Vocal Clinic🎷🎺🎸🎹🎻📡🔭


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Музыка


Vocal Clinic Project is a music project which aims at providing music training resources for singers and musicians.
Welcome to @MyVocalClinic_bot

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Музыка
Статистика
Фильтр публикаций




Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram




Vocal Exercise: Five notes scale








Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


ዛሬ ምሽት ከ 3:30 ሰአት ጀምሮ ከሙዚቀኛ አዲሱ ኩሰያ (composer) እና ከሙዚቀኛ ሙሴ መኮንን (drummer) ጋር በTikTok Live @vocalclinic22 እንጠብቃችኋለን።


ዛሬ ማታ ከ3:30 ሰዓት ጀምሮ በ ቮካል ክሊኒክ TikTok ላይቭ ገብቼ አንዳንድ የቮካል ትምህርቶችን አካፍላችኋለሁ፣ ከቻላችሁ ትካፈሉ ዘንድ እጋብዛችኋለሁ።
@vocalclinic22




Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


ልዩ የድምጽ ስልጠና ከቮካል ክሊኒክ

ጊዜ: ከመስከረም እስከ ህዳር 2016 (ሶስት ወራት)
ቦታ: መገናኛ ታላቁ ተልዕኮ ግቢ
በአማራጭ ፈረቃ
በሳምንት ለ 2 ቀናት ማታ 12:00 - 1:30
ቅዳሜ ጠዋት (3:00 - 6:30) ወይም ከሰዓት በኋላ (9:00 - 12:00)

ምዝገባ ተጀምሯል ፈጥነው ቦታ ይያዙ (0911697704)


👫 ይጋብዙ እና ገንዘብ ይስሩ !

🎁 አንድ ሰው ሲጋብዙ 3 ብር ይሰራሉ ።

እስካሁን የጋበዙት ሰው መጠን: 0 ሰው
ይሄን ሊንክ በመጠቀም እራሶም ይመዝገቡ ለሌም በማስመዝገበ ብር ይስሩ 👍👍👍👍👍👍
🔰 መጋበዣ ሊንክ : https://t.me/hulepay_official_bot?start=r0430380913

✅ ዛሬውኑ ጀምሮ ገንዘብ ያካማቹ እና በቴሌብር ይቀበሉ ።
100% ይሰራል አትጠራጠሩ ሞክሩ ምንም አትጎድም


ይድነቃቸው ተካ

ሁሉም ባህል ልምምድ እና የአምልኮ ሥርዓት ለክርስቶስ አካል አይዋጅም

በመናፍስቱ አለም የተፈበረኩና የሚዘወተሩ ልምምዶችን ባህላትን እና የአምልኮ ሥርዓቶችን በየቱም መልክ የክርስቶስ አካል ላይ አምጥቶ የአምልኮ እና የልምምድ አካል ማድረግ አግባብ አይደለም ምክንያቱም እነዚያ ልምምዶች እና ስርዓቶች በመናፍስቱ ዓለም እንደ ባህል ወይም እንደ ልምምድ ብቻ ተደርገው የሚወሰዱ ሳይሆኑ ከመንፈሳዊ ነገር ጋር የተያያዘ ትርጓሜ ያላቸው ናቸው

ለክርስቶስ አካል እንግዳ እና መጤ ከመሆናቸው ባለፈ በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ሲከበር ከኖረው ልምምድ እና የአምልኮ ሥርዓት ጋር የማይዛመዱ ናቸው።

You can't sanctify, exercise and domesticate the rituals and cultures in the body of Christ that are originated, cultured and fabricated in any form by the evil spirit world. Those cultures and rituals have spiritually associated connotations. They are not to be taken as mere cultures.

They are spiritually foreign and bizzare in the church of Christ and mismatch the longstanding heritage celebrated throughout church history.

