Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


كناشة ابن منور

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


አንብብ!
~
"ተማሪ በፈተና ሌሊት እንዴት እንሚያጠና ተመልከቱ። የዚያ አምሳያ - በየሌሊቱ አልልም - በየሳምንቱ አንድ ጊዜ ቢያጠና ትልቅ ዓሊም ይሆን ነበር።"

ጠ.
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ደርስ
~
* መንሀጁ ሳሊኪን
* ክፍል:- 4️⃣7️⃣
* የሚሰጥበት ቦታ፦ የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ ሑዘይፋህ መስጂድ
* የሚሰጥበት ጊዜ፦ ዘወትር እሁድ ረፋድ ላይ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


مجمل أحكام الصيام.pdf
1.3Мб
مجمل أحكام الصيام.pdf


አሰላሙ ዐለይኩም
~
ሳምንታዊ ደርሳችን እንደተጠበቀ ነው ኢንሻአላህ።


የሰዎች ተሰጥኦ ይለያያል። አንዳንዱ የድምፅ ትምህርት ላይ ለየት ያለ ብቃት ሲኖረው አንዳንዱ የኪታብ ዝግጅት ላይ የተካነ ይሆናል። ሸይኽ ዐብደላህ ቢን ሷሊሕ አልፈውዛን የተወሰኑ ኪታቦቻቸውን አይቻለሁ አዘገጃጀታቸው በጣም ግሩም ነው። ሸርሖቻቸው ጥንቅቅ ብለው የተዘጋጁ ናቸው።
1- ሚንሓቱል ዐላም ማውጫውን ጨምሮ 11 ሙጀለድ የቡሉጉል መራም ሸርሕ ነው። pdf ፋይል ነው ሙሉውን ያነበብኩት። እጅግ በጣም ምርጥ ሸርሕ ነው።
2- መውሪዱል አፍሃም 4 ሙጀለድ የዑምደቱል አሕካም ሸርሕ ነው። ዑምዳን ለማስተማር የምጠቀመው እሱንና የዛይድ አልወሷቢይን ሚስኩል ኺታም ነው። በጣም ምርጥ ሸርሕ ነው።
3- ተዕጂሉ ነዳ የቀጥሩ ነዳ ምርጥ ሸርሕ ነው።
4- ደሊሉ ሳሊክ የአልፈየቱ ኢብኒ ማሊክ ሁለት ሙጀለድ ሸርሕ ነው። ገዝቼ አስቀምጫለሁ። የተሻለ ለመጠቀም በሚል አንድ የድምፅ ትምህርት ይዤ ልከታተለው አስቤያለሁ ኢንሻአላህ። ዛሬ ነገ እያልኩ እስካሁን ገና አላየሁትም።

ሌሎችም በርከት ያሉ ኪታቦች አሏቸው። አቅሙና ፍላጎቱ ያላችሁ ኪታቦቻቸውን ብትገዙ ትጠቀማላችሁ። ማግኘት የማትችሉ በ pdf መልክ በዚህ ቻናል ታገኟቸዋላችሁ፦
https://t.me/ktbAlfuzan
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ደርስ
~
* መንሀጁ ሳሊኪን
* ክፍል:- 4️⃣6️⃣
* የሚሰጥበት ቦታ፦ የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ ሑዘይፋህ መስጂድ
* የሚሰጥበት ጊዜ፦ ዘወትር እሁድ ረፋድ ላይ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦
فكل من رجع إلى الحق، ازدادت منزلته عند الله سبحانه ثم عند خلقه.
"ወደ ሐቅ የተመለሰ ሁሉ ከአላህ - ሱብሓነህ - ዘንድ ደረጃው ይጨምራል። ከዚያም ከፍጥረቱ ዘንድ።" [አልቀውሉል ሙፊድ፡ 1/385]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ደርስ
~
• ዑምደቱል አሕካም
• ክፍል:- 2️⃣4️⃣
• የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• የሚሰጥበት ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 116፣ ሐዲሥ ቁ. 201


