ቸርች እንዴት ነበር?
(How was Church?)
....ልብን ይመረምራል...
✍️ ሁልጊዜ ልንረዳ የሚገባው ነገር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ልብ ሲል የስጋውን ልብ እንዳልሆነ ነው። ምክንያቱም የስጋው ልብ እና መጽሐፍ ቅዱስ ሊነግረን የፈለገው ልብ የተለያየ በመሆኑ ነው።
#የሰው_ሕይወት_ሁኔታ_የልቡ_ሁኔታ_ነው!
ሰዎች ሁልጊዜ የሚያዩት ፊትን ወይንም የሚታየውን ሁኔታ ነው። እግዚአብሔር ግን ልብን የሚመዝን እና የሚመረምር አምላክ ሲሆን፤ ክፍያንም የሚሰጠው እንደ ልብ ሁኔታ ነው። ለዛም ነው ብዙ ጊዜ ሰዎች የሚሸውዱን በሚያሳዩን የፊት ገፅታ ነው።
#ልብን_የመመርመር_ስራ_የእግዚአብሔር_ስራ_ነው!
እግዚአብሔር የሰውን ልብ መርምሮ በልቡ ውስጥ እንዳገኘው ንፅህና ወይም ቅንነት በተቃራኒው ደግሞ በልቡ
ጥፋት ሊመጣ ሲል ሞገስ በእግዚአብሔር ፊት ማግኘት ከኖኅ፤ ከልቡ ትህትና የተነሳ ለሌላው ኃጥያት የሆነ ለእርሱ ችግር ያልፈጠረበት ዳዊት በሰው አይን ቅጣት የሚያስፈርጅ ነው በእግዚአብሔር ፊት ግን ልባቸው ሚዛን ደፍቷል።
ዳዊት በዘመኑ ሁሉ እግዚአብሔርን ልብን እንደሚመረምር በማወቅ ደጋግሞ የሚለው ነገር ልቡን እንዲመረምር እና እንዲፈትን ነበር። ስለዚህ በእግዚአብሔር ፊት ልባችንን በማስፈተሽ እርሱ እንደሚፈልገው ልናደርገው ይገባል።
ሬቨረንድ ተዘራ ያሬድ
ቀን እሁድ 29/07/2016
⛪️ የክብር ሕይወት ቤተክርስቲያን
አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ
መልካም ምሽት!
Join Us:-
Telegram
https://t.me/GospelTvEthiopiaYoutube
@gospeltvethiopiaofficial9652?si=3D3RdKlFUZl7uZhh' rel='nofollow'>
https://youtube.com/@gospeltvethiopiaofficial9652?si=3D3RdKlFUZl7uZhh
Facebook
https://www.facebook.com/RevTezerayared?mibextid=ZbWKwL