Yidnekachew Teka


Репост из: Vocal Clinic🎷🎺🎸🎹🎻📡🔭
ላውያን አብያተ ክርስቲያናት ያስተዋወቀ ክስተት ነበር:: ይህም የአገልግሎት አቅጣጫ በመስፋፋት በአሁኑ ወቅት በመላ አገሪቱ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት አዲስ የአምልኮ ባህል ሆኖ እንደቀጠለ ይገኛል::

ማጣቀሻዎች:
* ሄርበርት ሎክየር ጁኒየር - ኦል ዘ ሚዩዚክ ኦፍ ዘ ባይብል,
  ፒቦዲ, ማሳሹሴትስ: ሄንድሪክሰን ፐብሊሸርስ, 2004.
* ዮናስ ጎርፌ - ቤት ያጣው ቤተኛ: ሙዚቃ, ሙዚቀኝነት እና
   የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን, አዲስ አበባ, ርሆቦት ፕሪንተርስ,
   2016.
* ጥበበ እሸቴ - ዘ ኢቫንጀሊካል ሙቭመንት ኢን ኢትዮጵያ:
   ሬዚስታንስ ኤንድ ሬዚሊየንስ, ቤይለር ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ,
   2009.
* ግሬግ ማካቤ - ቢብሊካል ዎርሺፕ: ፐርሱንግ ኢንቲሜሲ ዊዝ
   ጋድ, ብሉሚንግተን, ዌስትቦው ፕሬስ, 2015.

አማኑኤል አበራ
ሰኔ 2010
 


Репост из: Vocal Clinic🎷🎺🎸🎹🎻📡🔭
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሙዚቃ ታሪክ

የኢትዮጵያ የቤተ ክርስቲያን ሙዚቃ ታሪክ መነሻው "ያሬዳዊው" የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሙዚቃ እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ይጠቁማሉ:: ቅዱስ ያሬድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሙዚቃ ውስጥ ትልቁን ድርሻ ይዞ የሚገኝ ሲሆን የጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን ሙዚቃ ጠንሳሽና አባት ተደርጎ ይቆጠራል:: ቅዱስ ያሬድ ከ1500 ዓመት በፊት አክሱም ውስጥ የኖረና በዘመኑ ብቻ ሳይሆን እስከዛሬም ድረስ ሕያው የሆኑ ስራዎችን በማበርከቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አማኞች ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው እውቅ የዜማና የቅኔ ደራሲ ነበር:: የያሬድ ድርሰቶች በሶስት ዘርፍ የተከፈሉ ሲሆን እነርሱም ዕዝል: ግዕዝ እና አራራይ በመባል ይታወቃሉ:: ከዚህ ባሻገር ያሬድ የራሱን የሙዚቃ ምልክቶች በመፍጠርና ስራዎቹ ላይ በመጠቀም ይታወቃል::
ከዛ ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የዝማሬ አገልግሎት በያሬድ ስራዎች ላይ የተንጠለጠለ ሆኖ እናገኘዋለን:: በመሆኑም የቅዱስ ያሬድ ደቀ መዛሙርት የሱን ስራዎች በማዳረስና በቤተ ክርስቲያኒቱ የአምልኮ ስርአት ውስጥ ትልቅ ድርሻ እንዲኖረው የበኩላቸውን አስትዋፅኦ አበርክተዋል:: ከዛ በኃላም የተነሱት ዘማሪያን የርሱን ፈለግ በመከተል እስከዛሬም ድረስ "ያሬዳዊ ዝማሬ" የቤተ ክርስቲያኒቱ መለያ ሆኖ እንዲቀጥል አስችሎታል::

