Natinael Mekonnen


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Шок-контент


ይህ ቻናል ቴሌግራሜ hacked በተደረገበት ሳት ለግዝያዊነት የከፈትኩት ቻናል ነው ለችግር ጊዜ ይጠቅማል ተቀላቀሉ
በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ከፈለጉ @NatnaelMekonnen7 በማለት መረጃዎችን ይላኩልን
I blog about marketing and sales
Buy ads: https://telega.io/c/NatinaelMekonnen21

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Шок-контент
Статистика
Фильтр публикаций


“መች ይገጥማሉ አንተዬ፣ ወግ ነው ለካ ጎጃም” የነምሬ ወዳጆ ታጣቂ አመራር

የምሬ ታጣቂዎች የዘመነን ቡድን ንቀት በተሞላበት ሁኔታ ሲተቹ የተቀዳ የስልክ ልውውጥ እጃችን ላይ ገብቷል!

በስልክ ልውውጡ ላይ አንድነት እንመስርታለን በሚል ምሬ ወደጎጃም የላካቸው ታጣቂዎች እንደሚከለከተለው ዘመነን እና ተከታዮችን ይወርፋሉ።

👉በጎጃም ያለው ሃይል የመከላከያ ሰራዊቱን እርምጃ መቋቋም አቅቶት በየአቅጣጫው እየፈረጠጠ እና ከመከላከያ ሰራዊቱ ጋር የመግጠም የስነልቦና ጥንካሬ እንደሌለው፣

👉ጎጃም ውስጥ ወሬ ካልሆነ በስተቀር ምንም አቅም ያለው ሃይል እንደሌለ፣

👉እነዘመነም ሁል ጊዜ ታሪክ እና ወሬ ብቻ በመንዛት እንደቆዩ እና
👉እራሳቸውን በተሳሳተ መንገድ የፋኖ የጀርባ አጥንት አድርገው እንደሚቆጥሩም የምሬ ተላላኪዎች በድብቅ ይናገራሉ።


"ሀገርን ለማዳን ወደ ትኅትና፣ ወደ ዕርቅ እና ወደ ምክክር መስቀል አውርዶ ራስን መሠዋት ያስፈልጋል። መስቀል መከራ ነው፤ ስድብ ነው፤ ግርፋት ነው፤ ውርደት ነው። ራሳችንን ለሰላምና ለዕርቅ መንገድ ስናዘጋጅ ከብዙዎች ዘንድ ስድብ፣ ርግማን፣ መከራ፣ ይጠብቀናል። የሚያዋጣን ግን ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ የኢትዮጵያን መስቀል መሸከም ነው። ለኢትዮጵያ ትንሣኤ ስንል መስቀሏን መሸከም።"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)


ሕዝበ ክርስቲያኑ የትንሣዔ በዓልን በአብሮነትና በመረዳዳት በጋራ ማሳለፍ እንደሚገባው የኃይማኖት አባቶች ገለጹ፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል፣ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሀፊ ቄስ ደረጀ ጀንበሩ እና የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዚዳንት ፖስተር ጻድቁ አብዶ የትንሳኤ በዓልን በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ በመግለጫቸው፤ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለማስከበር በድንበር ለተሰማሩ ወታደሮች፣ በተለያዩ የዓለማት ክፍል ለሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮችና ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል፡፡
የትንሣዔ በዓል እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ፍቅሩን የገለጸበት ትህትናን ያስተማረበት መሆኑን ገልጸው፤ በዓሉን ሲከበር ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና አንድነት በመጸለይ እንዲሁም የተቸገሩትን በመርዳት መሆን እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
በዓሉ ለተቸገሩት ካለን የምናካፍልበት እና አብሮነታችንን የምናሳይበት ሊሆን ይገባል ሲሉም አሳስበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል የትንሣዔ በዓል የትህትናና የመከባበር እሴታችንን የምናሳይበት ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡
ትንሣዔ ጥላቻ በፍቅር፤ መለያየት በአንድነት፤ ሐዘን በደስታ የተቀየረበት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍቅር የተገለጠበት መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሀፊ ቄስ ደረጀ ጀንበሩ የትንሣዔን በዓል ከተቸገሩ ወገኖች ጋር በማሳለፍ የክርስቶስን ፍቅር ማሳየት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ትንሣዔ የተጣሉ የሚታረቁበት፤ የተራራቁ የሚቀራረቡበት እንዲሆን ታርቆ በማስታረቅ መልካም ምሳሌ መሆን እንደሚገባ ገልጸው፤ የኢትዮጵያን ሰላም እና የህዝቦቿን አንድነት በጽኑ ዓለት ላይ ለማቆም በመከባበርና መደማመጥ ላይ የተመሰረተ ውይይትና እርቅ የግድ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዚዳንት ፖስተር ጻዲቁ አብዶ፤ የትንሣዔን በዓል በማስመልከት በሰጡት መግለጫ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሆሳዕና ጀምሮ እስከ ትንሣዔ ድረስ ያደረጋቸው ተግባራት ለእኛ ለሰው ልጆች ትህትናና ፍቅርን የሚያስተምሩ ናቸው ብለዋል፡፡
ክርስቶስ ለእኛ የከፈለውን መስዋዕትነት በማሰብ ምዕመናን የተራቡትን በማብላት የተጠሙትን በማጠጣት የታረዙትን በማልበስና የተቸገሩትን በመርዳት ማሳላፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
በተጨማሪም ምዕምናን የትንሣዔ በዓልን ለኢትዮጵያውያን አንድነትና ዘላቂ ሰላም በመጸለይ እንዲያከብሩ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡


በትግራይ በባህላዊ የማዕድን ሥራ ላይ የተሰማሩ እስከ 10 ሚሊዮን ብር እንደሚቀጡ ተገለፀ!

በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በቅርቡ በወጣው የተሻሻለ የማዕድን አስተዳደር ደንብ መሠረት በባህላዊ የማዕድን ማምረት ሥራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች  እስከ 10 ሚሊዮን ብር እንደሚቀጡ ተገለጸ።

ረቡዕ ሚያዚያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም. ተግባራዊ እንዲደረግ በክልሉ ለሚገኙ ለመሬትና ማዕድን እንዲሁም ለሚመለከታቸዉ የመንግስት መ/ቤቶች በተላከዉ ደብዳቤ ይህኑን ደንብ እንዲያስፈፅሙ መጠየቁን ካፒታል ተመልክቷል።

ደንቡ በባህላዊ እና አነስተኛ ደረጃ የማዕድን ሥራዎች ላይ እንደ ሜርኩሪ እና ሳይናይድ ያሉ ጎጂ ኬሚካሎችን መጠቀም እንዲሁም ብረትና ብረት ነክ ማዕድናትን ያለዕሴት መጨመር መላክ ወይም መሸጥን በግልጽ ይከለክላል።

ይህን ጣሰ ማንኛውም ሰው ከ15 እስከ 20 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ሊቀጣ የሚችል ሲሆን በተጨማሪም እስከ 10 ሚሊዮን ብር የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ሊጣልበት ይችላል።

ከዚህም በላይ ጥፋተኛው ከማዕድን ሥራው ጋር የተያያዙ ማሽነሪዎችና ሌሎች መሣሪያዎች እንዲሁም ያመረተው ማዕድን ይወረሳል፤ ድርጅቱም ዝግ የሚሆን ከመሆኑም በላይ ለወደፊቱ በማንኛውም የማዕድን ሥራ እንዳይሳተፍ ይታገዳል።

የክልሉ መንግሥት ይህንን ደንብ ያወጣው በፌዴራል መንግሥት በተሰጠው ሥልጣን መሠረት መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን ዓላማውም የአካባቢን ደህንነት መጠበቅ፣ የሰዎችንና የእንስሳትን ጤና መከላከል እንዲሁም ማዕድናት በአግባቡ ተጨምሮባቸው ለሀገር ጥቅም እንዲውሉ ማድረግ ነው ተብሏል።


ሰበር ዜናው ቀጥሏል

የጎጃሙ ጽንፈኛ ቡድን እያለቀ ነው። ከውስጥ ለፀጥታ ኃይል እየተሰጡ ያሉ መረጃዎች ኦፕሬሽኑን እያሳኩት ይገኛሉ።

ትናት በገደብ ስልጠና እና ስብሰባ ላይ የነበሩት 126 ታጣቂዎች የተደመሰሱ ሲሆን ዛሬም በአደባባይ ስብሰባ ላይ የነበሩት 135 ስብሰባ ላይ እያሉ አንድም ሳይቀር ተደምስሰዋል። ከተደመሰሱት ውስጥ የትኞቹ አመራሮች እንዳሉ እየጣራ ነው::


breaking news loading… ጎጃም/ፋኖ


ሰበር

መንበሩ ጌታዬ ከጠባቂዎቹ ጋር ተደመሰሰ

በምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ሰዴ አካባቢ በሚንቀሳቀሰው የጽንፈኛው ፋኖ ቡድን ላይ የፀጥታ ኃይል በወሰደው እርምጃ መንበሩ ጌታዬ የተባለ የአማራ ፋኖ በጎጃም 2ኛ ተፈራ ዳምጤ ክ/ጦር መሪ የሆነውን ጨምሮ ጠባቂዎቹ እና ሌሎች አመራሮች ተደምስሰዋል። በዚሁ አካባቢ የነበሩ ቁጥራቸው ከ100 በላይ ታጣቂዎችም ተደምስሰዋል


