Law students Union ️️️


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


LSU is created mainly to inform you updated laws; access teaching materials, references, exit exam files, short notes available;and to support law students.
🎓|=|🎓🌟LSU 🌟GBS ⭐የሕ.ተ.ህ🌟
📩if any✍️ @LSU2012_bot

For More Accessibility of Laws!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


በፍትሀብሄር የክርክር መዝገብ ላይ የእስር ትእዛዝ የሚታዘዝበተ ሁኔታዎች

1ኛ)  በፍ/ስ/ህ/ቁ 156 ላይ አንደተደነገገው  ተከሳሹ በፍርድ ቤት የተሰጠውን የማገጃ ትእዛዝ ያላከበረ ወይም በትእዛዞቹ ላይ የተሰጡት ውሳኔዎች ያልጠበቀና እግዱን የጣሰ ከሆነ ፍርድ ቤቱ የእስር ትእዛዝ ሊሰጥ እንደሚችል ያስቀምጣል፡፡

2ኛ) በፍ/ስ/ህ/ቁ 161(2) መሰረት
ፍ/ቤቱ ከፍርድ በፊት ክርክር የተነሳበትን ንብረት እንዳይበላሽ ለመጠበቅ የሚሰጠውን ማንኛውም ዓይነት ትእዛዝ የማይፈጽም አካል ላይ የእስር ትእዛዝ እንደሚሰጥ መረዳት ይቻላል፡፡

3ኛ) በፍ/ስ/ህ/ቁ 267 እና 268 ላይ እንደተገለጸው አንድ ምስክር ወይም ተከራካሪ ወገን በችሎት ቀርቦ እንዲመሰክር ወይም በእጁ ወይም በስልጣኑ ስር  ማንኛውም ማስረጃ እንዲያቀርብ የፍርድ ቤት መጥሪያ ደርሶት ያለ በቂ ምክንያት ትእዛዙን ያልፈጸመ  ወይም የማይፈጽምበትን ምክንያት ቀርቦ ያላስረዳ ከሆነ ፍ/ቤቱ የእስር ትእዛዝ እንደሚያወጣ ያስቀምጣል፡፡

4ኛ) በፍ/ስ/ህ/ቁ 386(4) ላይ እንደተመለከተው የአፈጻጸም ማመልከቻው የቀረበው አንድ የተወሰነን ገንዘብ ለማስከፈል ወይም የተፈረደው ፍርድ እንዲፈጸም  ሆኖ የአፈጻጸም ተከሳሽ በመጥሪያው መሰረት ያልቀረበ ከሆነ ፍ/ቤቱ ታስሮ እንዲቀርብና   እንደፍርዱ የማይፈጽምበትን ምክንያት ለመጠየቅ ይችላል በማለት ተደንድጓል፡፡

5ኛ) በፍ/ስ/ህ/ቁ 387 መሰረት የፍርድ ባለእደው ፍርዱ እንዳይፈጸም መሰናክል የፈጠረ ወይም የፍረዱን አፈጻጸም ለማዘግየት ንብረቱን  ከፍርድ ቤቱ ስልጣን ክልል ውጪ ለማሸሸ፤ ለመደበቅ ወይም እራሱ ለመሰወር ያቀደ መሆኑን የሚያረጋገወጥ በቃለ መሀላ የተደገፈ አቤቱታ ከቀረበ ፍ/ቤቱ ባለእዳው በቀጥታ እንዲታሰር ትእዛዝ ሊሰጥ እንደሚችል ያስገነዝባል፡፡

6ኛ) በፍ/ስ/ህ/ቁ 389(1) ላይ እንደተመለከተው የፍርድ ባለእዳው ያለ በቂ ምክንያት ፍርዱን የማይፈጽም  መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም መፈጸም እየቻለ ለመፈጸም ፈቃደኛ ያልሆነ መሆኑን ሲረጋገጥ ፍ/ቤቱ የፍርድ ባለእደውን  እስከ 6ወር ሊደርስ የሚችል እስራት ሊፈርድበት ይችላል፡፡

7ኛ) በፍ/ስ/ህ/ቁ 481 ላይ እንደተገለጸው ማንም ሰው የችሎት ስራ ዳኛው በሚሰራበት ጊዜ ዳኛው ስራውን እዳይሰራ ያወከው ከሆነ ወይም በችሎት የተከለከሉ ተግባራት የፈጸመ ወይም ሀሰተኛ የምስክርነት ቃል የሰጠ መሆኑን የተረጋገጠ በአጠቃላይ ችሎት ደፍሮ ከተገኘ እስከ 3 አመት እንደሚቀጣ ተደንግጓል፡፡




በወንጀል ተጠርጥሮ ጉዳዩ በፍርድ ሂደት ላይ የነበረና በእስር ምክንያት በስራው ላይ ያልተገኘ ሰራተኛ ከቀረበበት ክስ ነፃ ቢባልም ደመወዝ ሊከፈለው የማይችል ስለመሆኑ፤
(ሰ/መ/ቁ፡ 201933)ጥቅምት 04/2014
===============================
ለሰበር የቀረበው ጉዳይ በአጭሩ ተጠሪ የስራ ሂደት መሪ ስሆን በሙስና የወንጀል ክስ ተመስርቶብኝ ስከራከር ቆይቼ ከቀረበብኝ ክስ በነፃ ብሰናበትም በእስር ምክንያት በስራዬ ላይ ላልተገኘሁባቸው ጊዜያት ተጠሪ ደመወዝ ሊከፍለኝ አልቻለም በማለት ክስ አቅርቧል፡፡ ተጠሪም በበኩሉ አመልካች በመታሰሩ ምክንያት የተቋረጠበት ደመወዝ ሊከፈለው አይገባም በማለት ምላሽ ሰጥቷል፡፡   