በአንፃሩ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሙዚቃ ታሪክ መነሻው ከአውሮፓውያን ሚሲዮናውያን ወደ ኢትዮጵያ መምጣትና ከጴንጤቆስጤአዊነት መስፋፋት ጋር የተቆራኘ እንደሆነ ታሪክ ያስረዳል:: ኢትዮጵያ ውስጥ የወንጌል እንቅስቃሴ የተጀመረው እ.አ.አ. በ1970ዎቹ መጨረሻ ገደማ የስዊድን ሚሽነሪዎች በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኘው ሐማሴን ወይም ባህረ ነጋሽ እየተባለ ይጠራ በነበረ ስፍራ የሚሽን ተቋም በመሰረቱበት ወቅት ነበር:: ሂካ ነሲብ ወይም ኦኒሲሞስ ይባል የነበረውና ነፃ የወጣው ባርያ በኢትዮጵያ የወንጌላውያን ሚሽነሪዎችን ስብከት የተቀበለና የውሃ ጥምቀት የወሰደ የመጀመሪያው ሰው ነበር:: በወቅቱ ይህ ክስተት በኢትዮጵያ የወንጌላውያን/ፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናትን ውልደት ያበሰረ ነበር:: ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ የወንጌላውያን እንቅስቃሴዎች ተካሂደው ስለነበር ትክክለኛውን የጴንጤቆስጤያዊነት መነሻ ጊዜ መናገር አይቻልም:: "The Free Finish Foreign Mission" የተባለ የፊንላንድ የሚሽን ተቋም በአናሊዛ እና ሳንፍሪድ ማትሰን እ.አ.አ. በ1951 በአዲስ አበባ እና በአስመራ ተመሰረተ:: በ1950ዎቹ የነበረው ጴንጤቆስጤያዊ እንቅስቃሴም በኢትዮጵያ ለነበረው የወንጌል ስራ ብዙ ገፅታ እንዳላበሰው ይታወቃል::

በንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዘመነ መንግስት ከተለያዩ የክርስትና ዘርፎች በርካታ ቁጥር ያላቸው ሚሲዮናውያን ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ በመፈቀዱ ምክንያት ለወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት መስፋፋት በር እንደከፈተ ይታመናል:: እንግዲህ ከአብያተ ክርስቲያናቱ መስፋፋት ጋር ተያይዞ ለጋራ አምልኮ የሚሆኑ ዝማሬዎች አስፈላጊነትም አብሮ በማደጉና በኢትዮጵያዊ ቋንቋዎች የተፃፉ ዝማሬዎች አለመኖር ምክንያት ሚሲዮናውያኑ ይዘዋቸው የመጡት አውሮፓዊ ዝማሬዎች (hymns) ወደ አማርኛ ተተርጉመው ለአገልግሎት ውለዋል:: እነዚህ ትርጉም ዝማሬዎች እንደ ፒያኖና ኦርጋን ባሉ መሳሪያዎች አጃቢነት በህብረድምፅ ተቀናብረው በምዕራባውያን የአምልኮ ስልት ይዜሙ ነበር:: ይህም አጋጣሚ በኢትዮጵያ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሙዚቃ ጅማሮና እድገት ውስጥ አዲስ የአምልኮ ዘይቤን በማስተዋወቅና የምዕራባውያንን መዝሙሮችና የአምልኮ ስልቶችን ቤተኛ በማድረግ ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክቷል::

በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናቱ የሚታየው የዝማሬአዊ አምልኮ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ የያሬዳዊ ዝማሬ ስልት በእጅጉ የተለየ ነው:: የሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ኢትዮጵያዊ የሆኑ ዝማሬዎችን በማስተዋወቅ ረገድ ትልቁን ድርሻ ይዛ እናገኛታለን:: ቀደም ሲል ይዘመሩ የነበሩት አውሮፓዊ ይዘት ያላቸው ዝማሬዎች በመሆናቸው ለኢትዮጵያውያን አድማጮች ባዕዳን ነበሩ:: በዚህም ምክንያት በርካታ ቁጥር ያላቸው የሶሎና የህብረት መዘምራን ከሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን በመነሳት ለወቅቱ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት የዝማሬና የሙዚቃ አገልግሎት እድገት ትልቅ ድርሻ አበርክተዋል:: በ1960ዎቹ አጋማሽ አካባቢ ሌሎች ተጨማሪ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት የየራሳቸውን የመዘምራን ህብረት በማቋቋም ህብረቶቹ ወጥ የሆኑ አዳዲስ ዝማሬዎችን እንዲያቀርቡ በማበረታታት የክርስቲያን አድማጮቻቸውን ልብ ለመግዛት ችለዋል: በአንፃሩም ኢትዮጵያዊ ጣዕም ያላቸውና በባህላዊው ፔንታቶኒክ ቅኝት ላይ የተመሰረቱ ወጥ የዝማሬ/የሙዚቃ ስራዎች እንዲፈጠሩ ምክንያት ሆነዋል:: ከዚህም የተነሳ አማኙ ሕብረተሰብ መዝሙሮቹን ሳቢና ከየዕለተ ተዕለት መንፈሳዊ ሕይወታቸው ጋር የተቆራኙ ሆነው አግኝቷቸዋል:: በወቅቱ የዝማሬዎቹ ይዘት÷ ቃላትና ፍልስፍና ኢትዮጵያዊ ቢሆኑም የሚጠቀሟቸው የሙዚቃ መሳሪያዎች ፍፁም አውሮፓውያን ነበሩ: በመጀመሪያ ላይ ፒያኖና ኦርጋን ይጠቀሙ የነበረ ቢሆንም ቀስ በቀስ ግን እንደ አኮርዲዮንና አኩስቲክ ጊታር የመሳሰሉት መሳሪያዎች መካተት ችለዋል:: ይሁን እንጂ እንደ ሲንቲሳይዘር÷ ኪቦርድ እና መሰረታዊ የባንድ የሙዚቃ መሳሪያዎች በአብያተ ክርስቲያናቱ የሙዚቃ አገልግሎት ውስጥ ለመካተት ረጅም ጉዞ መጓዝ አስፈልጓቸዋል::

በ1960ዎቹ አጋማሽ ገደማ በየአብያተ ክርስቲያናቱ የተቋቋሙት የመዘምራን ህብረቶች ለበርካታ ሶሎ ዘማሪያንና መዝሙር ደራሲያን መፍለቂያ በመሆን በወቅቱ ተፈጥሮ ለነበረው ፈጣን የሆነ የአገልግሎቱ የእድገት ጉዞ እጅግ ላቅ ያለ ድርሻ አበርክተዋል:: ይሁን እንጂ እንዳለመታደል ሆኖ ከ1967 እስከ 1982 ዓ.ም. ድረስ ባሉት ቀጣዮቹ ሁለት ምዕተ ዓመታት በወቅቱ የነበረው ወታደራዊ የአገዛዝ ፍልስፍና በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናትም ሆነ በመንፈሳዊው ሙዚቃ የእድገት ጉዞ ላይ አሉታዊ አሻራውን ጥሎ ያለፈ የታሪክ አጋጣሚ ሆኗል:: በርካታ ክርስቲያኖች ተሰደዋል: ታስረዋል:: ያም ቢሆን ግን እንደ አዲሱ ወርቁ÷ ደረጄ ከበደ÷ ተስፋዬ ጋቢሶ÷ ሸዋዬ ዳምጤ÷ ታምራት ኃይሌ እና ስዩም ገብረየስ ያሉ ድንቅ ዘማሪያን በጨለማው ውስጥ የወንጌልን ብርሃን ለማብራትና የምስራቹን ቃል ለማስፋፋት የተነሱበት ወቅት ነበር::