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋሩ
*********

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ፣ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች እና ጽሕፈት ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ሕጻናት ማዕድ አጋርተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የማዕድ ማጋራት መርሐ ግብሩን ዛሬ ጠዋት ማከናወናቸውን የጽሕፈት ቤቱ መረጃ ያመላክታል።


ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሃኖይ የሚገኝ የአይነስውራን ትምህርት ቤትን ጎበኙ

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሃኖይ የሚገኘውን የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ የአይነስውራን ት/ቤት ጎብኝተዋል፡፡

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ ዛሬ የቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ ቀዳማዊት እመቤት ማዳም ነኹ በሃኖይ የሚገኘውን የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ የአይነስውራን ት/ቤት አስጎብኝተውኛል ብለዋል፡፡

ባደረጉት ጉብኝት በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ ለሚገኘው እና በተለያዩ ክልሎች እየተሰሩ ላሉት አዳዲስ የአይነስውራን አዳሪ ት/ቤቶች የሚሆኑ ተሞክሮዎችን ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል፡፡


የመከላከያ ሰራዊት በጽንፈኛው ቡድን የስልጠና ማዕከል ላይ በወሰደው እርምጃ አንድ የሻለቃ አመራርን ጨምሮ በርካታ ታጣቂዎች ተደምስሰዋል!

ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ለሰላም ጀርባውን በመስጠት ህዝብን እያሰቃየ በሚገኘው ጥገኛ እና ጽንፈኛ ቡድን ላይ የማያዳግም እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል። በዚህም መሰረት ሰራዊቱ ዛሬ ሚያዚያ 09/2017 ዓ.ም በምስራቅ ጎጃም ዞን እናርጅና እናውጋ ወረዳ ገደብ አካባቢ በስልጠና ላይ በነበሩ የፀረ-ሰላም ቡድኑ አባላት ላይ በወሰደው እርምጃ አንድ የሻለቃ አመራርን ጨምሮ ከአርባ በላይ የቡድኑ አባላት የተደመሰሱ መሆናቸው ታውቋል። በተጨማሪም በእርምጃው አሁንም ብዛት ያለው ታጣቂ የቆሰለ መሆኑና የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል ተገልጿል። የጽንፈኛው ቡድን አመራሮች የጓደኞቻቸውን አስ*ከሬን ለማንሳት እንኳን በማይችሉበት ደረጃ እርምጃው ጠንካራ እንደሆነ እየገለጹ ይገኛሉ። ለሰላም አሻፈረኝ ያለውን ይህንን ከሃዲ እና ጸረ ህዝብ የሆነ ቡድን ጀግናው ሰራዊት በሚገባው ቋንቋ እያናገረው ይገኛል። የጽንፈኛው አባላት አሁንም ያላቸው ምርጫ ሁለት ነው እጅ ሰጥቶ ወደ ሰላማዊ ህይወት መመለስ አሊያም የማይቀረውን የሞት ጽዋ መጎንጨት! ይኸው ነው!


ትላንት የመከላከያ ፔጅ የፕ/ት መንግስት ኃ/ማርያም መገልገያ አውሮፕላን ከ37 ዓመት በኋላ upgrade እና overhaul ተደርጋ ዳግም መብረር ጀመረች የሚል የምስራች ዜና አወጣ።

ይህን መልካም ዜና አድርገው ከኛ ውጭ “ fact check “ አድራጊ የለም ብሎ በማለት ዜናውን አጣራሁ ብሎ ሀሰት አለ።

ይሄው ዛሬ “የኮሎኔል መንግስቱ ትዝታዎች” የሚል መፅሀፍ የፃፈቺው እና ለቀድሞ ፕሬዚደንቱ ቅርበት ያላት ጋዜጠኛ እና ፀኃፊ ገነት አየለ ዜናው እውነት መሆኑን ከእራሳቸው ፕ/ት መንግስቱን አፍ ጠይቃ አረጋግጣለች።