የአፋልጉኝ ማስታወቂያ☝️

ከላይ በምስሉ የምታዩት ወንድማችን
ሱፍያን አህመድ ይባላል።

ትንሽ ስለሚያመውም ቤተሰብ በጣም በጭንቅ ይገኛል። እና ወንድምና እህቶች
ይህንን ወንድማችን ያየ ካለ በስልክ ቁጥር እንድታሳውቁን እያልን በአሏህ ስም እንጠይቃለን።

ሀሙስ (ቀን 06/ 06/ 2017 ) ዙህር ሰላት አለም ባንክ (ሙስዓብ መስጂድ) ሰግዶ ከወጣ በኋላ የት እንደሄደ አልታወቀም።

የቤተ ሰብ ስልክ ፦

0931563114
0937616636
0977723274


የዑምደቱል አሕካም ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
~
• ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 116፣ ሐዲሥ ቁ. 201


የአብዛኞቹ ዑለማእ አቋም ምን የሚል ነው? አልሀሠሚይ “በሰነዱ ውስጥ ዐብዱረሕማን ብኑ ዚያድ አለበት። አሕመድ ብኑ ሷሊሕ ታማኝ ቢለውም ብዙሃኑ ሊቃውንት ደካማ ነው ብለዋል። ኢብኑ ለሂዐህም አለበት” ብለዋል።
ሌሎቹንም ሐዲሦች እንዳጠቃላይ ብንመለከት ኢብኑ ረጀብ አልሐንበሊይ እንዲህ ይላሉ፦
"وفي فضل ليلة نصف شعبان أحاديث متعددة، وقد اختُلف فيها، فضعّفها الأكثرون، وصحّح ابن حبان بعضها"
"የሸዕባን አጋማሽ ሌሊትን በላጭነት አስመልክቶ በርከት ያሉ ሐዲሦች አሉ። በነሱ ላይ ልዩነት ተንፀባርቋል። አብዛኞቹ (ሊቃውንት) ደካሞች እንደሆኑ በይነዋል። ኢብኑ ሒባን ከፊሎቹን ሶሒሕ አድርገው በይነዋል።" [ለጧኢፉል መዓሪፍ፡ 261]

አሁን ይህንን አቋም መምረጥ ያስኮንናል? የሚገርም ነው።

“ከጥንት ጀምሮ ይህንን እለት በተለየ የያዙ የሉም ወይ?” ከተባለ “አዎ ነበሩ” ነው መልሴ። እደግመዋለሁ! አዎ ነበሩ። ዋናውን ነጥብ በመሳት እንዲህ አይነት ማስቀየሻ ሙግት እንዳይከፈት ነው ቀድሜ ይህንን የማስታውሰው። የኔ ትኩረት “የብዙሃኑን ዑለማእ አቋም ያንፀባረቀን አካል በዚህ መልኩ በንቀትና በማንጓጠጥ መግለፅ ለምን?” የሚል ነው። ይሄ ሌሎችን በማጣጣል ራስን የመሰቃቀል ስልት ከዚህ ወንድም ጋር ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ጋር የሚንፀባረቅ ርካሽ አካሄድ ስለሆነ ነው ለመፃፍ የተነሳሁት። አቅሙ ያለው ሰው በስርአት ተንትኖ መሀየስ ይችላል። ታላላቅ ዑለማኦች ያውም ብዙሃን የኢስላም ሊቃውንት የተጓዙበትን መንገድ ካንተ ስሜት ጋር ስላልገጠመ ብቻ አንድ ኪታብ ቀርተው ፊጥ ፊጥ የሚሉ ወጣቶች አቋም እያደረጉ መግለፅ ግን፦