የሠበር ችሎቱም ተጠሪ በእስር ምክንያት ላልሰራው ስራ ደመወዝ ወደ ኋላ ተመልሶ ሊከፈለው ይገባል ? ወይንስ አይገባም? የሚለውን በጭብጥነት ይዞ ጉዳዩን መርምሯል፡፡

በመሰረቱ ደመወዝ ለተሰራ ስራ በአሰሪው አካል የሚከፈል የድካም ዋጋ በመሆኑ አንድ የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝ የሚከፈለው በመስሪያ ቤቱ በስራ ላይ ሁኖ በተመደበበት ስራ ለሰጠው አገልግሎት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ይህ መሰረታዊ መርህ ሲሆን በስራ ላይ ባልነበረበት ጊዜ አንድ የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝ የሚከፈለው በህግ በልዩ ሁኔታ የተመለከተ ግልፅ ድንጋጌ ሲኖር ብቻ ነው፡፡ በዚህ ረገድ የፌዴራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1064/2010 በክፍል አራት ስር አንድ ሰራተኛ ስራ ሳይሰራ ደመወዝ ሊከፈለው የሚችለው በህዝብ በዓላት፣ በዓመት እረፍት ፍቃድ፣ በሳምንት እረፍት ፣ በወሊድ ፍቃድ፣ በህመም ፍቃድ፣ ለግል ጉዳይ በሚሰጥ ልዩ ፍቃድ ምክንያት ብቻ ስለመሆኑ ከአንቀፅ 36 እና ከተከታዮቹ ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል፡፡ ስለሆነም ሰራተኛው በወንጀል ተጠርጥሮ በፍርድ ሂደት ላይ የነበረ በመሆኑ ምክንያት ቢሆንም በዚህ እና በመሰል ሁኔታዎች ምክንያት ሰራተኛው ከስራ የቀረ እንደሆነ በስራው ላይ ባይገኝም መስሪያ ቤቱ ደመወዝ የመክፈል ግዴታ ያለበት ስለመሆኑ አዋጅ ቁጥር 1064/2010 አይደነግግም፡፡ ስለሆነም በመርህ ደረጃ ደመወዝ የሚከፈለው በስራ ገበታው ላይ ተገኝቶ ተገቢውን አገልግሎት ለሰጠ የመንግስት ሰራተኛ በመሆኑ እና ስራ ሳይሰራ ደመወዝ የሚከፈለው በአዋጁ የተመለከተ ድንጋጌ ሲኖር ብቻ ስለሆነ እና ይህም ለመርሁ ልዩ ሁኔታ በመሆኑ በጠባቡ መተርጎም የሚገባው ስለሆነ በእስር ምክንያት በስራ ገበታው ላይ ላልተገኘ ሰራተኛ መስሪያ ቤቱ ደመወዝ ለመክፈል የሚገደድበት የህግ ምክንያት የለም በማለት አስገዳጅ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡



@LawStudentsUnion
@LawStudentsUnion


Репост из: የሕግ ምክር አገልግሎት እና የትርጉም ቢሮ (Legal Advice Service and translation office )🇪🇹
1. When is Human Rights Day observed each year?
Опрос
  •   A. 10th of December each year
  •   B. 15th of February each year
  •   C. 10th of January each year
  •   D. 15th of March each year
106 голосов


ሰ/መ/ቁጥር 208397
የካቲት 30/2014.
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 151 መሰረት ንብረት እንዲከበር የሚሰጥ ትዕዛዝ እንዲነሳ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ቀርቦ ካልተነሳ ይግባኝ ሊቀርብበት ይችላል፡፡
ትዕዛዙ እንደመጨረሻ ዉሳኔ የሚቆጠርና በዚያዉ ፍርድ ቤት እንደገና እንዲታይ በተዘረጋዉ ሥርዓት መሰረት እንደገና እንዲታይ ከተደረገ በኋላ በዋናው ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ዉሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ መጠበቅ ሳያስፈልግ ይግባኝ ሊባልበት የሚችል ነዉ፡፡

Credit: Bedru and Getachew law office

Join us for more accessibility of laws

@lawstudentsunion
@lawstudentsunion
@lawstudentsunion




3. CIVIL PROCEDURE P.2


Chap 1.pptx
109.5Кб
chap 2.pptx
122.5Кб
chap 3 &4.pptx
210.8Кб
Chap 5.pptx
97.0Кб
chap 6.pptx
80.4Кб
Chap 7.pptx
111.2Кб
Chap 8.pptx
84.8Кб
chap 9.pptx
66.1Кб
///////////

#YOU_NEED

ACCESSIBILITY OF LAWS
AVAILABILITY OF LEGAL SHORTNOTES, EXIT EXAM QUESTIONS& SUPPORTIVE EXIT NOTES
LEGAL PROPOSALS AND RESEARCHES
=====
BE OUR MEMBER
SHARE TO OTHERS
INVITE TO US
ENJOY FREELY
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/LawStudentsUnion
https://t.me/LawStudentsUnion


2. CRIMINAL PROCEDURE LAW
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️





Показано 11 последних публикаций.