የሚያከናውናቸውን ሥራዎች በዚሁ የዩኒቨርስቲ መንደር እሳቤ በመምራት በአህጉራችን አፍሪካ የከፍተኛ ትምህርት መዳረሻ ለመሆን ብሎም አገራችን ኢትዮጵያ ባላት ወጣት ትውልድ የስታርትአፖች መፍለቂያ ለመሆን ከተጀመረው ተግባር ጋር ተመጋጋቢ እንዲሆን ይረዳል::

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ለአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ የሚውል ገቢ፤ ከግለሰቦች እና ከሰራተኞች ደመወዝ እንዲሰበስብ የሚያስገድደው የአዋጅ ረቂቅ ጥያቄ ተነሳበት 

ከሁለት ሳምንት በፊት ለፓርላማ በቀረበው የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር የአዋጅ ረቂቅ የተካተተው እና “ለአደጋ ስጋት ምላሽ” የሚውል ገንዘብ ከግለሰቦች አንዲሰበሰብ የሚያዝዘው ድንጋጌ ጥያቄ ተነሳበት። የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በበኩሉ ከሰራተኞች ደመወዝ እና ከግለሰቦች የሚጠበቀው መዋጮ መጠን፤ ወደፊት ውይይት ከተካሄደበት በኋላ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚወጣ ደንብ የሚወሰን መሆኑን ገልጿል።

ለዝርዝር ዕይታ ለፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ የተመራው አዋጅ፤ የመንግስት እና የግል ተቋማት ከሚሰጧዋቸው የተለያዩ አገልግሎቶች “ለአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ” የሚውል ገቢ እንዲሰበስቡ ያስገድድዳል።

ከሀገር ውስጥ የገቢ ምንጭ ለመሰብሰብ በአዋጁ ከተዘረዘሩ 15 አይነት አገልግሎቶች መካከል “የመንግስት እና የግል ድርጅት ተቀጣሪ ሰራተኞች ከሚከፈላቸው የተጣራ ደመወዝ ላይ የሚታሰብ” የሚለው ይገኝበታል። 

አዋጁ የተመራለት የፓርላማው የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ሰኞ መጋቢት 29፤ 2017 ባዘጋጀው የአስረጂ እና የባለድርሻ አካላት መድረክ፤ ከተለያዩ አገልግሎቶች ላይ የሚሰበሰበው ገቢ የግለሰቦችን የመክፈል አቅም ያገነዘበ መሆኑን በተመለከተ ጥያቄ ቀርቦበታል።

የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የህግ ዳይሬክተር አቶ አማረ ኢቲቻ፤ ለአደጋ ስጋት ፈንድ ገቢ እንዲሰበሰብባቸው የሚጠበቁ አገልግሎቶች “ካየን ወደ ግለሰቦች ነው የሚሄደው” ብለዋል። “ይህንን ሁሉ ግለሰቦች afford ማድረግ ይችላሉ?” ሲሉ ጠይቀዋል።

Ethiopia insider

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


Job Title: Male Voiceover artist for youtube channel

Job Type: Remote - Contractual

Work Location: from Anywhere/remote

Applicants Needed: Male

Salary/Compensation: Monthly

Deadline: April 19th, 2025

Description:
ጥሩ ለትረካ የሚሆን ድምፅ ያለው ወንድ ተራኪ ለYoutube ቻናላችን እንፈልጋለን

-   የራሱ ጥሩ record ማድረጊያ ማይክ ያለው

-   ክፍያ 15 ብር በደቂቃ

-   ለማመልከት sample voice በ @kbtube251 ላይ መላክ ትችላላችሁ


Dr. Seid Adem እባላለሁ፡፡ ስራ ከጀመርኩ አንድ አመት ሆኖኛል፡፡ በ6ኛ ወሬ እናቴ ደውላ "ልጄ መጥቼ ልይህ?" አለች፡፡ ደነገጥኩ!! አትምጭ እናቴ እኔ መጥቼ አይሻለሁ ብዬ መለስኩላት፡፡ እሷም የቅሬታ በሚመስል ድምፅ "እሺ" አለችኝ፡፡

አትምጭ ያልኳት ሀኪም ሆነልኝ ያለችኝ እናቴ የምኖረውን ህይወት አይታ ልቧ እንዳይሰበርና እንዳታዝን ነበር፡፡ ቤት ውስጥ ከአንድ ፍራሽ ውጭ ምንም ነገር የለኝ... ምን ላይ ታርፋለች? እስካሁን እኔም ሄጄ አላየሗት፡ ምን ይዤ ልያት!