* አንደኛ፦ ድን ^ቁርና የወለደው ድፍረት ነው። በጉዳዩ ላይ የዑለማኦችን ንግግሮች ብዙ ሳይሆን ትንሽ እንኳ ቢፈትሽ ኖሮ ቢያንስ ድፍረቱን ይቀንስ ነበር ብዬ አስባለሁ።
* ሁለተኛ፦ የኺላፍ ርእስ አድርጎ ቢያስበው እንኳ መሰል ጉዳዮች በሚይያዙበት መጠን አይደለም ያቀረበው። አለማወቅ ወይስ የከረመ ቂም ኖሮት ማራገፍ ነው የፈለገው?
* ሶስተኛ፦ ንግግሩ በራሱ ሂሳብ ሲታይ ዑለማእ መዝለፍ አለበት።

ደግሞ በደፈናው “ኒስፉ ሸዕባን አዲስ አይደለም። ከጥንት እስከዛሬ የሚታወቅ ሐዲሥ ነው” ይላል። ወላሂ ይሄ ንግግሩ ስለ ጉዳዩ ጫፍ ይዞ እንጂ የረባ ግንዛቤ እንደሌለው ያጋልጣል። ሲጀመር በጉዳዩ ላይ አንድ ሐዲሥ አይደለም ያለው። ሁለተኛ ተቃውሞው እሱ እንዳስመሰለው ዛሬ ፌስቡክ ከመጣ በኋላ የጀመረ ሳይሆን ቀደም ብዬ እንደገለፅኩት እነዚህ ሐዲሦች ደካማ እንደሆኑ የገለፁት የሐዲሥ ኢማሞች፣ እለቱን በተለየ መያዝ ቢድዐ እንደሆነና በዚህ ጊዜ የሚፈፀሙ ተግባራትን የሚኮንኑ ንግግሮች የወጡት ጥንት ጀምሮ ነው። ሌላው ሁሉ ይቅር። ቢያንስ በቅጡ ባልፈተሽከው ጉዳይ ላይ ድፍረት ብትቀንስ መልካም ነው። ንቀትና ዘለፋህም ይጎዳሃል። ወላሂ ወንድሜ! የትርጉም ስራህ ጉሩር ውስጥ እየከተተህ እንዳይሆን እሰጋለሁ።
ከብዙሃን ዑለማኦች አቋም ይልቅ የጥቂቶቹ ሃሳብ የተሻለ እንደሆነ ከተሰማህ መረጃ ጠቅሰህ ማስረዳት ይበቃሀል፣ ከቻልክበት። መሳለቁን ምን አመጣው? መሳለቅ ቢፈቀድስ አንተ በምን አቅምህ? ለምን ቀድርህን አታውቅም? አንድ ደደውን በመጥቀስ ድምዳሜ መስራትስ ግልብነት አይደለም ወይ? ኺላፍ ያለበት ርእስ በዚህ መልኩ ነው የሚልለየው? ደግሞም ደደው ያቀረበው ትንታኔ'ኮ ያንተን ነውረኛ የንቀት ድምዳሜ የሚሰጥ አይደለም። ቢያንስ ከመለጠፍህ በፊት “ደሊልህን” በስርአት አዳምጥ እንጂ!
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ለ Muhammed Seid Abx፡ ቢድዐው ላይ ዝም እንዳልከው ዝምታው አይሻልህም ነበር?
~
የሸዕባን አጋማሽ ሌሊቱን ወይም ቀኑን ጨምሮ የተለየ ዋጋ እንዳለው የሚገልፁ ሐዲሦች አሉ። እነዚህን መነሻ በማድረግ በተለያዩ ሃገራት በጊዜው የሚፈፀሙ የተለያዩ ተግባራት አሉ። ለምሳሌ ያህል በየ መሳጂዱ በየ ጎዳናው ጧፍ የሚለኩሱ አሉ። ሌሊት ወጥተው ሴት ወንድ ተቀላቅለው ዜማ እያዜሙ፣ የሙዚቃ መሳሪያ እየተጫወቱ በየ ቤቱ የሚዞሩ፣ ገንዘብ የሚጠይቁ፣ ... አሉ። በዚህ ጊዜ ከሌሎች ጊዜያት በተለየ ቀኑን በፆም፣ ሌሊቱን በሶላት የሚያሳልፉ አሉ። “ሶላቱል በራአህ” ወይም “ሶላቱል አልፊያህ” ብለው ለየት ያለ አፈፃፀም ያለው 100 ረከዐ በጀማዐ የሚሰግዱም አሉ። የራሴን ፈጠራ እያወራሁ እንዳይመስል የሚጠራጠር ካለ የአቡ ሻመህን “አልባዒሥ ዐላ ኢንካሪል ቢደዕ ወልሐዋዲሥ” ኪታብ እጠቁማለሁ።