ጋዜጠኛ ገነትን እያመሠገንን fact check መልሰን fact check የማድረግ ስራችንን እንቀጥላለን። በግሌ እኔ አየር ሃይ ግቢውስጥ ይህን አውሮፕላን ቆሞ አይቼዋለሁ በሰአቱ እየታደሰ ስለነበር አንድ ኮሎኔል የመንግስቱ ሃይለማሪያም እንደበር ነግሮኝ በግዜው ከተወሰነ ጉዞ በላይ መንግስቱ ሃይለማሪያም እንዳልተጏዙበት ነግሮኛል ምክንያቱንም ነዳጅ በጣም ይበላ ስለነበር መንግስቱ ሃይለማሪያም በራሳቸው ትዕዛዝ እንዲቆም አድርገውታል ነበር ያለኝ::


#KeneniAdugna

የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች የድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ የችሎት ሂደትን እንዳይታደሙ በፍርድ ቤት ታገዱ።

ዛሬ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በፍቅረኛው ወጣት ሞዴል ቀነኒ አዱኛ ህልፈት ተጠርጥሮ በምርመራ ሂደት ላይ የሚገኘው የአርቲስት አንዱዓለም ጎሳ ጉዳይ በታየበት ችሎት ነው ፍርድ ቤቱ መገናኛ ብዙሃን ችሎቱን እንዳይታደሙ ያገደው፡፡

በዛሬው ችሎት ፖሊስ የመገናኛ ብዙሃን በተለያዩ ጊዜያት “ የችሎቱን ውሎ በተደጋጋሚ አዛብተው ዘግበውታል ” በሚል የምርመራ ሂደቱ ላይ እክል በመፍጠራቸው በችሎቱ እንዳይታደሙ ጠይቋል፡፡

በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ በችሎቱ የተጠየቁት የተከሳሽ ጠበቃ በፊናቸው ፖሊስ ያቀረበውን አቤቱታ እንደሚደግፉ ገልጸዋል፡፡

ችሎቱም ግራ ቀኙን ካደመጠ በኋላ “ መገናኛ ብዙሃን ካሁን በፊት አንድ ጊዜ ተከሳሽ ለፋሲካ በዓል ወጥቶ ኮንሰርት ለማዘጋጀት ጠይቋል፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ የሟች የግል ማህደር (ዳይሪ) በተከሳሽ ጠበቃ እጅ ነው የሚገኘው የሚሉ የተዛቡና ሀሰተኛ ዘገባዎች ማቅረባቸው በችሎቱና በምርመራ ሂደቱ ላይ እክል እንደሚፈጥር በመታመኑ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች (ጋዜጠኞች) ችሎቱን እንዳይታደሙ “ በሚል ብይን ሰጥቷል።

በዛሬው ችሎት የታደሙትን ጋዜጠኞችን በዳኛ ትዕዛዝ እንዲወጡ ተደርገዋል።

መጋቢት 01 ቀን ሌሊት ለመጋቢት 02 ቀን 2017 ዓ.ም. አጥቢያ የመኖሪያ ቤቷ ከሚገኝበት ህንጻ ወድቃ ህይወቷ ማለፉ በተሰማው በወጣት ቀነኒ አዱኛ ህልፈት በፖሊስ የተጠረጠረው ፍቅረኛዋ ድምጻሚ አንዱዓለም ጎሳ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት ይገኛል።


በርካታ ገንዘብ የያዙ በማስመሰል ከፊትና ከኋላ ሁለት ሁለት መቶ ብሮች በማድረግና ባለ አስር ብሮችን በመጠቅለል የማጭበርበር ወንጀል ሊፈጽሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን በግል ተበዳይ ጠቋሚነት በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገለጸ።

ግለሰቦቹ ሆን ብለው በመዘጋጀት በርከት ያለ ገንዘብ የያዙ ለማስመሰል በሁለት መቶ ብሮች የተጠቀለሉ ባለ አስር ብር ኖቶችን በመያዝ የተለያዩ የማታለያ ዘዴዎችን በመጠቀም ሰዎች ላይ የሚያዩትን ጌጣ ጌጥ አታለው በገንዘቡ ለመቀየር ካልሆነም የበለጠ ገንዘብ የሚያገኙበትን ዘዴ ይፈጥራሉ፤ ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ ቦታዎች ላይ እየተንቀሳቀሱ የሚፈፀሙት የወንጀል ድርጊት መሆኑን ፖሊስ በምርመራው አረጋግጧል፡፡

ሚያዚያ 8 ቀን 2017 ዓ/ም በተመሳሳይ የወንጀል አፈጻፀም ሙከራ በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታው ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል።