Credit: hakim

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የጤና ባለሙያዎች ፍትሃዊ ክፍያን ጨምሮ ሌሎች ጥያቄዎቻቸው ምላሽ ካላገኘ ስራ የማቆም አድማ እንደሚያደርጉ አስጠቀቁ

የጤና ባለሙያዎች ፍትሃዊ የደመወዝ ክፍያ፣ የጤና መድን ሽፋን እና የተሻሉ ጥቅማጥቅሞች እንሟሉላቸው የሚጠይቅ የተቀናጀ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ መጀመራቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ አስታወቁ።

ዶክተሮችን፣ ነርሶችን፣ ስፔሻሊስቶችን እና የቀዶ ጥገና ሐኪሞችን ጨምሮ የጤና ባለሙያዎች፤ "ህይወት ስናድን ኖረናል፤ አሁን የራሳችንን ህይወት ማዳን ይኖርብናል" የሚሉ ሃሽታጎችን በመጠቀም ጥያቄዎቻቸውን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች እያሰሙ ይገኛሉ።

አንድ የጤና ባለሙያ፤ "በዚህ ሰዓት የጤና ባለሙያው ለኑሮ ውድነት ተጋላጭ ሆኖ ነው ያለው። ሲያመው እንኳን ለመታከም የማይችልበትና ወደ ልመና የሚገባበት ክስተት ተፈጥሯል። የቤት ኪራይ እንኳን መክፈል አቅቶት መኖር ያልቻለበት ሁኔታ በመፈጠሩ ድምጻችንን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲሰማን ነው ንቅናቄውን የጀመርነው" ሲሉ ተናግረዋል።

Credit: addis standard

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ትግራይ ክልል 1.2 ሚሊየን ልጆች ወደ ትምህርት ገበታ አልተመለሱም

በትግራይ ክልል 1.2 ሚልዮን ሕፃናት እና አዳጊ ልጆች ወደ ትምህርት ገበታ አለመመለሳቸው ተገለጸ።  የክልሉ ትምህርት ቢሮ እንደገለጸው በትግራይ ከጦርነቱ በኋላ ጭምር የቀጠለው ሰብአዊ፣ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግር ሚልዮኖች ከትምህርት ገበታ እንዲርቁ አድርጓል።

በዚህም ላይ እስካሁን መፍትሔ ያላገኘው የተፈናቃዮች ጉዳይ ሌላው ልጆች ትምህርት ቤት እንዳይ ሄዱ እንቅፋት እንደሆነም ተገልጿል። በዚህ ዓመት በትግራይ ክልል 2.5 ሚልዮን ተማሪዎች ነበሩ ወደ ትምህርት ቤት ይገባሉ ተብሎ የታሰበው፤ ሆኖም አሁን በትምህርት ገበታ ላይ የሚገኙት 1.3 ሚልዮን ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን የትግራይ ትምህርት ቢሮ ሐላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዑሽ ተናግረዋል።

ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱ ተማሪዎች ቁጥር ከመቀነሱ ጎን ለጎን የትምህርት ጥራቱ ላይም ክፍተት እየተስተዋለ መሆኑ ተገልጿል ።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library








ሃገር በቀል እውቀት ጥንቁልናን ይጨምራል ማለት ነው?
አንዱ ይጨምራል አይለኝም መሰላቹ!

በነገራችን ላይ አዲሱ የትምህርት ካሪኩለም የሃገር በቀል እውቀትን አካቷል ተብሏል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


"ታቱ" /ንቅሳት/ የማይፀዳ ቆሻሻ ነው - አሌክስ አብርሃም

ንቅሳት (Tattoos) በፈቃደኝነት ቆዳን ዳግመኛ እንዳይፀዳ አድርጎ ማቆሸሽ ነው። በምንም የማይፀዳ ብቸኛ አካላዊ ቆሻሻ ታቱ ብቻ ነው። በጨረር ህክምና /Laser Removal/ እንኳን በተሳካ መንገድ ማፅዳትና ቆዳ ወደነበረበት ተፈጥሮ መመለስ አይቻልም። የንቅሳቱ መልዕክት ምንም ይሁን ንቅሳቱ በራሱ ግን ለቆዳ ያው ቆሻሻ ነው። ባለማወቅ ይደረግ በማወቅ ለውጥ የለውም።

ይህ ማለት ግን ንቅሳት ያላቸው ሰወች መጥፎ ናቸው ማለት አይደለም። 67 በመቶ የሚሆኑ ባለንቅሳቶች ከተነቀሱ ከ5-10 ዓመታት በመነቀሳቸው ይፀፀታሉ። 82 በመቶ የሚሆኑ ወጣቶች ዕድሚያቸው ከፍ ሲል በተነቀሱት ፅሁፍ ወይም ምስል ያፍራሉ፤ ይህም የሚሆነው አሁን ካሉበት የእምነት ፣ የፖለቲካ ወይም የሕይወት ፍልስፍናቸው ጋር ስለሚጣረስ ነው።

ንቅሳት ዘመናዊነት አይደለም። ለምሳሌ ጥርሳችሁን ማብለዝ ወይም ማጥቆር ፋሽን ቢሆን ብላችሁ አስቡት። የሰው ልጅ በጊዜ ሂደት ሐሳቡን የሚቀይር ፍጡር ነው። ለሚያልፍ ቀን የማያለፍ ቃል አትናገር ሲባል ሰምታችኋል። ለታቱም ይሰራል። ለሚያልፍ ስታይል ቆዳችሁን በማያልፍ ንቅሳት አታቆሽሹ።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

Показано 20 последних публикаций.