ሰሞኑን አንዳንድ ወንድሞች ለነዚህ ተግባራት መነሻ የሚደረጉት ሐዲሦች ለማስረጃነት የሚበቃ ጥንካሬ ስለሌላቸው እለቱን በተለየ ማክበር ቢድዐ እንደሆነ እየፃፉ ነበር። ይሄ ነገር የጎረበጠው ሙሐመድ ሰዒድ ታዲያ እንዲህ ሲል በጅምላ ወቅጧቸዋል፦
“እንደ ትንሽ ዒልም ፈተና የለም። አንድ መትን ኪታብ ብቻ መቅራትም ሙሲባው ከባድ ነው። የቀራህ ሲመስልህ ነገሮችን በቢድዓ ጀምረህ በቢድዓ ትጨርሳለህ። በድፍረት ታነፍቃለህ፣ ታከፍራለህ። ትላልቅ ዑለሞችን ያለምንም ይሉኝታ ትናገራለህ።”

የወንድም ሙሐመድን ፅሁፍ በቅንነት ብንወስደው ሁለት ወሳኝ ነጥቦችን እንደሳተ እንረዳለን።
1ኛ፦ ይህንን እለት በተለየ እንዲይያዝ የሚጠቁሙ ሐዲሦች አብዛኞቹ የሐዲሥ ሊቃውንት ዘንድ ደካማዎች እንደሆኑ አላወቀም።
2ኛ፦ ይህንን እለት በተለየ በመያዝ የሚፈፀሙት ተግባራት ቢደ0 እንደሆነ የገለፁ ከጥንት እስከ ዛሬ በርካታ ዓሊሞች እንዳሉም እንዲሁ አላወቀም።

እነዚህ ሁለት ነጥቦች በቅጡ ቢረዳ ኖሮ እንዲህ አይነት አደብ የቀለለው ነገር አይፅፍም ነበር ብዬ ስላሰብኩ ዑዝር መስጠቴ ነው። ግን ግራ የሚገባው እነዚህ ወንድሞች ተሳስተዋል ቢባል እንኳ ንቀትና ዘለፋውን ምን አመጣው? ያለ እውቀት የተናገረው እሱ ወይስ እነሱ? እውነት በዚህ እለት በርካታ ቢድዐዎች እንዳለ አያውቅም? ታዲያ ምነው እሱን ዘነጋሀው? የትኛው ይበልጥ አሳሳቢ ነው? እውነት ይህንን ጊዜ “በተለየ መያዝ አይገባም፣ ቢድዐ ነው” ያሉ ዑለማኦች ስለሌሉ ነው “ትንሽ ዒልም” “አንድ መትን ኪታብ ያልቀራ” እያለ የሚወርፈው?

ወላሂ ወንድሜ! በመልካም ኒያ ብንተረጉምልህ ያሰፈርከው ፅሁፍ አንተን ነው ይበልጥ የሚገልፅህ። አላዋቂ አደብ ሊይዝ ሲገባ አንተ ግን ንቀትና ድፍረትህ ይገርማል። “አይ ይህንን ቀን በተለየ መያዝ እንደማይገባ የገለፁ ብዙ ዓሊሞች እንዳሉ አውቃለሁ” ካልክ ሙሲባው የከፋ ነው። ከዘለፍካቸው ወንድሞች ይልቅ አንተ ነህ ዑለማኦችን እየነካህ ያለኸው። ምክንያቱም ሸዕባን አጋማሽን በተለየ መያዝ አይገባም የሚሉ ወንድሞችን ዓሊሞችን ነክተዋል ብለህ የምትወነጅላቸው ከሆነ አንተ ራስህ “ይህንን ጊዜ በተለየ መያዝ አይገባም” የሚሉትን ዓሊሞች እየወረፍክ ነውና። ነው ሂሳብህ አንተን ይዘላል? አንዴ ይህን ፅሁፍህን ለራስ የተፃፈ ደብዳቤ ብለህ አንብብልኝማ። ይሄው ቃልህ፦