የደርግ አገዛዝ መውደቅን ተከትሎ የሶሎ የዝማሬ አገልግሎት ሰፊ እውቅና ያገኘ ሲሆን አዲስ የሆነም የጋራ የአምልኮ ስርአት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ማቆጥቆጥ ጀመረ:: ጌታያውቃል ግርማይና ብሩክታዊት ደግሞ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ናቸው ÷ በርካታ የሁለትዮሽ የዝማሬ ቅጂዎችን በማዘጋጀትና በማሰራጨት ጉልህ ድርሻ አበርክተዋል:: ጌታያውቃል በቤተ ክርስቲያን የሙዚቃ ቅጂ ታሪክ ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ ይዞ የሚገኝ ሲሆን የርሱ ታናሽ የዘመናዊ ስቱዲዮ ጅማሬ ከመንፈሳዊው የሙዚቃ ዘርፍ አልፎ ለአገሪቱ የሙዚቃ እድገትም ላቅ ያለ ሚና ማበርከቱ አይካድም:: በአሁኑም ወቅት በርካታ ቁጥር ያላቸው ትንንሽ ስቱዲዮች በመላ አገሪቱ በሚገኙ ዋና ዋና ከተሞች ይገኛሉ:: ከዚህ ጋርም ተያይዞ በ1980ዎቹ እና 90ዎቹ እንደ ቃልኪዳን ጥላሁን (ሊሊ) እና እንዳልካቸው ሐዋዝ (እናዋ) የመሳሰሉ ዘማሪያን መነሳት "የአምልኮ መምራት" አገልግሎትን ለኢትዮጵያ ወንጌ


ኧረ መቼ ነው????

ከ1980ዎቹ አጋማሽ አንስቶ እስከ 90ዎቹ መጨረሻ ድረስ በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ያመልክና ያገለግል የነበረ አማኝ ሁሉ በወቅቱ ስለነበሩ የእነ ተስፋዬ ጫላ፣ ዳንኤል አ/ሚካኤል፣ ሊሊ ጥላሁን፣ ቤቲ ወልዴ፣ ዮሴፍ አያሌው፣ አውታሩ ከበደ፣ መስፍን ጉቱ፣ ቤቲ ተዘራ፣ ወዘተ ዝማሬዎች ብዙ ማለት ይችላል ብዬ አምናለሁ። መዝሙር ከነሙሉ ለዛውና ጣዕሙ፣ ድንቅ በሆኑት የወቅቱ የሙዚቃ ጠበብት ክርስቲያን ግርማ፣ አቤንኤዘር ግርማ፣ እንቁ ግርማ፣ ብሩክ በድሩና ሌሎችም ተቀናብሮ በሲዲ ከእጃችን ይደርስ ነበር (እድለኛው ትውልድ)። ዝማሬዎቹ የነበራቸው ዜማዊና ሙዚቃዊ መልክ በእያንዳንዱ ዝማሬ ውስጥ ከሚነሱት ጠንካራ ጭብጦች ጋር ተዋህደው የሚቀርቡበት ሁኔታ እጅግ ማራኪና ፍጹም አለማዊነት የማይንጸባረቅበት ነበር። ያ ዘመን በኢትዮጵያ የዝማሬ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ድርሻ እንደሚወስድ ባምንም በሁሉ ረገድ እንከን የማይወጣለትና ፍጹም ነበር ሊባል አይችልም፣ ነገር ግን የእድገት ተስፋን የሰነቀና ጉዞውን የጀመረ ነበር ለማለት እደፍራለሁ።

ይሁን እንጂ ምክንያቱን በግልጽ እንዲህ ነው ማለት በማይቻልበት ምክንያት የዝማሬአችን መልክ ተቀይሮ ፍጹም አለማዊ መልክን ተላብሶ ከመገንባት ይልቅ የማፍረስ ጉዞውን ከተያያዘ ሁለት አስርት አመታት ሊደፍን እየተንደረደረ ይገኛል፣ በተለይ ደግሞ ባለፉት አስር አመታት። በእርግጥ ሁሉም ዘመን የየራሱ መልክና አካሄድ እንዳለው ባምንም መሰረቱን እየሳተ ሳይሆን በተመሰረተው ላይ እየተገነባ መሄድ እንዳለበት ነው የማምነው። ዛሬ ዛሬ እጅግ በርካታ ዘማሪያንና ሙዚቀኞች በአገልግሎት መስኩ ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ ይታወቃል። እንግዲህ ይሄ ሁሉ የዝማሬ አገልጋይ ምን አይነት አስተዋጽኦ እያደረገና ምን አይነት በጎ ተጽዕኖ እየፈጠረ እንደሆነ ቆም ብለን ልንጠይቅ ያስፈልገናል። እስከመቼ ድረስ ነው መድረኮቻችን የጭፈራና የዝላይ ማዕከል እንደሆኑ የሚቀጥሉት? መቼ ነው ህይወት ያለው እውነተኛ መዝሙር ህይወት ባለው መንገድ ተዘምሮ የአምልኮ ጥማችንን የምናረካው? አንዴ መስማት ከጀመርን ማቆም እስከማንችል ድረስ የምንሰማቸው ዝማሬዎችን ዘማሪዎቻችን እንካችሁ የሚሉን? ቤተክርስቲያንን ከመድረኳ ገለል ያደረገችው የሶሎና የኳየር አገልግሎት ወደቤቱ የሚመለሰው? በዚህ ሁሉ ውጥንቅጥ ውስጥ ብቅ ብቅ የሚሉ የዝማሬና የሙዚቃ ስጦታዎችን አክብረን የምንይዘው? ጆሮዎቻችንን እና ልቦቻችንን በእግዚአብሔር ቃልና መንፈስ ለተሞሉ ዝማሬዎች የምናዘነብለውስ? ኧረ መቼ ነው????