ዳንኤል ታደሰና ታዬ ዋቅጅራ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ከላይና ከታች በባለ 200 ብር ኖት የተሸፈነና መሀሉ በባለ 10 የብር ኖት ጥቅልል የተዘጋጀ ገንዘብ በመያዝ በሆስፒታሉ እናቷን እያስታመመች የነበረችና መድኃኒት ለመግዛት የወጣችን ግለሰብ በማግባባት የታወቁ ስፔሻሊስት ዶክተሮች መሆናቸውን በመግለፅ ለማጭበርበሪያነት የያዙትን ጥቅልል ብር ካሳዩኋት በኋላ በ10 ብር እንዲቀይሯት ይጠይቋታል ።

ሁኔታቸው ያላማራት የግል ተበዳይም የግለሰቦቹን ሁኔታ በመጠራጠር ጩኸት ታሰማለች ግለሰቦቹም ወዲያውኑ በአካባቢው ማህበረሰብ ትብብር በፖሊስ ቁጥጥር ስር ይውላሉ፡፡

በምርመራው ለማረጋገጥ እንደተቻለው የግል ተበዳይ በፍጥነት ነቅታባቸው ባይያዙ ወደ ባንክ ወይም ወደ ኤ.ቲ.ኤም ይዘዋት በመሄድ ከዚህ በፊት እንደሚያደርጉት ገንዘብ ሊያስወጧት እንደነበርም ፖሊስ ገልጿል።

የግል ተበዳይ ለፖሊስ በሠጠችው ጥቆማ መነሻነት ምርመራው የቀጠለ ሲሆን ከሳምንት በፊት በተመሳሳይ የወንጀል አፈፃፀም የጣት ቀለበት የተወሰደባት ሌላ ግለሰብ መረጃ ለመስጠት ወደ ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንደመጣች ታውቋል፡፡ ሌሎች ተመሣሣይ ወንጀል ተፈፀሞብናል የሚሉ ለየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ መረጃ መስጠት እንደሚችሉ ፖሊስ አስታውቋል።

ወንጀል ፈጻሚዎች የተለያዩ የማጭበርበሪያ ዘዴዎችን በመጠቀም ወንጀል ሊፈጽሙ እንደሚችሉ ታሳቢ በማድረግ በማንኛውም እንቅስቃሴያችን ትኩረት ሊለየን አይገባም ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
*


ከአገልግሎት ውጪ የነበረውን የፕሬዝዳንት መንግሥቱ ሃይለ ማርያም አውሮፕላን ጠግኖ ጥቅም ላይ ማዋል መቻሉ ተገለፀ።

የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ሃይለ ማርያም አውሮፕላን ከተጣለበት ጥሻ በማንሳት አፕግሬድና ኦቨር ሆል በማድረግ ከ37 ዓመት በኋላ የበረራ አገልግሎት እንዲሠጥ ማድረጋችን በተቋሙ በሁሉም መስክ ውጤታማ ሥራ እየተሠራ ሥለመሆኑ ማሳያ ነው ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገልፀዋል።

አውሮፕላኑ አሥፈላጊውን ጥገና አግኝቶ መብረር እና ወደ ኃይል መመለስ እንዲችል በሰጠነው መመሪያ መሠረት ለተሳተፋችሁ የአየር ሃይል አመራሮች ቴክኒሺያኖች  የመከላከያ ድጋፍ ሰጪ ሁሉ አመሠግናለሁ ሲሉ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ምስጋና አቅርበዋል።

የኢፌዴሪ አየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በበኩላቸው አየር ሃይል በሰው ሃይል ግንባታ ፣ትጥቆችን ማሣደግና ከዘመኑ አቅም ላይ ማድረስ፣ መሠረተ ልማቶችን ተቋሙን በሚመጥን ልክ ማሥፋፋት ትኩረት የተሠጠባቸው መሠረታዊ ነጥቦች መሆናቸውን ገልፀው አውሮፕላኑን ጠግኖ ወደ ኃይል መመለስ የዚሁ አንድ አካል ነው ብለዋል።

ዳሽ ፋይፍ ወይም ቡፋሎ በሚል መጠሪያ የሚታወቀውና ለቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም አገልግሎት ይሠጥ የነበረውን አውሮፕላን ከአንድ ዓመት ጊዜ በላይ አሥፈላጊውን ጥገና በአየር ሃይል ቴክኒሺያኖች በመሥጠት ከሰላሣ ሰባት ዓመት በኋላ ለበረራ ማብቃት እንደተቻለ ተናግረዋል።

ለትራንስፖርት ፣ለፓራሹት ዝላይ፣ የካርጎ አገልግሎት መሥጠት የሚችለው አውሮፕላን ተጠግኖ ወደ ኃይል እንዲመለስ የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ለሠጡት ድጋፍ ሙያተኞች ላደረጉት ሙያዊ አበርክቶ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ምስጋና አቅርበዋል።

Показано 14 последних публикаций.