“እንደ ትንሽ ዒልም ፈተና የለም። አንድ መትን ኪታብ ብቻ መቅራትም ሙሲባው ከባድ ነው። የቀራህ ሲመስልህ ነገሮችን በቢድዓ ጀምረህ በቢድዓ ትጨርሳለህ። በድፍረት ታነፍቃለህ፣ ታከፍራለህ። ትላልቅ ዑለሞችን ያለምንም ይሉኝታ ትናገራለህ።”
ንግግርህ በልክህ የተሰፋ ነው። ከብዙ ዑለማእ ጋር እንደተቃረንክ አላወቅክም። ሳታውቅም ላንተ ስላልጣመህ ብቻ በንቀትና ዘለፋ ተጠምደሃል። በፅሁፍህ ተመከርበት።

ለማንኛውም “የሸዕባን አጋማሽ ሌሊት ሲሆን ሌሊቷን ስገዱ፣ ቀኑን ፁሙ” የሚለው ሐዲሥ ደካማ እንደሆነ የገለፁት ዓሊሞች አንድና ሁለት አይደሉም። የተወሰኑትን ልዘርዝር።
1. ኢብኑል ጀውዚይ፦ ከዚህ እለት ጋር የተያያዙ በርካታ ሐዲሦችን መሰረተ ቢስ የፈጠራ ወሪዎች እንደሆኑ ደጋግመው ገልፀዋል። [አልመውዱዐህ ተመልከት]
2. አዘሀቢይ፦ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል። [ተልኺሱ አልዒለሊል ሙተናሂያህ፡ 184]
3. ኢብኑል ቀይዪም፦ የሸዕባን አጋማሽ የሌሊት ሶላትን የሚጠቁሙ ሐዲሦች መሰረተ ቢስ ፈጠራ (መውዱዐህ) ናቸው ብለዋል። [አልመናሩል ሙኒፍ፡ 78]
4. አልዒራቂይ፦ [ተኽሪጁል ኢሕያእ፡ 1/273]፦
5. አልቃሪ፦ [አልአስራሩል መርፉዐህ ፊል አኽባሪል መውዱዐህ፡ 461 462]
6. ሸውካኒይ፦ [አልፈዋኢዱል መጅሙዐህ፡ 51]
7. አልሙባረክፉሪ፦ “በጣም ደካማ ነው።” [ቱሕፈቱል አሕወዚይ፡ 3/163]
8. ኢብኑ ባዝ፦ “ጠንካራ መሰረት የሌለው ደካማ ሐዲሥ ነው።” [ፈታዋ ኑሪን ዐለደርብ፡ 16/467] [መጅሙዑል ፈታዋ፡ 1/192፣ 197] ደግመው ደጋግመው በሰፊው ነው ይህን ቀን በተለየ መያዝ ቢድዐ እንደሆነ የገለፁት።
9. ኢብኑ ዑሠይሚን፦ “የሸዕባን አጋማሽ ቀኑን በፆም ሌሊቱን በሶላት ለይቶ መያዝን የሚጠቁሙ ሐዲሦች ደካማ ናቸው።” [መጅሙዑ ፈታዋ ኢብኒ ዑሠይሚን፡ 7/280] ሌሎች ተያያዥ ሐዲሦችንም “መሰረተ ቢስ ወሪዎች ናቸው” ብለዋል። [20/30]
10. ዐብዱልዐዚዝ አራጂሒይ፦ “እነዚህ ሐዲሦች ሁሉም ደካማዎች ናቸው።” ከድረ ገፃቸው የተወሰደ።