እኔ "ዝማሬ ድሮ ቀረ" ከሚሉት ወገን አይደለሁም ነገር ግን ከዛሬ ነገ ይሻል ይሆን ይሆናል ብለን የጠበቅነው ይሄ የአገልግሎት ዘርፍ እለት እለት በተለያዩ አቅጣጫዎች ሲፈራርስ ዝም ብሎ የማየት አቅሙም ፍላጎቱም ስለሌለኝ ነው ይህን ጽሑፍ ለመጻፍ የተነሳሁት። እግዚአብሔር በየዘመናቱ የሚሰራባቸው ቅሬታዎች ስላሉት ዛሬም በአገልግሎታቸውና በህይወታቸው የሚባርከን ድንቅ የዝማሬና የሙዚቃ አገልጋዮችን እንዳስነሳ እመሰክራለሁ። ቢሆንም ግን እነኚህ አገልጋዮች እንደሚገባ መድረክና ሚዲያ ሳያገኙ በአንጻሩ ደግሞ ሌላ ዘማሪ የሌለ እስኪመስል ድረስ ተመሳሳይ መድረክ መሪ ግለሰቦችን እዚህም እዚያም ማየቱ የተለመደ ሆኗል።

በእግዚአብሔር ዘንድ እውቅና በሌለው አገልግሎት በሚመስል ውክቢያ ውስጥ ተጠላልፋችሁ ያላችሁ ዘማሪያን ወገኖቼ እባካችሁ ልብ ግዙ። ብዙዎች ዋጋ ከፍለውበት እኛ ጋር የደረሰውን ወንጌልና የዝማሬ አገልግሎት አትቀልዱበት አታቃልሉት፣ እግዚአብሔር የሰጣችሁንም ጸጋና ጥሪ አታቃልሉት፣ አክብራቹ ያዙት። በእርግጥ አገልግሎታችሁ ለሌሎች መሰናከል ወይስ በረከት ስለመሆናችሁ ቆም ብላችሁ ራሳችሁን ጠይቁ። እግዚአብሔር ባሰማራችሁ መስክ ላይ እየተጋችሁ ካልሆነ ፈጥናችሁ ለመመለስና የአባታችሁን ፈቃድ ዋጋ በመክፈል ለመፈጸም ትተጉ ዘንድ ጥሬን አቀርብላችሁአለሁ። የቤቱ ባለቤት ወደመቅደሱ በመጣ ጊዜ ስንሸቅጥ እንዳያገኘን ፈጥነን እንንቃ። እንግዲህ እኛ በብዙ ውጥንቅጥ ውስጥ ሆነን ደህና ነን ብለን ከምንገበዝ ካለፈው ስህተታችን ተምሮ የሚያርም ልቦና እንዲሰጠን በእግዚአብሔር ፊት ራሳችንን ብናዋርድ ይበጀናል።




Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram

Показано 20 последних публикаций.

3 775

подписчиков
Статистика канала