Habesha news🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


News and entertainment

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций






ሚኒስትሯ የአፍሪካ ምርጧ የባህልና ቱሪዝም መሪ ተብለው ተሸለሙ፡፡
ባሕር ዳር፡ ኅዳር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ኂሩት ካሳው የ2019 ምርጧ የአፍሪካ ቱሪዝም መሪ (WOMEN IN AFRICA TOURISM 2019 MOST ENERGETIC AND PASSIONATED AFRICAN TOURISM LEADER AWARD) አሸናፊ ሆነው መመረጣቸውን በጋና የሚገኘው ስትሪት ኦፍ ጎልድ ፋውንዴሽን የተሰኘው ድርጅት አስታውቋል፡፡
ሽልማቱ ከቀናት በኋላ ከአስር ቀን በኋላ ታህሳስ 3 ቀን 2013 ዓ.ም አዲስ አበባ እንደሚደረግ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከሽልማት ኮሚቴው ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ በይፋዊ የማኀበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡
ሚኒስትሯ በይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው ሽልማቱን አስመልክቶ ባሰፈሩት መልዕክት "በቱሪዝም፣ በሆቴልና መስተንግዶ በአጠቃላይ በዘርፉ ላይ ለተሰማራችሁ እና ለባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሰራኞተችና የሥራ ኃላፊዎች በሙሉ እውቅናው የእናንተው ነውና እንኳን ደስ አላችሁ" ብለዋል፡፡
እጅ ለእጅ ተያይዘን ከሰራን ገና ሩቅ እንጓዛለን ነው ያሉት ሚኒስትሯ 👍


ሚኒስትሯ የአፍሪካ ምርጧ የባህልና ቱሪዝም መሪ ተብለው ተሸለሙ፡፡
ባሕር ዳር፡ ኅዳር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ኂሩት ካሳው የ2019 ምርጧ የአፍሪካ ቱሪዝም መሪ (WOMEN IN AFRICA TOURISM 2019 MOST ENERGETIC AND PASSIONATED AFRICAN TOURISM LEADER AWARD) አሸናፊ ሆነው መመረጣቸውን በጋና የሚገኘው ስትሪት ኦፍ ጎልድ ፋውንዴሽን የተሰኘው ድርጅት አስታውቋል፡፡
ሽልማቱ ከቀናት በኋላ ከአስር ቀን በኋላ ታህሳስ 3 ቀን 2013 ዓ.ም አዲስ አበባ እንደሚደረግ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከሽልማት ኮሚቴው ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ በይፋዊ የማኀበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡
ሚኒስትሯ በይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው ሽልማቱን አስመልክቶ ባሰፈሩት መልዕክት "በቱሪዝም፣ በሆቴልና መስተንግዶ በአጠቃላይ በዘርፉ ላይ ለተሰማራችሁ እና ለባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሰራኞተችና የሥራ ኃላፊዎች በሙሉ እውቅናው የእናንተው ነውና እንኳን ደስ አላችሁ" ብለዋል፡፡
እጅ ለእጅ ተያይዘን ከሰራን ገና ሩቅ እንጓዛለን ነው ያሉት ሚኒስትሯ


የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአስር ዓመት ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ሽልማትን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 22፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአስር ዓመት ውስጥ የአፍርካ ምርጥ አየር መንገድ ሽልማት አሸናፊ መሆኑ ተገለጸ። ለአቪዬሽን ኢንዱስትሪው አስቸጋሪ በሆነው የአፍሪካ ቀጣና እና ፈታኝ በሆነ ወቅት ባስመዘገበው ድንቅ ስኬት መሸለሙም ታውቋል። እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እውነተኛው የፓን አፍሪካኒዝም ምሳሌ በመባል አድናቆት ተችሮታል። አየር መንገዱ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ያስመዘገበው ትርፍም የስኬት…