መቼም እነዚህን ዓሊሞች “እንደ ትንሽ ዒልም ፈተና የለም። አንድ መትን ኪታብ ብቻ መቅራትም ሙሲባው ከባድ ነው። የቀራህ ሲመስልህ ነገሮችን በቢድዓ ጀምረህ በቢድዓ ትጨርሳለህ። በድፍረት ታነፍቃለህ፣ ታከፍራለህ። ትላልቅ ዑለሞችን ያለምንም ይሉኝታ ትናገራለህ” እያልክ የምትገልፃቸው አይመስለኝም።

በነገራችን ላይ ከሸዕባን አጋማሽ ጋር ተያይዘው ከመጡ ሐዲሦች ውስጥ እንዲህ የሚል አለ፦
"إِنَّ اللَّهَ لَيَطَّلِعُ فِي لَيْلَةِ النِّصْفِ مِنْ شَعْبَانَ، فَيَغْفِرُ لِجَمِيعِ خَلْقِهِ إِلَّا لِمُشْرِكٍ أَوْ مُشَاحِنٍ".
"አላህ በርግጥም በሸዕባን አጋማሽ ሌሊት ይመለከታል። ለሁሉም ፍጥረቱም ምህረት ያደርጋል፤ ለአጋሪ እና ለተቀያየመ ሰው ሲቀር።" [ኢብኑ ማጀህ፡ 1390]
ይህንን ሐዲሥ አልባኒይ ድክመት እንዳለበት ከመጠቆማቸውም ጋር ከደጋፊ መስመሮች ጋር በማያያዝ "ሐሰን" ወይም “ሶሒሕ” ብለውታል። ተመሳሳይ ድምዳሜ ላይ የደረሱ ሌሎችም ሙሐዲሦች አሉ።

በሌላ በኩል ይህንኑ ሐዲሥ በይሀቂይ [ሹዐቡል ኢማን፡ 3831]፣ ኢብኑል ጀውዚይ [አልዒለሉል ሙተናሂያህ፡ 2/561]፣ አዘሀቢይ [ተልኺሱ አልዒለሊል ሙተናሂያህ፡ 184]፣ አልዐላኢይ [ፈታወል ዐላኢይ፡ 37]፣ ኢብኑ ሐጀር [አልካፊ አሻፊ፡ 252]፣ አሶንዓኒይ [አተንዊር፡ 3/344]፣ ሙሐመድ ጃረላህ አሶዒዲይ [አነዋፊሑልዐጢረህ፡ 220]፣ ኢብኑ ዐዲይ [አልካሚል ፊዱዐፋእ፡ 6/535]፣ ኢብኑል ቀይሰራኒይ [ዘኺረቱል ሑፋዝ፡ 5/2805]፣ አልቡኻሪይ [ሊሳኑል ሚዛን፡ 5/269]፣ ወዘተ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል።




ደርስ
~
• ዑምደቱል አሕካም
• ክፍል:- 2️⃣3️⃣
• የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• የሚሰጥበት ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 112፣ ሐዲሥ ቁ. 192


የዑምደቱል አሕካም ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
~
• ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 112፣ ሐዲሥ ቁ. 192


Репост из: የቡታጅራ አህለሱና ቂራኣትና ዳዕዋ ቻናል
ታላቅ የዳዕዋና ኮርስ ፕሮግራም      
           በቡታጅራ ከተማ!

