መለኮታዊ ስጦታችሁን አግኙ
ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ አምስት መክልት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ሌላ አገር ወዲያው ሄደ።ማቴ 25፥15
በእያንዳንዱ ሰው ውስጥ ስጦታ ወይም መክሊት የሚባል የተቀመጠ ነገር አለ እግዚአብሔር እያንዳንዱ ሰው በምድር ስፍራውን እንዲይዝ አንድ ነገር ሰጥቶታል።
አንዳንዶቹ አምስት ሁለት ወይም አንድ ብቻ አላቸው ነገር ግን ሁሉም ሰው አንድ የተሰጠው ነገር አለው።
በውስጣችሁ ያለውን መለኮታዊ ስጦታ ማወቅ ዓላማችሁን ማግኛ ታላቅ መንገድ ነው።
ነገር ግን አንድ ቀን የመክልቱ ባለቤት ይመለስና ምን እንደ ሰራችሁበት ይጠይቃል:: ያተረፈውን ብርቱ ሥራተኛ ይሾማል:: ያልሰራውን ሰው ግን ወደ ውጭ ይጥላል::
ማቴዎስ ወንጌል 25:16-30
16 አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፤
17 እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ።
18 አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ።
19 ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው።
20 አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ። ጌታ ሆይ፥ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ።
21 ጌታውም። መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።
22 ሁለት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት አለ።
23 ጌታውም። መልካም፥ አንተ በጎ፥ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፥ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።
24 አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤
25 ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ።
26 ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው። አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ፥ ካልዘራሁባት እንዳጭድ ካልበተንሁባትም እንድሰበስብ ታውቃለህን?
27 ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፥ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር።
28 ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አሥር መክሊትም ላለው ስጡት፤
29 ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል።
30 የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።
@new_life_ministry @new_life_ministry