https://www.fanabc.com/የኢትዮጵያ-አየር-መንገድ-የአስር-ዓመት-ም/


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከህዳር 22 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በአሮጌው የብር ኖት መገበያየት እንደማይቻል ገልጿል፡፡
በባሕር ዳር ከተማ ግብይት እንዴት እየተፈፀመ እንደሚገኝ አብመድ ቅኝት አድርጓል፡፡
ባሕር ዳር፡ ኅዳር 22/2013 ዓ.ም (አብመድ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከህዳር 22 ጀምሮ በነባሩ የብር ኖት መገበያየት እንደማይቻል አስታውቋል፡፡
የብር ኖቶቹ በባንክ ቤት እንዲቀየሩ መመሪያ ቢያስተላልፍም ጥቂት የማይባሉ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተገበያዩበት መሆኑን አብመድ ዛሬ በባሕር ዳር ከተማ ገበያ ባደረገው ቅኝት መታዘብ ችሏል።
በባሕር ዳር ከተማ አዲሱ የብር ኖት በአብዛኛው በግብይት ላይ እየዋለ ቢገኝም በግብይት ላይ እንዳይውል መከልከል በጀመረበት በዛሬው ዕለት ግን አሮጌው የብር ኖትም ሥራ ላይ እየዋለ ነው፡፡
አቶ ሰርጉ አክሊሉ የሚተዳደሩት በንግድ ሥራ ዘርፍ ነው፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ነባሩ የብር ኖት በገበያ ላይ እንደማይውል መረጃ ቢኖራቸውም ደምበኞቻቸውን ላለማስከፋት ብለው ሲቀበሉ መዋላቸውን ተናግረዋል፡፡
የተሰጠው የቀን ገደብ ከመጠናቀቁ በፊት ነባሩን የብር ኖቶች መቀየር ስለሚችሉ ከደንበኞቻቸው እየተቀበሉ መሆኑን ነው አቶ ሰርጉ የተናገሩት፡፡ ደንበኞች በድጋሜ ሲመጡ አዲሱን የብር ኖት ብቻ ይዘው እንዲመጡ እየመከሩ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
ሲገበያዩ ካገኘናቸው ውስጥ ወጣት ትዕግስት አለነ እንደተናገረችው "ከዛሬ ጀምሮ በአሮጌው ብር መገበያየት እንደማይችል መረጃው አለኝ፤ ለዚህም ነው አዲሱን የብር ኖት ለግብይት ይዤ ወደ ገበያ የወጣሁት" ብላለች፡፡
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የባሕር ዳር ተወካይ ጥናትና ምርምር ባለሙያ አቶ አንተነህ ገረመው ኅብረተሰቡ የቀሩት ቀናት ውስን ስለሆኑ ሳይዘናጋ አሮጌውን የብር ኖት ወደ ባንክ በማምራት እንዲለውጥ አሳስበዋል፡፡
አሮጌውን የብር ኖት በአዲሱ የብር ኖት ለመቀየር መንግሥት ሦስት ወራትን የሰጠ መሆኑ ያስታወሱት ተወካዩ ከዛሬ ጀምሮ ኅብረተሰቡ በነባሩ ብር ግብይት መፈጸም ሳይሆን ወደ ባንክ ቤት ሄዶ መቀየር እንደሚገባውም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡


አስተያየት
ሀሳብ
ጥያቄ
ካላችሁ @Daverrr በዚህ ሊንክ ጻፉልኝ




መልካም ቀን ይሁንላችሁ
አዳዲስ መረጃዎች ቶሎ እንለቃለን😘😘😘👍👍👍








የዩኒቨርሲቲዎች ጥሪ ፦

1. የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የ2012 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች እና የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች (2 ኛ ዓመት እና ከዛ በላይ) ዳግም ቅበላ ህዳር 25 እና 26 (አርብ እና ቅዳሜ) ቀን 2013 ዓ/ም እንዲሆን ተወስኗል። ስለዚህ ከላይ በተገለፁት ቀናት ወደ ዩኒቨርሲቲ እንድትገቡ ተብሏል። ትምህርት ህዳር 28/2013 ይጀምራል።

2. የጅማ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ተመራቂ ተማሪዎች ምዝገችሁ ህዳር 28 ፣29 እና 30/2013 ዓ/ም ነው።

በዚህ ምዝገባ ቀናት የሁሉም ዓመት የትያትር፣ መዚቃ እና ቪዡዋል አርት፣ ነባር PGDT እንዲሁም የ3ኛ ዓመት የባዮሜዲካል እና የ4ኛ ዓመት የማቴሪያል ሳይንስ እና የኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባችሁብ እንድትፈፅሙ ተብሏል።

የነባር እና አዲስ ድህረ ምርቃ ፕሮግራም ተማሪዎች ከላይ በተጠቀሱት ቀናት ምዝገባችሁን እንድትፈፅሙ ተብሏል።

3. የጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የ2012 ተመራቂ ተማሪዎች ብቻ መግቢያ ቀን ህዳር 26 እስከ ህዳር 28 ነው።

@tikvahethmagazine @tikvahmagBot


ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም ለመንግስት እጅ ሰጡ

ከተፈላጊ የህወሓት ጁንታ አባላት አንዷ የሆኑት ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም ለመንግስት እጅ ሰጡ።

ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም የህውሓት ከፍተኛ አመራርና በመንግስት ከፍተኛ ሃላፊነት የነበራቸው እንዲሁም በፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤነት አገልግለዋል።

ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም የህወሓት ጁንታው ጥቅምን ይሻለኛል ብለው ወደ መቀሌ የሸሹ ሲሆን ሾፌራቸው ግን የመንግሥትን ንብረት ለጁንታው አልሰጥም ብሎ ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ ይዞት መምጣቱ ይታወሳል።

ከዚህም ጋር ተያይዞ በሰላማዊ መንገድ እንደ ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም ሌሎችም የህወሓት አመራሮች እጅ እንዲሰጡ መንግሥት ጥሪውን አቅርቧል።

@newsetv


እንዴት ናችሁ ወገኖች ሰላም






👉አጠር ያለ አስተማሪ መልዕክት👈

♥አንድ ሰው ነበር በባህር ብቻውን በመርከብ እየተጓዘ
በመዓበል ተመታና መርከብ ተሰባብሮ በባህሩውሰጥ
ሰመጠች ሰውዬው እንደምንም እራሱን አድኖ አንድ ደሴት ላይ ያርፍና ጎጆ ነገር ሰርቶ ለቀናት ለብቻው
እዛች ደሴት ላይ ይኖራል ,,,,,,,,ምግብን ዓሳ እያጠመደ እየተመገበ ብዙ ቆየ።

♥አንድ ቀን ዓሳ ሊያጠምድ ወደ ባህሩ እየሄደ በመሀል እዛች ባህር ላይ ጭስ ይሸተዋል ዞር ብሎ ሲመለከት
ያቺ ጎጆው እየነደደች ነው ,,,,,,,እየሮጠ ቢመለስም ጎጆዎን ሊያድናት አልቻለም ለካ ዓሳ ለማብሰል ያቀጣጠለው እሳት ተያይዞ ጎጆውን አንድዷታል አለቀሰ ፈጣሪወን ወቀሰ እንዴት እዚህ ባህር ላይ ለብቻዬ ጥለከኝ ከቤተሰቦቼ ነጥለክኝ ስታበቃ በስንት ልፋት የሰራዋትን ጎጆ ታቃጥልብኛለክ ብሎ አለቀሰ
አማረረ,,,,,,,, ከደቂቃዎች በዋላ አንድ ድምፅ ሰማ ወደ
ድምፁ ፊቱን ሲያዞር አንድ ትልቅ መርከብ አየ ተደሰተ ,,,,,, የመርከብ ሰዎችም መጥተው ጭነው ወሰዱት
ከዚያም ለመርከብ ሰዎች ጠየቃቸው !
እንዴት አገኛችሁኝ እዚህ አካባቢ እዚህ ባህር ላይ ማንም አይመጣም እኮ እናንተ እንዴት መጣችሁ ?
አላቸው ,,,,, መርከበኞቹም እኛም በዛኛው በኩል ዞረን
እየሄድን ነበር ከዚያ በኩል ጭሰ አየንና እዚህ ሰው ይኖራል ብለን መጣን አንተ አገኘን አሉት።

♥አቤት ጌታዬ ለካ ከዚህ ከስቃይ ልታወጣኝ ፈልገህ
ነው ትንሻ ጎጆዬን ያፈርሰከው ወደ ትልቁ ቤቴ ልትወሰደኝ ነው ። አለ
♥አንዳንዴ የሆነ ነገር ስናጣ ሲበላሽብን ፈጣሪንም ሰውንም ስናማርር እንኖራለን ግን ካጣነው ነገር ከጎደለብን ነገር ጀርባ ብዙ ጥሩ ነገር ልናገኝ እንደምንችል እንዘነጋለን በችግራችን ጊዜ መጠጋት
ያለብንን አንድዬን እንረሳለን ከዚያም አልፈን የሁሉ ነገር ፈጣሪውን እንኮንነዋለን ።

🌹ያጣነውን የሰጠን አንድዬ ! አህምሮችን ከሚያስበው በላይ ሊሰጠን እንደሚችል ማመን አለብን !

ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር ማድረጎን አይርሱ

🌷መልካም ቆይታ🌷
🌹🌷🌷🌹
🌹
ጎራ በሉ👇👇👇
@TRUTHZONE
@TRUTHZONE




የቻናላችን ቤተሰቦች

Показано 20 последних публикаций.

9 174

подписчиков
Статистика канала