=
እነሆ የፊታችን ሐሙስ ቀን 06/06/2017 ከመግሪብ ሰላት በኋላ ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ቀን 08/06/2017 ድረስ የሚቆይ የዳዕዋና ኮርስ ፕሮግራም በቡታጅራ ተሰናድቶ ይጠብቅዎታል።

በዕለተ እሁድ ደግሞ ሰፋ ባለ መልኩ በኢንሴኖ ከተማ ደማቅ ፕሮግራም የሚካሄድ ይሆናል። በዚህ ፕሮግራም የተለያዩ ጊዜውን ያማከሉ አርእስቶችና ረሳኢል በኮርስና ዳዕዋ መልክ ይሰጣሉ።

እርሶም የዚህ ታላቅ ፕሮግራም ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ጥሪ ስናቀርብልዎ በታላቅ ደስታ ነው።

☞ ተጋባዥ እንግዶች፦
     * ሸይኽ አወል አሕመድ አልከሚሴ
     * ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አልከሚሴ እና ሌሎችም ኡስታዞችና ዱዓት ይገኛሉ።

«እውቀትን ፍለጋ መንገድን የጀመረ አላህ የጀነትን መንገድ ያገራለታል።» ረሱልﷺ

https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group


حب الرئاسة والظهور
የሁቡ አሪኣሰቲ ወዙሑሪ ሙሉ ደርስ በሙሐመድ ሲራጅ ሙ/ኑር {1—8}


“ደዕዋውን በተሰውፍ የጀመረ ነብይ የለም፡፡ ልክ እንዲሁ በፍልስፍና፣ በዒልመልከላም፣ በፖለቲካ የጀመረም አልሰማንም፡፡ ይልቁንም በአንድ መንገድ ነው የተጓዙት፡፡ ትኩረታቸውም አንድ ነበር፣ በመጀመሪያ በቀዳሚነት ወደ አላህ ተውሒድ በመጣራት፡፡”

ሸይኽ ረቢዕ አልመድኸሊይ [ሚንሀጁልአንቢያእ ፊደዕዋ፡ 91]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ተጨማሪ ማሳሰቢያ ለወላጆች!
~
የሃገሪቱ ህግ ሳይፈቅድ፣ ወላጆች ሳያውቁ ለተማሪዎች የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ብል ~ ^ ግና የሚያስተምሩ ትምህርት ቤቶች መኖራቸው ተረጋግጧል። በተለይ እነዚህ ኢንተርናሽናል ስኩል የሚባሉትን በአይነ ቁራኛ ተመልከቱ። አንዳንድ ወላጆች የገንዘብ አቅማቸው ሲፈረጥም ልጆቻቸው እንዲህ አይነት ስም ያላቸው ትምህርት ቤቶች ውስጥ መማራቸውን እንደ ደረጃ ማሳያ የሚያዩ አሉ። ይሄ ግልብነት ነው። ከሁሉም ነገር ቀዳሚው የልጆች ደህንነት ነው። ለጉራ እና ለማይጨበጥ ነገር ስትጓጉ የልጆቻችሁን ህይወት እንዳታበላሹ።

የት/ሚኒስቴርን ነገር ሆድ ይፍጀው፡፡
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ለተማሪ ወላጆች!
~
ልጆቻችሁን የምታስተምሩባቸውን ትምህርት ቤቶች እያስተዋላችሁ። አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኝ ፍሊፐርስ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት ለተመሳሳይ ጾታ እና ለአፈንጋጭ ግንኙነት ተማሪዎች ምቹ መደላድል እና ከባቢ ስለ መፍጠር ለመምህራን ስልጠና ሊሰጥ እንደተዘጋጀ እዚሁ ሰፈር ሲዘዋወር አነበብኩኝ። እንደዚህ ይፋ ያልወጡ ሌሎች ሌሎችም ይኖራሉና ጥንቃቄ አድርጉ። በተለይ በውጭ ሃገራት ኤምባሲዎች ስር ያሉ ወይም በውጭ ድርጅቶች የሚታገዙ ትምህርት ቤቶችን በጣም ተጠንቀቁ። ኋላ ልጆቻችሁን እንዳታጧቸው።

ጉዳዩ በሃገሪቱ ህግ ወንጀል ቢሆንም ይሄ በውሃ ቀጠነ ሙስሊም ተማሪዎችን የሚበጠብጠው ት/ሚኒስቴር እርምጃ ይወስዳል ተብሎ አይጠበቅም።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor

Показано 20 последних публикаций.